STUDENTS NEWS CHANNEL (የተማሪዎች ዜና መስኮት)
40.7K subscribers
11K photos
272 videos
452 files
1.94K links
የተማሪ እና ተማሪ ነክ መረጃዎች ይቀርቡበታል፡
Download Telegram
ማስታወቂያ: ያሬድ ሙዚቃ ትምህርት ቤት በቀን የዲግሪ መርሃ ግብር ለመግባት የምትፈልጉ ተማሪዎች በሙሉ

የምዝገባ ቀን፦ ከሃምሌ 20 እስከ ጳጉሜ 1 - 2011 ዓ/ም

#Via _ያሬድ_ሙዚቃ_ት/ቤት
#Tikvah

@nationalexamsresult
@nationalexamsresult
አዲሱ የትምህርትና ስልጠና ፍኖተ ካርታው የፌደራል ስርአቱን የማይንድ እንደሆነ የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ።

የኦሮሚያ እና የትግራይ ክልላዊ መንግስታት አዲሱ የትምህርት ፍኖተ ካርታ ላይ ከፍተኛ ቅሬታ እንዳላቸው ገልጸው ነበር

አዲሱ የትምህርትና ስልጠና ፍኖተ ካርታው የፌደራል ስርአቱን የማይንድ እንደሆነ የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ በአዲሱ የትምህርትና ስልጠና ፍኖተ ካርታ ዙሪያ ተጨማሪ ማብራሪያ በሚጠይቁ ጉዳዮች ላይ የትምህርት ሚኒስቴር መግለጫ ተሰጥቷል፡፡

አዲሱ የትምህርት ፍኖተ ካርታ ከዚህ ቀደም ከነበረው ጋር ተመሳሳይነት አለው በሚል ከህብረተሰቡ ሰፊ አስተያየት መሰጠቱን መግለጫው ተመልክቷል፡፡

የትምህርት ሚንስቴር ሚንስትሩ ዶ/ር ጥላዬ ጌቴ በሰጡት ማብራሪያ በሁሉም ት/ቤቶች ቢያንስ ለ1 አመት የቅድመ መደበኛ ትምህርት እንዲሰጥ አስገዳጅ መሆኑ ፍኖተ ካርታውን ከዚህ ቀደሙ ልዩ ያደርገዋል ብለዋል፡፡

አዲሱ ፍኖተ ካርታ የተሟላ የትምህርት ስርአትን ይከተላል ያሉት ሚንስትሩ እንደ ጆኦግራፊ እና ታሪክ ያሉ የትምህርት አይነቶች በአገር በቀል እውቀት እንዲቃኙ ይደረጋል ብለዋል፡፡

ከ1ኛ ክፍል እስከ 8ኛ ክፍል በአፍ መፍቻ ቋንቋ ትምህርት እንዲሰጥ የሚፈቅድ ሲሆን የፌደራል የስራ ቋንቋ እንደ አንድ የትምህርት አይነት እንዲሰጥ በፍኖተ ካርታው ምክረ ሀሳብ የቀረበ ቢሆንም ይህ በክልሎች ስልጣን የሚወሰን መሆኑን የትምህርት ሚንስቴር ሚንስትር ድኤታ አቶ ገረመው ሁሉቃ ገልፀዋል፡፡ ፍኖተ ካርታው 36 የተለያዩ ነጥቦች ያሉት ሲሆን ለሚንስትሮች ምክር ቤት ለውሳኔ ቀርቧል፡፡

Via #tikvah from Ebc


STUDENTS NEWS CHANNEL !!!

ስለተማሪ እና ተማሪ ነክ መረጃዎች እንዘግባለን።

ተቀላቀሉን
@nationalexamsresult
@nationalexamsresult
@nationalexamsresult

Group / አዲሱ group
@Ethio_national_exam_result


Contact us
@NERCBOT

አስተያየት ለመስጠት ብቻ
@NERC2BOT


አብራችሁን መስራት የምትፈልጉ የቻናል አድሚኖች ብቻ
@OWNERADMINSCHATROOMBOT

መልዕክት ከላካችሁ በኋላ botኡን stop ካደረጋችሁ ምላሽ ስለማያሳያችሁ ቢዘገይም stop አትበሉት
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆
ማስታወቂያ⬆️

ለኣክሱም ዩኒቨርሲቲ አዲስ መደበኛ የቅድመ-ምረቃና ድህረ-ምረቃ ተማሪዎች በሙሉ፦

የ2012 የትምህርት ዘመን የመግቢያ ጊዜ ጥቅምት 8-9 ቀን 2012 ዓ/ም መሆኑን እየገለፅን፦

• በቅድመ-ምረቃ በNatural Science የተመደባችሁ ወንድ ተማሪዎች የስማችሁ የመጀመርያው ፊደል ከA እስከ D እና ሴት ተማሪዎች ከA እስከ E የሆናችሁ በሽረ ካምፓስ እንዲሁም ሌሎች ሁሉም አዲስ ተማሪዎች በዋና ግቢ በአካል በመቅረብ ሪፖርት እንድታደርጉ እናሳውቃለን።

በተጨማሪም በ2011 ዓ/ም የአንደኛ ዓመት ቅድመ-ምረቃ ተማሪዎች የነበራችሁ በተለያዩ ምክንያቶች ዊዝድረው ያደረጋችሁና የመልሶ ቅበላ መስፈርት የምታሟሉ ተማሪዎች የስርዓተ-ትምህርት ( ካሪክለም) ለውጥ የተደረገ በመሆኑ በተጠቀሰው ቀን ቀርባችሁ ሪፖርት እንድታደርጉ እናሳውቃለን።

ማሳሰቢያ፦

ሁሉም የቅድመ-ምረቃ ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲው ስትመጡ፡

• የ10ኛ ክፍል ሰርቴፊኬት፣ የመሰናዶ ትምህርት ትራንስክሪፕት እና የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ውጤት ሰርቴፊኬት ዋናውንና ፎቶኮፒ

• የፓስፖርት መጠን ያለው የቅርብ ጊዜ 8 ጉርድ ፎቶግራፍ

• የግል መጠቀሚያ አልባሳት ማለትም አንሶላ፣ ብርድ-ልብስ፣የስፖርት ትጥቅ

• የወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት ክብ ማህተም ያረፈበት የተማሪ፣ ወላጅ እና ዩኒቨርሲቲ ውል በመያዝ በግቢያችሁ እንድትገኙ እያሳሰብን

• የሁለተኛ ዲግሪ አመልካቾች የአንደኛ ዲግሪ ኦፊሽያል ትራንስክሪፕታችሁን ከተማራችሁበት ዩኒቨርሲቲ ቀድማችሁ እንድታስልኩ እናሳውቃለን።

የአክሱም ዩኒቨርሲቲ ሬጅስትራር ጽ/ቤት

From ዶ/ር ኪሮስ ጉዕሽ (የዩንቨርሲቲው ኣካዳሚክ ም/ፕሬዝዳንት)
Via #tikvah
@Nationalexamsresult
ከተማሪዎች...

የጅማ ዩኒቨርሲቲ ቤተሰቦቻችን በተፈጠረው አለመረጋጋት ሳቢያ ቁጥሩ ቀላል የማይባል ተማሪ ግቢውን ለቆ መውጣቱን እና ወደየቤተሰቡ መሄዱን ነግረውናል፤ ለወትሮ በተማሪ የሚጨናነቀው ጅማ ዩኒቨርስቲ ጭር ብሏል ሲሉ ሁኔታው ገልፀዋል። ወደ ቤታቸው መሄድ ያልቻሉም በየመስጊዱና በየቤተክርስቲያኑ ተጠልለዋል።

በተመሳሳይ በሃረማያ ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ስርዓቱ ከተስተጓጎለ ሳምንት ሆኖታል፤ ሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ለጉዳዩ ትኩረት ነፍጎታል ሲሉ አማረዋል። በሰሞኑ ከተፈጠረው አለመረጋጋት ጋር በተያያዘ ቁጥራቸው ቀላል የማይባሉ ተማሪዎች ወደ አቅራቢያ ከተሞች ሄደዋል።

ራቅ ባሉ ከተሞች የሚገኙ ተማሪዎች የመንገድ ደህንነት አስተማማኝ ባለመሆኑ እዛው ለመሆን እንደተገደዱ ነግረውናል። ወልዲያ ዩኒቨርሲቲ የሚማሩ ተማሪዎች ደግሞ እኛ ያለንበትን ሁኔታ ሚዲያው በግልፅ አይናገርም፤ እስከመቼ በፀጥታ ሃይሎች እየተጠበቅን በስጋት እናድራለን፤ ወደቤተሰባችን ሄደን ነገሮች ሰከን ሲሉ እንመለሳለን ብለዋል።
Via #tikvah
@nationalexamsresult
@nationalexamsresult
@nationalexamsresult
የኦሮሞ እና የአማራ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች አመራሮች ውይይት እያካሄዱ ነው!

የኦሮሞ እና የአማራ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች አመራሮች በክልሎቹ ባሉ ዩኒቨርስቲዎች በተፈጠሩ ችግሮች የመፍትሔ አካል ለመሆን ውይይት እያካሄዱ ነው። በውይይቱ አመራሮቹ የህዝብን ሰላም እና ደህንነት የሚያረጋጉ የጋራ አጀንዳዎች ላይ እየመከሩ እንደሆነ ተገልጿል።

ከዚህ ቀደም በሁለቱ ክልሎች የፖለቲካ ምሁራን፣ አክቲቪስቶች እና ባለሀብቶች መካከል የተለያዩ ውይይቶች ሲደረጉ ቆይተዋል ተብሏል። በሁለቱ ወገን ያሉ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ከፍተኛ የሆነ የህዝብ ድጋፍ ስላላቸው ችግሮችን ለመፍታት ወሳኝ ሚና አላቸው ነው የተባለው።

ተሳታፊዎቹ፣ ፖለቲካ የህዝብን ጥቅም ማእከል ማድረግ አለበት፤ ህዝብ ችግር ውስጥ በሚከት አካሄድ መሆን የለበትም ብለዋል። በውይይቱ ላይ ዶ/ር ዲማ ነገዎ፣ አቶ ሌንጮ ለታ እና አቶ ንጉሱ ጥላሁንን ጨምሮ አንጋፋ የፖለቲካ ሰዎች ተሳትፈዋል።
@nationalexamsresult
Via #Tikvah
@nationalexamsresult
#Breaking_News

የዓዲ ግራት ዩንቨርስቲ ቦርድ ባደረገው ኣስቾኳይ ስብሰባ የሶስት ምክትል ፕሬዝዳንቶች ሹመት ኣፅድቋል:: በዚህም መሰረት

1. ዶ/ር ፀጋይ በርሀ- የኣካዳሚክ ም/ፕሬዝዳንት

2. ዶ/ር ገ/ኪዳን ተስፋይ የምርምርና ማሕበረሰብ ኣገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት

3. ኣቶ ፅጋብ ኣረጋዊ(ተባባሪ ፕሮፌሰር) የኣስተዳድርና ልማት ም/ፕሬዝዳንት ሆነው መሾማቸውን የአዲግራት ዩኒቨርሲቲ አስታውቋል፡፡
@nationalexamsresult
Via #tikvah
@nationalexamsresult
በኢትዮጵያ የሟቾች ቁጥር 4 ደርሷል!

በዛሬው መግለጫ ላይ የተጠቀሱት የ75 ዓመት ዕድሜ ያላቸው ሴት በተጓዳኝ ህመም በሆስፒታል ውስጥ ተኝተው ሲታከሙ የነበሩ ሲሆን በገጠማቸው የመተንፈስ ችግር ምክንያት በኮሮና ቫይረስ በሽታ ተጠርጥረው ምርመራ ናሙና ከተወሰደ በኃላ በምርመራ ውጤቱ ቫይረሱ እንደተገኘባቸው ከመረጋገጡ በፊት ህይወታቸው ሊያልፍ ችሏል።

#MoHETHIOPIA #EPHI #TIKVAH

መረጃ ቻናላችንን ተቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT
@NATIONALEXAMSRESULT
" ተማሪዎቹ ከተሳሳተ ውሳኔያቸው እንዲመለሱና ወርቃማ ዕድላቸውን እንዲጠቀሙ የተቻለንን አድርገናል " - ዶክተር የህይስ አረጉ

የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት ዶክተር የህይስ አረጉ የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና አንፈተንም ብለው ማዕከሉን ለወቀው በወጡ ተማሪዎች ጉዳይ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ዶ/ር የህይስ ፤ " በጤና ካምፓስ " የ12ኛ ክፍል ፈተና ከሚፈተኑ ተማሪዎች መካከል የተወሰኑ ተማሪዎች ፈተና ከበደን ወይም ቁጥጥር በዛብን በሚል ሰበብ ፈተና አቋርጠዉ ወጥተዋል ብለዋል።

አብዛኞቹ ተማሪዎች ግን ፈተናቸዉን በሰላም በመዉሰድ ላይ ይገኛሉ ሲሉ ገልፀዋል።

" ፈተና ጥለዉ የወጡ ተማሪዎች በአከባቢው አስተዳደር አማካኝነት ወደ ቤተሰቦቻቸው ተሸኝተዋል። " ያሉት ምክትል ፕሬዜዳንቱ " ከዚህ ውጭ የሚወራውና የሚዟዟረው መረጃ ፍፁም ስህተት ነዉ። " ብለዋል።

" ተማሪዎቹ ከተሳሳተ ውሳኔያቸው እንዲመለሱና ወርቃማ ዕድላቸውን እንዲጠቀሙ የተቻለንን ሁሉ አድርገናል " ሲሉም ገልፀዋል።

#Tikvah
ተማሪ ነክ መረጃዎችን ያግኙ
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
#MoE #ExitExam

የትምህርት ሚኒስቴር ፤ በመጪው ሀምሌ ወር ላይ በዩኒቨርሲቲዎች #በኦንላይን ለሚካሄደው የመውጫ ፈተና 30 ሺህ ኮምፒውተሮች ዝግጁ መሆናቸውን አሳውቋል።

ሚኒስቴሩ ፤ ከ240 ሺህ በላይ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የቅድመ ምረቃ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና ለመስጠት ዝግጅት መጠናቀቁን ገልጿል። 

በዩኒቨርሲቲዎች የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና የማያልፉ ተማሪዎች ድግሪ የማይሰጣቸው በመሆኑ ተማሪዎች ለሚሰጠው ፈተና ራሳቸውን አንዲያዘጋጁ ማሳሰቢያ ተላልፏል።

በሀምሌ ወር ከሚሰጠው ፈተና በፊት በግንቦት ወር መጨረሻ ላይ የሙከራ ፈተና እንደሚሰጥ ተገልጿል።

ሚኒስቴሩ ፤ በኦንላይን ፈተናው መሰጠቱ ኩረጃን ለማስቀረት፣ የወረቀት ወጪና ማጓጓዣን ለመቀነስ ይረዳል ብሏል።

ለፈተናው በአጠቃላይ ከ15 በላይ ኮርሶች በየትምህርት መስኩ ተወጣጥተው ዝግጁ መሆናቸውን የገለፀው ሚኒስቴሩ " የፈተናው ውጤት በኦንላይን ይፋ የሚደረግና ሚስጥራዊነቱ የተጠበቀ ይሆናል " ብሏል።

ፈተናውን የማያልፉ ተማሪዎች ያለገደብ በተደጋጋሚ የመፈተን እድል እንደሚኖራቸው በመመሪያ መቀመጡን ያስታወሰው ትምህርት ሚኒስቴር " የመውጫ ፈተናው የተለየ ዓላማ የሌለው እና የተማሩትን ብቻ የሚመዝን በመሆኑ ተማሪዎች ሳይደናገጡ እንዲዘጋጁ ለተማሪዎች ጥሪ አቅርቧል።

ሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመፈተኛ ጣቢያ እንደሚሆኑ ይፋ ተደርጓል።

#ኢብኮ #tikvah

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
ነጻ የትምህርት ዕድል!

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ት/ቤት በ2016 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በአዲስ አበባ በሚገኙ የመንግሥት እና የግል ት/ቤቶች በመማር ላይ ከሚገኙ በትምህርታቸው፣ በመልካም ምግባራቸው እና በልዩ ተሰጥኦዋቸው የተመሰከረላቸውን ተማሪዎች አወዳድሮ ነጻ የትምህርት ዕድል ለመሥጠት መዘጋጀቱን ገልጾልናል።

ተወዳዳሪ ተማሪዎች የሚከተሉትን መስፈርቶች አሟልተው መምጣት ይጠበቅባቸዋል፦

1. ነዋሪነታቸው በአዲስ አበባ የሆነ፣

2. የ2ኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ት/ቤቱ በሚከተለው ሥርዓተ ትምህርት በኬምብሪጅ ኢንተርናሽናል አይ.ጂ.ሲኤስ.ሲ እና በኬምብሪጅ ኢንተርናሽናል አድቫንስድ (Cambridge International IGCSC and Cambridge International Advanced) ለመማር እና በዚሁ ሥርዓተ ትምህርት ለመፈተን ፈቃደኛ የሆኑ፣

3. የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት መግለጫ ኮፒ ማቅረብ የሚችሉ፣

4. በ2015 ዓ.ም መጨረሻ የክፍል ውጤታቸው ከ90% በላይ የሆነ እንዲሁም የ8 ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና አማካይ ውጤታቸው ከ95% በላይ የሆነ፣

5. ስለመልካም ምግባራቸው እና ልዩ ተሰጥኦዋቸው ከሚማሩበት ት/ቤት የጽሑፍ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፣

6. ት/ቤቱ የሚሰጠውን የመግቢያና ቃለመጠይቅ ፈተናዎችን የተሻለ ውጤት በማስመዝገብ ማለፍ የሚችሉ፣

7. የልደት የምሥክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፣

8. የወላጅ/አሳዳጊ ሙሉ ፈቃድ ማግኘት የሚችሉ፣

በመሆኑም መስፈርቱን የሚያሟሉ እና ፍላጎቱ ያላቸው ተማሪዎች እስከ ነሐሴ 19/2015 ዓ.ም ሰሚት ፍርድ ቤት አካባቢ በሚገኘው ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል በመቅረብ መመዝገብ ይችላሉ።

#Tikvah

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT
የ12ኛ ክፍል ውጤት ለማየት መቸገራቸውን በርካታ ተማሪዎች እና ወላጆች አስተያየታቸውን ለቲክቫህ ሰጥተዋል።

የ2015 ዓም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና ውጤት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት 6284፣ በዌብሳይት eaes.et እንዲሁም በቴሌግራም ቦት @eaesbot የሬጅስትሬሽን ቁጥር በማስገባት ማየት እንደሚቻል መገለጹ ይታወቃል።

ነገር ግን በርካታ ተማሪዎች እና የተማሪ ወላጆች ውጤት ለማየት መቸገራቸውን ለቲክቫህ ገልጸዋል።

የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት በውጤት መመልከቻ አማራጮቹ ላይ ምንም አይነት ቴክኒካል ችግር እንደሌለና መጨናነቅ ብቻ መኖሩን ለቲክቫህ ገልጿል።

ሙራድ ታደሰ የተባሉ የቲክቫህ ቤተሰብ ውጤት ለማየት የተቸገሩ ተማሪዎች ሊጠቀሙት የሚችሉ አማራጭ መፍትሔ ጠቁሞናል።

ውጤት የመመልከቻ አማራጮች ላይ ማለትም eaes.eteaes.gov.eteaes.edu.et ከገባችሁ በኋላ Forgot Admission Number የሚለውን በመጫን፣ Your Name, Father's Name, Grand Father's Name በሚሉት ላይ ስማችሁን እስከአያት ስትሞሉ ካለምንም ID ይሠራል።

ተማሪዎች በትዕግስት በመሞከር ውጤታቸውን እንዲያዩ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት መክሯል።

በተጨማሪ ቅሬታ ማቅረቢያው ቅፅ እየሰራ እንዳልሆነ በርካታ ተማሪዎች አስተያየታቸውን ለቲክቫህ አድርሰዋል።

በነዚህ ጉዳዮች ላይ የሚመለከታቸውን አካላት በማናገር ተጨማሪ የምናደርሳችሁ ይሆናል። #tikvah

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
" በጦርነቱ ምክንያት ወደኃላ ባልቀር አሁን የ4ኛ ዓመት የዩኒቨርሲቲ ተማሪ ነበርኩ " - ተማሪ ሙሴ ኪዳነ

በትግራይ ክልል የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከወሰዱ ከ9,000 በላይ ተማሪዎች 657 በማምጣት ከፍተኛውን ውጤት ያስመዘገበው የቀላሚኖ ት/ት ተማሪ ሙሴ ኪዳነ " መድረስ ከነበረብኝ የትምህርት ደረጃ ባለመድረሴ ዓመታት ከእድሜ ላይ ተሰርቋል " ሲል ገልጿል።

የትግራይ #ሃውዜን ነዋሪ የሆነው ተማሪ ሙሴ አሁን ላይ እድሜው 22 ሲሆን ፤ ባስመዘገበው ከፍተኛ ውጤት ደስ መሰኘቱን ለክልሉ ቴሌቪዥን ጣቢያ ተናግሯል።

አስከፊው ጦርነት በይከሰትና ወደኃላ ባይቅር ኖሮ አሁን ላይ የ4ኛ ዓመት የዩኒቨርሲቲ ተማሪ እንደነበርም ገልጿል።

ሙሴ ኪዳነ ፥ " አሁን የመጣው የፈተና ውጤት ጥሩ ነው። ደስም ብሎኛል ከውጤቱ ጋር አያይዤ ማለት የምፈልገው ሁሉም ሰው ያሰበውን ደረጃ ለመድረስ የሚያስችለውን ጥረት ካደረገ ማሳካት እንደሚቻል ማሳያ ነው። " ብሏል።

መድረስ ከነበረበት የትምህርት ደረጃ ባለመድረሱ ዓመታት ከእድሜው እንደተሰረቀበት የሚገልፀው ተማሪ ሙሴ አሁን የሚገባውን ሁሉ የሚማርበት እድል ሊመቻች ይገባል ሲል ለትግራይ ቴሌቪዥን ተናግሯል።

በትግራይ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከወሰዱ ከ9,000 በላይ ተማሪዎች 73.09 በመቶ የሚሆኑት የተፈጥሮ ሳይንስ እንዲሁም 51.38 በመቶ የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች በአጠቃላይ 66.96 በመቶ ተማሪዎች 50 በመቶና በላይ ውጤት በማምጣት የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ነጥብ አግኝተዋል።

#Tikvah

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot