STUDENTS NEWS CHANNEL (የተማሪዎች ዜና መስኮት)
40.7K subscribers
11K photos
272 videos
452 files
1.94K links
የተማሪ እና ተማሪ ነክ መረጃዎች ይቀርቡበታል፡
Download Telegram
በአዲስ አበባ የ2016 ትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ሒደት መስከረም 07/2016 ዓ.ም ይጀምራል።

በአዲስ አበባ ከ1.2 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎችን የሚያስተምሩ ከ2,200 በላይ የትምህርት ተቋማት መኖራቸውን ከመዲናዋ የትምህርት ቢሮ የተገኘ መረጃ ያሳያል።

በሌላ በኩል በኦሮሚያ ክልል ' ኪድ -ኢንተርፕረነርሺፕ ' የተሰኘ ከቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤት ጀምሮ ህጻናትን በክህሎት ለማነጽ የተዘጋጀ መጽሐፍና ' በርኖታ ሰፉ ' የተሰኘ ከ1ኛ ክፍል እስከ 6ኛ ክፍል የሚሰጥ የግብረ ገብ ትምህርት መፅሃፍ ተመርቋል።

በዚህም ፤ ' ኪድ-ኢንተርፕርነርሺፕ ' እና ' በርኖታ ሰፉ / የግብረ ገብ ትምህርት ' ይሰጣል።

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
የአጠቃላይ ትምህርት የ2016 የትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ሂደቱ የሚመራበት ሀገር አቀፍ የትምህርት ካላንደር

ማሳሰቢያ :- ክልሎች በብሔራዊ ፈተናና በተለያዩ ክልላዊ ነባራዊ ሁኔታዎች መነሻ የተወሰኑ የቀናት ለውጦች ሊያደርጉ እንደሚችሉ ታሳቢ ይደረግ

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
" ትምህርት የሚጀምረው መስከረም 7 ነው " - የአ/አ ትምህርት ቢሮ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ2016 የትምህርት ዘመን ትምህርት የፊታችን ሰኞ መስከረም 7 /01/2016 ዓ.ም በሁሉም ትምህርት ተቋማት እንደሚጀምር አስታወቀ።

ቢሮው ይህን ያሳወቀው የትምህርት ሚኒስቴር የ2016 ዓ/ም የትምህርት ካላንደርን ለህዝብ ካሰራጨ በኃላ በማህበራዊ ትስስር ገፁ ባወጣው አጭር መልዕክት ነው።

የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ ፤ " የ2016 የትምህርት ዘመን ትምህርት መስከረም 14 /1/2016 ዓ.ም እንደሚጀመር በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች እየተሰራጨ የሚገኘው መረጃ #የተሳሳተ ነው " ብሏል።

ቢሮው የትኞቹ የማህበራዊ ሚዲያዎች የተሳሳተ መረጃ እንደተሰራጨ በግልፅ አላሰፈረም።

የትምህርት ሚኒስቴር ዛሬ ቅዳሜ በተረጋገጠው የማህበራዊ ትስስር ገፁ ላይ ይፋ ባደረገው የ2016 የትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ሂደቱ የሚመራበት #ሀገር_አቀፍ የትምህርት ካላንደር መሰረት ከመስረም 7 እስከ 11 ድረስ የትምህርት ሳምንት ሆኖ ይከበራል ብሏል።

መስከረም 14 ደግሞ የአንደኛ ሴሚስተር መደበኛ የክፍል ውስጥ ትምህርት እንደሚጀምር አሳውቋል።

ትምህርት ሚኒስቴር በዚህ ካላንደሩ ላይ ክልሎች በብሔራዊ ፈተናና በተለያዩ ክልላዊ ነባራዊ ሁኔታዎች መነሻ #የተወሰኑ የቀናት ለውጦች ሊያደርጉ እንደሚችሉ ታሳቢ ይደረግ ብሏል።

የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ከዚህ ቀደም ይፋ ባደረገው መሰረት የ2016 ዓ/ም ትምህርት ሰኞ መስከረም 7 ቀን 2016 ዓ/ም በሁሉም ተቋም እንደሚጀምር አስረግጦ ተናግሯል ፤ መላው የከተማው ማህበረሰብ ይህን እንዲያውቀው ብሏል።

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2016 የትምህርት ዘመን ትምህርት ዛሬ በሁሉም ትምህርት ቤቶች ተጀምራል፡፡

@NATIONALEXAMSRESULT
@InEthiopia_Opportunities ቴልግራም ቻናልን ይቀላቀሉና በየእለቱ እነዚህን መረጃዎች ያግኙና የእድሉ ተጠቃሚ ይሁኑ!!!
Join
@InEthiopia_Opportunities
@InEthiopia_Opportunities
@InEthiopia_Opportunities
ሴት ለመሆን መቸኮልም ተጀምሯል.....,

በዲማ ወረዳ ፆታውን በመቀየር በመስተንግዶ የተቀጠረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ።

በጋምቤላ ክልል በአኙዋ ብሔረሰብ ዞን በዲማ ወረዳ ዲማ ከተማ በዛሬው ዕለት መስከረም 6 ቀን 2016 ዓ.ም ፆታውን በመቀየር በመስተንግዶ የተቀጠረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር መዋሉ ተነግሯል።

ግለሰቡ የአራት ዓመት ልምድ እንዳለው በመናገር ስሙን እና አለባበሱን የሴት በማድረግ በሆቴል መስተንግዶ ተቀጥሮ ለሁለት ቀናት ከቆየ በኋላ በቁጥጥር ስር መዋሉን የዲማ ወረዳ ኮሚኒኬሽን ሃላፊ የሆኑት አ/ቶ ኡመድ ኦቶው ለብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥን ተናግረዋል።

ግለሰቡ ቢንያም ከበደ የሚባል ሲሆን ስሙን እና አለባበሱን ለመለየት በሚያዳግት መልኩ ሴት በመምሰል በደላላ አማካኝነት ቃልኪዳን ወርቁ ተብሎ ገረመው ሆቴል የተቀጠረ ሲሆን መነሻውን ጂማ ከተማ በማድረግ ወደ ከተማዋ የገባ መሆኑን አክለዋል።

በዚህም ህብረተሰቡ ለፖሊስ በሰጠው ጥቆማ አማካኝነት በቁጥጥር ስር ውሎፕ ፆታው ወንድ እንደሆነ የተረጋገጠ ሲሆን ለምን እንደዚህ ማድረግ እንደፈለገ ምርመራ እየተደረገበት እንደሚገኝ ተገልጿል።

@NATIONALEXAMSRESULT
#WolloUniversity
#ጥሪው_ተራዝሟል‼️


ወሎ ዩኒቨርሲቲ ለመደበኛ ተማሪዎቹ የ2016 የትምህርት ዘመን የተማሪዎች ምዝገባን ማሳወቁ ይታወሳል። ሆኖም ግን ከዩንቨርሲቲው ዛሬ ባገኘነው መረጃ መሰረት ለመደበኛ ተማሪዎች ተደርጎ የነበረው ጥሪ #ላልተወሰነ ጊዜ መራዘሙን ሰምተናል።

⛔️⛔️⛔️⛔️⛔️⛔️⛔️⛔️⛔️⛔️⛔️⛔️⛔️
አማራ ክልል ላይ የኢንተርኔት አገልግሎት በመቋረጡ ይህን መረጃ ለዩንቨርሲቲው ተማሪዎች በተለይም አማራ ክልል ላይ ለሚገኙ የወሎ ዩንቨርሲቲ መደበኛ ተማሪዎች በስልክ በመደወል ታሳውቋቸው ዘንድ የወሎ ዩንቨርሲቲ ተማሪዎች ህብረት ጠይቋል።

ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@NATIONALEXAMSRESULT
@InEthiopia_Opportunities ቴልግራም ቻናልን ይቀላቀሉና በየእለቱ እነዚህን መረጃዎች ያግኙና የእድሉ ተጠቃሚ ይሁኑ!!!
Join
@InEthiopia_Opportunities
@InEthiopia_Opportunities
@InEthiopia_Opportunities
በትግራይ ክልል የ2016 ትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ሒደት ነገ መስከረም 09/2016 ዓ.ም ይጀምራል፡፡

የ2016 ዓ.ም መማር ማስተማር ሒደቱን ለማስጀመር የተለያዩ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች መከናወናቸውን የክልሉ ትምህርት ቢሮ አሳውቋል፡፡

በዚህም ከመስከረም 03/2016 ዓ.ም ጀምሮ ለ5 ተከታታይ ቀናት 37 ሺህ ለሚሆኑ መምህራንና የትምህርት ባለሙያዎች ስልጠና መሰጠቱን ቢሮው ገልጿል፡፡

በክልሉ የ2016 ትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ሒደት ነገ መስከረም 09/2016 ዓ.ም እንደሚጀመር ከቢሮው ይፋዊ የፌስቡክ ገጽ የተገኘው መረጃ ያሳያል።

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
በፀጥታ እና በሌሎች ምክንያቶች ፈተና ላልወሰዱ ከ15 ሺህ በላይ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ከመስከረም 08 እስከ 11/2016 ዓ.ም ፈተና ይሰጣል መባሉ ይታወቃል።

በጎንደር እና በጋምቤላ ሙሉ በሙሉና በከፊል ፈተና ያልወሰዱ እንዲሁም በማረሚያ ቤቶች ለሚገኙ ተፈታኞች ፈተናውን ለመስጠት ዝግጅት መደረጉን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ጳጉሜን 03/2015 ዓ.ም ማሳወቁ አይዘነጋም።

በፈተናው ዙሪያ የሚወጡ መረጃዎችን እናደርሳችኋለን።

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
በ " ናዝሬት ትምህርት ቤት " እና በ " አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን " መሃከል የተፈጠረው ምንድነው ?

በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኘው የናዝሬት ትምህርት ቤት እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን መሃከል በተፈጠረ ውዝግብ ምክንያት የናዝሬት ት/ቤት መደበኛ ተማሪዎች ትምህርት መጀመር አለመቻላቸው ተገለፀ።

በሁለቱ አካላት መሃከል የተፈጠረው ውዝግብ የመማር ማስተማር ሂደቱን እንዳስተጓጎለው ወላጆች ለቲክቫህ ገልፀዋል።

ውዝግቡ እንዴት ሊፈጠር ቻለ ?

- ናዝሬት ትምህርት ቤት ባሳለፍነው 2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በትምህርት ቤቱ ከሚማሩ ተማሪዎች መሀከል 15 ተማሪዎች ውጤት አጭበርብረዋል በማለት በዲሲፕሊን ጉድለት ምክንያት ከትምህርት ገበታ አግዷቸዋል።

- ይህንን ተከትሎ በናዝሬት ትምህርት ቤት ልጆቻቸው የታገዱባቸው የተማሪ ወላጆች ለአራዳ ክፍለ ከተማ የትምህርት ጽ/ቤት ቅሬታቸውን አሰምተዋል።

- ቅሬታቸውን የሰማው የአራዳ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት፤ ልጆቻቸው የታገዱባቸውን ወላጆች እና ናዝሬት ትምህርት ቤትን በጋራ ለማነጋገር ጥሪ አድርጎ ነገር ግን የናዝሬት ትምህርት ቤት የቦርድ አባላት ጉዳዮን ቀርቦ ለማስረዳት እንዳልቻሉ በፃፈው ደብዳቤ ገልጿል።

- የናዝሬት ትምህርት ቤት በበኩሉ "ጉዳዩን ቀርቤ ለማስረዳት ሞክሬ ነበር ነገር ግን የአራዳ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት የታገዱት ተማሪዎች በምን ምክንያት እንደታገዱ ሳይረዳ ተማሪዎቹን ወደ ትምህርት ገበታቸው እንድንመልሳቸው ጫና እያደረገብን ነው" በማለት ለጽ/ቤቱ በፃፉት ደብዳቤ ቅሬታቸውን ገልፀዋል። 

- አለመግባባቱን ተከትሎ የአራዳ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት ጉዳዮን የበላይ አካል ወደ ሆነው የአዲስ አበባ የትምህርትና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን መስሪያ ቤት የወሰደው ሲሆን ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የታገዱ ተማሪዎች ወላጆችን እና ትምህርት ቤቱን በጋራ ለማነጋገር ሞክሮ እንዳልተሳካ ገልጿል።

- ይህንን ተከትሎ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የትምህርት ቤቱን እውቅና ፈቃድ አግዶ የነበረ ሲሆን በነሃሴ 19 2015 ዓ.ም በፃፈው ደብዳቤ "ትምህርት ቤቱ የታገዱ ተማሪዎችን ለመመለስ ተስማምቷል" በማለት የእውቅና ፈቃድ እገዳውን ማንሳቱን አሳውቋል።

- ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የእውቅና ፈቃድ እገዳውን አንስቻለሁ በማለቱ ትምህርት ቤቱ የተማሪዎች ምዝገባ ጀምሮ የነበረ ቢሆንም እንደገና ከባለ ስልጣን መስሪያ ቤቱ ምዝገባ አቁሙ የሚል የቃል ትእዛዝ መምጣቱን በመስከረም 4 , 2016 ዓ.ም ለወላጆች በማሳወቅ ምዝገባ በይፋ ማቆሙን አሳውቋል።

በዛሬው እለት የወላጅ ኮሚቴ መደበኛው ትምህርት እንዲጀመር ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ተቀራርቦ መነጋገሩ የተገለፀ ሲሆን የወላጅ ኮሚቴ አባል የሆኑት ዶ/ር ወንድወሰን ሙሉጌታ የታገዱት ተማሪዎች ተመልሰው እንዲመዘገቡና አዲስ የዲሲፕሊን ኮሚቴ ተቋቁሞ ታግደው የነበሩት ተማሪዎች ጉዳይ በድጋሚ እንዲታይ እንደተወሰነ ከቲክቫህ ጋር በነበራቸው ቃለምልልስ አንስተዋል።

የወላጅ ኮሚቴው ከሚመለከተው አካል ጋር ከተነጋገረ በኋላ ፤ በነገው እለት የተማሪዎች ምዝገባ እንደሚጀምር ሲገለፅ ሰኞ መስከረም 14 ቀን 2016 ዓ/ም በይፋ ትምህርት እንደሚጀመር  ትምህርት ቤቱ አሳውቋል።

#ቲክቫህ

@NATIONALEXAMSRESULT
#ማስታወቂያ!!

ለወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የመደበኛ ሁለተኛ ዓመትና ከዚያ በላይ ተማሪዎች በሙሉ!!

ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የ2016 ዓ.ም ተማሪዎች ቅበላ ከመስከረም 21- 22/ 2016 ዓ.ም መሆኑን እየገለፅን ከወዲሁ ዝግጅት እንድታደርጉ እናሳዉቃለን።

Date of Online registration (Meskerem 19 - 22/2016 L.C) ባላችሁበት ሆናችሁ ከመስከረም 19 ጀምሮ መመዝገብ እንደምትችሉ እና ወደ ግቢ መግቢያ ከ21–22/01/2016 ዓ.ም. መሆኑን እያሳሰብን ትምህርት የሚጀምረዉ (DOCO) በ23/01/2016 ዓ.ም መሆኑንም ጭምር እናሳስባለን፡፡

#ማሳሰቢያ፡-

➢ ስትመጡ የስፖርት ትጥቅ አንሶላና የትራስ ጨርቅ ይዛችሁ እንድትመጡ፤

➢ ከተጠቀሰዉ ጊዜ ቀድሞም ሆነ ዘግይቶ የሚመጣ ተማሪ ዩኒቨርሲቲዉ የማያስተናግድ መሆኑን፣

➢ የአንደኛ ዓመት ተማሪዎችን (ማለትም ከራመድያል ያለፉ፤ “ADR and Withidraw ያደረጉ እንዲሁም ድህረ-ምረቃ (MS MA/PHD ተማሪዎችን) በቀጣይ ማስታወቂያ የምንጠራችሁ መሆኑን እናሳስባለን።

ከወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ሬጅስትራርና አልሙናይ ዳይሬክቶሬት!

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
#AsosaUniversity

ለአሶሳ ዩኒቨርሲቲ መደበኛ ተማሪዎች በሙሉ

የአሶሳ ዩኒቨሲቲ የ2016 ዓ.ም ለ2ኛ እና 3ኛ ዓመት መደበኛ ተማሪዎች የመግቢያ ጊዜ ከመስከረም 21-22/2016 ዓ.ም እንዲሁም

ለ5ኛ ዓመት እና ሁሉም 2ኛ ድግሪ መደበኛ ተማሪዎች መግቢያ ጊዜ ጥቅምት 5-6/2016 ዓ.ም መሆኑን እየገለፅን በተጠቀሰው ቀን ሬጅስትራር ኣገ ዳይሬክቶሬት በአካል በመገኘት እንድትመዘገቡ እናሳስባለን፡፡

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
We can handle your assignments, thesis, classes, projects, proposals and dissertation in various fields, good rate. Inbox .@ResearcherETH
@ResearcherETH
@ResearcherETH
@ResearcherETH
የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት በሩሲያ ትምህርት ቤቶች መሰጠት መጀመሩን የሞስኮ ትምህርት ቤቶች አስተዳደር አስታወቀ‼️
የአማርኛ ቋንቋ መሰጠት መጀመሩ በኢትዮጵያና በሩሲያ መካከል ያለውን ኢኮኖሚያ፣ ባህላዊ እና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ያጠናክራል ነው የተባለው፡፡

ተማሪዎቹ በበኩላቸው አማርኛ ቋንቋ ከማወቅ በተጨማሪ ወደ ኢትዮጵያ በመምጣት ህዝቡን እና የኢትዮጵያን ባህል ማየት እንደሚፈልጉ ገልፀዋል፡፡

ተጨማሪ የአፍሪካ ቋንቋዎችን የመማር ፍላጎት እንዳላቸውም ተናግረዋል፡፡

ከአማርኛ በተጨማሪ በአፍሪካ ከፍተኛ ተናጋሪ ያለው የስዋሂሊ ቋንቋ በሞስኮ ትምህርት ቤቶች መሰጠት መጀመሩን ስፑትኒክ አፍሪካ ዘግቧል፡፡

#የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
#Update

በአማራ ክልል የ2016 ትምህርት ዘመን የተማሪዎች ምዝገባ እስከ መስከረም 11/2016 ዓ.ም ተራዝሟል፡፡

በክልሉ የተማሪዎች ምዝገባ ከነሐሴ 23/2015 ዓ.ም ጀምሮ ሲከናወን መቆየቱ ይታወቃል። እስካሁን 2.5 ሚሊዮን ተማሪዎች መመዝባቸውን የክልሉ ትምህርት ቢሮ አሳውቋል።

የተማሪዎች ምዝገባ ከሌሎች ዓመታት አንጻር ሲታይ የተጓተተ መኾኑን የክልሉ ትምህርት ቢሮ የሕዝብ ግንኙነትና ጽ/ቤት ኃላፊ ጌታቸው ቢያዝን ተናግረዋል።

በአማራ ክልል በተፈጠረው የፀጥታ ችግር ምክንያት ምዝገባው በተፈለገው ልክ መሔድ አለመቻሉን የገለፁት ኃላፊው፤ ከባለፉት ዓመታት የምዝገባ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የዘንድሮው ዝቅተኛ መኾኑንም ጠቁመዋል፡፡

በክልሉ ከቅድመ መደበኛ እስከ ሁለተኛ ደረጃ 6.2 ሚሊዮን ተማሪዎችን ለመመዝገብ ዕቅድ ተይዞ እየተሠራ መኾኑን የተናገሩት ኃላፊው፤ የጸጥታ ችግር በሌለባቸው አካባቢዎች ምዝገባው መቀጠሉንም ገልጸዋል፡፡

በዚህም የተማሪዎች ምዝገባ በተፈገው ልክ ባለመኾኑ እስከ መስከረም 11/2016 ዓ.ም መራዘሙን ተናግረዋል፡፡

ተማሪዎች እንዲመዘገቡና መደበኛ የመማር ማስተማር ሥራው መስከረም 14/2016 ዓ.ም እንዲጀመር ሁሉም ርብርብ እንዲያደርግ ኃላፊው ጥሪ አቅርበዋል፡፡ #አሚኮ

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot