ቅዱሳን ኅሩያን የዲ°ን ዮርዳኖስ ትምህርቶች
4.97K subscribers
919 photos
5 videos
33 files
239 links
የዲ.ን ሄኖክ ሀይሌን ስብከት በድምጽ እንለቃለን
ለአስተያየት @EMNE_TSYON @unitte_bot
በቴሌግራም ከፈለጉን @henokhailee
በfacebook ከፈለጉን https://www.facebook.com/tewahidosewhone/
በyoutube ከፈለጉን https://youtube.com/channel/UCq2ueVG6O3ZuKHJ485y7hfg
Download Telegram
ንስሓ  ማለት ምን ማለት ነዉ?                                                                                                         ንስሃ የቃሉ ፍች እና ማብራሪያ ማዘን፣መፀፀት፣መቆጨት፣መቀጣት፣ቀኖና መቀበል፣ስለተሰራዉ ኃጢአት ካሳ መክፈል፣የሰሩትን በደል እና ጥፋት ማመን ነዉ።በተጨማሪ ሌላ ጊዜ ከፈጣሪ ጋር የሚያጣላዉን እና ሰማያዊ የዘላለም ህይወት ሊያሳጣዉ የሚችል ኃጢያት ላለመፈፀም የመጨረሻ ዉሳኔ የሚደርስበት የመደምደሚያ ሃሳብ ነዉ።


1/ንስሓ ወደ እግዚአብሄር መመለስ ነዉ                                                                                        የእግዚአብሔር ሰዉ ነቢዩ ሚልክያስ እንደተናግረው "ከአባቶቻችሁ ዘመን ጀምሮ ከስርዓቴ ፈቀቅ ብላችኋል።ወደ እኔ ተመለሱ እኔም ወደ እናንተ እመለሳለሁ"በማለት ከ እግዚአብሔር ሕግ በመተላለፍ እና ተዛዙን በማፍረስ ለበደሉት ሰወች የንስሓ ጥሪ እንዳቀረበላቸው እንመለከታለን።(ሚል 3 ፥ 7 )

ጠቢቡ ሰለሞን "ኃጢአቱን የሚሰዉር አይለማም፤የሚናዘዝባት እና ተሚተዋት ግን `ምህረትን ያገኛል "በማለት ስለ ኃጢአት ግልጸኝነትና ከእግዚአብሔር ዘንድ ስለሚሆንልን ምህረት ተናግሯል።(ምሳሌ28፥13)                                                                       #ጌታችን_መድሃኒታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ በምሳሌ ሲናገር በኅጢአት ወድቆ በንስሓ ስለተመለሰው የሰው ልጅ ኅጥያቱን ተመራምሮ እና በልቡ ተጸጽቶ ወደ ሰማያዊ አምላክ ወደ እግዚአብሔር ለመመለስ ዉሳኔ ላይ ቢደርስ የምህረት እና የችርነት አባት እግዚአብሔርም በደስታ እና በፍቅር እንዴት እንደሚቀበለዉ ተመዝግቦ እናገኛለን።(ሉቃ 15፥  )

2/ንስሓ #ከእግዚአብሔር ጋር መታረቅን ያመለክታል                                      #ሐዋርያው_ቅዱስ_ጳዉሎስ ለቆሮንቶስ ሰወች በጻፈላቸዉ መልእክቱ ስለዚህ ሲናገር "እንግዲህ #እግዚአብሔር ስለኛ እንደሚማለድ ስለ #ክርስቶስ መለዕክተኞች ነን #ከእግዚአብሔር ጋር ታረቁ ብለን እንለምናችኋለን"ሲል ተናግሯል።(2ቆሮ 5፥20)

3/ ንስሓ ክርስቲያን ከኃጢአት እንቅልፍ የሚነቃበት ደወል ነዉ                                              ክርስቲያን ኃጢአትን በሰራ ጊዜ በመንፈሳዊ ህይወቱ እና በክርስቲያናዊ ስነምግባሩ ማንቀላፋቱን የምናስተዉልበት ምልክት ነዉ።"የሰው ልጅ ኃጢአተኛ መሆን ሲጀምር በክርስቲያናዊ ህይወቱ የነበሩት እሴቶች ሁሉ ከሱ ጨርሰዉ ስለሚጠፉ ኃጢአት የሚያሰራው የክፉ መንፈስ ባለቤት የሆነዉ ሰይጣን በኃጢአት የማደንዘዝ መርፌ አይምሮውን ስለሚያሳጣው የቆመበትን ስፍራ እና የወደቀበትን ጉድጓድ ፈጽሞ ሊያዉቀዉ አይችልም እና በንስሓ ደወል እንድንቀሰቅሰው ያስፈልጋል።                                                                                          4/ንስሓ በኃጢአት ምክንያት ወድቆ የነበረ ክርስቲያን ወደ መንፈሳዊ ህይወቱ መመለሱን ያመለክታል                                                                                                           የኃጢአት ደዌ ያደረበት ማንኛውም ኦርቶዶክሳዊ ክርስቲያን በንስሓ ህክምና ፈውስ ካላገኘ በመጨረሻ የሚገጥመው እድል የነፍስ ሞት ነው።ሓዋርያው ቅዱስ ጳዉሎስ ስለዚህ ጉዳይ ሲናገር "አንተ የተኛህ ንቃ ከሙታንም ተነሳ #ክርስቶስም ያበራልሃልና "ሲል ተናግሯል(ኤፌ5፥14)።                                                                                                                            #ወንጌላዊ_ቅዱስ_ዩሃንስም "እኛ...ከሞት ወደ ህይወት እንደተሻገርን እናውቃለን"በማለት ስለ ህይወት መንገድ መስክሯል

ሰይጣን ከሚዋጋቸው የድኅነት መንገዶች ውስጥ ንስሓን የሚያክል የለም ምክንያቱም ንስሐ ጠላት ዲያብሎስ የክርስቲያኖችን ሕይወት ለማጥፋት የገነባውን የኃጢአት ሕንፃ ሁሉ #በእግዚአብሔር ቸርነት እንዳልነበረ በማድረግ ስለሚያፈርስበት ነው። ከዚህ የተነሳ የሰው ልጅ ንስሐ እንዳይገባ ቢገባም ቶሎ እንዳይሆን የተቻለውን ከማድረግ ፈፅሞ አያርፍም። ጠላት ዲያብሎስ ሰዎችን በኃጢአት ለማቆየት ወይም ንስሐ የሚገቡበትን ጊዜ ለማራዘም ከሚጠቀምባቸው የንስሐ መሰናክሎች መካከል ፦                                                              1/ እንቅፋት መፍጠር፦ ድንገተኛ ፈተናዎች ወይም አጋጣሚዎች ሊሆኑ ይችላሉ ብቻ እንቅፋት በመፍጠር ያሰናክላቸዋል።

2 / ኃጢአተኛው ራሱን ከእርሱ የበለጠ ኃጢአት ሠሩ ከሚላቸው ጋር በማነፃፀር የተሻለ እንደሆነ እንዲገምትና ንስሓም እንደማያስፈልገው ራሱን ማሳመን፥ ማንም ክርስትያን ከሌላው ጋር ኃጢአቱን ሊያነጻጸር አይገባም ።

3/ ከሥጋ ድካም የተነሣ በአካባቢ ተጽእኖ መመራት#ቅዱስ_ጳውሎስ "ይህን ዓለም አትምሰሉ" በሏል ሮሜ 12፥2 ዓሳ ትንሽ ሲሆን ማዕበል በሚያናውጠው ባሕር ውስጥ ይዋኛል ክርስቲያንም እንዲህ ፈተናን ተቋቁሞ ለንስሓ መብቃትና መንፈሳዊ ህይወት መኖር ይገባዋል።

4 /መዘግየት ፦ ዲያብሎስ ንስሓ እንዳንገባ የሚዋጋን በቀጥታ አይደለም ነገር ግን የተለያዩ ስውር ፈተናዎችንና ምክንያቶች እየደቀነ ንስሐ እንዳንገባ ያዘገየናል። መዘግየት ከሚያስከትለው አደጋ መካከል አንዱ ለንስሐ የተዘጋጀውን ልቡና መለወጥና ለንስሓ ያለውን ዕድል ማጥፋት ነው። ኃጢአት ወዲያው ካልተቀጨና ከቀጠለ ሥር ይሰዳል ሱስ ሆኖ ይዋሀደንና ከዚያም ለንስሓ የተዘጋጀውን ጸጸትና ፍላጎት ሊያጠፋው ይችላል።

5/ ተስፋ መቁረጥ ፦ሰይጣን በኃጢአት ከመውደቃችን በፊት የእግዚአብሔርን ቸርነትና ይቅርታ በማሰብ ኃጢአት እንድንሠራ ያደርገናል ከሠራነው በኋላ ደግሞ ሎቱ ስብሓት የእግዚአብሔርን ፍርድ ኩጣን የተሞላ እንደሆነ ያሳስበናል ንስሐ እንዳንገባም ተስፋ ያስቆርጠናል።                                   6/ ተነሳሒው ራሱን በማድነቅ በመመጻደቅ ኃጢአተኛ እንዳልሆነ እንዲያስብ በማድረግ፦ ሰው መልካም ነው ብሎ የሚገምተው የራሱ ሕይወት በኃጢአት የተዳደፈ መሆኑን ካላመነ በቀር ሊለወጥ አይችልም። በሕይወቱ ውስጥ መንፈሳዊ ለውጥ ከሌለ ደግሞ ስለ ንስሐ አያስብም፤ ንስሐም አይገባም ስለዚህ ራሱን አይመረምርም ።

7/ በልቡና ውስጥ #ፈሪሃ_እግዚአብሔር አለመኖሩ#ቅዱስ_ይስሐቅ እንዳለው #ፈሪሃ_እግዚአብሔር ከሌለ ንስሐ መግባት የለም ብሏል አንዳንድ ሰዎች በፍቅር ሰበብ #ፈሪሃ_እግዚአብሐርን ከልቡናቸው ፈጽመው ያስወግዳሉ። በዚህ ጊዜም ስለ ንስሐ ህይወታቸው ግድ የለሽ ይሆናሉ በኃጢአት ይወድቃሉ። ከኃጢአት የተነሳም ፍርሃትን አውጥቶ በመጣል ወደ ንስሓ የሚያቀርበውን #የእግዚአብሔርን_ፍቅር ያጣሉ።
አብርሃምም ወደ #እግዚአብሔር ለመነ #እግዚአብሔርም አቤሜሌክን ፈወሰው ሚስቱንም ባሮቹንና ቤተሰቦቹንም ልጆቹንም ሁሉም ወለዱ ስለ አብርሃም ሚስት ስለሣራ #እግዚአብሔር ማሕፀንን ሁሉ በአፍአ በውስጥ ዘግቶ ነበርና።

ከዚህም በኃላ በጎ ተጋድሎውን ፈጽሞ #እግዚአብሔርንም አገልገሎ በመቶ ሰባ አምስት ዕድሜው ወደ ወደደው #እግዚአብሔር ሔደ።

#ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአባታችን በቅዱስ አብርሃም ጸሎት ይማረን ለዘላለሙ አሜን።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_ይስሐቅ

በዚህችም ቀን ዳግመኛ የአባቶች አለቃ ለሆነ ለአብርሃም ልጅ ለይስሐቅ የዕረፍቱን መታሰቢያ እንድናደርግ የቅድስት ቤተ ክርስቲያን መምህራን አባቶቻችን አዘዙን። ይህ ጻድቅ ይስሐቅም በልዑል አምላክ ብሥራት ተወለደ።

ይህንንም ንጹሕ ይስሐቅን #እግዚአብሔር ለልጁ ክርስቶስ ምሳሌው አደረገው። አብርሃምን እንዲህ ብሎታልና የምትወደው ልጅህ ይስሐቅን ከአንተ ጋራ ውሰደውና ወደላይኛው ተራራ ሒደረ እኔ ወደ እምነግርህ ወደ አንዱ ተራራ ላይ አውጥተህ በዚያ ሠዋው።

አብርሃምም በጥዋት ተነሥቶ አህያውን ጫነ ልጁ ይስሐቅንና ሁለቱ ብላቴኖቹንም ወሰደ ለመሥዋዕትም ዕንጨትን ፈልጦ አሸክሞ ሔደ። በሦስተኛም ቀን #እግዚአብሔር ወዳለው ወደዚያ ቦታ ደረሰ አብርሃምም በዐይኑ ቃኘ ቦታውንም ከሩቅ አየ።

አብርሃምም ብላቴኖቹን እናንተ አህያውን ይዛችሁ ከዚህ ቆዮ እኔና ልጄ ግን ወደ ተራራ እንሔዳለን ሰግደንም ወደ እናንተ እንመለሳለን አላቸው። አብርሃምም መሥዋዕት የሚቃጠልበትን ዕንጨት አምጥቶ ለልጁ ለይስሐቅ አሸከመው እሱም ወቅለምቱንና እሳቱን በጁ ያዘ ሁለቱም በአንድነት ሔዱ።

ይስሐቅም አባቱ አብርሃምን አባ አለው እርሱም ልጄ ምነው አለው እነሆ እሳትና እንጨት አለ መሥዋዕት የሚሆነው በጉ ወዴት ነው አለው አብርሃምም መሥዋዕት የሚሆነውን በግ #እግዚአብሔር ያዘጋጃል አለው።

አብረውም ሔደው #እግዚአብሔር ወዳለው ወደዚያ ቦታ ደረሱ አብርሃምም በዚያ መሠዊያን ሠራ ዕንጨቱን ደረደረ ልጁ ይስሐቅንም አሥሮ ጠልፎ በመሠዊያው በዕንጨቱ ላይ በልቡ አስተኛው። አብርሃምም ልጁን ያርደው ዘንድ እጁን ዘርግቶ ወቅለምቱን አነሣ።

#እግዚአብሔርም አብርሃምን አብርሃም አብርሃም ብሎ ጠራው እርሱም አቤት አለ በልጅህ ላይ እጅህን አትዘርጋ ምንም ምን አታድርግበት አንተ #እግዚአብሔርን እንደምትፈራው አሁን አወቅሁ ለምትወደው ለልጅህ አልራራህለትምና አለው።

አብርሃምም በተመለከተ ጊዜ ቀንድና ቀንዱ በዕፀ ሳቤቅ የተያዘ አንድ በግ አየ አብርሃምም ሔደና ወስዶ በልጁ በይስሐቅ ፈንታ ሠዋው። ይህም ንጹህ ይስሐቅ ጎልማሳ ሲሆን አባቱ ሊሠዋው በአቀረበው ጊዜ #እግዚአብሔር በበግ እስከ አዳነው ድረስ ለአባቱ በመገዛት ለመታረድ አንገቱን ዘርግቶ ሰጠ።

እርሱም በአባቱ በአብርሃም ሕሊና ፍጽም መሥዋዕተ ሆነ። ከዚህም በኃላ ይስሐቅን መቸገርና ስደት አግኝቶታል በአባቱ በአብርሃም ዘመን ከሆነው ሌላ በሀገር ረኃብ ሁኖ ነበርና የፍልስጥዔም ንጉሥ አቤሜሌክ ወዳለበት። ወደ ጌራራ ይስሐቅ ሔዶ በዚያ ተቀመጠ።

የአገር ሰዎችም ይስሐቅን የሚስቱን የርብቃን ነገር ጠየቁት እርሱም እኅቴ ናት አላቸው ስለ ሚስቱ ስለ ርብቃ የዚያች አገር ሰዎች እንዳይገድሉት ሚስቴ ናት ብሎ መናገርን ፈርቷልና መልከ መልካም ነበረችና። በዚያም ብዙ ዘመን ኖሩ አቤሜሌክም በመስኮት በተመለከተ ጊዜ ይስሐቅን ከርብቃ ጋር ሲጫወት አየው።

አቤሜሌክም ይስሐቅን ጠርቶ እኅቴ ናት አልከኝ እንጂ እነሆ ሚስትህ ናት አለው ይስሐቅም በርሷ ምክንያት ይገድሉኛል ብዬ ነው አለው። አቤሜሌክም ይህ ያደረግኽብኝ ነገር ምንድን ነው ከዘመዶቼ የሚሆን አንድ ሰው ከሚስትህ ጋር ሊተኛ ጥቂት ቀርቶት ነበር ባለማወቅም ኃጢአትን ልታመጣብኝ ነበር።

ንጉሡም የዚህን ሰው ሚስቱን የነካ ሁሉ ፍርዱ ይሙት በቃ ነው ብሎ ሕዝቡን አዘዛቸው። ይስሐቅም በዚያች ምድር ዘርን ዘራ መቶ ዕጽፍም ሆነለት #እግዚአብሔርም ባረከው ከፍ ከፍም አለ እጅግም ገነነ ወንድ ባርያን ሴት ባርያን ላምን በግን አብዝቶ ገዛ የፍልስጥኤም ሰዎችም ቀኑበት።

በአባቱም ዘመን የአብርሃም ብላቴኖች የቆፈሩአቸውን ጉድጓዶች የፍልስጥኤም ሰዎች ደፈኑዋቸው አፈርንም መሏቸው። አቤሜሌክም ይስሐቅን ፈጽመህ በርትተህብናልና ከእኛ ተለይተህ ሒድ አለው።

ይስሐቅም ከዚያ ተነሥቶ በጌራራ ሸለቆ ሰፍሮ በዚያ ተቀመጠ። ይስሐቅም ያባቱ አገልጋዮች የቆፈሩዋቸውን አባቱ አብርሃምም ከሞተ በኃላ የፍልስጥኤም ሰዎች የደፈኗቸውን የውኃ ጉድጓዶች እንደገና ቆፈራቸው አብርሃም እንደጠራቸው ጠራቸው።

የይስሐቅም አገልጋዮች በጌራራ ቆላ ጉድጓድ ቆፍረው የሚጣፍጥ የውኃ ምንጭ አገኙ የይስሐቅ እረኞችና የጌራራ እረኞች ይህ ውኃ የኛ ነው የኛ ነው በማለት ተጣሉ ያችንም የውኃ ጉድጓድ የዓመፅ ጉድጓድ ብሎ ጠራት ዐምፀውበታልና።

ይስሐቅም ከዚያ ተጎዞ ሒዶ በዚያ ሌላ ጉድጓድ ቁፈረ በርሷም ምክንያት ተጣሉት ስሟንም ጠብ ብሎ ምክንያት ተጣሉት ስሟንም ጠብ ብሎ ጠራት። ከዚያም ተጎዞ ሒዶ ሌላ ጉድጓድን ቁፈረ በርሱም ምክንያት ግን አልተጣሉትም ስሙንም ሰፊ አለው ዛሬ #እግዚአብሔር አሰፋልን በምድርም አበዛን ሲል።

ከዚህም በኃላ ሁለት ልጆችን ኤሳውንና ያዕቆብን ወለደ። ይስሐቅም ኤሳውን ጽኑዕ ኃይለኛ ስለሆነ ይወደዋል። ይስሐቅም አርጅቶ ዐይኖቹ ፈዘው የማያይ ከሆነ በኃላ እንዲህ ሆነ ታላቁ ልጁ ኤሳውን ጠርቶ እነሆ አረጀሁ የምሞትበትንም ቀን አላውቅም ማዳኛ መሣሪያህን የፍላፃ መንደፊያህን ይዘህ ወደ በረሃ ውጣ። ሳልሞት ነፍሴ እንድትመርቅህ እበላ ዘንድ እንደምወደው አድርገህ አምጣልኝ አለው።

ርብቃም ልጁ ኤሳውን እንዲህ ሲለው ይስሐቅን ሰማችው ኤሳውም ወደ አደን ሔደ። ርብቃም ታናሹ ልጇ ያዕቆብን እንዲህ አለችው እነሆ አባትህ ወንድምህን ኤሳውን ሳልሞት በ #እግዚአብሔር ፊት እንድመርቅህ ከአደንከው አዘጋጅተህ የምበላውን አምጣልኝ ሲለው ሰምቼዋለሁ።

አሁንም ልጄ ሆይ በማዝህ ነገር እሽ በለኝ ወደ በጎቻችንም ሒደህ ያማሩ ሁለት ጠቦቶችን አምጣልኝና አባትህ እንደሚወደው አዘጋጃቸው ዘንድ ሳይሞት በልቶ እንዲመርቅህ ወስደህ ለአባትህ እንድትሰጠው አለችው።

ያዕቆብም እናቱ ርብቃን እንዲህ አላት እነሆ ወንድሜ ኤሳው ጠጉራም ነው እኔ ግን ጠጉራም አይደለሁም ምናልባት አባቴ ቢዳስሰኝ በፊቱ እንደምዘብትበት እሆናለሁና ምርቃን ያይደለ በላዬ መርገምን አመጣለሁ።

እናቱም ልጄ ሆይ መርገምህ በእኔ ይሁን ቃሌን ብቻ ስማኝ ሒድና የምልህን አምጣልኝ አለችው ሒዶም ለእናቱ አመጣላትና አባቱ እንደሚወደው አድርጋ መብሉን አዘጋጀች።

ርብቃም ከርሷ ዘንድ የነበረ ያማረውን የታላቅ ልጅዋ የኤሳውን ልብስ አምጥታ ለታናሽ ልጅዋ ለያዕቆብ አለበሰችው ያንንም የሁለቱን ጠቦቶች ለምድ በትከሻውና በአንገቱ ላይ አደረገች ያንን ያዘጋጀችውን እንጀራና ጣፋጭ መብልን ለያዕቆብ በእጁ ሰጠችው።

ወደ አባቱ ገብቶ አባቴ ሆይ አለው አባቱም እነሆኝ ልጄ ሆይ አንተ ማነህ አለው ያዕቆብም እኔ የበኩር ልጅህ ኤሳው ነኝ ያልከኝን አዘጋጅቻለሁ ተነሥና ተቀመጥ ከአደንኩልህም ብላና ነፍስህ ትመርቀኝ ዘንድ አለው።