TIKVAH-ETHIOPIA
1.43M subscribers
55.6K photos
1.39K videos
200 files
3.74K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#GERD #FDREDefenseForce

ሀገር መከላከያ ሰራዊት፥ ኢትዮጵያ እየገነባች ያለውን ግዙፉን የታላቁ ሕዳሴ የኃይል ማመንጫ ግድብ ግንባታ ለማደናቀፍ ከሱዳን በአልምሃል ሰርጎ ለመግባት የሞከረውን የህወሓት ቅጥረኛ ሃይል ደመሰስኩኝ አለ።

የግድቡን ግንባታ ለማደናቀፍ ተልዕኮ ውስደው የተንቀሳቀሱና ሰራዊቱ የማያዳግም እርምጃ የወሰደባቸው ኃይሎች (የተገደሉ) በቁጥር 50 ሲሆኑ ፤ ከ70 በላይ የሚሆኑት ቁስለኛ ሆነዋል።

መከላከያ ሰራዊት ፥ እርምጃ የወሰደበት ኃይል የተለያዩ ፀረ ሰው እና ፀረ ተሽከርካሪ ፈንጂዎችን ለማጥመድ መሞከሩን ነገር ግን መቋቋም ተስኖት መበታተኑን አሳውቋል።

ይኸው ጥፋት ሊፈፅም የነበረው ኃይል ይጠቀምባቸው የነበሩ ቀላል እና ከባድ የቡድን መሳሪያዎች፣ ፈንጂዎች ወድመዋል ፤ የተቀሩትን ሰራዊቱ ተቆጣጥሯቸዋል።

የመተከል ዞን የተቀናጀ ግብረ ሃይል ኮማንድ ፖስት የኦፕሬሽን ዘርፍ አሰተባባሪ ኮ/ል ሰይፈ ኢንጊ ፣ "አሸባሪው ሕወሃት በግንባር ድል አልቀና ሲለው አብዛኝው ጦር ወደ ሰሜኑ ክፍል አቅንቷል በሚል ከታሪካዊ ጠላቶቻችን ተቀናጅቶ የህዳሴ ግድባችንን ስራ ለማስተጓጎል ለማጥቃት ቢሞክርም አልተሳካለትም" ብለዋል።

በአሁን ሰዓት የኢትዮጵያ የሀገር መከላከያ ሃይል፣ እግረኛና ሜካናይዝድ ክፍለጦሮች እንዲሁም የክልል ልዩ ኃይሎች አስፈላጊውን ዝግጁነት በማረጋገጥ ግዳጃቸውን እየፈፀሙ እንደሚገኙ ተገልጿል።

@tikvahethiopia
#GERD : በህዳሴው ግድብ 2ኛ ዙር የደን ምንጣሮ የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ከ40 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ማግኘታቸው ተገለጸ።

ይህ የተገለፀው የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ቴክኒክ እና ሙያ ስራ እድል ፈጠራ ኤጀንሲ የስራ አፈጻጸሙን በክልሉ መዲና አሶሳ በገመገመበት ወቅት ነው።

የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር የሆኑት አቶ በሽር አብዱራሂም የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ተጠቃሚ መሆን ጀምሯል ያሉ ሲሆን በ2ኛው ዙር የግድቡ ውሃ ሙሌት ደን ምንጣሮ ስራ በክልሉ የሚገኙ በ149 ኢንተርፕራይዞች የተደራጁ ከ1 ሺህ 300 በላይ ስራ አጦች ተሳታፊ መሆናቸውን ገልፀዋል።

አክለውም ፥ የኢንተርፕራዞቹ አባላት 2 ሺህ 736 ሄክታር መሬት የደን ምንጣሮ ስራ ማካሄዳቸውንና በዚህም ከ40 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ማግኘታቸውን ገልጸዋል፡፡

ዘጠኝ ሚሊዮን የሚጠጋ ብር በመቆጠብ ወደ ቋሚ ስራ መሸጋገራቸውን ዋና ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል።

Credit : ENA

@tikvahethiopia
#GERD

ታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን በተመለከተ በአፍሪካ ህብረት በኩል የሚደረገው የሶስቱ ሀገራት ድርድር ውጤት ያመጣል ብለን እናምናለን ይህንንም እንደግፋለን አሉ በኢትዮጵያ እና በአፍሪካ ህብረት የኒውዚላንድ አምባሳደር ሚካኤል አፕተን።

አምባሳደሩ ይህ ያሉት በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ተገኝተው ከሚኒስቴሩ ሚኒስትር ዶ/ር ኢ/ር ሃብታሙ ኢተፋ ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ በመከሩበት ወቅት ነው።

በዚሁ ግዜ ነው አምባሳደሩ የአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነትን እንደሚደግፉ አሳውቀዋል።

በቀጣይ ግዜም የዜሮ ካርበን ልቀት መጠን ግብን ለማሳካት በአፍሪካ ህብረት በኩል የገንዘብ ድጋፍ ለማድረግ ሃገራቸው ማቀዷን ገልጸው ከዚህ ውስጥ #ኢትዮጵያ አንዷ መሆኗን ጠቁመዋል።

ሚኒስትሩም በጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አቢይ አህመድ መሪነት ባለፉት ሁለት አመታት ከ4 ቢሊየን በላይ የተለያዩ አይነት ችግኞት መተከላቸውን ገልጸው ይህ ተግባር የአባይ ወንዝ ጨምሮ በሃገሪቱ ያሉ የውሃ አካላትን ደህንነት ለመጠበቅ የሚያስችል ነው ብለዋል።

የህዳሴ ግድብም ለሱዳንና ልግብፅ ያለውን ጥቅም አስረድተዋቸዋል።

ሚኒስትሩና አምባሳደሩ በቀጣይ በጋራ በሚሰሯቸው ታዳሽ ሀይል ልማት፤ የውሃና ሳኒቴሽን፤ ድርቅን፣ የአከባቢ ጥበቃና እንክብካቤ እንዲሁም የአየር ንብረት ለውጥን በተመለከቱ ጉዳዮች ላይ መምከራቸው ተገልጿል።

@tikvahethiopia
#GERD

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ እና ምክትል ጠ/ሚና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን የታላቁ ህዳሴ ግድብን የግንባታ ሂደት ጎበኙ፡፡

በጉብኝት መርሀ ግብሩ የተለያዩ የፌዴራል መስሪያ ቤቶች ሚኒስትሮች ተሳትፈዋል፡፡

የሁሉም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች የ100 ቀናት የእቅድ አፈጻጸም ግምገማ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት በህዳሴ ግድብ መገኛ በሆነችው ጉባ እየተካሄደ ነው፡፡

Credit : FBC

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ItsMyDam🇪🇹 ሀገራችን ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. ከ2022 ጀምሮ ከታላቁ የኅዳሴ ግድብ በዓመት 700 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት እንደምትጀምር የኢትዮጵያ የኢኖቬስን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የአይሲቲ እና ዲጂታል ኢኮኖሚ ሚኒስትር ደኤታ ሁሪያ አሊ ማህዲ አስታወቁ። ኢትዮጵያ በዚሁ ከመጀመሪያ ዙር እንደምታመነጭ ከሚጠበቀው የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት አጠቃላይ የሀገሪቱን የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት…
#GERD🇪🇹

አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ስለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በዚህ ሳምንት በሰጡት መግለጫ ከተናገሩት ፦

(ከሪፖርተር)

" ... የታላቁ ህዳሴ ግድብ ኤሌክተሪክ ማመንጨት የሚጀምርበትን ቀን ይህ ነው ብሎ መነገር ባይቻልም፣ በጣም በቅርብ ጊዜ ይጀምራል።

የግድቡ ጉዳይ ሊለወጥ የማይችልና ያለቀ ነገር በመሆኑ፣ የታችኛው ተፋሰስ አገሮች ከዚህ ካለቀ ጉዳይ ጋር አብረው መቆም አለባቸው።

ከዚህ በኋላ ግድቡ ሲያመነጭ ለግብፆችም ሆነ ለሱዳኖች ጠቃሚ ከመሆኑም በላይ ፣ በሚመነጨው ኃይል ሌሎችም አገሮች ተጠቃሚ እንዲሆኑ እነዚህ አገሮች ቢሠሩ መልካም ነው። ነገር ግን የሦስትዮሽ ድርድሩ ይቁም ማለት አይደለም።

ሱዳን እና ግብፅ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት ከጀመራቸሁ ችግር ይፈጠራል፣ ሰማዩ ይገለባበጣል የሚሉት ነገር አዲስ አይደለም፡፡

ቀድሞውንም ሙሌት ከጀመራችሁ አደጋ ይፈጠራል፣ ጉድ ይፈላል ሲሉ ነበር ይህ ፉከራ የተለመደ ቢሆንም አሁን ግን ያረጀና ጊዜው ያለፈበት ሆኗል።

በህዳሴ ግድቡ ውኃው ተርባይኑን አንቀሳቅሶ አልፎ ስለሚሄድ መጠኑ ስለማይቀንስ፣ ሱዳኖች የግድቡ ኃይል ማመንጨት መጀመር ሊያስደስታቸው እና ሊያከብሩት ይገባል። "

@tikvahethiopia
#GERD #ItsMyDam 🇪🇹

የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ለአል-አረቢያ ሚዲያ የተናገሩት ፦

" ... ሀገራችን ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታን በፍጥነት እንድታጠናቅቅ ግብፅ ማበረታታት አለባት።

ግድቡ ግብፅን በድርቅ ወቅት እንኳ የውሃ ቋት ሆኖ የሚያገለግል እንደመሆኑ ፕሮጀክቱን ልትደግፈው ይገባል።

ሱዳን በአነስተኛ ግድቦቿ ላይ ይደርስብኛል ብላ የምታነሳውን የደህንነት ስጋት በሚመለከት መደበኛ የሆነ የመረጃ ልውውጥ ለማድረግ ኢትዮጵያ ዝግጁ እንደሆነች አቋሟን አስርድታለች።

ሀገሪቱ ግን አሁን ላይ የራሷን ብሄራዊ ጥቅም ከማስጠበቅ ይልቅ የሶስተኛ ወገን ጉዳይ አስፈፃሚ አየሆነች መጥታለች።

ኢትዮጵያ አንድ ወገን ብቻ ከአባይ ሀብት ተጠቃሚ ሲሆን ዘላለም አለሟን መጠበቅ አትችልም። በመሆኑም ሱዳን እና ግብፅ አሁን ላይ ከያዙት ግትር አቋም መላቀቅ አለባቸው።

ኢትዮጵያ የግድቡን ግንባታ በሚመለከት ብዙ አዎንታዊ የሆኑ እድሎችን አቅርባ ነበር። ግብፅና ሱዳን ባለመቀበላቸው ምክንያት ግን ሳይሳኩ ቀርተዋል።

የህዳሴ ግድብ ከጭቅጭቅ ይልቅ የቀጠናዊ ህብረትና አንድነት ማሳያ ነው። ኢትዮጵያ በታችኞቹ ተፋሰስ ሀገራት ላይ ምንም አይነት የጎላ ጉዳት ሳታደረስ የራሷን ሀብት መጠቀም ትችላለች "

(ኤፍቢሲ)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ጉዳይ ? ከሰሞኑን በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ "የታላቁ ህዳሴ ግድብ ኃይል ማመንጨት ጀመረ" የሚሉ በርካታ መልዕክቶች እየተዘዋወሩ ይገኛሉ። መንግስት በዚህ ጉዳይ በይፋ ያሳወቀው ነገር ባይኖርም ከዚህ ቀደም የታላቁ ህዳሴ ግድብ ኃይል ለማመንጨት መቃረቡ በተደጋጋሚ ተገልጿል። ከሰሞኑን በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ሲሰራጩ ለነበሩት የግድቡ መረጃዎች ምንጫቸውን ለማወቅ ብናስስም ልንደርስበት…
#GERD

የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ነገ እሁድ የካቲት 13 ቀን 2014 ዓ.ም የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት እንደሚጀምር አጀንስ ፍራንስ ፕሬስ (AFP) ሁለት ስማቸው ያልተገለፀ የኢትዮጵያ ከፍተኛ ባለስልጣናትን ዋቢ አድርጎ በዛሬው ዕለት ዘግቧል።

ዛሬ አንድ ከፍተኛ የኢትዮጵያ መንግስት ባለስልጣን [ስማቸው ያልተገለፀ] " ነገ የግድቡ የመጀመሪያው የሃይል ማመንጫ ይሆናል" ሲሉ ቃላቸውን ሰጥተዋል።

አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ (AFP) ሌላ ሁለተኛ ከፍተኛ ባለስልጣን መረጃውን ማረጋገጣቸውን ገልጿል።

ሁለቱም ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ስማቸው እንዳይገለጽ የፈለጉት ጉዳዩ በይፋ ስላልተገለፀ ነው ተብሏል።

ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ መንግስት የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በቅርቡ ኃይል ማመንጨት እንደሚጀምር የገለፀ ሲሆን መቼ ? ለሚለው ግን መረጃ አልሰጠም ነበር።

ይኸው ጉዳይ ባለፉት ቀናት በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ሲዘዋወር ነበር፤ ነገር ግን በመንግስት በኩል ይፋዊ መረጃ አልተሰጠም።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#GERD የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አንደኛው ሁኒት [ ዩኒት 10 ] ኃይል ማመንጨት መጀመሩን የግድቡ ሰራተኞች ለብሄራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ ተናግረዋል። @tikvahethiopia
#GERD

የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ስራ አስኪያጅ ኢ/ር ክፍሌ ሆሮ ፦

"... ማመንጨት ተጀመረ እንጂ ፕሮጀክቱ ተጠናቀቀ ማለት አይደለም።

ፕሮጀክቱን ለመጠናቀቅ አሁን ብለው ሁኔታ ከሁለት ዓመት ተኩል እስከ ሶስት ዓመት ሊፈጅብን ይችላል።

ስለዚህ ህዝቡ ከመጀመሪያውም ፕሮጀክቱ የኢትዮጵያውያን ፕሮጀክት ነው። ፋይናንስ ሚደረገው በመንግስትና በኢትዮጵያ ነው ስለዚህ ይሄን ተገንዝበን ፕሮጀክቱን እስከመጨረሻው ፋይናንስ ማድረግ አለብን።

የኢትዮጵያን እውነታ አሁን ተርባይኑን መቶ ነው ውሃ እየፈሰሰ ያለው ስለዚህ ኢትዮጵያ ከዚህ ውሃ ምንም የምትቀንሰው ነገር ስለሌለ ዓለምም ይህን እንዲረዳ እያንዳንዳችን ተረባርበን ለፕሮጀክቱ ዲፕሎማት ሆነን መንቀሳቀስ አለብን። "

@tikvahethiopia
#GERD

" ግድቡን እኛ ሳንሆን እነሱ ናቸው የሚጠብቁት " - የቀድሞ የሀገራችን ጠ/ሚ መለስ ዜናዊ

@tikvahethiopia
#GERD

" ... በወንዞቻችን ለመጠቀም እና ድህነትን ለማስወገድ የምናደርገው ጥረት እራሳችንን እና ጎረቤቶቻችንን ጭምር ለመጥቀም እንጂ ማንንም ለመጉዳት እንዳልሆነ ለዓባይ ልጆች ሁሉ ለማረጋገጥ እፈልጋለሁ " - የቀድሞ የሀገራችን ጠ/ሚ ሀኃይለማርያም ደሳለኝ

@tikvahethiopia
#GERD

" ... የታላቁ ህዳሴ ግድብን እንጨርሰዋለን። የታላቁ ህዳሴ ግድብን የምንጨርሰው ልጆቻችንን መጀመር ብቻ ሳይሆን መጨረስም እንደምንችል እንዲያውቁት ስለምንፈልግም ጭምር ነው " - የአሁኑ የሀገራችን ጠ/ሚር ዶክተር ዐቢይ አህመድ

@tikvahethiopia
#GERD🇪🇹

" የታላቁ ህዳሴ ግድብ 3ኛውን የውሃ ሙሌት ለማከናወን በ21 ሺ ሄክታር መሬት ላይ የምንጣሮ ስራ እየተከናወነ ነው ፤ ሰራተኞች ያለምንም የፀጥታ ስጋት ስራቸውን እንዲያከናውኑ በትኩረት እየተሰራ ነው " - ሌ/ጀኔራል ደስታ አብቼ

የመተከል ዞን የተቀናጀ ኮማንድ ፖስት ዋና አስተባባሪ ሌ/ጀኔራል ደስታ አብቼ ፥ ኢትዮጵያ በአባይ ወንዝ ላይ እየገነባችው የምትገኘው የታላቁ ህዳሴ ግድብ ያለምንም ፀጥታ ችግር እንዲከናወን በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል።

ሌ/ጀኔራል ደስታ " ሠራዊቱ የተሠጠውን ተልኮ ሌት ተቀን በቁርጠኝነት መፈፀም በመቻሉ ለህዳሴ ግድብ ግንባታ የሚውሉ ግብአቶች በሰላም ተጓጉዘው እንዲደርሱ እና ሰራተኞችም ደህንነታቸው ተጠብቆ እንዲሰሩ ማድረግ ተችሏል " ብለዋል።

የታላቁ ህዳሴ ግድብ #3ኛውን_የውሃ_ሙሌት ለማከናወን በ21 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የምንጣሮ ስራ እየተከናወነ መሆኑን የገለፁት ሌ/ጀኔራሉ " የግድቡ ግንባታ ሰራተኞች ያለምንም የፀጥታ ስጋት ስራቸውን እንዲያከናውኑ የተቀናጀ የፀጥታ ሃይሉ በትኩረት እየሰራ ነው " ብለዋል።

አክለውም " የተቀናጀ የፀጥታ ሃይሉ ዕድገታችንን ለማደናቀፍ #ከሱዳን ሰርገው የሚገቡ ኃይሎችን እየተከታተለ ሴራቸውን እያከሽፈው ይገኛል ፤ በቀጣይም ከአካባቢው ማህበረሰብ እና ሲቪል አመራሮች ጋር ተቀናጅቶ ግዳጁን በአስተማማኝ ለመወጣት ዝግጁነቱ የላቀ ነው " ሲሉ ተናግረዋል።

#FDRE_Defense_Force🇪🇹

ፎቶ ፦ ፋይል

@tikvahethiopia
#GERD

የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ 3ኛ ዙር ሙሌት ከመጪው ሐምሌ ወር አንስቶ መከናወን እንደሚጀምር አንድ ስማቸው እንዲገለፅ ያልወደዱ የግድቡ ከፍተኛ የስራ ኃላፊን ዋቢ አድርጎ ሪፖርተር ጋዜጣ አስነብቧል።

ከክረምቱ መግባት ጋር ተያይዞ ወደ ግድቡ የሚፈሰው የውኃ መጠን ከሰኔ አጋማሽ ጀምሮ ከፍ እያለ ከሄደ በኋላ ወደ ግድቡ የሚገባውን ውኃ በመያዝ በሐምሌ ወር ሙሌቱ ይጀመራል ብለዋል ኃላፊው።

በዚህ ዓመት ወደ ግድቡ እንዲገባ የሚጠበቀውን የውኃ መጠን ለመያዝ የግድቡን ቁመት የመጨመር ሥራ እየተከናወነ መሆኑንም ገልፀዋል። የውኃ ሙሌቱ ሲጀመር የግድቡ ቁመት በሚፈለገው መጠን እንደሚደርስ አስረድተዋል፡፡

ባለፈው ዓመት ሁለተኛው ዙር የውኃ ሙሌት በሰኔ ወር መጨረሻ ሲጀመር በነሐሴ ወር አጋማሽ እንደሚጠናቀቅ ተነግሮ የነበረ ቢሆንም፣ በዓመቱ በነበረው ከፍተኛ መጠን ያለው የዝናብ ፍሰት የተነሳ መጠናቀቁ የተበሰረው ሐምሌ 12 ቀን 2013 ዓ.ም. ነበር።

#ሪፖርተር

@tikvahethiopia
#GERD #ETHIOPIA 🇪🇹

🇪🇹 የቀድሞ የሀገራችን ጠ/ሚ አቶ መለስ ዜናዊ ፦

" ... ምንም የሚያጠራጥር ነገር የለም፤ ይሄ ግድብ ይሰራል።

ይሄን ግድብ የሚያቆም ምንም ኃይል የለም። "

🇪🇹 የቀድሞ የሀገራችን ጠ/ሚ ሀኃይለማርያም ደሳለኝ ፦

" ... በወንዞቻችን ለመጠቀም እና ድህነትን ለማስወገድ የምናደርገው ጥረት እራሳችንን እና ጎረቤቶቻችንን ጭምር ለመጥቀም እንጂ ማንንም ለመጉዳት እንዳልሆነ ለዓባይ ልጆች ሁሉ ለማረጋገጥ እፈልጋለሁ "

🇪🇹 የአሁኑ የሀገራችን ጠ/ሚር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ፦

" ... የታላቁ ህዳሴ ግድብን እንጨርሰዋለን። የታላቁ ህዳሴ ግድብን የምንጨርሰው ልጆቻችንን መጀመር ብቻ ሳይሆን መጨረስም እንደምንችል እንዲያውቁት ስለምንፈልግም ጭምር ነው "

#ታላቁ_የኢትዮጵያ_ህዳሴ_ግድብ💪

@tikvahethiopia
#ETHIOPIA #GERD

" አሁን ላይ በተገኘው አንፃራዊ ሰላም የኮንቮይ ጉዞ ያለምንም ችግር #በአንድ_ቀን መድረስ ችሏል " - ኢ/ር በላቸው ካሳ

የኢትዮጵያ ታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ እየተካሄደ በሚገኝበት ቀጠና በተገኘው ሰላም የግድቡ ግንባታ እየተፋጠነ መሆኑ ተገልጿል።

የግድቡ ምክትል ስራ አስኪያጅ የሆኑት ኢንጂነር በላቸው ካሳ ፤ " በቀጠናው የተገኘው አስተማማኝ ሰላም የግድቡን የግንባታ ሂደት #እያፋጠነው ይገኛል " ሲሉ አሳውቀዋል።

" የፀጥታው ጉዳይ ለግድቡ ግንባታ መሠረታዊ ፍላጎት መሆኑን በመገንዘብ #የሀገር_መከላከያ_ሰራዊት ከሌሎች የፀጥታ ሃይሎች ጋር ተቀናጅቶ ተልዕኮውን በጀግንነት በመፈፀም በቀጠናው የከፈለው መስዋዕትነት የኢትዮጵያን ህዝብና መንግስት ያኮራ በታሪክ የሚኖር ነው  " ብለዋል።

ኢ/ር በላቸው፤ በቀጠናው በነበረው የሰላም ችግር ምክንያት ወደ ግድቡ የሚመላለሱ ተሽከርካሪዎች ከሁለትና ከሶስት ቀን በላይ በመቆም መስተጓጎል ይፈጥር እንደነበር አስታውሰው አሁን ላይ የኮንቮይ ጉዞ በተገኘው አንፃራዊ ሰላም ያለምንም ችግር #በአንድ_ቀን መድረስ መቻሉን አስረድተዋል።

የግድቡን ግንባታ ዳር ለማድረስ ሌት ተቀን ሃያ አራት ሰዓት ያለ ዕረፍት የሚተጉ የግንባታዉ ሰራተኞች የአካባቢውን የሙቀት ሁኔታ ተቋቁመው ታሪካዊ ሃላፊነታቸውን በደማቅ ሞራል እየተወጡ እንደሚገኙ አረጋግጠዋል።

በስፍራው ከሚገኙ የሀገር መከላከያ አባላት የቀጠናውን ዘላቂ ሰላም በአስተማማኝ የዝግጁነት ደረጃ በማረጋገጥ ሰራዊቱ የተሰጠውን ግዳጅ በሞራል እየተወጣ እነደሆነ ተናግረዋል።

ሰራዊቱ የሀገሪቱን ሰላም የማይፈልጉ ፀረሠላም የሆኑ ኃይሎችን ፍላጎት በማምከን የግድቡን የፍፃሜ ትንሳኤ ለማብሰር ደከመኝ ሳይል ሀገራዊ ተልዕኮዉን እየተወጣ ነው ብለዋል።

#FDREDefenseForce

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#GERD🇪🇹

" በተያዘው በጀት ዓመት ሌሎች ተጨማሪ ተርባይኖች ወደ ስራ ይገባሉ " - ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ

ኢትዮጵያ ዛሬ 4ኛውን የታላቁ የህዳሴ ግድብ (የአባይ ግድብ) የውሃ ሙሌት መጠናቀቁን በይፋ አብስራለች።

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ይኸኛው 4ኛ ዙር ሙሌት የመጨረሻው ስለመሆኑን በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ አስፍረዋል።

ሙሌቱ በስኬት በመጠናቀቁ በገንዘባቸው፣ በዕውቀታቸው ፣ በጉልበታቸው ፣ በፀሎታቸው በስራው ለተሳተፉ ምስጋና አቅርበው " እንኳን ደስ አላችሁ " ብለዋል።

ለኢዜአ ቃላቸውን የሰጡት የኢትዮጵያ ተደራዳሪ ቡድን መሪና በአሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ ዳግሞ ፤ ባለፉት 4 ዓመታት የውሃ ሙሌት ስራውን ለማከናወን የሚያስችል በቂ የዝናብ መጠን መገኘቱን አስረድተዋል።

የውሃ ሙሌት ስራው በታችኛው ተፋሰስ አገራት ላይ ምንም አይነት ጉዳት በማያደርስ መልኩ መከናወኑን ገልጸዋል።

ለአብነትም በዘንድሮው ክረምት በግብጽ የሚገኘው የአሰዋን ግድብ ከበቂ በላይ ውሃ በመያዙ ምክንያት በግድቡ ማስተንፈሻ አማካኝነት ውሃ የማፋሰስ ስራ ሲያከናወን መቆየቱን ጠቁመዋል፡፡

ይህም ታላቁ የህዳሴ ግድብ የሶስቱ አገራት የትብብር ምንጭ ከመሆን ባሻገር በታችኛው ተፋሰስ አገራት የሚያስከትለው ጉዳት እንደሌለ በተግባር ያመላከተ ስለመሆኑ አብራርተዋል፡፡

አሁን ላይ ኃይል ማመንጨት የጀመሩት ሁለቱ ተርባይኖች በስራ ላይ መሆናቸውን ጠቅሰው፤ በተያዘው በጀት ዓመት ሌሎች ተጨማሪ ተርባይኖች ወደ ስራ እንደሚገቡ አሳውቀዋል።

4ኛው ዙር የውሃ ሙሌት በስኬት መጠናቀቁ በግድቡ ግንባታ ሂደት ሌላኛውን አዲስ ምዕራፍ የከፈተ መሆኑንም ገልጸዋል።

ከዚህ በኋላ የሚኖሩት ስራዎች ከዚህ ቀደም ከተለፈባቸው የተሻሉ እንደሚሆኑ የጠቀሱት ዶ/ር ኢንጅነር ስለሺ ፤ " ይህ ለኢትዮጵያዊያን ትልቅ ስኬት ነው " ብለዋል፡፡

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#GERD🇪🇹 " በተያዘው በጀት ዓመት ሌሎች ተጨማሪ ተርባይኖች ወደ ስራ ይገባሉ " - ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ ኢትዮጵያ ዛሬ 4ኛውን የታላቁ የህዳሴ ግድብ (የአባይ ግድብ) የውሃ ሙሌት መጠናቀቁን በይፋ አብስራለች። ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ይኸኛው 4ኛ ዙር ሙሌት የመጨረሻው ስለመሆኑን በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ አስፍረዋል። ሙሌቱ በስኬት በመጠናቀቁ በገንዘባቸው፣ በዕውቀታቸው ፣ በጉልበታቸው…
#GERD🇪🇹

ግድቡ ከዚህ በኃላ ውሃ አይዝም ?

" 4ኛና የመጨረሻው ሲባል ከዚህ በኋላ የውሃ ሙሌት አይደረግም ማለት እንዳልሆነ መታወቅ አለበት " - ዶ/ር ኢ/ር ሃብታሙ ኢተፋ

የታላቁ ሕዳሴ ግድብ አራተኛ ዙር ሙሌት መጠናቀቅን ተከትሎ ጠቅላይ ሚኒስትሩ " የመጨረሻ ሙሌት " ሲሉ መግለፃቸውን ተከትሎ በርካቶች " ግድቡ ከአሁን በኃላ ውሃ አይዝም ? " የሚል ጥያቄ ፈጥሮባቸዋል።

ይህንን በተመለከተ ቃላቸውን ለኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 ሬድዮ ጣቢያ የሰጡት የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶክተር ኢንጂነር ሃብታሙ ኢተፋ ተከታዩን ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ዶ/ር ኢ/ር ሃብታሙ ኢተፋ ፦

" አራተኛና የመጨረሻው የውሃ ሙሌት የተባለው  አራቱ ዙሮች ከፍተኛ የውሃ መጠን የሚያስፈልጋቸው በመሆኑ ነው።

በእነዚህ አራት ዙሮች ግድቡ መያዝ ያለበትን የውሃ መጠን መያዝ ችሏል።

አራተኛና የመጨረሻው ሲባልም ከዚህ በኋላ የውሃ ሙሌት አይደረግም ማለት እንዳልሆነ መታወቅ አለበት።

ይልቁንም ግድቡ #እየተጠናቀቀ በመሆኑ ፣ ከፍተኛ የውሃ መጠን ሳያስፈልግ ይከናወናል። "

Credit - Ethio FM 107.8

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#GERD🇪🇹 " በተያዘው በጀት ዓመት ሌሎች ተጨማሪ ተርባይኖች ወደ ስራ ይገባሉ " - ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ ኢትዮጵያ ዛሬ 4ኛውን የታላቁ የህዳሴ ግድብ (የአባይ ግድብ) የውሃ ሙሌት መጠናቀቁን በይፋ አብስራለች። ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ይኸኛው 4ኛ ዙር ሙሌት የመጨረሻው ስለመሆኑን በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ አስፍረዋል። ሙሌቱ በስኬት በመጠናቀቁ በገንዘባቸው፣ በዕውቀታቸው ፣ በጉልበታቸው…
#GERD🇪🇹

ኢትዮጵያ በትላንትናው ዕለት አራተኛውን ዙር የውሃ ሙሌት ማጠናቀቋን በይፋ ማሳወቋ ይታወሳል።

የውሃ ሙሌቱን በተመለከተ የኢትዮጵያ ተደራዳሪ ቡድን መሪና በአሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር ዶ/ር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ ፤ የውሃ ሙሌት ስራው በታችኛው ተፋሰስ አገራት ላይ ምንም አይነት ጉዳት በማያደርስ መልኩ መከናወኑን መግለፃቸው አይዘነጋም።

በተለይ በዘንድሮው ክረምት በግብጽ የሚገኘው የአሰዋን ግድብ ከበቂ በላይ ውሃ በመያዙ ምክንያት በግድቡ ማስተንፈሻ አማካኝነት ውሃ የማፋሰስ ስራ ሲያከናወን መቆየቱን በመጠቆም ታላቁ የህዳሴ ግድብ የሶስቱ አገራት የትብብር ምንጭ ከመሆን ባሻገር በታችኛው ተፋሰስ አገራት የሚያስከትለው ጉዳት እንደሌለ በተግባር ያመላከተ ስለመሆኑ አብራርተዋል።

ግብፅ ግን በግድቡ ውሃ ሙሌት ዜና መበሳጨቷን የሚገልፅ መግለጫ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሯ በኩል አውጥታለች።

ኢትዮጵያ የግድቡን ውሃ ሙሌት ያከናወነችው መጋቢት 14፣ 2007 ዓ/ም ላይ በግብፅ ፣ ኢትዮጵያ ፣ ሱዳን የተፈረመውን የመርሆዎች ስምምነት በሚጥስ ሁኔታ ነው ብላለች ግብፅ።

" በተፈራረምነው የመርህዎች ስምምነት መሠረት በግድቡ አሞላል እና ኦፕሬሽን ላይ አስገዳጅ ስምምነት ሳይደረስ የውሃ ሙሌት ማድረግ የተከለከለ ነው " ስትል ገልጻለች።

" የኢትዮጵያ የአንድ ወገን እርምጃ በዓለም አቀፍ ሕግ መርሆዎች የተረጋገጡትን የታችኛው ተፋሰስ አገራትን ጥቅምና መብት እንዲሁም የውሃ ደኅንነታቸውን ያላገናዘበ ነው "  ብላለች።

በሥልጣን ሹኩቻ በርስ በርስ ጦርነት ውስጥ የገባችው የታችኛው ተፋሰስ አገር ሱዳን የ4ኛው ዙር የውሃ ሙሌትን በተመለከተ እስካሁን ያለችው ነገር የለም።

ኢትዮጵያ፣ ሱዳን እና ግብፅ የሕዳሴ ግድብ ውሃ አሞላል እና ኦፕሬሽንን በተመለከተ በአዲስ አበባ፣ ካይሮ እና ካርቱም ተደጋጋሚ ድርድሮችን ያደረጉ ቢሆንም እስካሁን ከስምምነት መድረስ ሳይችሉ ቆይተዋል።

በቅርቡም ለሁለት ዓመት ያህል ተቋርጦ የቆየው ድርድር በነሐሴ ወር አጋማሽ ላይ በካይሮ ተካሂዶ ያለውጤት ተበትኗል። ይህ ውይይት በመስከረም 2016 በኢትዮጵያ እንዲቀጥል ከስምምነት ላይ ተደርሷል።

ኢትዮጵያ የውሃ ሙሌቱ እንዲሁም አጠቃላይ የግድቡ ግንባታ፣ በታችኛው የተፋሰስ አገራት ላይ ምንም አይነት ጉዳት እንደማያደርስ በተደጋጋሚ ማሳወቋ ይታወቃል።

@tikvahethiopia
#GERD🇪🇹

" ግብፅ #የቅኝ_ግዛት ዘመን አስተሳሰቧን ይዛ በመቀጠል ወደ ስምምነትና ትብብር የሚወስደውን መንገድ ዘግታለች " - ኢትዮጵያ

ባለፉት ቀናት ኢትዮጵያ፣ ግብፅ እና ሱዳን አዲስ አበባ ውስጥ የሕዳሴ ግድብ የውሃ አሞላል እንዲሁም ዓመታዊ የሥራ ሂደትን የተመለከተ መመሪያ ላይ የሦስትዮሽ ድርድር ሲያካሂዱ ነበር።

ድርድሩ ያለ ስምምነት ነው የተጠናቀቀው።

ኢትዮጵያ ምን አለች ?

- ኢትዮጵያ በሰላማዊ መንገድ እና በፍትሐዊ ድርድር የሶስቱን ሀገራት ጥቅም የሚያስጠብቅ የመፍትሔ ሀሳብ ላይ ለመድረስ ያላትን ቁርጠኝነት ይዛ እንደምትቀጥል ገልጻለች።

- አራት ዙር ድርድር ተካሂዷል ፤ ይህ ድርድር የተካሄደው በጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) እና በፕሬዚዳንት አብዱልፈታህ ኤል ሲሲ የጋራ መግባባት ነው።

- በአራት ዙሮች ኢትዮጵያ ከታችኛው የተፋሰሱ ሀገራት ጋር ልዩነቶችን ለመፍታትና የሰላም ስምምነት ላይ ለመድረስ ጥረት አድርጋለች።

- ግብፅ #የቅኝ_ግዛት ዘመን አስተሳሰቧን ይዛ በመቀጠል ወደ ስምምነትና ትብብር የሚወስደውን መንገድ ዘግታለች።

- የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የመጀመሪያ አሞላል እና ዓመታዊ አሰራር መመሪያ እና ደንቦች ላይ የተደረገው ድርድር በሶስቱ ሀገራት መካከል መተማመን ለመፍጠር እንጂ በአባይ ውሃ አጠቃቀም ላይ የኢትዮጵያን መብት ለመንጠቅ ያለመ አይደለም።

- ኢትዮጵያ የውሃ ሀብቷን በፍትሃዊና ምክንያታዊ አጠቃቀም መርህ ላይ በመመስረት የአሁንና የመጪውን ትውልድ ፍላጎት ለማሟላት ጥረቷን አጠናክራ ትቀጥላለች።

- አራተኛው ዙር ድርድር ከተጠናቀቀ በኋላ የተባበሩት መንግስታት ድርጅትን ቻርተር እና የአፍሪካ ህብረት ህገ-መንግስታዊ ድንጋጌን የሚጻረር መግለጫ ግብጽ አውጥታለች። ኢትዮጵያ በግብፅ በኩል የቀረበባትን የተሳሳተ መረጃ አትቀበለውም።

ግብፅ ምን እያለች ነው ?

* " ኢትዮጵያ የሦስቱንም አገራት ጥቅም ሊያስጠብቅ እና ሊያስማማ የሚችል የሕግም ሆነ የቴክኒክ መፍትሄዎችን ለመቀበል ዝግጁ አይደለችም " የሚል ነገር ይዛ ብቅ ብላለች።

* " የግድቡን አሞላል እና ኦፕሬሽን በቅርበት በመከታተል መብቴን አስከብራለሁ " ስትልም ጠንከር ያለ መግለጫ አውጥታለች።

* ግብፅ " በግድቡ ምክንያት የትኛውም አይነት ጉዳት ቢደርስብኝ በዓለም አቀፍ ቻርተሮች እና ስምምነቶች መሠረት የውሃ ድርሻዬን እና ብሔራዊ ደኅንነቴን የመጠበቅ መብቴ የተጠበቀ ነው " ስትልም መግለጫ አውጥታለች።

🇪🇹 ኢትዮጵያ #በተደጋጋሚ ጊዜ አንዳቸውም የታችኛው ተፋሰስ ሀገራት በአባይ ግድብ ምክንያት ጉዳት እንደማይደርስባቸው ይልቁንም እነሱኑ እንደሚጠቅም አሳውቃለች።

@tikvahethiopia