TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#GERD🇪🇹 " በተያዘው በጀት ዓመት ሌሎች ተጨማሪ ተርባይኖች ወደ ስራ ይገባሉ " - ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ ኢትዮጵያ ዛሬ 4ኛውን የታላቁ የህዳሴ ግድብ (የአባይ ግድብ) የውሃ ሙሌት መጠናቀቁን በይፋ አብስራለች። ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ይኸኛው 4ኛ ዙር ሙሌት የመጨረሻው ስለመሆኑን በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ አስፍረዋል። ሙሌቱ በስኬት በመጠናቀቁ በገንዘባቸው፣ በዕውቀታቸው ፣ በጉልበታቸው…
#GERD🇪🇹

ግድቡ ከዚህ በኃላ ውሃ አይዝም ?

" 4ኛና የመጨረሻው ሲባል ከዚህ በኋላ የውሃ ሙሌት አይደረግም ማለት እንዳልሆነ መታወቅ አለበት " - ዶ/ር ኢ/ር ሃብታሙ ኢተፋ

የታላቁ ሕዳሴ ግድብ አራተኛ ዙር ሙሌት መጠናቀቅን ተከትሎ ጠቅላይ ሚኒስትሩ " የመጨረሻ ሙሌት " ሲሉ መግለፃቸውን ተከትሎ በርካቶች " ግድቡ ከአሁን በኃላ ውሃ አይዝም ? " የሚል ጥያቄ ፈጥሮባቸዋል።

ይህንን በተመለከተ ቃላቸውን ለኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 ሬድዮ ጣቢያ የሰጡት የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶክተር ኢንጂነር ሃብታሙ ኢተፋ ተከታዩን ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ዶ/ር ኢ/ር ሃብታሙ ኢተፋ ፦

" አራተኛና የመጨረሻው የውሃ ሙሌት የተባለው  አራቱ ዙሮች ከፍተኛ የውሃ መጠን የሚያስፈልጋቸው በመሆኑ ነው።

በእነዚህ አራት ዙሮች ግድቡ መያዝ ያለበትን የውሃ መጠን መያዝ ችሏል።

አራተኛና የመጨረሻው ሲባልም ከዚህ በኋላ የውሃ ሙሌት አይደረግም ማለት እንዳልሆነ መታወቅ አለበት።

ይልቁንም ግድቡ #እየተጠናቀቀ በመሆኑ ፣ ከፍተኛ የውሃ መጠን ሳያስፈልግ ይከናወናል። "

Credit - Ethio FM 107.8

@tikvahethiopia