TIKVAH-ETHIOPIA
1.43M subscribers
55.6K photos
1.39K videos
200 files
3.74K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#አክሱም #Axum

በጣሊያን ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስተር የተመራ ልዑካን ቡድን #የአክሱም_ሀውልትን ጎበኘ። ለስራ ጉብኝት ኢትዮጵያ የሚገኘው በጣሊያን ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒትሯ አማንኤላ የተመራው ቡድን የአክሱም ሀውልት ጎብኝቷል፡፡ በጉብኝቱ ወቅት በቅርሱ ላይ እየታየ ያለውን ችግር በባለሞያዎቹም ገለፃ ተደርጎላቸዋል።

የልዑካን ቡድን አባላቱ ቅርሱ የተደቀነበትን ችግር በአስቸኳይ ለመንግስታቸው በማሳወቅ ቅርሱ ጥገና የሚደረግበትን መንገድ እናመቻቻለን ብለዋል፡፡ በቀጣይ ሁለት ሳምንታት ዉስጥም ባለሞያዎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚላኩም ተናግረዋል።

ልዑካን ቡድኑ በቅርሱ በአካል የተመለከቱትን ችግር ለመንግስታቸው አቅርበው ምላሽ እንደሚያገኙ እምነት እንዳለቸው የባህልና ቱሪዝም ሚኒስተር የባህል ዘርፍ ሚኒትር ዴኤታ ክብርት ቡዝነሽ መሰረት ተናግረዋል።

ቅርሱ በዋናነት የከርስ ምድርና የገፀ ምድር ውሃ መጠን መጨመር ምክንያት በሀውልቱ ስር ያለውን አፈር የመሸርሸር አደጋ በማጋጠሙ ሀውልቱ ላይ የመዝመም አደጋ እንዲከሰት አድርጓል ተብሏል፡፡

ምንጭ፡- የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Shire #Axum #Mekelle

በሽረ ከተማ ህዝቡ ወደመረጋጋት እና ወደቀደመው ህይወቱ እየተመለሰ መሆኑን ዶ/ር ሙሉ ነጋ (የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈፃሚ) ለኢቲቪ ተናገሩ።

የወረዳ ፣ የቀበሌ ስራ አስፈፃሚዎች ተመርጠዋል ፤ ወደ ስራም ገብተዋል ብለዋል።

በተመሳሳይ በአክሱም ከተማ የወረዳና የቀበሌ አደረጃጀቶች ተዘርግተዋል ፤ እንቅስቃሴም እንደተጀመረ ገልጸዋል።

መቐለ ከተማ በሚመለከት አሁን ላይ ከተማው ሙሉ በሙሉ በመከላከያ ሰራዊት ቁጥጥር ስር እንደሆነና ሰላማዊ ሁኔታ እንዳለ ዛሬ ከመቐለ ከተማ ሆነው አሳውቀዋል።

ህዝቡ ወደስራው እንዲመለስ ፣ በስጋት ከከተማው ሸሽቶ የወጣም እንዲገባ ጥሪ ቀርቧል።

በሌላ በኩል በመቐለ ከተማ የህዝቡ ስጋት ዝርፊያ እንደሆነና ይህም ዝርፊያ እንዲቆም ጥያቄ እንዳቀረበ አንስተዋል ፤ ዝርፊው በቡድን በመደራጀት የሚፈፀም እንደሆነም ዶክተር ሙሉ ገልፀዋል።

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ከሀገር መከላከያ ሰራዊት እና ከፌዴራሉ መንግስት ጋር በመነጋገር በፍጥነት ይህ ሁኔታ መፍትሄ እንዲያገኝ እየሰራ እንደሆነ አሳውቀዋል።

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#Axum

Save the Children ዛሬ በላከልን መግለጫ በአክሱም ከ3 ወራት ወዲህ የመጀመሪያ እርዳታ ማከፋፈሉን አሳውቆናል።

በዕርዳታው በከተማው የሚገኙ እና በሺዎች የሚቆጠሩ ተፈናቃይ ህፃናትና ቤተሰቦቻቸው ምግብ፣ መጠለያና የንፅህና መጠበቂያዎችን እንዳገኙ ገልጿል።

አክሱም በቅርብ ጊዜ በተፈጠረው ግጭት የተፈናቀሉ በርካታ ተፈናቃዮችን ያስጠለለች ሲሆን ከ6 ሺህ የሚልቁ ተፈናቃዮች በተጣበቡ ትምህርት ቤቶች ፣ ጊዜያዊ መጠለያ ጣቢያዎችና በአከባቢው ነዋሪዎች ቤት ተጠልለው ይገኛሉ።

የSave the Children ልገሳ ለተፈናቃዮች መሰረታዊ የምግብ፣ መጠለያ እና ሌሎች አቅርቦቶችን ያካተተ ነው።

Save the Children በአክሱም በየካቲት መባቻ እጅግ አስፈላጊ ድጋፍ ማቅረብ ከጀመረ አንስቶ ለቀናት እህል ያልቀመሱና በሆስፒታሎች ባለው እጅግ ውስን የህክምና አቅርቦቶች የተነሳ አስፈላጊ የጤና አገልግሎቶች ማግኘት ያልቻሉ ቤተሰቦችን አግኝተዋል።

ድርጅቱ በእስካሁኑ የምግብ እና ሌሎች እርዳታ ለ1,063 ቤተሰቦች ወይም 4,368 ሰዎችም መድረስ እንደቻለ ቢገልፅም አሁብም ተጨማሪ ድጋፍ ያስፈልጋል ብሏል።

* ከSave the Children የተላከልን ዝርዝር መግለጫ ከላይ የያይዟል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
The_Massacre_of_Axum_-_AFR_25.3730.2021.pdf
ትግራይ አክሱም ፅዮን ቅድት ማሪያም ቤተ ክስርቲያን ውስጥ 750 ሰዎች ተገድለዋል ?

አምነስቲ ኢንተርናሽናል በማህበራዊ ሚዲያ በአክሱም ጽዮን ያለውን ጽላት የኤርትራ ወታደሮች ለመውሰድ ሲሞክሩ በተፈጠረ ግርግር የሰው ህይወት ጠፍቷል በሚል ሲሰራጭ የነበረውን መረጃ የሚያረጋግጥ መረጃ እንዳላገኘ ለቢቢሲ አሳውቋል።

ነገር ግን ኅዳር 19 እና 20 ቀን 2013 ዓ/ም በአክሱም አስከፊ የተባለ ጭፍጨፋ መካሄዱን አረጋግጫለሁ ብሏል።

እንደ አምነስቲ ገለፃ ኅዳር 19 የተወሰኑ የህወሓት ሚሊሻዎች አክሱም ጽዮን ቤተ-ክርስቲያን አጠገብ ካለች አንድ ተራራ ወይም ጉብታ ላይ ወደ ኤርትራ ወታደሮች ላይ በከፈቱት ተኩስ ግጭት ተቀስቅሶ ነበር።

ይህ ካበቃ በኋላ እዛው የነበረው የኤርትራ ሠራዊት ሌላ ተጨማሪ ኃይል እና የጦር መሳሪያ ተጨምሮ (ታንኮችን ጭምር) ጥቃት ሰነዘሩ። በመንገድ ላይ ያገኙትን እና በየቤቱ እያገቡ ያገኙትን ጎረምሳ ወንዶች ሲገድሉ እደነበረ ያገኘነው መረጃ ያስረዳል ብሏል ተቋሙ።

በማግስቱ ህዳር 20 ይህ ድርጊት ቀጥሎ ነበር የሚለው አምነስቲ አስከሬን ማንሳንትም አይቻልም ነበር ፤ ኅዳር 21 2013 ዓ.ም. በአክሱም ጽዮን ክብረ በዓል ዕለት ነው እንዲቀበሩ የተደፈቀደው ብሏል።

አምነስቲ በ21 ትልቅ ግድያ እንደነበረ የሚያስረዳ ነገር የለም ፤ ይልቁንም አስከሬን መቅበር የተጀመረውም በእዛው ዕለት ነው በማለት በማህበራዊ ሚዲያ ሲሰራጩ የነበሩ መረጃዎችን ውድቅ የሚያደርግ መረጃ ሰጥቷል።

#AmnestyInternational #Ethiopia #Tigray #Axum

https://telegra.ph/Amnesty-International-02-26-2
#Tigray #Axum

አክሱምን ለጎብኚዎች ክፍት ለማድረግ ያቀደ ሀገር አቀፍ ኮንፍረንስ በአክሱም ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።

ኮንፈረንሱ ከትላንት የጀመረ ሲሆን ዛሬ ይጠናቀቃል።

ይኸው ኮንፈረንስ በኢኒሼቲቭ አፍሪካ (IA) እና Centre for International Private Enterprise (CIPE) አስተባባሪነት የተዘጋጀ ሲሆን በትግራይ በተከሰተው ጦርነት ሳቢያ ለሁለት አመታት ተቋርጦ የነበረውን የአክሱም ቱሪዝም ለማነቃቃት ያለመ ነው።

በመድረኩ ከትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር፣ ከግሉ ዘርፍ፣ የቱሪዘም ሴክተር ባለድርሻ አካላት እና ባለሃብቶች እየተሳተፉ ይገኛሉ፡፡ 

በመድረኩ በጦርነቱ ሳቢያ በቅርሶች ላይ ስለደረሰው ጉዳት እና ቱሪዝምን ለማነቃቃት ምን መደረግ አለበት በሚለው ዙሪያ በአክሱም ዩኒቨርስቲ የተሰራ የዳሰሳ ጥናት ቀርቧል፡፡

በዚህ ኮንፍረንስ በግሉ ዘርፍ እና በመንግስት በኩል ምን ለማስራት ታቅዷል በሚለው ዙሪያ የፓናል ውይይት ይካሄዳል፡፡

Credit - Daniel (Tikvah Family)

@tikvahethiopia
#Axum #EthiopianAirlines

የአክሱም ኤርፖርትን ለመጠገን የእቃዎች ግዥ መጀመሩ ተነግሯል።

ትግራይ ባስተናገደችው አስከፊው ጦርነት ወቅት ክፉኛ የወደመው የአክሱም ኤርፖርት እስካሁን ተጠግኖ ወደስራ አልተመለሰም።

የአክሱም ህዝብ ኤርፖርቱ ባለመጠገኑ ዘርፈ ብዙ ችግሮች እየተከሰቱ ነው።

በተለይም የተለያዩ አልባሳትን፣ ባህላዊ ጌጦችን እያዘጋጁ የሚሸጡ፣ ከቱሪዝም ገቢ የሚያገኙ ወገኖች ኤርፖርቱ ስለሌለ ስራ መስራት እንዳልቻሉ ገልጸዋል።

በንግድ ዘርፍ ላይ ያሉ ወገኖች ብዙ ደክመው የሚያዘጋጇቸውን ቁሳቁሶች እና ባህላዊ አልባሳት የሚገዛቸው እንዳጡ አመልክተዋል።

ከሰሞኑን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ልዑክ ከኣክሱም ነዋሪዎች ጋር ምክክር አድርጎ ነበር። በዚህም ወቅት የአክሱም ኤርፖርት ጥገና ዋነኛው አደጀንዳ እንደነበር ታውቋል።

በኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋናው መ/ቤት የክልሎች የጥገና ሂደት አስተባባሪ አቶ ተወልደ ግርማይ ፤ አየር መንገዱ ለኤርፖርቱ ጥገና የሚያስፈልጉትን ቁሳቁሶች መገብየት እንደጀመረ አሳውቀዋል።

አቶ ተወልደ ፤ " ምን አለ ? ምን ቀረ ? የሚለውን ለይተን ኤርፖርቱን ለመጠገን የሚያስፈልጉን መሳሪያዎች በመግዛት ላይ ነን። በግዢ ሂደት ላይ ያሉ አሉ። " ብለዋል።

ጥገናው ለህዳር ጽዮን በዓል ይደርሳል ?

ጥገናው ለህዳር ጽዮን ማርያም በዓል አይደርስም ተብሏል።

በየአመቱ ኣክሱም ከተማ የሚከበረው የህዳር 21 ጽዮን በዓል በተለይም ከጦርነት በፊት እጅግ ብዙ ሺህ ሰዎች ከሀገር እና ከውጭ ይገኙበት እንደነበር ይታወሳል።

አሁን ላይ ያለው የሰላም ሁኔታም እጅግ በርካታ ሰዎች ወደ ከተማው በብዛት እንዲገቡ እድል የሚፈጥር ነው።

ነገር ግን እስከ በዓሉ ድረስ ያሉት ውስን ቀናት ስለሆነ የኣክሱም ኤርፖርት ተጠግኖ የመጠናቀቅ እድል የለውም ተብሏል።

አቶ ተወልደ ግርማይ ፤ " የህዳር ጽዮን በዓልን ለማድመቅ የሽረ እንደስላሰ ኤርፖት አስፈላጊ በሆነ መሳሪያዎች እንዲሁም የቦይንድ አውሮፕላን የሚያርፉባቸው ስፍራዎች ለማስተካከል፣ ለማጠናከር እና ለማስፋፋት ባለሞያዎች ተሰማርተዋል " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከቴሌቪዥን ትግራይ ነው ያገኘው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Axum #EthiopianAirlines የአክሱም ኤርፖርትን ለመጠገን የእቃዎች ግዥ መጀመሩ ተነግሯል። ትግራይ ባስተናገደችው አስከፊው ጦርነት ወቅት ክፉኛ የወደመው የአክሱም ኤርፖርት እስካሁን ተጠግኖ ወደስራ አልተመለሰም። የአክሱም ህዝብ ኤርፖርቱ ባለመጠገኑ ዘርፈ ብዙ ችግሮች እየተከሰቱ ነው። በተለይም የተለያዩ አልባሳትን፣ ባህላዊ ጌጦችን እያዘጋጁ የሚሸጡ፣ ከቱሪዝም ገቢ የሚያገኙ ወገኖች ኤርፖርቱ…
#Axum

" እንደኛ ፍላጎትማ #ለህዳር_ጽዮን እንዲደርስ ነበር ... እርግጠኛ ሆኜ የምናገረው ግን የአክሱም ኤርፖርታችን ክረምት ከመግባቱ በፊት ስራውን ይጀምራል " - አቶ ለማ ያዴቻ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በጦርነት ምክንያት እጅግ ከፍተኛ ውድመት የደረሰበት የአክሱም አውሮፕላን ማረፊያ ክረምት ከመግባቱ በፊት ስራውን እንደሚጀምር አሳውቋል።

በተለይም የአክሱም ነዋሪዎች፣ እንዲሁም የተለያዩ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ቱሪስቶች ፣ በጦርነት የወደመው የአክሱም ኤርፖርት መቼ ስራ ይጀምራል የሚል ጥያቄ አላቸው።

ከዚህ ቀደም ከተሰጠው ማብራሪያ በኃላ
(https://t.me/tikvahethiopia/82211?single) የጥገናው ስራ ከምን ደረሰ የሚለው የብዙሃን ጥያቄ ነው።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የንግድ ዘርፍ ዋና ኃላፊ ለማ ያደቻ ፤ የአውሮፕላን ማረፊያውን ወደ ስራ ለማስገባት ጥረት ሲደረግ መቆየቱን ነገር ግን በተለያዩ ምክንያቶች ስራውን ማከናወን እንዳልተቻለ ተናግረዋል።

አቶ ለማ ፤ " እንደሚታወቀው የመንግሥት የግዢ ስርዓት አለ፤ ጨረታ ወጥቶ በስነስርዓት evaluate ተደርጎ ጨረታው መሰጠት ያለበት " ብለዋል።

" እንደኛ እንደ ኢትዮጵያ አየር መንገድ ፍላጎት ቢሆን ኖሮ ለህዳር ጽዮን እናደርስ ነበር ፤ መሬት ላይ ያለው የግዢ ስርዓት የጨረታው ስርዓት ለዛ ጊዜ አላደረሰንም " ሲሉ ተናግረዋል።

የአውሮፕላን ማረፊያው መቼ ነው ወደ አገልግሎት የሚመለሰው ? ለሚለው ጥያቄም አቶ ለማ " ኤርፖርቱ በጣም ነው የተጎዳው ፤ ስራው መሰረታዊ ስራ ይፈልጋል ፤ ተጫራች ምርጫ ጨርሰናል የመጨረሻዎቹ negotiation ላይ ነው ያለውነው ከ10 ቀን ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ ተጫራቹ ታውቆ ስራውን ይጀምራል " ብለዋል።

" እነሱንም ግፊት የምናደርግባቸው በሁለት እና በሶስት ወር ውስጥ ሰርተው ሊጨርሱ ይችላሉ ፥ ግን ደግሞ ካንትራክተሩ ሲመጣ የራሱን Schedule / መርሃ ግብር  ይዞ ስለሚመጣ የነሱንም Schedule ማክብረ ይጠበቅብናል " ሲሉ ገልጸዋል።

" የሆነው ሆኖ ግን በእርግጠኝነት የምናገረው ክረምት ከመግባቱ በፊት የአክሱም ኤርፖርታችን ስራውን ይጀምራል ፣ ቱሪስቶችን እናመጣለን ፣ የአካባቢው ነዋሪም የሚገባውን አገልግሎት እንዲያገኝ እናደርጋለን ፀንተንም እንሰራለን " ሲሉ ተናግረዋል።

እጅግ ከፍተኛ ምዕመን ይገኝበታል ተብሎ ለሚጠበቀው ለህዳር ጽዮን በዓል አየር መንገዱ አቅራቢው ባለው የሽረ አውሮፕላን ማረፊያ የሚደረጉ በረራዎችን ለማሳደግ ከወዲሁ ቅድመ ዝግጅት እያደረገ ነው ተብሏል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ያገኘው አቶ ለማ ያደቻ ለኤፍ ቢ ሲ ከሰጡት ቃለምልልስ መሆኑን ያሳውቃል።

@tikvahethiopia
#Axum

ትላንት ምሽት በርእሰ አድባራት ወገዳማት አክሱም ፅዮን ቅጥር ግቢ የእሳት ቃጠሎ  አደጋ አጋጥሞ ነበር።

የመቐለ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ታማኝ ምንጮች እንዳሉት ፡ የካቲት 15/2016 ዓ.ም ከ 2:30 ምሽት ጀምሮ " እንዳ ፍሕሚ " ተብሎ በሚጠራውና ፅላቱ በሚቀመጥበት አከባቢ ነው የእሳት ቃጠሎ የተነሳው።

ባጋጠመው የእሳት አደጋ ቃጠሎ በሰው ህይወት ያጋጠመ አደጋ እንደሌለ የገለፁት የቲክቫህ ምንጮች ፤ ቃጠሎድ በከተማው ነዋሪዎችና በፀጥታ አካላት ከፍተኛ ተሳትፎ በአጭር ጊዜ በቁጥጥር ስር ሊውል ችሏል።   

የትግራይ ማእከላይ ዞን ፓሊስ የካቲት 15/2016 አመሻሽ በማህበራዊ የትስስር ገፁ  " የተነሳው የእሳት ቃጠሎ በቁጥጥር ስር ውሏል " ከማለት ውጪ ያለው የለም። 

በርካታ የማህበራዊ የትስስር ገፅ ፀሃፊዎች የእሳት አደጋ ቃጠሎው ተጣርቶ ለህዝብ ይፋ እንዲሆንና ፣ ቅዱስ ቦታ ከተመሳሳይ አደጋ ለመታደግ የሚመጠነው ጥበቃ ያሻዋል የሚሉ አስተያየቶች በብዛት በማንሸራሸር ላይ እንደሚገኙ የመቐለ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ዘግቧል።
                             
@tikvahethiopia            
#Axum

በጭንቅላት የተጣበቁ መንትዮች ተወለዱ።

ሴት መንትዮቹ  (Conjoined twins) እንዲሁም እናቲቱ በመልካም የጤና ሁኔታ ይገኛሉ ተብሏል።

መጋቢት 22 /2016 ሌሊት በሪፈር የተላከች እናት በቆዶ ጥገና 5 ኪሎ የሚመዘኑ በጭንቅላት የተጣበቁ ሴት መንትዮች እንደተገላገለች የአክሱም ዩኒቨርሲቲ ኮምፕረሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ገልጿል። 

ወላጅ እናት ለአዋላጅ ሃኪም የሰጠችው መረጃ በመጥቀስ ባለሙያዎች እንዳሉት ፥ እናቲቱ የፅንስ ክትትል በአቅራቢያዋ በሚገኝ የጤና ማእከል ውስጥ ስታደርግ የቆየች ብትሆንም የአልትራሳውንድ ምርመራ ባለማድረግዋ በማህፀንዋ የነበሩት መንትዮች ሁኔታ ቀድማ ማወቅ አልቻለችም። 

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከአክሱም ዩኒቨርሲቲ  ኮምፕረሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ነው ያገኘው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#አክሱምኤርፖርት የኢትዮጵያ ኤርፖርቶች ድርጅት የአክሱም ሃፀይ ዮሃንስ አውሮፕላን ማረፍያ ለማደስ በጨረታ ላሸነፈው የኮንስትራክሽን ድርጅት ይፋዊ የርክክብ ስነ-ሰርዓት አላካሄደም ተብሏል። ይህ ሁኔታ ደግሞ የእድሳት ሰራው በፍጥነት በሙሉ አቅም እንዳይሰራና እንዲዘገይ ምክንያት እየሆነ ነው በሚል ነዋሪዎች ቅሬታቸውን ገልጸዋል። መምህር ሙሉወርቅ ኪዳነማርያም የኢትዮጵያ የንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር…
#Axum

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሰኔ 2016 ዓ/ም ወደ ትግራይ አክሱም ከተማ በረራ እንደሚጀመር መግለጹን ትግራይ ቴሌቪዥን ዘግቧል።

የአክሱም ሃፀይ ዮውሃንስ አራተኛ አውሮፕላን ማረፍያ በትግራይ በነበረው ደም አፋሳሽ ጦርነት በደረሰበት ወድመት ምክንያት ከበረራ አገልግሎት ውጪ ሆኖ መቆየቱ ይታወሳል።

በቅርቡ ግን አውሮፕላን ማረፊያው መልሶ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምር የኢትዮጵያ አየር መንገድ ገልጿል።

የአየር መንገዱ የንግድ ዘርፍ ዋና ስራ አስፈፃሚ ለማየ ያደቻ ለትግራይ ቴሌቪዥን በስልክ በሰጡት መረጃ ፤ " በአውሮፕላን ማረፍያው ሲካሄድ የቆየው የጥገና ምዕራፍ ወደ መጨረሻ መደረሱን ተከትሎ በሰኔ ወር 2016 ዓ.ም የመጀመሪያ ሳምንት መልሶ አገልግሎት መስጠት ይጀምራል " ብለዋል። 

ወደ ታሪካዊቷ አክሱም ሲከናወን የነበረው የአውሮፕላን በረራ በመቋረጡ ምክንያት ነዋሪዎች መቸገራቸው እንዲሁም በአከባቢው የሚገኙ የቱሪዝም መዳረሻዎች ላይ ከፍታኛ መቀዛቀዝ እንዲታይ ማድረጉ በተደጋጋሚ መዘጋቡ ይታወሳል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia
#Axum

" የሃውልቱ ዲዛይንና መሬት ላይ የተገነባው ለየቅል ነው ፤ አይገናኝም ! "
 
ዛሬ በአክሱም ከተማ የማህሌታይ ቅዱስ ያሬድ ሃውልት ተመርቋል።

ነገር ግን ከሃውልቱ ግንባታ ጋር በተያያዘ በርካቶች " አይመጥንም " በሚል ተቃውመዋል።

በአክሱም በይፋ የተመረቀው የማህሌታይ ቅዱስ ያሬድ ሃወልት ለግንባታው አራት (4) አመት መፍጀቱን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለመስማት ችሏል።

በምረቃ ስነ-ሰርዓቱ የተገኘው የመቐለ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል በሃውልቱ ግንባታ ዙሪያ የተነሳው ተቃውሞ ተከታትሏል።

በምረቃ ስነ-ስርዓት ላይ የተገኙ ምእመናን እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የኢትዮጵያና የዓለም የዜማ አባት የሆነው ማህሌታይ ቅዱስ ያሬድ የሚያስታውስ ሃወልት መቆሙ ቢያስደስታቸውም " ሃውልቱ የዜማ አባቱን ክብርና ዝና የሚመጥን አይደለም " ሲሉ ቅሬታቸውን ገልጸዋል።

በስነ-ሰርዓቱ ላይ የተገኙት የአክሱም ገዳማት ወ አድባራት አስተዳዳሪ ንቡረ እድ ጎደፋ መርሃ ምእመናኑና እና ታዳምያን " ሃወልቱ አይመጥንም " ሲሉ ያነሱትን ቅሬታ ተጋርተውታል።

የምረቃ ስነ-ሰርዓቱ በሚድያ ለህዝብ ይፋ ከሆነ በኃላ ' ሃወልቱ ቅዱስ ያሬድን አይወክልም ፤ አይመጥም ' የሚል በሀገር ውስጥ እና በውጭ ያለው ወገን ተቃውሞውን በማህበራዊ ሚድያ ትስስር ገጾች ላይ በስፋት እያጋራ ነው።

ከዚህ አለፍ ሲል ፈርሶ ድጋሜ እንዲገነባና ሃወልቱ ማህሌታይ ያሬድን በሚመጥን መልኩ በሀገር ያሉና በውጭ ያሉ ባለሞያዎችን አሳትፎ እንዲገነባ " ገንዘብ እናዋጣለን " እንዲሁም እውቀታችንን እናካፍላለን ያሉ አሉ።

" የሃውልቱ ዲዛይን እና መሬት ላይ የተገነባው ለየቅል ነው አይገናኝም " ያሉ አንዳንድ አስተያየት ሰጪዎች ደግሞ የትግራይ የባህልና ቱሪዝም ባለመከታተሉ ወቅሰዋል።

ሃወልቱ #በመቐለ_ዩኒቨርስቲ እና በአክሱም ገዳማት ወ አድባራት አስተዳደር ትብብር የተገነባ ሲሆን ለግንባታው ከ1 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ተደርጎበታል ተብሏል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle                                               
@tikvahethiopia            
TIKVAH-ETHIOPIA
#Axum የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሰኔ 2016 ዓ/ም ወደ ትግራይ አክሱም ከተማ በረራ እንደሚጀመር መግለጹን ትግራይ ቴሌቪዥን ዘግቧል። የአክሱም ሃፀይ ዮውሃንስ አራተኛ አውሮፕላን ማረፍያ በትግራይ በነበረው ደም አፋሳሽ ጦርነት በደረሰበት ወድመት ምክንያት ከበረራ አገልግሎት ውጪ ሆኖ መቆየቱ ይታወሳል። በቅርቡ ግን አውሮፕላን ማረፊያው መልሶ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምር የኢትዮጵያ አየር መንገድ…
#Ethiopia

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በመጪው #ሰኔ_ወር 2016 ዓ/ም ወደ ሁለት የሀገር ውስጥ የበረራ መዳረሻዎች በረራ ይጀምራል።

አየር መንገዱ #ከሰኔ_10_ጀምሮ ወደ ወለጋ ፣ ነቀምቴ በረራ እንደሚጀምር አሳውቋል።

በረራው በሳምንት 4 ጊዜ እንደሚካሄድ ተገልጿል።

ከዚህም ባለፈ ፥ በትግራይ ጦርነት ምክንያት ተቋርጦ የቆየው ወደ አክሱም የሚደረገው በረራ ከሰኔ 1 ጀምሮ ዳግም እንደሚጀምር ታውቋል።

የአክሱም ሃፀይ ዮውሃንስ አራተኛ አውሮፕላን ማረፍያ በጦርነቱ በደረሰበት የከፋ ወድመት ምክንያት ከበረራ አገልግሎት ውጪ ሆኖ መቆየቱ ይታወሳል።

ከሰኔ 1 ጀምሮ ግን የመንገደኞች በረራ ያስተናግዳል ተብሎ ይጠበቃል።

#Ethiopia #OromiaRegion #TigrayRegion #Wollega #Axum
 
@tikvahethiopia
#Axum #Tigray

" በጦርነቱ ጊዜ እኮ #መከራው ከባድ ነበር !! "

ወ/ሮ በላይነሽ መኣሾ (የአክሱም ነዋሪ ለድምጺ ወያነ) ፦

" ሰላም በመሆኑ ጥሩ ነው ያለው።  ብርሃን አየን።

በሰላም እየተንቀሳቀስን ነው። #ሕጻናት እየተጫወቱ ነው።

ብዙ ለውጥ ነው ያለው።

በጦርነቱ ጊዜ እኮ #መከራው እጅግ ከባድ ነበር። አሁን በጣም በጣም ይሻላል ፤ ቢያንስ #እፎይ ብለን  መተኛት እንችላለን።

ቢሆንም ግን #የከፋው_ሰው_አለ ፤ ሰው የሚበላው የሚጠጣውን አጥቶ በጣም ከፍቶታል ፣ የመንግስት ሰራተኛውም ያለፉት ዓመታት ደመወዝ ባለመከፈሉ ለተለያዩ ችግሮች ተጋልጦ ነው ያለው ፣ የተፈናቃዮች ነገርማ #አይወራም ፣ ሕጻናት ልጆች የሚበሉትን አጥተው በየከተማው #በልመና ነው ተሰማርተው ያሉት። "

#Ethiopia #TigrayRegion #Peace

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia የኢትዮጵያ አየር መንገድ በመጪው #ሰኔ_ወር 2016 ዓ/ም ወደ ሁለት የሀገር ውስጥ የበረራ መዳረሻዎች በረራ ይጀምራል። አየር መንገዱ #ከሰኔ_10_ጀምሮ ወደ ወለጋ ፣ ነቀምቴ በረራ እንደሚጀምር አሳውቋል። በረራው በሳምንት 4 ጊዜ እንደሚካሄድ ተገልጿል። ከዚህም ባለፈ ፥ በትግራይ ጦርነት ምክንያት ተቋርጦ የቆየው ወደ አክሱም የሚደረገው በረራ ከሰኔ 1 ጀምሮ ዳግም እንደሚጀምር ታውቋል።…
ፎቶ ፦ የአክሱም አፄ  ዮውሀንስ አራተኛ  ኤርፖርት #በተያዘለት_የጊዜ_ሰሌዳ አገልግሎት መስጠት እንዲጀመር የሚያስችሉት የጥገና ስራዎች አሁን ላይ ወደመጠናቀቁ መሆናቸው ተነግሯል።

በትግራይ ጦርነት ከፍተኛ የሆነ ጉዳት የደረሰበት ኤርፖርቱ የጥገና ስራው ቀን እና ሌሊት እየተሰራ ነበር።

የጥገና ተቆጣጣሪ አካል የአውሮፕላን ማረፍያው የሚገባውን ጥራት በያዘ ደረጃ ስራው እየተሰራ መሆኑን ጠቁሟል።

በረራው እንዲጀመር በተቀመጠለት የጊዜ ሰሌዳ በረራው እንዲጀመር የማጠናቀቅ ስራ እየተሰራ እንደሆነ ገልጿል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከሰኔ 1 ቀን 2016 ዓ/ም ጀምሮ ወደ አክሱም መደበኛ በረራ እንደሚጀመር ማሳወቁ ይታወሳል።

#Ethiopia #Tigray #Axum

Photo Credit - Tigray TV

@tikvahethiopia            
TIKVAH-ETHIOPIA
ፎቶ ፦ የአክሱም አፄ  ዮውሀንስ አራተኛ  ኤርፖርት #በተያዘለት_የጊዜ_ሰሌዳ አገልግሎት መስጠት እንዲጀመር የሚያስችሉት የጥገና ስራዎች አሁን ላይ ወደመጠናቀቁ መሆናቸው ተነግሯል። በትግራይ ጦርነት ከፍተኛ የሆነ ጉዳት የደረሰበት ኤርፖርቱ የጥገና ስራው ቀን እና ሌሊት እየተሰራ ነበር። የጥገና ተቆጣጣሪ አካል የአውሮፕላን ማረፍያው የሚገባውን ጥራት በያዘ ደረጃ ስራው እየተሰራ መሆኑን ጠቁሟል። በረራው…
#Update #Axum

የአክሱም ኤርፓርት ሰኔ 2/2016 ዓ/ም ዳግም የበረራ አገልግሎት መስጠት ይጀምራል። 

በትግራይ ጦርነት ከፍተኛ  የሆነ ጉዳት የደረሰበት የአክሱም አፄ ዮውሀንስ አራተኛ  ኤርፖርት ሰኔ 2 የመጀመሪያ ዳግም በረራውን ያደርጋል።

እሁድ ሰኔ 2 በኤርፓርቱ ዳግም መደበኛ የበረራ  አገልግሎት ስነ-ሰርዓት ማስጀመሪያ ጥሪ የተደረገላቸው የክልልና የፌደራል ባለስልጣናት እንደሚገኙ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከአክሱም ከተማ ኮሙኒኬሽንና ህዝብ ግንኙነት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia            
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update #Axum የአክሱም ኤርፓርት ሰኔ 2/2016 ዓ/ም ዳግም የበረራ አገልግሎት መስጠት ይጀምራል።  በትግራይ ጦርነት ከፍተኛ  የሆነ ጉዳት የደረሰበት የአክሱም አፄ ዮውሀንስ አራተኛ  ኤርፖርት ሰኔ 2 የመጀመሪያ ዳግም በረራውን ያደርጋል። እሁድ ሰኔ 2 በኤርፓርቱ ዳግም መደበኛ የበረራ  አገልግሎት ስነ-ሰርዓት ማስጀመሪያ ጥሪ የተደረገላቸው የክልልና የፌደራል ባለስልጣናት እንደሚገኙ ቲክቫህ…
#Axum #Update
 
የአክሱም ሃፀይ ዮሃንስ አራተኛ አውሮፕላን ማረፍያ ከሶስት ዓመት በኃላ ዛሬ እሁድ ሰኔ 2 ቀን 2016 ዓ/ም ከቀኑ 6:00 ሰዓት የመጀመሪያውን ይፋዊ የአውሮፕላን  በረራ አስተናግዷል።

የዳግም በራራ አገልግሎት ማስጀመሪያ ስነ-ስርዓት የክልል እና የፌደራል ባለስልጣናት በተገኙበት እየተካሄደ ይገኛል።

በቦታው የሚገኘው የመቐለ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል በላከው መረጃ ከቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን አዲስ አበባ ተነስቶ ከቀኑ 6:00 ላይ አክሱም የደረሰው የመጀመሪያው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቦይንግ 737-700 አውሮፕላን 140 ተጓዦች ይዟል።

ከተጓዦቹ ውስጥም የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈፃሚ መስፍን ጣሰው ፣ የፌደራልና የክልል የስራ ሃላፊዎች ይገኙበታል።

የትግራይ ክልል ጊዚያዊ  አስተዳደር ፕረዜዴንት አቶ ጌታቸው ረዳ አቀባበል አድርገውላቸዋል።

#Axum #Ethiopia #Tigray

@tikvahethiopia