TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
The_Massacre_of_Axum_-_AFR_25.3730.2021.pdf
ትግራይ አክሱም ፅዮን ቅድት ማሪያም ቤተ ክስርቲያን ውስጥ 750 ሰዎች ተገድለዋል ?

አምነስቲ ኢንተርናሽናል በማህበራዊ ሚዲያ በአክሱም ጽዮን ያለውን ጽላት የኤርትራ ወታደሮች ለመውሰድ ሲሞክሩ በተፈጠረ ግርግር የሰው ህይወት ጠፍቷል በሚል ሲሰራጭ የነበረውን መረጃ የሚያረጋግጥ መረጃ እንዳላገኘ ለቢቢሲ አሳውቋል።

ነገር ግን ኅዳር 19 እና 20 ቀን 2013 ዓ/ም በአክሱም አስከፊ የተባለ ጭፍጨፋ መካሄዱን አረጋግጫለሁ ብሏል።

እንደ አምነስቲ ገለፃ ኅዳር 19 የተወሰኑ የህወሓት ሚሊሻዎች አክሱም ጽዮን ቤተ-ክርስቲያን አጠገብ ካለች አንድ ተራራ ወይም ጉብታ ላይ ወደ ኤርትራ ወታደሮች ላይ በከፈቱት ተኩስ ግጭት ተቀስቅሶ ነበር።

ይህ ካበቃ በኋላ እዛው የነበረው የኤርትራ ሠራዊት ሌላ ተጨማሪ ኃይል እና የጦር መሳሪያ ተጨምሮ (ታንኮችን ጭምር) ጥቃት ሰነዘሩ። በመንገድ ላይ ያገኙትን እና በየቤቱ እያገቡ ያገኙትን ጎረምሳ ወንዶች ሲገድሉ እደነበረ ያገኘነው መረጃ ያስረዳል ብሏል ተቋሙ።

በማግስቱ ህዳር 20 ይህ ድርጊት ቀጥሎ ነበር የሚለው አምነስቲ አስከሬን ማንሳንትም አይቻልም ነበር ፤ ኅዳር 21 2013 ዓ.ም. በአክሱም ጽዮን ክብረ በዓል ዕለት ነው እንዲቀበሩ የተደፈቀደው ብሏል።

አምነስቲ በ21 ትልቅ ግድያ እንደነበረ የሚያስረዳ ነገር የለም ፤ ይልቁንም አስከሬን መቅበር የተጀመረውም በእዛው ዕለት ነው በማለት በማህበራዊ ሚዲያ ሲሰራጩ የነበሩ መረጃዎችን ውድቅ የሚያደርግ መረጃ ሰጥቷል።

#AmnestyInternational #Ethiopia #Tigray #Axum

https://telegra.ph/Amnesty-International-02-26-2
#AmnestyInternational

አምነስቲ ኢንተርናሽናል ለወራት በትግራይ እየተካሄደ ያለውን ጦርነት ተከትሎ (በኤርትራና የኢትዮጵያ መንግሥት ወታደሮች) የተፈጸሙ ጾታዊ ጥቃቶችን የዳሰሰበትን የጥናት ውጤት ይፋ አድርጓል።

አምነስቲ ከተለያዩ የጤና ተቋማት በሰበሰበው መረጃ መሠረት ከየካቲት እስከ ሚያዚያ ባሉት ወራት ብቻ በጦርነቱ አውድ ውስጥ ብቻ 1288 የሚሆኑ የአስገድዶ መድፈር ጥቃቶች የተፈጸመባቸው ተጠቂዎች ወደ ህክምና መስጫ ተቋማት ሄደው ሪፖርት ማድረጋቸውን አመላክቷል።

ለጥናቱ ቃለ መጠይቅ ከተደረገላቸው 68 የጥቃቱ ሰለባዎች መካከል አብዛኛዎቹ ወደ ጤና ተቋም አለመሄዳቸውን በመጥቀስ ወደ ሕክምና ተቋማት የሄዱ ሰዎች ቁጥር የጥቃቱን ስፋት አያሳይ ሲል አምነስቲ ጠቅሷል።

አምነስቲ ካነጋገራቸው 68 የጥቃቱ ሰለባዎች ውስጥ ብዙሃኑ ከአንድ በላይ በሆኑ ሰዎች ተገደው ተደፍረዋል።

ከእነዚህ ውስጥ የተወሰኑት ነፍሰጡርና ኤችአይቪ ቫይረስ በደማቸው ውስጥ የሚገኝ ሲሆኑ የተወሰኑት በልጆቻቸው ፊት ተገደው የተደፈሩ መሆናቸውን ሪፖርቱ በዝርዝር አስነብቧል።

አምነስቲ ካነጋገራቸው 68 ሰዎች መካከል 38ቱ ናቸው በቡድን የተደፈሩት።

አምነስቲ ኢንተርናሽናል ይፋ ያደረገውን ሪፖርት ተከትሎ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ምላሽ ሰጥቷል።

ሚኒስቴሩ አምነስቲ ተፈጽመዋል ስለተባሉ ጾታዊ ጥቃቶች ያወጣው ሪፖርት ተዓማኒነት የለውም ብሎታል።

የአምነስቲ መረጃ አሰባሰብ ዘዴ ተዓማኒነት የሌለው እና ሱዳን በሚገኙ ስደተኛ መጠለያዎች እና ትግራይ ካሉ ሰዎች በርቀት በስልክ ብቻ በተደረጉ ቃለ ምልልሶች ላይ ብቻ የተመሠረተ ሪፖርት ነው ብሏል።

አምነስቲ የኢትዮጵያ መንግሥትን ስም ለማጥፋት ሐሰተኛ መረጃዎችን ሲያሰራጭ ቆይቷል በማለትም ሚንስቴሩ ከሷል።

@tikvahethiopia