TIKVAH-ETHIOPIA
1.38M subscribers
54.6K photos
1.35K videos
197 files
3.61K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ጥንቃቄ📌ክላሲ የታሸገ ውሃ በጤና ላይ #ጉዳት የሚያደርስ መሆኑ በመረጋገጡ ህብረተሰቡ ጥቅም ላይ እንዳያውለው የንግድ ሚኒስቴር አሳስቧል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ኢሕአፓ⬇️

በነገው ዕለት ወደ ኢትዮጵያ የሚመለሱት የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) አመራሮች በቀይ ሽብር ወቅት #ጉዳት የደረሰባቸውን ዜጎች እንደሚጎበኙ አስታወቁ፡፡ ከጉዳተኞች ጋር በቋሚነት የሚያገናኝ ኮሚቴ የመመስረት ዕቅድ እንዳላቸውም ተገልጿል፡፡ ቡድኑ ነገ ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ የሚደረግለት አቀባበል እንደተጠናቀቀ በቀጥታ ወደ ቀይ ሽብር ሠማዕታት ሙዚየም ያመራል፡፡ የኢሕአፓ አመራሮች በሀገር ቤት ቆይታቸው በትግሉ የተሰዉ የኢሕአፓ አባላት ገድል የሚዘከርበትን መንገድ ያመቻቻሉ ተብሏል፤ ከመንግስት ባለሥልጣናት ጋር ይወያያሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

©ዋዜማ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ቤንሻንጉል⬇️

በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልልና በአጎራባች የኦሮሚያ ወረዳዎች #የጸጥታ ችግር መከሰቱ ተገለጸ።

በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከማሺ ዞንና በአጎራባች የኦሮሚያ ወረዳዎች በተከሰተው የጸጥታ ችግር በሰዎች ሕይወትና በንብረት ላይ #ጉዳት መድረሱን የኦሮሚያ ክልል የኮሙኒኬሽን ቢሮ ገልጿል፡፡

አሁን ለተከሰተው የጸጥታ ችግር መስከረም 16 ቀን 2011 ዓ.ም በኦነግ ስም የሚንቀሳቀሱ የታጠቁ ኃይሎች በምዕራብ ወለጋ ዞን ቢላ አሙማ አገሎ በተባለው ስፍራ በቤንሻንጉል ጉሙዝ የከማሺ ዞን አመራሮች ላይ ባደረሱት ጥቃት 4 የከማሺ ዞን አመራሮች #መገደላቸውን ተከትሎ መሆኑን ቢሮው ገልጿል፡፡

በእነዚህ ታጣቂዎች ግድያ የተፈጸመባቸው የከማሺ ዞን አመራሮች ከኦሮሚያ ክልል ከተላኩ አመራሮች ጋር ከዚህ ቀደም ከክልሉ #ተፈናቅለው የነበሩ የኦሮሚያ ክልል ተወላጆች ወደነበሩበት #በሚመለሱበት ሁኔታ ላይ በአሶሳ ከተማ ተወያይተው ወደ ከማሺ ዞን በመመለስ ላይ እያሉ ነበር ተብሏል፡፡

በከማሺ ዞንና እንዲሁም በምዕራብና ምስራቅ ወለጋ ዞን ስር በሚገኙት የሳስጋ፣ ድጋ፣ ሐሮ ሊሙ፣ ሊሙ፣ ቦጂ ብርመጂ ወረዳዎችና በሌሎች አከባቢዎች በተከሰተው በዚህ ግጭት ከነቀምቴ ሆስፒታል በተገኘው መረጃ መሰረት እስከ አሁን የ5 ሰዎች ሕይወት አልፏል፣ በርካቶች ቆስለዋል፣ በንብረት ላይም ውድመት ደርሷል፡፡

በተከሰተው ችግር ሳቢያ በቤንሻንጉል ክልል ሲኖሩ የነበሩ የኦሮሚያ ክልል ተወላጆች ተፈናቅለው በቤንሻንጉል ጉሙዝ ወሰን አካባቢ ወደሚገኙት የኦሮሚያ ወረዳዎችና ወደ ነቀምቴ ከተማ መሰደዳቸውንም ቢሮው ገልጿል፡፡

በአከባቢው የተከሰተውን ችግር #ለማረጋጋት የጸጥታ ኃይሎችና የአስተዳደር አካላት፣ የፌዴራል መንግስትና ሁለቱ ክልሎች በቅንጅት እየሰሩ መሆኑንም የኮሙኒኬሽን ቢሮው ገልጿል፡፡

በዜጎች ላይ ለደረሰው ጉዳት የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት የተሰማውን ጥልቅ #ሀዘን ገልጿል፡፡

የቤንሻንጉል ጉሙዝ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ዘላላም ጃለታ በበኩላቸው፣ በአከባቢው የጸጥታ ችግር መከሰቱን አምነው፣ በከማሺ ዞን የሚገኙት ነዋሪዎች ጥቃት ይደርስብናል በሚል ፍርሃት የጉሙዝ ተወላጆች ቤታቸውንና ንብረታቸውን ትተው ወደ ጫካ #እየተሰደዱ ሲሆን፤ የኦሮሚያ ክልል ተወላጆች ደግሞ ወደ አጎራባች የኦሮሚያ ክልል ወረዳዎች እየተሰደዱ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

በተፈጠረው ችግር በርካታ የኦሮሞ ማህበረሰብና የጉሙዝ ተወላጆች ቤቶች ላይ ቃጠሎ ደርሷል፡፡

ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ራያ አላማጣ⬇️

የራያ አላማጣ የማንነት ጥያቄ #ሊታፈን እንደማይገባ የቆቦ ከተማ ነዋሪዎች ጠየቁ።

የራያ አላማጣ ነዋሪዎች ማንነታችን አማራ በመሆኑ ሊከበርልን ይገባል ሲሉ በተደጋጋሚ እየጠየቁ ይገኛሉ። ይሁን እንጂ እንግልት እና ወከባ እየደረሰባቸው መሆኑን ነው የሚናገሩት። አላማጣ ላይ ከትናንት ምሽት ጀምሮ የፀጥታ ችግር መኖሩንና #ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች መኖራቸውንም ከአካባቢው የዓይን እማኞች ተናግረዋል።

ስለ ጉዳዩ የጠየቅናቸው የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ በአካባቢው ስለሌሉ መረጃ መስጠት እንደማይችሉ ነው የተናገሩት።

የቆቦ ከተማ ነዋሪዎችም ዛሬ በሰላማዊ ሰልፍ ድርጊቱን አውግዘዋል። "ማንነታቸውን ስለጠየቁ መብታቸው ሊታፈን፣ ሊንገላቱ እና ሊዋከቡ አይገባም" ሲሉ ነው የጠየቁት።

ከዚህ በፊት ስለ ጉዳዩ የተጠየቀው የትግራይ ክልል መንግስት "ጥያቄው ከማንነት ጋር አይያያዝም" ማለቱ ይታወሳል።

ነዋሪዎቹ ግን ጥያቄያቸው የማንነት እና የነፃነት መሆኑን ነው የሚያስረዱት። በሰልፉ "ጣናና ላል ይበላን እንታደግ!" የሚሉ መልዕክቶችንም አስተላልፈዋል።

የሰሞኑን የሚኒስትሮች ሹመት አሰጣጥም ተቃውመዋል።

ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Update አራት ኪሎ በግንባታ ላይ ያለ ህንጻ #ተደርምሶ በሰዎች ላይ ጉዳት ደረሰ።

በተለምዶ አራት ኪሎ እሪ በከንቱ በሚባለው አካባቢ በግንባታ ላይ ያለ ህንጻ መጠነኛ የመደርመስ አደጋ ደርሶበት በሰራተኞች ላይ #ጉዳት ደረሰ።

ዛሬ ከሰዓት በኋላ በደረሰው በዚሁ አደጋ በግንባታ ስራው ላይ በነበሩ #ስድስት ሰራተኞች ላይ ጉዳት ደርሶ ወደሆስፒትል መወሰዳቸው ታውቋል።

የአካባቢው ፓሊሶች ለኢትዮጵያ ፕሬሥ ድርጅት እንደገለጹት በአደጋው ህይወቱ ያለፈ ሰው የለም። የአደጋውም መንስኤ እየተጣራ ነው።

ምንጭ :- የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት
ፎቶ እና ቪድዮ፦ TikvahEthiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የደብረማርቆስ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ #ጉዳት በመድረሱ ደብረ ማርቆስ ፣ፍኖተ ሰላምና ብቸና ከትናንት ጀምሮ ኃይል ተቋርጧል፡፡

ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አባያ ሀይቅን እንታደግ‼️በአባያ ሀይቅ ላይ እየደረሰ ያለውን #ጉዳት ለህዝብ ለማስገንዘብ እና ትኩረት እንዲሰጠው እየተደረገ የሚገኘው የ3 ቀን የማህበራዊ ሚዲያ ዘመቻ ዛሬ 2ኛ ቀኑን ይዟል።

"የእንቦጭ አረምን ከሃይቁ እናስወግድ"
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ወላይታ ሶዶ⬇️

በወላይታ ሶዶ ከተማ ተፈጥሮ በነበረው የጸጥታ መደፍረስ ችግር  ንብረት ለወደመባቸውና #ጉዳት ለደረሰባቸው ነዋሪዎች በክልሉ መንግስት ከ11 ሚሊዮን ብር በላይ የገንዘብ #ድጋፍ ተደረገ፡፡

የደቡብ ክልል መንግስት ላደረገላቸው ድጋፍ ምስጋናቸውን ያቀረቡት ተጎጂዎችም ድጋፉ ተስፋ ከመቁረጥ እንዳዳናቸው ተናግረዋል፡፡

የሶዶ ከተማ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ፕሬዚዳንት አቶ #ባታላ_ባራና ሰኔ 8 ቀን 2010 ዓ.ም በከተማው ተፈጥሮ በነበረው የጸጥታ ችግር የንብረት ጉዳት መድረሱን አስታወሰዋል፡፡

ከተጎጂዎች መካከል አብዛኞቹ በተለያዩ የንግድ ሥራዎች የተሰማሩ ሲሆን በንግድ ተቋማት፣ በመኖሪያ ቤቶችና በተሽከርካሪዎች ላይ ጉዳት መድረሱንም አመልክተዋል፡፡

ባለፉት ጥቂት ወራት የማጣራትና መረጃ የማሰባሰብ ሥራ መሰራቱን ገልጸው በተገኘው መረጃ መሰረት ለ89 ተጎጂ ግለሰቦች ድጋፍ መደረጉን ተናግረዋል፡፡

ተጎጂዎቹ ራሳቸው ባቀረቡትና ከአካባቢው ህብረተሰብ በተሰበሰበ መረጃ እንዲሁም በንግድ ፈቃዳቸው ላይ ያስመዘገቡት ካፒታልና የገቢ ግብር ማህደርን መነሻ በማድረግ የማጣራት ሥራው መከናወኑንም አቶ ባታላ ገልጸዋል፡፡

በዚህ መሰረት የክልሉ መንግስት ጉዳት ለደረሰባቸው የህብረተሰብ ክፍሎ ከ11 ሚሊዮን 478 ሺህ ብር በላይ ድጋፍ ማድረጉን አስታውቀዋል።

የሶዶ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ዋና አፌ ጉባኤና የአጣሪ ኮሚቴው ሰብሳቢ ወይዘሮ ታልጎሬ ታደሰ በበኩላቸው የተሰበሰበውን መረጃ መሰርት በማድረግ እንደጉዳታቸው መጠን ድጋፉ መደረጉን ተናግረዋል፡፡

“እስከ 10 ሺህ ብር ጉዳት ያቀረቡ 34 ተጎጂዎች ገንዛባቸው ሙሉ በሙሉ እንዲተካላቸው የተደረገ ሲሆን ቀሪዎቹ 55ቱ የጉዳታቸውን 50 በመቶ እንዲያገኙ ተደርጓል” ብለዋል፡፡

ባለሁለት ጎማ የሞተር ብስክሌት ለተቃጠለባቸው ወገኖች ምትክ እንዲገዛ መወሰኑንና በመኖሪያ ቤታቸው ጉዳት ለደረሰባቸው ደግሞ ጥገና ለማድረግ የሚያስችል ድጋፍ መደረጉን አስረድተዋል፡፡

ድጋፍ ከተደረገላቸው ተጎጂዎች መካከል ወይዘሮ ምህረት መሸሻ በከተማዋ ጤና ጣቢያ ሰፈር የህጻናት አልባሳትና ኮስሞቲክስ ይነግዱ እንደነበረና በዕለቱ በድንገት በተፈጠረው ችግር መዘረፋቸውን ገልጸዋል፡፡

የክልሉ መንግስት ላደረገው ድጋፍ ምስጋና ያቀረቡት ወይዘሮ ምህረት ችግሩ ከደረሰ በኋላ ከፍተኛ ጉዳት ውስጥ ቢቆዩም ድጋፉ ሥራቸውን ዳግም ለመጀመር የሚያስችልና ተስፋ ከመቁረጥ እንደታደጋቸው ገልጸዋል፡፡

በሶዶ ከተማ መሃል ከተማ በኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች ንግድ ሥራ የተሰማሩት አቶ ኑሪ ባዲ በበኩላቸው ድንገት በተፈጠረው ችግር  በህገ-ወጦች ቢዘረፉም የመንግስት ድጋፍ ዳግም ወደስራቸው ለመመለስ እንዳገዛቸው ተናግረዋል፡፡

ችግሩ ሰላም የማይፈልጉና በሁከት ሰበብ ለዘረፋ የተዘጋጁ ነውጠኞች ያደረጉት መሆኑን ጠቁመው የተዘረፈውን ንብረት ለማስመለስ ነዋሪውና የከተማው ጸጥታ ኃይል ያደረገው ርብርብ የማይረሳ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ሰኔ 8 ቀን 2010 ዓ.ም በከተማዋ ተከስቶ በነበረው የጸጥታ መደፍረስ ምክንያት በንብረታቸው ላይ ጉዳት የደረሰባቸው ግለሰቦች መንግስትና የከተማዋ አስተዳደር ከቃል ባለፈ ተጨባጭ ድጋፍ ባለማድረጋቸው ተቸግረናል ሲሉ ያቀረቡትን ቅሬታ ኢዜአ በተደጋጋሚ መዘገቡ ይታወሳል፡፡

ምንጭ፦ ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ምስራቅ ወለጋ‼️

በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ወለጋ ዞን እና በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አዋሳኝ አካባቢ በተፈጠረ ግጭት የሰው #ህይወትና ንብረት ላይ #ጉዳት መድረሱን የኦሮሚያ ክልል የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ አስታወቀ።

የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ ዴሬሳ ተረፈ ለfbc አንደተናገሩት፥ በግጭቱ የኦሮሚያ ክልል ፖሊስን ጨምሮ የበርካታ የአካባቢው ነዋሪዎች ህይወት አልፏል።

እንዲሁም ለጊዜው ግምቱ ያልታወቀ በርካታ ንብረት መውደሙንም ነው አቶ ዴሬሳ የተናገሩት።

ችግሩ ያጋጠመውም ባሳለፍነው ማክሰኞ ህዳር 18 2011 ዓ.ም በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ወለጋ ዞን ሊሙ ወረዳ አርቁምቤ በሚባል አካባቢ መሆኑንም ነው የቢሮው ምክትል ኃላፊ ያስታወቁት።

በግጭቱም በአካባቢው ነዋሪዎች እና በኦሮሚያ ፖሊስ አባላት ላይ አሰቃቂ ወንጀል ተፈጽሟል ያሉት አቶ ዴሬሳ፥ በግጭቱ ህይወታቸው ያለፈ እና የተጎዱ ሰዎች ቁጥር በቅርቡ ይፋ ይደረጋልም ብለዋል።

በግጭቱ ህይወታቸው ያለፈ ሰዎች አስክሬን በትናንትናው እለት ነቀምቴ ከተማ ሲገባ ህዝቡ ሰልፍ በመውጣት #ስሜታዊ በመሆኑ የአንድ ሰው #ህይወት ማለፉንም ተናግረዋል።

ምክትል ኃላፊው አቶ ዴሬሳ ተረፈ፥ በምእራብ ኦሮሚያ አዋሳኝ አካባቢዎች ላይ እየተፈጠሩ ያሉ ግጭቶች ዋነኛ ምክንያት የክልሉን እና የሀገሪቱን ሰላም የማይፈልጉ እንዲሁም አሁን በሀገሪቱ እየመጣ ያለውን ለውጥ ለማደናቀፍ የሚሯሯጡ አካላት ናቸው ብለዋል።

የእነዚህ አካላት እቅድም እንደ ኦሮሚያ ክልል እና እንደ ሀገር እየመጣ ያለውን ለውጥ ማደናቀፍ በመሆኑ፤ ህዝቡ ከስሜታዊነት በመውጣት መንግስት ችግሩን በዘላቂነት ለመቅረፍ የሚወስደውን እርምጃ እንዲደግፍ ጥሪ አቅርበዋል።

ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ ኮሮፖሬሽን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
መንገዶች ተከፍተዋል‼️

በአፋር የነበረው የመንገድ መዝጋት #አድማ #እንደተጠናቀቀና መንገዶች #እንደተከፈቱ ተገልጿል፡፡ ሶማሊ ነዋሪዎች የሚበዛባቸው ሶስት ቀበሌዎች ላይ እየተፈጠረ ያለውን #ግጭት ለማርገብ በሚል ከቀበሌዎቹ የአፋር ክልል ልዩ ሃይል #እንዲወጣ መደረጉን #በመቃወም ነበር የክልሉ ወጣቶች ተቃውሞ የጀመሩት፡፡ የተቃውሞ እንቅስቃሴው ተጓዦችንም ሆነ ንብረቶቻቸው ላይ ምንም አይነት #ጉዳት_ያላደረሰ ነበር፡፡ከአዋሽ ወደትግራይ የሚወስደው መንገድ ትላንት ጠዋት 2 ሰዓት ላይ የተከፈተ ሲሆን ከመሃል አገር ወደምስራቅ ኢትዮጵያና ወደ ጂቡቲ የሚወስዱት መንገዶችም ተከፍተዋል፡፡

Via VOA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሀላባ ከተማ‼️

በደቡብ ክልል ሀላባ ከተማ ትናንት በተሰራጨ #ሀሰተኛ_ወሬ የተነሳሱ ወጣቶች በከተማው በሚገኙ ቤተክርስቲያናት ላይ #ጉዳት ማድረሳቸውን የከተማው ነዋሪዎች ገለጹ፡፡

ነዋሪዎቹ እንዳሉት በከተማው #የማቃጠልና የንብረት #ማውደም ድርጊቱ የተፈጸመው ሌንዳ በር እና ዋጃ በር በተባሉ ቀበሌያት ውስጥ በሚገኙ የፕሮቴስታንት ቤተክርስቲያናት ላይ ነው፡፡ በስፍራው ነበርኩ ያሉ እንድ የከተማው አዛውንት ጥቃቱ የተጀመረው በድራሜ ከተማ መስኪድ መቃጠሉንና ኢማም መገደሉን የሚገልጹ ወሬዎች ከተናፈሱ በኋላ በቡድን የተሰባሰቡ ወጣቶች በቤተክርስቲያናቱ ላይ ጥቃት ሲያደርሱ መመልከታቸውን ለጀርመን ድምፅ ራድዮ ገልጸዋል፡፡

የጀርመን ድምፅ ራድዮ በሥልክ ያነጋገራቸው የሀላባ ዞን ሰላምና ፀጥታ መምሪያ ሃላፊ አቶ #ዓለሙ_ሌንቢሶ ደግሞ በከተማው በተሳሳተ ወሬ የተነሳሱ ወጣቶች አንድ ቤተክርስቲያን በእሳት ያቃጠሉ ሲሆን በሌሎች ሰባት ቤተክርስቲያናት ላይ ደግሞ ንብረቶችን የማውደም ድርጊት መፈጸማቸውን ገልጸዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት እጅ ከፍንጅ የተያዙ 20 ግለሰቦችን ጨምሮ 63 ተጠረጣሪዎች በህግ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን የጠቆሙት ሃላፊው የዞኑ ፖሊስ ኮሚሽነርም ጥቃቱን ለመከላከል ጥረት ባለማድረጋቸው ከሃላፊነታቸው ተነስተው ምርመራ እየተካሄደባቸው እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡

በኢትዮጲያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ምንጫቸው ባልተረጋገጡ ወሬዎች በመነሳሳት የሚፈጸሙ የደቦ ጥቃቶች እየተበራከቱ መምጣታቸው ይታወቃል፡፡ በቅርቡ በጉዳዩ ዙሪያ ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ጥያቄ የቀረበላቸው ጠቅላይ ሚንስትር ዶክተር አብይ አህመድ ቀደም ባሉት ጊዚያት ደቦ እርሻን በህብረት ለመሥራት ይውል እንደነበር አስታውሰው አሁን ግን ጸብም በደቦ እየሆነ መምጣቱ አሳሳቢ ነው ሲሉ ምላሽ መስጠታቸው ይታወሳል፡፡

ምንጭ፦ የጀርመን ድምፅ ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አሳዛኝ ዜና‼️

በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ ከተማ ኮተቤ ዩኒ ቨርሲቲ አካባቢ በግንባታ ላይ የነበረ #ድልድይ አርማታ #ተደርምሶ 12 ሰዎች #ጉዳት ደረሰባቸው፡፡ ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች ወደ #ሆስፒታል ተወስደዋል። በአደጋው #ህይወቱ ያለፈ ሰው ስለመኖሩ #የታወቀ ነገር የለም።

Via EBC
ፎቶ፦m & jes(tikvahethiopia)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በሰሜን ተራሮች ብሄራዊ ፓርክ ተከስቶ የነበረው እሳት ሙሉ ለሙሉ #መጥፋቱን የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ልማትና ጥበቃ ባለስልጣን ያስታወቀ ሲሆን፣ በፓርኩ የተከሰተው የእሳት ቃጠሎ እስካሁን 700 ሄክታር የሚሆነው መሬት ላይ #ጉዳት ማድረሱን ገልጿል።

Via #ELU
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"ትላንት በቃሊቲ #አብዱልቃድር_መስጂድ የተፈጠረው ችግር ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዕውቅና ውጪ የተደረገ ነው፡፡ ምንም ዓይነት ጥያቄ ቢኖር በመነጋገር መፍታት እየተቻለ አላስፈላጊ #ጉዳት ወደሚያደርስ እንቅስቃሴ ውስጥ መግባት ከየትኛውም አካል የማይጠበቅ ተግባር ነው፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጉዳዩ #ከዕውቅናው_ውጪ እንዴት እንደተፈፀመ እና በቀጣይም መጣራት የሚያስፈልጋቸውን ነገሮች በሙሉ በመፈተሽ በመዋቅሩ የማስተካከያ ዕርምት እንደሚወስድ በዚህ አጋጣሚ ያረጋግጣል፡፡ በተፈፀመው ነገር ሁሉ የከተማ አስተዳደሩ የተሰማውን #ሃዘን ይገልፃል፡፡" Mayor Office of Addis Ababa

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#NewsAlert

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ድራማዊና አሳዛኝ ሂደቶችን አስተናግዶ ተጠናቋል አለ ፋሲል ከነማ የእግር ኳስ ስፖርት ክለብ፤ ክለቡ በይፋዊ የፌስቡክ ገፁም ተከታዩን መረጃ አሰራጭቷል፦

"የፋሲል ከነማ ስፖርት ክለብ ሽሬን ገና በ5ኛው ደቂቃ መምራት ቢጀምርም በደጋፊዎቻችን ላይ በደረሰው ጉዳት ውጥረት ላይ የገቡት ተጫዋቾቻችን በጥንቃቄ በመጫዎት መሪነታቸውን ቢያስጠብቁም በ70ኛው ደቂቃ #ጥፋት ተሰርቷል በማለት በፍፁም ጨዋታውን ካስጀመሩ በኃላ ፍፁም ቅጣት ምት የሰጡብን ሲሆን ከጎሉ መቆጠር በኃላ በደጋፊዎቻችን ላይ በደረሰው የድንጋይ ውርዋሮ ብዛት ያላቸው ደጋፊዎች #ጉዳት በማስታገሳቸው ጨዋታው ለበርካታ ደቂቃዎች ተቋርጦ የጀመረ ሲሆን በዛው 1ለ1 ተጠናቋል።"

በሌላ በኩል፦ ቡድኑ በይፋዊ የፌስቡክ ገፁ ባሰራጨው መረጃ እስካሁን ድረስ ደጋፊዎቼ ከስታዲየሙ #ሊወጡ አልቻሉም ብሏል።

የኢትዮጵያ ፕሪሜር ሊግ
🗞ቀን ሰኔ 30/2011 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በትላንትናው ዕለት በጎንደር ከተማ በተፈጠረው የፀጥታ ችግር አንዳንድ የንግድ ተቋማት ላይ #ጉዳት መድረሱን፤ የደረሰውን የጉዳት መጠንም የማጣራት ስራ መጀመሩን #የጎንደር ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ የህዝብ ግንኙነት ኦፊሰር ኮማንደር ማረልኝ ወንድሙ ተናግረዋል። በጥፋቱ የተሳተፉ ግለሰቦችም በቀጣይ የማጣራት ስራ ከተከናወነ በኋላ በህግ #ተጠያቂ እንደሚደረጉም ገልፀዋል።

🗞ቀን ሃምሌ 2/2011 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ጊዜው ያለፈበት የኦርጂናል ማንጎ ጭማቂ በቁጥጥር ስር ዋለ!

በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ አስር ወደ 1 ሺህ 500 ካርቶን የሚጠጋ ጊዜው ያለፈበት የራኒ ማንጎ ጭማቂ በቁጥጥር ስር ዋለ፡፡ በቁጥጥር ስር የዋለው ምርት በገበያ ላይ ቢውል በህብረተሰቡ ጤና ላይ ከፍተኛ #ጉዳት ሊያደርስ የሚችል መሆኑም ተጠቁሟል፡፡

Via AMN
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#attention

በደቡብ ወሎ ዞን በቃሉ ወረዳ እስካሁን ማለትም እስከ 27/02/2012 ዓ./ም ድረስ በ12 ቀበሌወች የአንበጣ መንጋ የተከሰተ መሆኑ ተገልጿል። በወረዳው በ013፣ 016፣ 017፣ 018፣ 019፣ 020፣ 021፣ 022፣ 023፣ 024፣ 026 እና 027 ቀበሌዎች የተከሰተ ሲሆን 16 ሺ ሄክታር መሬትንም ይሸፍናል። ከዚህም ውስጥ 4800 ሄክታር በማሽላና በሌሎች ሰብሎች የተሸፈነው በአንበጣ መንጋው የተጠቃ በመሆኑ ለጊዜው በአማካይ ከ15-20% ምርት ላይ #ጉዳት አድርሷል። ወረዳው ለበላይ አካል የድረሱልን ጥሪ ለማሰማት ጥረት ያደረገ ቢሆንም አካባቢው ለአውሮፕላን ርጭት ምቹነት የለውም በሚል ተጀምሮ ቀርቷል። በመሆኑም ወረዳው በራሱና ለድጋፍ ከሌሎች ወረዳወችና ተቋማት በመጡ አካላት እንድሁም በጎ ፈቃደኞች ሰፊ ርብርብ እያደረገ ይገኛል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#የፀጥታ_ጉዳይ " የክልል እና የፌደራል የጸጥታ ሀይል እንዲገባልን አመልክተናል " - አቶ ውብሸት አበራ ታጣቂዎች በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ደራ ወረዳ ከሌሊት 8 ሰዓት ጀምሮ ተኩስ እንደከፈቱ ተሰምቷል። ለአል ዓይን ኒውስ የደራ ወረዳ፤ ጉንዶ መስቀል ከተማ ነዋሪዎችን ዋቢ አድርጎ እንደዘገበው ፤ መንግስት በአሸባሪነት የፈረጀው የኦነግ ሸኔ ቡድን ታጣቂዎች ወደ ከተማዋ ዘልቀው በመግባት ከባድ…
#ትኩረት

በሰሜን ሸዋ ፤ ደራ ወረዳ ያለው ሁኔታ ከፍተኛ ትኩረት እንደሚያስፈልገው በወረዳው ቤተሰቦቻቸው የሚኖሩ የቲክቫህ አባላት አመልክተዋል።

" ንፁሃን በጭንቀት ውስጥ ነው ያሉት " ሲሉ የገለፁት የቤተሰብ አባላቶቻችን ዛሬ በጉንዶ መስቀል ከተማ ከፍተኛ የሆነ የተኩስ እሩምታ ሲሰማ እንደነበር እና ነዋሪውም #ለደህንነቱ_በመስጋት በየቤቱ ተቀምጦ እንደነበር ተናግረዋል።

በሰው ህይወት እና በንብረት ላይ #ጉዳት መድረሱን አመልክተው አፋጣኝ እንዲሁም አስተማማኝ መፍትሄ እንዲፈልግ ድምፃቸውን አሰምተዋል።

የደራ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ውብሸት አበራ ዛሬ ለአል ዓይን ኒውስ በሰጡት ቃል ፤ የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ወደ ደራ ወረዳ ዋና ከተማ ጉንዶ መስቀል መግባታቸውን ገልፀዋል።

ከጠዋት ጀምሮ በከተማዋ ባሉ ባንኮች፣ የመንግስት ተቋማት እና የግለሰቦች ንብረት ላይ ዘረፋ ሲፈፀም እንደነበር ጠቁመው ወረዳው የክልል እና የፌደራል የጸጥታ ሀይል እንዲገባለት ማመልከቱን አሳውቀዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

" ተማሪዎች ላይ የደረሰ ጉዳት የለም " - የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የጤና ሳይንስ ኮሌጅ ሁነኛ አካል

በአማራ ክልል ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ጥበበ ግዮን ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የሚገኙ ተማሪዎች ማክሰኞ ጥር 28 ቀን ከምሽቱ 2፡30 ገደማ ታጣቂዎች በካምፓሱ ውስጥ ተኩስ መክፈታቸውን፣ ተማሪዎቹ ከግቢው እንዲወጡም ማስጠንቀቂያ መስጠታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸው፣ የሚመለከተው አካል ሰላም ወዳለበት ግቢ እንዲቀይርላቸው ጠይቀዋል።

በኮሌጁ የጸጥታ ችግር አለ የሚል መረጃ ደርሶናል እውነት ነው ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ ያቀረበላቸው ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ አንድ የኮሌጁ ሁነኛ አካል ፣ " ተማሪዎቹ የነገሯችሁ #እውነት ነው። ችግሩ ተፈጠረ፣ ግቢው ተደበደበ። ተማሪዎች ወጡ " ሲሉ አረጋግጠዋል።

በተማሪዎች ላይ የደረሰ ጉዳት አለ ? ተብሎ ለቀረበላቸው ጥያቄ ፤ " ተማሪዎች ላይ የደረሰ #ጉዳት የለም። ከግቢው ገቡ፣ ከዚያ ተኩስ ተጀመረ፣ ከዚያ #ቦምብ አፈነዱ፣ ጥይት ተተኮሰ " ሲሉ አስረድተው፣ " ‘ተማሪዎች መውጣት አለባችሁ የሚል ነገር ተናገሩ እነርሱ (ታጣቂዎቹ) " ብለዋል።

ታጣቂዎቹ ተማሪዎቹን ከግቢ መውጣት እንዳለባቸው ይህን ካላደረጉ ግን በቀጥይ እርምጃ እንደሚወስዱ እንዳስጠነቀቁ ገልጸዋል።

የሴቶች ብሎክ 1 እና 3 ሕንጻ የተወሰነ በታጣቂዎች መመታቱን የገለፁ ሲሆን " ተማሪ ግን #አልጎዱም  " ብለዋል።

" ተማሪዎች ላይ ታርጌት አላደረጉም ሕንጻውን ነው የደበደቡት። ቦምቡ ደግሞ ከተማሪዎች ወደ ካፌ መሄጃ በኩል እዚያው ከግቢው ውስጥ ፈንድቷል። የፈነዳበት ቦታ ይታወቃል " ሲሉ አክለዋል።

ተኩስ የከፈቱት ታጣቂዎች ፍላጎታቸው ምንድን ነው ? ለሚለው ጥያቄ እኚሁ ግለሰብ " ‘ዩኒቨርሲቲ በቃችሁ፣ ከመጀመሪያውስ ለምን መጣችሁ?’ እያሉ ሲናገሩ ነበር " ያሉ ሲሆን " ‘አሁንም ግቢውን ለቃችሁ ውጡ። ዛሬ አንጎዳችሁም። ቀጣይ ግን ስንመጣ ብናገኛችሁ ቀጥታ እርምጃ እንወስዳለን’ የሚል እንድምታ ነበር ብለዋል።

በግቢው አጠቃላይ ከ1,500 እስከ 2,000 ተማሪ የሚገኝበት ሲሆን ከትላንት ጠዋት ጀምሮ #አብዛኞቹ ተማሪዎች ግቢውን ለቀው መውጣታቸውን ተናግረዋል።

" ወደ ቤት የሚሄዱ አሉ (ምክንያቱም በጣም ጭንቅ ነበር በተለይ ሴቶች፣ ሌሊትም #ሲያለቅሱ ነበር) ዘመድ ጋ ወደ ከተማ የሚጠጉም አሉ። #ሆቴል ይዘው ያደሩ ልጆችም አሉ። ቤተሰብ ሩቅ የሆነባቸው፣ ገንዘብ የሌላቸው ተማሪዎች አሉ ግቢ ውስጥ ቁጭ ብለው በጭንቀት " ሲሉ የሁኔታውን አሳሳቢነት አስረድተዋል።

ታጣቂዎቹ ወደ ካምፓሱ ሲገቡ ጥበቃዎች አልነበሩም ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ላቀረበው ጥያቄ ፣ " የእኛ ካምፓስ አዲስ ስለሆነ አጥር የለውም። በዙሪያው ጥበቃዎች አሉ። ግን ጥበቃዎች በኮማንድ ፓስቱ ምክንያት መሣሪያ አይዙም። መሣሪያ ቢይዙም የመጣው ኃይል በጣም ብዙ ነው " ብለዋል።

የተማሪዎቹ ፍላጎትስ ምንድነው ? ለሚለው ጥያቄም፣ " ተማሪዎች መማር ይፈልጋሉ። ምክንያቱም በኮሮና ጊዜ፣ በጦርነት ምክንያት አማራ ክልል ላይ ብዙ ታሹ። አብዛኛው ተማሪ መማር ይፈልጋል፣ ግን ደግሞ ከሕይወት የሚበልጥ ነገር የለም " የሚል ምላሽ ተሰጥተዋል።

የካምፓሱ ከፍተኛ ባለስልጣናት በጉዳዩ ዙሪያ ረቡዕ ጥር 29 ቀን 2016 ዓ/ም አስቸኳይ ስብሰባ እንደነበራቸው፣ በዚህም " በጥበቃ (በመከላከያ) ተጠብቀው ይማሩ ወይስ ሌላ ግቢ እናመቻችላቸው ? " በሚለው ጉዳይ እንደተወያዩና ውሳኔው ግን እንዳልታወቀ ተመላክቷል።

መረጃው የተዘጋጀው በአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።

@tikvahethiopia