TIKVAH-ETHIOPIA
1.38M subscribers
54.5K photos
1.35K videos
197 files
3.61K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
በደቡብ አፍሪካ እስካሁን በትንሹ 10 ኢትዮጵያውያን ሞተዋል!

በደቡብ አፍሪካ እስካሁን ከ10 የማያንሱ #ኢትዮጵያውያን በኮቪድ-19 መሞታቸውን በደቡብ አፍሪካ የኢትዮጵያውያን ማህበረሰብ ፀሃፊ አቶ ፋኖስ ሃይሌ ለቪኦኤ ተናግረዋል።

ጁሃንስበርግ ፣ ሊንፖፖ፣ ማፑማላንጋ እንዲሁም ዌስተርን ኬፕ ኢትዮጵያውያን ከሞቱባቸው አካባቢዎች ይጠቀሳሉ።

አስክሬናቸውን ወደ ሀገር ቤት መላክ ስለማይፈቅድ የሁሉም ቀብር ስነስርዓት በዛው በደቡብ አፍሪካ ውስጥ ተፈፅሟል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ከፍተኛ_ጥንቃቄ የኢትዮጵያ ቆንስላ ፅ/ቤት፤ ጅዳ #ለኢትዮጵያውያን የጥንቃቄ መልዕክት አስተላልፏል። ለፅ/ቤቱ ከትላንት ምሽት ጀምሮ እየደረሱ ባሉት መረጃዎች መሠረት የሳዑዲ የፀጥታ አስጠባቂ አካላት ፦ - በጄዳ ፣ - መዲና ፣ - ጂዛን እና መካ ከተሞች ላይ የመኖርያ ፈቃድ ባላቸውም ይሁን በሌላቸው ዜጎች ላይ የፍተሻና የአፈሳ እርምጃ እየወሰዱ ይገኛሉ። በዚህም ምክንያት ጉዳዩ እስኪጣራ ኢትዮጵያውያን…
#Update #SaudiArabia #Attention

"...የአካል ወይም ንብረት ጉዳት የደረሰባችሁ ዜጎች ያላችሁን ማስረጃ በመያዝ ለቆንስላ ጽ\ቤቱ ማቅረብ ትችላላችሁ" - በጅዳ የኢትዮጵያ ቆንስላ

የሳዑዲ ዓረቢያ የፀጥታ ኃይሎች በሳዑዲ የተለያዩ ከተሞች ላይ የመኖርያ ፈቃድ ባላቸውም ይሁን በሌላቸው ነዋሪዎች ላይ የፍተሻና የአፈሳ እርምጃ እየወሰዱ መሆኑን ተከትሎ ዜጎች ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ማሳሰቢያ ማስተላለፉ ይታወቃል።

በዚህ ሂደት በተለይ ህጋዊ የመኖርያ ፈቃድ ኖሯቸው በህግ አስከባሪ አካላት ከመጠን ያለፈ ኃይል አጠቃቀም ምክንያት የአካል ወይም የንብረት ጉዳት የደረሰባቸው ዜጎች ያላቸውን ማስረጃ በመያዝ ለቆንስላ ጽህፈት ቤቱ ማቅረብ እንደሚችሉ ተገልጿል።

አሁንም #ኢትዮጵያውያን ተገቢውን ሁሉ ጥንቃቄ ማድረግ እንዲቀጥሉ የቆንስላ ጽ\ቤቱ በድጋሚ የጥንቃቄ መልዕክቱን አስተላልፏል።

@tikvahethiopia
#ምርጫ2013

ዛሬ ማምሻውን የአሜሪካ መንግስት ባወጣው መግለጫ ከምርጫ በኋላ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ውይይት እንዲደረግ ጥሪ አቅርቧል።

የኢትዮጵያን የወደፊት አካሔድ ለመወሰን እና የአገሪቱን ዴሞክራሲ እና ብሔራዊ አንድነት ለማጠናከር ጠ/ ሚ ዐቢይ አህመድ የሚመሩት መንግሥት እና መላ ኢትዮጵያውያን ከምርጫ በኋላ ለሚካሔድ አካታች የፖለቲካ ብሔራዊ ውይይት ቁርጠኛ እንዲሆኑ ነው የባይደን አስተሳደር ጥሪ ያቀረበው።

ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን የሚመሩት የአሜሪካ አስተዳደር ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እና ለሠራተኞቹ ጥረቶች እውቅና ቢሰጥም ፤ 6ኛው አገራዊ ምርጫ የሚካሔድበት ከባቢ “አሳሳቢ ነው” ብሏል። 

የአሜሪካ መንግስትን አቋም የሚያንጸባርቀው መግለጫ ዛሬ ማምሻውን አንቶኒ ብሊንከን በሚመሩት የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት በኩል ነው የወጣው።

የባይደን አስተዳደር የኢትዮጵያ ምርጫ አሉበት ያላቸው ፈተናዎች ፦
- የተቃዋሚ ፖለቲከኞች እስር፣
- የገለልተኛ ሚዲያ መዋከብ፣
- የአካባቢያዊ እና ክልላዊ መንግሥታት ወገንተኝነት እንዲሁም በመላ ኢትዮጵያ በብሔሮች እና በማህበረሰቦች መካከል የተቀሰቀሱ ግጭቶች ለነፃ እና ፍትሐዊ ምርጫ እንቅፋት ናቸው ብሏል።

"በኢትዮጵያ በርካታ አካባቢዎች በክልሎች እና ብሔሮች መካከል ያለው ልዩነት መካረር የአገሪቱን አንድነት እና የግዛት ሉዓላዊነት ያሰጋል” ያለው የአሜሪካ መንግስት #ከምርጫው_በኋላ መፍትሔ ሊፈለግ እንደሚገባ አሳስቧል።

የአሜሪካ መንግስት ፥ “ከምርጫው በኋላ ያለው ጊዜ #ኢትዮጵያውያን ተባብረው እነዚህን ልዩነቶች ለመጋፈጥ ኹነኛ ወቅት ነው” ብሏል።

የአሜሪካ መግለጫ : www.state.gov/elections-in-ethiopia/

#EthiopiaInsider #SpokespersonNedPrice #Ethiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update #SaudiArabia #Attention "...የአካል ወይም ንብረት ጉዳት የደረሰባችሁ ዜጎች ያላችሁን ማስረጃ በመያዝ ለቆንስላ ጽ\ቤቱ ማቅረብ ትችላላችሁ" - በጅዳ የኢትዮጵያ ቆንስላ የሳዑዲ ዓረቢያ የፀጥታ ኃይሎች በሳዑዲ የተለያዩ ከተሞች ላይ የመኖርያ ፈቃድ ባላቸውም ይሁን በሌላቸው ነዋሪዎች ላይ የፍተሻና የአፈሳ እርምጃ እየወሰዱ መሆኑን ተከትሎ ዜጎች ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ማሳሰቢያ…
#Update

በሳዑዲ ዓረቢያ የህግ አስከባሪ አካላት ተይዘው የነበሩ ህጋዊ የመኖርያ ፈቃድ ያላቸው ኢትዮጵያውያን ከእስር እንዲፈቱ መደረጉ ተገፀ።

የሳዑዲ የፀጥታ አስከባሪ አካላት በሳዑዲ የተለያዩ ከተሞች ላይ የመኖርያ ፈቃድ ባላቸውም ይሁን በሌላቸው ነዋሪዎች ላይ የፍተሻና የአፈሳ እርምጃ እየወሰዱ እንደሆነ እና ዜጎችም ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ማሳሰቢያ መሰራጨቱ ይታወሳል።

ይህንን ተከትሎ ከተለያዩ ከተሞች በህግ አስከባሪ አካላት የተያዙ የነበሩና ህጋዊ የመኖርያ ፈቃድ ያላቸው ከጅዳና መካ ከተሞች ከአርባ በላይ ኢትዮጵያውያን ከጂዛን ዘጠና አራት ከመዲና ስድስት መቶ እንዲሁም ከአብሃ ሰላሳ ስምንት ኢትዮጵያውያን የበጅዳ የሚገኘድ የኢትዮጵያ ቆንስላ ጽ\ቤቱ ባደረገው ክትትል እንዲፈቱ መደረጉ ተነግሯል።

ጉዳዩን አስመልክቶም የቆንስላ ጽ\ቤቱ ከሚመለከታቸው የሳዑዲ መንግስት የሥራ ኃላፊዎች ጋር በቅርበት እየተነጋገረ መሆኑን ያሳወቀ ሲሆን በተለይ በህጋዊ የመኖርያ ፈቃድ አማካኝነት ነዋሪ በሆኑ ኢትዮጵያውያን ላይ የሚደርስ ማንኛውም የማዋከብና እንግልት ምክንያት እንዲገለፅለትና ይሄው በአስቸኳይ እንዲቆም የቆንስላ ጽ\ቤቱ በኦፊሴል ጉዳዩ ለሚመለከተው የሳዑዲ መንግስት ተቋም እንዳመለከተ አሳውቋል።

ቆንስላ ጽህፈት ቤቱ ፥ በቀጣይ ቀናት በጉዳዩ ላይ ተገቢውን ክትትል በማድረግ አስፈላጊውን እንቅስቃሴ እንደያደርግ እና እንደሚያሳውቅ ገልጿል።

#ኢትዮጵያውያን አሁንም ቢሆን ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ እንዲቀጥሉ የጥንቃቄ መልዕክት ተላልፏል።

መረጃው የኢፌድሪ ቆንስላ ፅ/ቤት (ጅዳ) ነው።

@tikvahethiopia
#Attention

የሳዑዲ የፀጥታ አስጠባቂ አካላት በሳዑዲ የተለያዩ ከተሞች ላይ የመኖርያ ፈቃድ ባላቸውም ይሁን በሌላቸው ነዋሪዎች ላይ የፍተሻና የአፈሳ እርምጃ እየወሰዱ እንደሆነ ይታወቃል።

በዚሁ መሰረት:-

- አስቸኳይ ጉዳይ ካልገጠማችሁ በስተቀር አሁን በሳዑዲ ያለው የአፈሳና ፍተሻ ሁኔታ እስኪረጋጋ ድረስ ሁሉም ዜጎች ወደ ቆንስላ ጽ\ቤቱ አካባቢ እንዳትሄዱ።

- የሳዑዲ የፀጥታ አስከባሪ አካላት በሚወስዱት እርምጃም በተለይ ህጋዊ የመኖርያ ፈቃድ ኖሯቸው በህግ አስከባሪ አካላት ከመጠን ያለፈ ኃይል አጠቃቀም ምክንያት የሰብዓዊ መብት ጥሰት ያጋጠማቸው የአካልና የንብረት ጉዳት የደረሰባቸው / ዘረፋ ያጋጠማቸው ዜጎች ተጨባጭ ማስረጃ በመያዝ ለቆንስላ ጽ\ቤቱ መጠቆም ይችላሉ። መረጃውን መሰረት በማድረግ የቆንስላ ጽ\ቤቱ ከሳዑዲ ወገን ጋር እነጋገራለሁ ብሏል።

-የመኖርያ ፈቃዳቸው ተቃጥሎ በራሳቸው ወጪ ወደአገር ለመግባት አሻራ ለመስጠት ሲጠባበቁ የነበሩ ዜጎች ከትላንት በስቲያ ጀምሮ የሳዑዲ ወገን የአሻራ አገልግሎት መስጠቱን ያቋረጠ በመሆኑ ከአገሪቱ የመንግስት ኃላፊዎች ጋር በመነጋገር አገልግሎቱ ዳግም እስኪጀመር ድረስ እንዲታገሱ።

- ዜጎች በቆንስላ ጽ\ቤት አካባቢ ጨምሮ በየትኛውም አካባቢ ሲንቀሳቀሱ የሳዑዲ የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ከኮሮና ቫይረስ ጋር ተያይዞ ባወጣው ደንብ መሰረት የራሳቸውን እና የሌላውን ጤና ለመጠበቅ / ደንቡን ካለማክበር ከሚደርስ ቅጣት ለመዳን ሙሉ አፍና አፍንጫችሁን በማስክ ሸፍናችሁ እንድትንቀሳቀሱ አደራ ተብሏል።

አሁንም #ኢትዮጵያውያን ተገቢውን ሁሉ ጥንቃቄ ማድረግ እንድትቀጥሉ በጅዳ የሚገኘው ቆንስላ ጽ\ቤት የጥንቃቄ መልዕክቱን አስተላልፏል።

(የኢትዮጵያ ቆንስላ ፅ/ቤት፣ ጅዳ)

@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#ALERT

ኑሯችሁን በደቡብ አፍሪካ ያደረጋችሁ የቲክቫህ - ኢትዮጵያ ቤተሰቦች ሰሞኑን የቀድሞ የደቡብ አፍሪካ ፕሬዘዳንት ጃኮብ ዙማ ለፖሊስ እጃቸውን መስጠታቸው ተከትሎ በተለያዩ አካባቢዎች በሚገኙ ደጋፊዎቻቸው የተጀመረው ረብሻ አሁን መልኩን ቀይሮ የስደተኛ ንብረቶች እና የሀገሪቱ ትልልቅ ካምፓኒዎች (Checkers and Shopright ) የመሳሰሉትን ማውደም ላይ ትኩረት አድርጓል።

ስለዚህም ደቡብ አፍሪካ ውስጥ የምትኖሩ #ኢትዮጵያውያን እራሳችሁን ከጥቃት እንድትጠብቁ እና የሀገሪቱን ሚዲያዎች በትኩረት እንድትከታተሉ አደራ እንላለን።

ከዚህ ጋር ተያይዞ ትላንት ማታ የደ/ አፍሪካ ፕሬዘዳንት ሲርል ራማፎሳ " ግጭት እያስከተሉ ያሉ ተቃውሞዎች እንዲቆሙ የጠየቁ ሲሆን፤ "ለዚህ አመጽ እና የንብረት ውድመት ምንም ዓይነት ምክንያት ሊቀርብ አይችልም" ማለታቸው የሚታወስ ነው።

Faya (Tikvah-Family)
South Africa
Limpopo

@tikvahethiopia
" ከ70 በላይ #ኢትዮጵያውያን 🇪🇹 ፖላንድ ገብተዋል " - በኢትዮጵያ የፖላንድ ኤምባሲ

በአዲስ አበባ የሚገኘው የፖላንድ ኤምባሲ ሩስያ ዩክሬን ላይ ወረራ ከፈፀመች በኃላ በፖላንድ ስላለው ሁኔታ ከተማሪዎች እና ከቤተሰቦች በርካታ ጥያቄዎች እየደረሰው መሆኑን ገልጿል።

በፖላንድ ግዛት ምንም አይነት የፀጥታ ችግር የለም ያለው ኤምባሲው እንደሁል ጊዜው ዩኒቨርሲቲዎች ክፍት ናቸው ፣ ትምህርትም ቀጥሏል ፤ እንዲሁም ሆስፒታሎች፣ የትራንስፖርት አገልግሎት (ባቡር፣ ባስ) ፣ ሬስቶራንቶች፣ ቢሮዎች ሁሉ እንደሁልጊዜ ስራ ላይ ናቸው ብሏል።

በአሁን ሰዓት ከ1,500 በላይ ተማሪዎች በፖላንድ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ እንደሚገኙም ተጠቁሟል።

ኤምባሲው ሩስያ በዩክሬን ላይ ህገወጥ ወረራ ከፈፀመች አንስቶ ከ1.5 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ጦርነት ሽሽት ወደ ፖላንድ መግባታቸውን አመልክቶ ከእነዚህም መካከል በርካታ አፍሪካውያን እንደሚገኙበት እና ከ70 በላይ የሚሆኑትም #ኢትዮጵያውያን 🇪🇹 መሆናቸውን ገልጿል።

ፖላንድ ጦርነት ሸሽተው ወደ ሀገሯ የሚመጡ ሰዎች ደንበር ላይ የተቀላጠፈ አገልግሎት እንዲያገኙና ፤ የምግብና መጠለያ ጨምሮ አስፈላጊ የሆኑ ድጋፎችን እያደረገች እንደሆነው በአዲስ አበባ የፖላንድ ኤምባሲ አሳውቋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#KenyaElection🇰🇪

የኬንያን ምርጫ እየታዘቡ የሚገኙ #ኢትዮጵያውያን እነማን ናቸው ?

ኬንያ እያካሄደች ያለችውን 5ኛው ዙር ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ለመታዘብ ኢትዮጵያውያን ኬንያ ይገኛሉ።

🇪🇹 አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ፦

የቀድሞ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃለማርያም ደሳለኝ መቀመጫውን ደቡብ አፍሪካ ያደረገውን 'ብሬንትረስት ፋውንዴሽን'ን በመወከል ምርጫውን እየታዘቡ ናቸው።

አቶ ኃይለማርያም በሚመሩት ልዑክ ውስጥ እውቁ ኡጋንዳዊ ፖለቲከኛ እና ሙዚቀኛ ቦቢ ዋይን ይገኝበታል።

🇪🇹 ዶ/ር ሙላቱ ተሾመ ፦

የቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት ዶክተር ሙላቱ ተሾመ ደግሞ የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በየነ መንግሥታት (ኢጋድ) ታዛቢ ቡድንን በመምራት ኬንያ ናቸው።

🇪🇹 ፕ/ር መረራ ጉዲና ፦

የተቃዋሚው የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ፓርቲ መሪ እና አንጋፋው ፖለቲካኛ ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና በኬንያ ተገኝተው ምርጫውን እየታዘቡ ይገኛሉ።

🇪🇹 ሌንሳ ቢየና ፦

የኢትዮጵያ የህግ ባለሙያ ሴቶች ማህበር ዋና ስራ አስፈጻሚ ሌንሳ ቢየና የኤን ዲ አይ/አይ አር አይ (NDI/IRI) ዓለም-አቀፍ ምርጫ ታዛቢ ልኡክ አካል ሆነው በኤልዶሬት ከተማ በዩዜን ጊሹ ካዉንቲ የሚደረገዉን ምርጫ በመታዘብ ላይ ይገኛሉ፡፡

መረጃው ከቢቢሲ እና ከኢትዮጵያ የህግ ባለሙያ ሴቶች ማህበር ያገኘነው ነው።

@tikvahethiopia
#ጥቆማ #YALI2023

የማንዴላ ዋሽንግተን ፌሎ ሺፕ ፕሮግራም የ2023 (Mandela Washington Fellowship) ማመልከቻ ዛሬ ክፍት ተደርጓል።

በአህጉሪቱ ያሉ ወጣቶች ተወዳድረው #በአሜሪካ ሀገር በሚደረግ ሥልጠና ላይ እንዲሳተፉ እድሉ ተመቻችቶላቸዋል።

ከዚህ ቀደም በርካታ #ኢትዮጵያውያን ወጣቶች እድሉን ተጠቅመው ይህንን ሥልጠና ወስደዋል።

በሥልጠናው ላይ ለመሳተፍ የሚያስፈልጉትን መስፈርቶችን ለማየትና ለማመልከት ይህን ይጫኑ👇
https://www.mandelawashingtonfellowship.org/apply/

👉 Application Timeline :

• August 16, 2022 | Application opens

• September 13, 2022 | Application deadline

• November 2022 – January 2023 | Semi-finalists interviewed by local U.S. embassies and consulates

• March 2023 | Applicants are notified of their status

• May 2023 | Visa processing and Pre-Departure Orientations for Finalists

June 2023 | Fellowship begins in the United States

Via @tikvahethmagazine
ፎቶ ፦ ዛሬ ረቡዕ የአፍሪካ የበሽታዎች መከላከልና መቆጣጠር ማዕከል የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ በቻይናው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቺን ጋንግ እና በአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ተመርቋል።

ስለ ማዕከሉ ምን ይታወቃል ?

- ማዕከሉ የኢትዮጵያ መንግሥት ኃይሌ ጋርመንት ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ከሊዝ ነፃ ባቀረበው በ90 ሺሕ ሜትር ስኩዌር መሬት ስፋት ያለው መሬት ላይ የተገነባ ነው።

- የህንፃው ግንባታ ብቻ በ40 ሺሕ ሜትር ስኩዌር ላይ ያረፈ ነው፡፡

- የቻይና መንግሥት 80 ሚሊዮን ዶላር በማውጣት የግንባታውን ሙሉ ወጪ ሸፍኗል።

-  የመጀመሪያው ምዕራፍ ግንባታ 25 ወራትን  ፈጅቷል።

- ማዕከሉ የድንገተኛ አደጋ ኦፕሬሽን፣ የመረጃ፣ የላብራቶሪ፣ የስልጠና ፣ የኮንፈረንስ ማዕከል ፣ ቢሮዎች እና አፓርትመንቶች አሉት።

- የማዕከሉ ሁለተኛ ምዕራፍ ግንባታ (አገልግሎት ለማስጀመር የሚያስችሉ የማጠቃለያ ሥራዎች) እየተካሄደ ነው።

- ማዕከሉ በቅርቡ ሙሉ ስራው ተጠናቆ ወደ ሥራ ይገባል።

- በግንባታው ላይ #ቻይናውያንና #ኢትዮጵያውያን የህንፃ ባለሞያዎች እየተሳተፉበት ነው።

Info : ENA
Photo Credit : Tesfaye Wube (Tikvah Family)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" የሱዳን ጎረቤቶች የእርስ በርስ ጦርነትን አይፈልጉም " - ኦቪግዌ ኢግዌጉ የጂኦፖለቲካ እና የፀጥታ ጉዳይ ተንታኝ ኦቪግዌ ኢግዌጉ ለአልጀዚራ በሰጡት ቃለ ምልልስ ፤ የሁሉም ቀጠናዊ ሀገራት ዋና ጉዳይ በሱዳን የሚካሄደው ጦርነት ወደ " ሙሉ የእርስ በርስ ጦርነት " እንዳይቀየር ማረጋገጥ ነው ብለዋል። " ለዚያ #ቅርብ ነን ነገር ግን በእውነቱ በዚያ ደረጃ ላይ አይደለንም። " ያሉት ተንታኙ ፤ ከሱዳን…
#Update

በሱዳን እየተካሄደ ባለው ውጊያ ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ በርካታ ሰላማዊ ሰዎች እየተገደሉ ናቸው።

በሱዳን የኢትዮጵያ ኤምባሲ ፤ በሱዳን እየተካሄደ ባለው ውጊያ በርካታ ሲቪሎች ለጉዳት መዳረጋቸውና ህይወትም እየተቀጠፈ መሆኑን ገልጿል።

ከእነዚህ መካከል #ኢትዮጵያውያን እንደሚገኙበት መረጃዎች እንደደረሱት አመልክቷል።

ኤምባሲው ምን ያህል ኢትዮጵያውያን እንደሞቱ እና እንደተጎዱ በዝርዝር አልገለፀም።

ነገር ግን በኢትዮጵያውያን ሞት እና ጉዳት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እደተሰማው እና ለሟች ቤተሰቦች እና ወዳጅ ዘመዶቻቸው መፅናናትን ተመኝቷል።

" ይህን አስቸጋሪ ጊዜ ለማለፍ ኢትዮጵያዊን የተቻላቸውን ሁሉ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ በድጋሜ እናሳስባለን " ብሏል።

መረጃ ለመለዋወጥ እና ለምክክር የኤምባሲው ባልደረባ የሆኑትን አቶ ነጅብ አብደላ በስልክ ቁጥር +249911646547 ማነጋገር እንደሚቻል በሱዳን ካርቱም የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ አሳውቋል።

በሌላ በኩል ፥ ከትላንት ምሽት አንስቶ በሱዳን የማህበራዊ መገናኛዎች ላይ አንድ ቪድዮ ሲሰራጭ ነበር (ከላይ ተያይዟል) ።

ቪድዮው በመድፍ የተመታ ቤትን የሚያሳይ ሲሆን በቤቱ ውስጥ የሚኖሩት ኢትዮጵያውያን እንደነበሩና ሁሉም ወዲያው ህይወታቸው እንዳለፈ ተነግራል። ቁጥራቸው ምን ያህል እንደሆነ የተገለፀ ነገር የለም።

ስለተሰራጨው ቪድዮ እና ስለደረሰው ጉዳት ትክክለኝነት በሱዳን የኢትዮጵያ ኤምባሲ ያለው ነገር የለም።

በሱዳን እየተካሄደ ያለው ውጊያ በከተማ ውስጥ እየተደረገ መሆኑ በዛው የሚኖሩ የሀገራችንን ዜጎች ጨምሮ የመላው ሱዳናውያንን ደህንነት አደጋ ላይ ጥሏል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የሱዳን ውጊያ 6ኛ ቀኑን ይዟል። በተዋጊዎቹ ኃይሎች መካከል ለ2ኛ ጊዜ ትላንት የ24 ሰዓታት ለሰብዓዊት ተኩስ ለማቆም ሙከራ ተደርጎ የነበር ቢሆንም ሳይሳካ ቀርቶ ውጊያው ቀጥሎ እንደነበር ተሰምቷል። የተኩስ አቁም እንዲደረግ የተሞከረው ዜጎቻቸውን ከሱዳን ለማስወጣት እየጣሩ ባሉ ሀገራት ግፊት መሆኑን አልጀዚራ ዘግቧል። ዛሬም በሱዳን የተለያዩ ከተሞች ውጊያ መኖሩ በተለይ በካርቱም የፕሬዜዳንቱ ቤተመንግስት…
#ሱዳን

" ቤተሰቦቻችን ስላሉበት ሁኔታ ለማወቅ አልቻልንም ፤ጭንቀት ላይ ነን "

በሱዳን እየተካሄደ ያለው ውጊያ ዛሬ 6ኛ ቀኑን መያዙ ይታወቃል።

በሱዳን ያሉ ቤተሰቦቻችን ያሉበትን ሁኔታ ለማወቅ ካርቱም ወዳለው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ስልክ ብንደውልም ምላሽ አላገኘንም ሲሉ እዚህ ኢትዮጵያ የሚገኙ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት መልዕክት ልከዋል።

በሱዳን ያሉ ቤተሰቦቻቸውን ለማግኘት ባለመቻላቸው እንደተጨነቁ የገለፁት እንዚሁ አባላት ፤ ማንን መጠየቅ እንዳለብን ግራ ገብቶናል ይህ ጉዳይ የሚመለከተው አካል ምላሽ ሊሰጠን ይገባል ብለዋል።

ለበርካታ ኢትዮጵያውያን ሁለተኛ ቤት በሆነችው ሱዳን ውስጥ ኢትዮጵያውያን ለስራ እና በቋሚነት ለኑሮ እንደሚገኙ ይታወቃል።

የሰሞኑ የሱዳን ውጊያ ደግሞ እዛ ያሉትን ብቻ ሳይሆን እዚህ ያሉ ቤተሰቦችንም ጭምር ጭንቀት ውስጥ ጥሏል።

ከትላንት በስቲያ በሱዳን የኢትዮጵያ ኤምባሲ ፤ በሱዳን እየተካሄደ ባለው ውጊያ በርካታ ሲቪሎች ለጉዳት መዳረጋቸውና ህይወትም እየተቀጠፈ መሆኑን በመግለፅ ከእነዚህ መካከል #ኢትዮጵያውያን እንደሚገኙበት መረጃዎች እንደደረሱት አሳውቋል።

ኤምባሲው ምን ያህል ኢትዮጵያውያን እንደሞቱ እና እንደተጎዱ በዝርዝር ባይገልፅም ይህን አስቸጋሪ ጊዜ ለማለፍ ኢትዮጵያዊን የተቻላቸውን ሁሉ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አሳስቧል።

መረጃ ለመለዋወጥ እና ለምክክር የኤምባሲው ባልደረባ የሆኑትን አቶ ነጅብ አብደላ በስልክ ቁጥር +249911646547 ማነጋገር እንደሚቻልም ገልጿል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Metema

የምዕራብ ጎንደር ዞን ፥ ከ6 ሺህ በላይ የሱዳን ተፈናቃዮች በመተማ በኩል ወደ ኢትዮጵያ መግባታቸውን አስታውቋል።

ዞኑ ፥ በሱዳን በተፈጠረው የእርስ በርስ ጦርነት የ42 ሀገራት ዜጎች  በመተማ በኩል ወደ ኢትዮጵያ መግባታቸውን ነው ያመለከተው።

ወደ አካባቢው ሊገባ የሚችለውን ተፈናቃይ ለመቀበል በሚቻልበት ጉዳይ ቅድመ ዝግጅት  ሲያደርግ መቆየቱን የገለፀው ዞኑ እስከ ሚያዝያ 20/2015 ዓ.ም ባለው ጊዜ ብቻ  ከ6 ሺህ በላይ የ42 ሀገራት  ዜጎች መግባታቸውን አመልክቷል።

ከዚህ ውስጥ ደግሞ 941  #ኢትዮጵያውያን መሆናቸውን ገልጿል።

ተፈናቃዮቹ የጤና ችግር እንዳይገጥማቸው የጤና ባለሙያ በመመደብ  አገልግሎት እየተሰጠ ነው ያለው ዞኑ በዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት በኩል መካከለኛና ከፍተኛ ተሽከርካሪዎች ተመድቦ ተፈናቃዮች ወደ የሚፈልጉት አካባቢ የመሸኘት ሥራ ተሠርቷል ብሏል።

የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበርም ውኃና ብስኩት በማቅረብ እያገዘ እንደሆነ ዞኑ ገልጿል።

በቀጣይ ችግሩ እየሰፋ የሚሄድ ከኾነ ወደ ቀጣናው ሊገባ የሚችለውን ስደተኛ ሊያስተናግድ የሚችል ቦታ የመለየት ሥራ መሰራቱን ዞኑን ማስታወቁን አሚኮ ዘግቧል።

ፎቶ ፦ ፋይል

@tikvahethiopia
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ 20 ሺህ ሰራተኞችን ሊቀጥር ነው ?

ከሀሰተኛ መረጃ ተጠንቀቁ !

በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ " ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በማህበራዊ ትስስር ገፁ 20 ሺህ #ኢትዮጵያውያን ሰራተኞችን መቅጠር እንደሚፈልግ አስታወቀ ፤ ኢትዮጵያውያን ሰራተኞችን የሚቀጥረው ትግራይ ፣ አፋር፣ ሶማሌ ክልሎችን ጨምሮ በሁሉም ክልሎች የቴሌኮም አገልግሎቱን ለማስፋፋት በማቀድ ነው ፤ የስራ ቅጥሩ ዲግሪ አይጠይቅም 10ኛ እና 12ኛ ክፍል ያጠናቀቁ ማመልከት ይችላሉ " እየተባለ የሚሰራጨው መረጃ ፍፁም #ሀሰተኛ መሆኑን ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ገልጾልናል።

ከጥዋት አንስቶ ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ የተሰራጨውን የ20 ሺህ ሰራተኞች ቅጥር መረጃ በተመለከተ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለሚመለከተው የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ክፍል " በየትኛው የማህበራዊ ትስስር ገፃችሁ ላይ ነው ይህ ያሳወቃችሁት ? መረጃው እውነት ከሆነስ በየትኛው መንገድ ነው ማመልከት የሚቻለው ? " ስንል ጥያቄ ያቀረብን ሲሆን መረጃው #ሀሰተኛ ነው የሚል ምላሽ ተሰጥቶናል።

" እኛ 20 ሺህ ሰራተኞች ለመቅጠር በየትኛውም የማህበራዊ ትስስር ገፃችን ላይ ጥሪ አላቀረብንም ፤ መሰል ሀሰተኛ መረጃዎች የሚሰራጩት ሆን ተብሎ ተመሳስለው በተከፈቱ #ሀሰተኛ_ገፆች ነው " ሲል የሚመለከተው የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ክፍል ገልጾልናል።

በመሆኑም " ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ 20 ሺህ ኢትዮጵያውያን ሰራተኞችን ሊቀጥር ነው " በሚል የሚሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ ነው።

@tikvahethiopia
" 7 ስድተኞች ህይወታቸው አልፏል ፤ 9 ተጎድተዋል " - IOM

ታንዛኒያ ውስጥ በደረሰ አደጋ ስደተኞች ህይወታቸው አለፈ።

ዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት (IOM) በተባበሩት ታንዛኒያ ሪፐብሊክ ፤ ኒጆምቤ ክልል በደረሰ የመኪና አደጋ ስደተኞች ላይ የሞት እና አካል ጉዳት መድረሱን ባወጣው መግለጫ አሳውዋል።

ድርጅቱ አደጋው እንደደረሰ የታመነው እኤአ መስከረም 14 መሆኑን አመልክቷል። #ኢትዮጵያውያን ናቸው ተብለው የታሰቡ 29 ስደተኞችን የጫነ መኪና ወደ ዛምቢያ ድንበር ቱንዱማ በመጓዝ ላይ እያለ አደጋው መድረሱን ገልጿል።

በአደጋው 7 ስደተኞች እንደሞቱና 9ኙ ጉዳት እንደደረሰባቸው ገልጿል። 13 ስድተኞች ያሉበት ሁኔታ አይታወቅም ብሏል።

ዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት በዚህ አሰቃቂ አደጋ ለተጎዱት ሁሉ የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ገልጿል።

ሰራተኞቹ በታንዛኒያ ከሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ሰራተኞች ጋር በመሆን በቦታው ተገኝተው ስለሁኔታው የበለጠ ዝርዝር መረጃ ለማግኘት እና በተቻለ መጠን ድጋፍ ለማድረግ እየሰሩ እንደሆነ አሳውቋል።

በኢትዮጵያ ኤምባሲ ወይም በውጭ ጉዳይ በኩል ጉዳዩን በተመለከተ የሚወጣ መረጃ / መግለጫ ካለ ተከታትለን እንልካለን።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሔራዊ ደህንነት አማካሪ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ፤ ምንም ያህል #ጫና ቢደረግ የህዳሴውን ግድብ እንዳሳካነው የባህር በሩም በተመሳሳይ ይሳካል አሉ። አምባሳደር ሬድዋን፤ " የህዳሴውን ግድብ ያሳካነው ተጨብጭቦልን ሳይሆን ከቅርብም ከሩቅም እየተላጋን፣ የሥጋት ከበሮ እየተደለቀ፣  ዛቻና ማስፈራሪያ በምድርም በአየርም ልምምድ እያስገመገመብን ፣ ሁሉንም ዓይነት ጫና…
#ኢትዮጵያ

" ስለ ስምምነቱ ቀድሞውኑ የሚመለከታቸው ሀገራት እና ተቋማት እውቅናው ነበራቸው ፤ ግን አላዋቂ ለመምሰል ጥረት እያደረጉ ነው " - አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን

የጠቅላይ ሚኒስትሩ ብሄራዊ ደህንነት አማካሪ ሬድዋን ሁሴን ስለ ኢትዮጵያ እና ሶማሌላንድ የመግባቢያ ስምምነት ምን አሉ ?

" ኢትዮጵያ ከባህር በር ጋር በተያያዘ ዕድል ያላት የሚመስለው ከሰሜን በኩል ነበር።

ሁሉም ሰው ስለ ባህር በር ሲወራ ቀይ ባህር ነው፤ ስለ ባህር ሲወራ ኤርትራ ነው ፤ ስለ ባህር ከተወራ አሰብ ነው። ይሄን አሁን ለመገልበጥ የሚያችል አዲስ አቅጣጫ ነው የወሰድነው።

ኢትዮጵያ ዙሪያዋ እድሎች አሏት፣ ዙሪያዋ ያሉ እድሎችን መጠቀም የሚያስችል አቅምም አላት፤ መጋራት የሚያስችል በጎ ፍላጎትም መነሻም አላት።

በአንድ ወይ በሌላ መንገድ ኢትዮጵያ አንድ የሆነ የባህር በር ሊኖራት ይገባል በሆነ መንገድ የሚለው ብዙዎች እየገዙት የመጣ ነው።

አትጋጩ፣ ችግር አትፍጠሩ፣ በሰላማዊ መንገድ የሚመጣበትን መንገድ በትዕግስት ሂዱ ነው እንጂ የሚለው ኢትዮጵያ unfair የሆነ ነገር እየፈለገች ነው የሚል ብዙ ምልከታ የለም።

ኢትዮጵያ ፍላጎቷን፣ ያላት concern ትክክል ነው፣ የህዝብ እግደቷም ትክክል ነው፣ ኢኮኖሚዋም ትክክል ነው ፣ የቀጠናው ችግር ትክክል ነው በዚህ ረገድ ኢትዮጵያ በአውንታዊነት ሚና ልጫወት ማለቷ ተገቢ ነው የሚለውን አጀንዳ ማድረግ ተችሏል።

... ይሄንን ፊርማ (ከሶማሌላንድ ጋር) እስክንፈርም ድረስ በUN ተቋማትም፣ በአንዳድን ትላልቅ ሀገሮች መረጃዎችም ፣ በእኛ Think tank በሚባሉ NGOዎችም ይሰራ የነበረው ጥናት የኢትዮጵያ መንግሥት ወይ ኤርትራን ይወራል፣ ወይ ደግሞ ሶማሌላንድን በአውዳል ግዛት በኩል ረብሻ ፈጥሮ ቀጠናውን ያተራምሳል የሚል ጥናት ነበር ሲሰራ የነበረው።

በዚህ ላይ draft ቀርቦ የቀረበው draft official ከመሆኑ በፊት የተመለሰ draft እናውቃለን። ይሄንን እነማን እንደሚሰሩት እናውቃለን፣ እሱ ውስጥ #ኢትዮጵያውያን እንዳሉበትም እናውቃለን። ስለዚህ ትላልቆቹ ሀገራት የሳቱት ነገር ፤ እኛም ባገኘናቸው ቁጥር ጦርነት አንፈልግም ውጊያ አንፈልግም ሲባል ' አይ መዋጋታችሁማ አይቀርም አናምናችሁም ' የሚባል ነው ጭቅጭቁ ከዋሽንግተን እስከ ሌሎቹ ድረስ ፤ ስለዚህ በዚህ ሊዋጉ ነው ብለው ሲገምቱ በዚህ በኩል በሰላም መጣን አልተገመትንም ግን ያልተገመትነው ለበጎ ነው።

... መንግሥት ፍላጎቱን ይፋ ካደረገበት ጊዜ ጀምሮ ለጎረቤት ሀገሮች ፣ በአጠቃላይ ለምስራቅ አፍሪካ ሀገሮች ከአንዴም ሁለት ጊዜ envoy ተልኳል። የማያውቁት ነገር ቢኖር ሙሳቤሂ መቼ እንደሚመጣ (ወደ አዲስ አበባ) እና እዚህ ውስጥ የሼር ጉዳይና የእውቅና ጉዳይ MoU ውስጥ እንደሚካተት አያውቁም። ስለዚህ ከሞላ ጎደል አሰብ አካባቢ የምንከራተት አድርገው ስለወሰዱ ይሄን ጉዳይ ትርጉም አልሰጡትም።

አሁን አፍጥ ሲመጣ ነው ሰው የደነገጠው እንጂ የአብዛኛው ሰው ፍርሃት #በአሰብ በኩል ችግር ትፈጥራላችሁ ፣ ስለዚህ እጃችን ላይ በቂ ችግር አለ የዩክሬን አለ የጋዛ አለ፣ ከምትጨምሩብን በሰላማዊ መንገድ አድርጉትና በሰከነ መንገድ እኛም እናግዛችኃለን የሚል ነውና የpredictability deficit የተነሳበት angle ትክክል አይመስለኝም።

ስለ ጉዳዩ ለእያንዳንዱ ለሚመለከተው መንግሥት አስረድተናል። "

#AmbassadorRedwanHussien #etv

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#IOM በጅቡቲ የባህር ዳርቻ የ38 ሰዎች አስክሬን ተገኘ። በጀልባ መስጠም አደጋ የህፃናትን ጨምሮ አጠቃላይ 38 ሰዎች ሞተው አስክሬናቸው መገኘቱን የዓለም አቀፉ የስድተኞች ድርጅት አሳውቋል። 6 ሰዎች የገቡበት ያልታወቀ ሲሆን ሳይሞቱ እንዳልቀረ ተነግሯል። ከሞት የተረፉ 22 ሰዎች በጅቡቲ እርዳታ እየተደረገለቸው ይገኛል። @tikvahethiopia
" 38 #ኢትዮጵያውያን ፍልሰተኞች ህይወታቸው አልፏል " - በጅቡቲ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ

በጅቡቲ የባህር ዳርቻ ፍልሰተኞችን አሳፍራ ወደ #የመን በመጓዝ ላይ በነበረች ጀልባ ላይ በደረሰ የመስጠም አደጋ 38 ኢትዮጵያውያን ፍልሰተኞች ህይወታቸውን እንዳጡ በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አሳውቋል።

ትላንትና ሰኞ በጅቡቲ ሰሜን ምስራቅ " #ጎዶሪያ " በሚባል የባህር ዳርቻ አቅራቢያ ስልሳ (60) ኢትዮጵያውያን ፍልሰተኞችን አሳፍራ ወደ #የመን ትጓዝ የነበረች ጀልባ ላይ በደረሰው የመገልበጥ አደጋ የ38 ፍልሰተኞች ሕይወታቸውን አጥተዋል።

በጅቡቲ የኢፌዴሪ ሚሲዮንም አደጋው ከደረሰ በኋላ ወደ ስፍራው በመጓዝ የአደጋውን መንስኤ በማጣራት ላይ እንደሚገኝ ተገልጿል።

ኤምባሲው ፥ በየዓመቱ ከ200 ሺህ የሚበልጡ ፍልሰተኞች ከጅቡቲ ባህር ዳርቻ የኤደን ባህረ ሰላጤ በመነሳት መካከለኛው ምስራቅ አገራት ለመድረስ በየብስና በባህር አደገኛ ጉዞ ያደርጋሉ ብሏል።

ባለፉት አምስት ዓመታት #በጀልባ_መስመጥ አደጋ ብቻ የ189 ዜጎቻችን ሕይወት እንዳለፈ ጠቁሟል።

በየጊዜው የሚደርሰው አደጋ እንዳለ ቢሆንም የፍልሰተኞቹ ቁጥር ግን አሁንም #እየጨመረ እንደሆነ ገልጿል።

ዜጎች በህገ ወጥ #ደላሎች የሀሰት ስብከት በመታለል ውድ ሕይወታቸውን አደጋ ላይ ጥለው በዚህ አደገኛ የጉዞ መስመር ከመንቀሳቀስ እንዲቆጠቡ አስጠንቅቋል።

የፍትህ አካላት ሕገ ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎችን #ከገጠራማ የአገራችን አካባቢዎች ዜጎችን በመመልመል ለስደት በሚዳርጓቸው ግለሰቦች ላይ ተገቢውን እርምጃ እንዲወስዱ በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አሳስቧል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

ከየመን የባህር ዳርቻ ልዩ ስሙ " #አራ " ከሚባል ስፍራ 77 #ኢትዮጵያውያን ፍልሰተኞችን አሳፍራ ወደ ጅቡቲ ስትጓዝ የነበረች ጀልባ መገልበጧ መገለጹ ይታወሳል።

በዚህም አደጋ የ5 ዓመት #ሕጻናት እና #ሴቶችን ጨምሮ 16 ኢትዮጵያውያን እንደሞቱ መገለጹ አይዘነጋም።

የIOM የጅቡቲ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ታንጃ ፓሲፊክ ፤ የሟቾች ቁጥር ቀደም ሲል ከሰጠው መረጃ ማለትም 16 ከፍ ማለቱንና 21 መድረሱን ተናግረዋል።

የሞቱት ሁሉም #ኢትዮጵያውያን መሆናቸውን ገልጸዋል።

23 ሰዎች አሁንም ድረስ የት እንደገቡ እንኳን አይታወቅም ብለዋል።

33 ሰዎች ከአደጋው እንደተረፉ ገልጸዋል።

ይህ አደጋ #38_ኢትዮጵያውን ከሞቱበት አደጋ ከሁለት ሳምንት ባነሰ ጊዜ ውስጥ የተከሰተ ነው።

በርካታ ሰዎች በተለይም ወጣቶች ህይወታቸውን ለመቀረ ሲሉ በአደገኛው እና ህገወጥ በሆነው መንገድ ሀገራቸውን ጥለው ይሰደዳሉ ፤ በዚህም ህይወታቸውን ባህር ላይ ያጣሉ ፣ ይታሰራሉ፣ በየበረሃው ይንገላታሉ ፣ በደላሎች ታግተው ይሰቃያሉ ።

ሀገር ጥለው በህወጥ መንገድ የሚሰደዱ ሰዎች ቁጥር ሲጨምር እንጂ ሲቀንስ አይታይም።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#INSA

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢመደአ) ያዘጋጀው የ2016 ዓ/ም “ ብሄራዊ የሳይበር ታለንት ቻሌንጅ ” ፕሮግራም ምዝገባ እስከ ሰኔ 10/2016 ዓ/ም ድረስ መራዘሙን አሳውቋል።

እስካሁን በርካታ ልዩ ተሰጥኦ ያላቸው ታዳጊ ወጣቶች መመዝገባቸው ተገልጿል።

ምዝገባው እስከ ሰኔ 10 ድረስ መራዘሙ ተጠቁሟል።

በሳይበር ደህንነት እና በተያያዥ ዘርፎች ልዩ ተሰጥኦ ያላቸው ታዳጊ ወጣቶች እንዲመዘገቡ ጥሪ ቀርቧል።

የታለንት መስኮች ፦

- Cyber Security
- Cyber Development
- Embedded Systems
- Aerospace ሲሆኑ ስልጠናው በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ለ1 ወር ይሰጣል።

ተመራቂዎች ፦

° #እንደየችሎታቸው እና #እንደስራዎቻቸው ከተለያዩ ባለሀብቶች ጋር የማስተሳሰር፤

° ኢመደአን (INSA) ጨምሮ በተለያዩ ተቋማት ውስጥ ተቀጥረው መስራት የሚችሉበት ሁኔታ እንደሚማቻች ከተቋሙ ተሰምቷል።

የመመዝገቢያ ፖርታል ፦ https://talent.insa.gov.et

NB. እድሜ ፦ ከ11 አመት ጀምሮ ( #ኢትዮጵያውያን)

@tikvahethiopia
#Yemen

በአብዛኞቹ #ኢትዮጵያውያን የሆኑ ስደተኞችን አሳፍራ ስትጓዝ የነበረች ጀልባ ከየመን የባሕር ዳርቻ አቅራቢያ ተገልብጣ 39 ሰዎች ሞቱ።

እንደ IOM እና ከአደጋው ከተረፉ ሰዎች በተገኘ መረጃ ጀልባዋ 260 የሚጠጉ ሰዎችን አሳፍራ የነበር።

በካባድ ነፋስ ምክንያት መገልበጧ ተጠቁሟል።

መሞታቸው ከታወቀው 39 ሰዎች ውጪ ሌሎች 150 ሰዎች የደረሱበት አልታወቀም። እነሱን ለማግኘት ፍለጋ እየተደረገ ነው።

71 ሰዎች ከአደጋው ተርፈዋል።

የሩደም አካባቢ ባለሥልጣናት ጀልባዋ ላይ ተሳፈረው ከነበሩት 260 ስደተኞች በአብዛኞቹ #ኢትዮጵያውያን ስደተኞች እንደነበሩ አመልክተዋል።

#Reuters #IOMYemen #IOMspokesperson

@tikvahethiopia