TIKVAH-ETHIOPIA
1.41M subscribers
55K photos
1.37K videos
199 files
3.67K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
አቶ ጌታቸው አሰፋ‼️

የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኢህአዴግ) 11ኛ ድርጅታዊ ጉባኤውን ከነገ ጀምሮ በሀዋሳ ያደርጋል። አራቱ የኢህአዴግ እህት ድርጅቶችም ከድርጅታዊ ጉባኤው በፊት የፓርቲዎቻቸውን ሊቀ መንበር፣ ምክትል ሊቀ መንበር፣ የማዕከላዊ እና የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት ምርጫን አካሂደዋል።

የኦሮሞ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅት (ኦህዴድ) መጠሪያውን ወደ የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኦዴፓ) በተመሳሳይ መልኩ የብሔረ አማራ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ብአዴን) ደግሞ ወደ የአማራ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (አዴፓ) መቀየራቸው ይታወሳል። ሁለቱ ፓርቲዎች ከስማቸው ባሻገር የአርማ ለውጥም አድርገዋል። በሌላ በኩል ሕዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ (ህወሓት) እና የደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ደኢህዴን) የቀድሞ ስማቸውን እና አርማቸውን ይዘው ቀጥለዋል።

ኦዴፓ፣ አዴፓ እና ዴኢህዴን በርካታ የቀድሞ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባሎቻቸውን በአዲስ እና ወጣት አባሎች ተክተዋል። ይህ በእንዲህ
እንዳለ ህውሓት ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል አድርጎ የመረጣቸው ግለሰቦች ነባር እና ከሞላ ጎደል የድርጅቱ ታጋዮች መሆናቸው አነጋጋሪ ሆኖ ቆይቷል።

በተለይ ደግሞ የቀድሞው የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት ዋና ዳይሬክተር የነበሩት አቶ #ጌታቸው_አሰፋ ከዐሥራ አንዱ የድርጅቱ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት መካከል አንዱ ሆነው መመረጣቸው ብዙዎች ህወሓት #ከለውጡ ራሱን ገሽሽ እያደረገ ስለመሆኑ እንደ አንድ ማሳያ አድርገው ወስደውታል።

ለመኾኑ አቶ ጌታቸው አሰፋ ወደ ሥራ አስፈጻሚ መምጣታቸው አሁን ባለው የለውጥ አውድ ምን ፖለቲካዊ ትርጉም ይሰጣል?

በጉዳዩ ላይ አስተያየታቸውን ለቢቢሲ የሰጡት የህወሓት የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል እና የቀድሞ የመንግሥት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ የነበሩትን አቶ #ጌታቸው_ረዳን እንዲህ ብለዋል፦

''ጌታቸው አሰፋ #ጎበዝ መሪ መሆኑን አውቃለሁ። ጎበዝ #ኢህአዴግ መሆኑን አውቃለሁ። ጎበዝ #ህወሓት መሆኑን አውቃለሁ። ህወሓት ሲወስን በሚዲያ #ሃሜት ላይ ተመሥርቶ አይደለም የሚወስነው'' በማለት በቀድሞው የደኅንነት ሹም አቶ ጌታቸው አሰፋ ላይ የሚቀርቡ ወቀሳዎችን አጣጥለዋል።

አቶ ጌታቸው ጨምረውም ''ይፋዊ መግለጫ ሳይኖር ሚዲያዎች ሃሜት ሲያወሩ ነበር። ሃሜት ላይ ተወስነን ውሳኔ የምናስተላልፍ ቢሆን ኖሮ ሃገር #ይጠፋል። ክስ ስለመመስረቱም የማውቀው ነገር የለም። አቶ ጌታቸው አሰፋን ፈልጎ ህውሓት ጋር የመጣ አካል የለም።'' በማለት አቶ ጌታቸው አሰፋ ላይ ክስ አለመመሥረቱን አመላክተዋል።

አቶ ጌታቸው አያይዘው እንደሚሉት ከሆነ አቶ ጌታቸው አሰፋ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል ሆኖ የመመረጥ ፍላጎት አልነበራቸውም።

''ማዕከላዊ ኮሚቴ ውስጥ መግባትም አልፈለገም፤ ሲሪየስሊ [አጥብቆ] ነው የተከራከረው። ጉባኤው ግን ከማዕከላዊ ኮሚቴ ውስጥ እንዲገባ ወሰነ። ማዕከላዊ ኮሚቴው ደግሞ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል ውስጥ መግባት አለበት ብሎ ወሰነ።'' ይላሉ አቶ ጌታቸው ረዳ።

"አቶ ጌታቸው አሰፋ በጉባኤው ላይ ለመሳተፍ ወደ ሀዋሳ ይሄዳሉ ወይ?" ተብለው ለተጠየቁት ጥያቄ አቶ ጌታቸው ረዳ ሲመልሱ ''የማዕከላዊ ኮሚቴ አባል በጉባኤው እንዲሳተፍ ይጠበቃል። እንደማንኛው የኮሚቴ አባል ሀዋሳ ላይ ልታይዋቸው ትችላላችሁ።

እንደማንኛውም የማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ተሳትፎ ማድረግ ስላለብን አንዳንዶቻችን ያው መንገድ ላይ ነን። ለምሳሌ አውሮፕላን ካመለጠኝ ልቀር እችላለሁ'' ብለዋል።

ይህ አገላለጽ 'አቶ ጌታቸው አሰፋ ላይገኙ ይችላሉ' የሚለውን ያመላክት እንደሆነ ከቢቢሲ የተጠየቁት አቶ ጌታቸው ረዳ፣"እኔ የእያንዳንዱ ሰው ስኬጁል አላወጣም። ሁላችንም ተበትነን ነው ወደ ሀዋሳ እየሄድን ያለነው፤ ጌታቸውም በራሱ ጊዜ ስኬጁሉን አሬንጅ ያደርጋል፤ ካገኘሁት እነግራችኋለሁ" ሲሉ በቀልድ የታጀበ ምላሽ ሰጥተዋል።

ነገ በሚጀመረው የኢህአዴግ 11ኛ ድርጅታዊ ጉባኤ ላይ የድርጅቱ ሊቀ መንበር ማን ሊሆን ይችላል ተብለው ለተጠየቁት ጥያቄ ''አሁን ያሉት ሊቀ መንበር ላለፉት 5 ወይም 6 ወራት ሲያገለግሉ ቆይተዋል። እስካሁን የሠሩት ሥራ ተገምግሞ ለውጥ ማድረግ ያስፈልገናል ወይስ አያስፈልገንም የሚለው የጉባኤው ውሳኔ ነው የሚሆነው'' በማለት መልሰዋል።

ህወሓት ማንን በእጩነት ለማቅረብ እንደተሰናዳ የተጠየቁት አቶ ጌታቸው ረዳ ፓርቲዎች እንደማይመርጡ አስረድተዋል። ''ህወሓት፣ ብአዴን
ወይም ኦህዴድ ዕጩዎችን አያቀርቡም። ፓርቲዎች አይደሉም ዕጩዎችን የሚጠቁሙት። ከ180ዎቹ የኢህአዴግ ምክር ቤት አባላት ግለሰቦችን ለሊቀ መንበርነት ለጉባኤው ጥቆማዎችን ይሰጣሉ። ከዚያም ምርጫ ይካሄዳል። ድምጽ ያገኘ ያሸንፋል።'' ብለዋል።

በግንባሩ ጉባኤ ላይ ሊነሱ የሚችሉ ዋና ዋና ጉዳዮች ምን ሊሆኑ እንደሚችሉ የተጠየቁት አቶ ጌታቸው፤ ''የዕድገት እና ትራንስፎርሜሽን ዕቅዱ አፈጻጸም ላይ መቀዛቀዝ ይታያል።

ለሚቀጥሉት ሁለት ዓመታት እሱን እንዴት አድርገን ነው በፍጥነት የምናስቀጥለው የሚለው ትልቁ አጀንዳ ነው። ወደ ሃገር እንዲገቡ የተደረጉ ተፎካካሪ፣ ተቃዋሚ የሚባሉ ፓርቲዎች ወደ ሃገር ከገቡ በኋላ አንዳንዱ 'አሸንፌ ነው የመጣሁት' ይላል። ሌላኛው 'ወደሽ ሳይሆን ተገደሽ ነው የተቀበልሺኝ' ይላል። ይህ ዓይነት ስሜት የሚፈጥረው #የሰላም እና #የመረጋጋት ዝብርቅርቅ አለ። ይህን ለመሰሉ ጉዳዮች ጉባኤው #ምላሽ ይሰጣል። ይህ የሁላችንም አጀንዳ ነው'' ብለዋል።

ምንጭ፦ ቢቢሲ የአማርኛው አገልግሎት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#የካቲት11 #ሚሊንየምአዳራሽ #ህወሓት

የህወሀት 45ኛ ዓመት የምስረታ በአል የማጠቃለያ ዝግጅት በድርጅቱ ደጋፊዎችና አዲስ አበባ የሚገኙ የክልሉ ተወላጆች በሚለኒየም አዳራሽ በደማቅ ሁኔታ መከበሩን ቀጥሏል።

በበዓሉ ላይም በርካታ የድርጅቱ ከፍተኛ አመራሮች ፣ ደጋፊዎች፣ አባላትና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

በአሁኑ ሰዓት በትግሉ ወቅት የነበሩ ማነቃቂያ ሙዚቃዎችና ሙዚቃዊ ድራማዎች በበዓሉ ለተገኙ ታዳሚዎች እየቀረበ ይገኛል። የይህም ትግራይ ህዝብ የደርግ ስርዓትን ለመገርሰስ የከፈለውን መስዋዕትነት እየተዘከረ ያለበት መድረክ ነው።

#TikvahFamily

የቲክቫህ ቤተሰቦች ከሚሊኒየም አዳራሽ!

PHOTO : የትግራይ ኮሚኒኬሽን
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
እስካሁን ድረስ #ህወሓት የገደላቸው፣ ያፈናቸው፣ ያቆሰላቸው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር አባላት ፦

- በደቡባዊ ዞን 1 የአስተዳደሩን አባል ገድሏል፤ 1 አቁስሏል።

- ደቡብ ምስራቃዊ ዞን 3 የአስተዳደረን አባላት ሲገድል ፤ 9 አባላትን አፍኗል።

- በምስራቅ ዞን 1 የአስተዳደሩን አባል ሲገድል ፤ 2 አባላትን አፍኗል።

- በደቡብ ምስራቅ ዞን (ተንቤን) 1 የአስተዳደሩን አባል ሲገድል ፤ 1 አባል አቁስሏል፤ 5 አባላትን አፍኗል።

- በማዕከላዊ ዞን 6 የአስተዳደሩን አባላት ሲገድል፤ 4 አባላትን አፍኗል፤ 1 አቁስኗል።

- በሰሜን ምስራቅ 9 የአስተዳደሩን አባላት ገድሏል።

- በመቐለ አንድ የአስተዳደሩን አባል ሲገድል ፤ 1 አቁስሏል።

በአጠቃላይ 46 የትግራይ ጊዜያዊ አሰተዳደር አባላት ላይ "ህወሓት" ጥቃት አድርሷል።

ከዚህ በተጨማሪም ህወሓት ቤቶችን ማቃጠሉን እና መኖሪያ ቤቶችን በጥይት መደብደብ ቀጥሏል ፤ የኢትዮጵያ ሀገር መከላከያ ሰራዊት እንዲሁም የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ክልሉ ለማረጋጋት እና አጥፊዎችንም ተጠያቂ ለማድረግ ቁርጠኞች ናቸው ሲል የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መረጃ ማጣሪያ ገልጿል።

@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ሰኔ 1 ቀን 1997 ዓ/ም !

" ኢህአዴግ " ስልጣን ከያዘ በኃላ ለ3ተኛ ጊዜ የተካሄደውን #የ1997ቱ ሀገር አቀፋዊ ምርጫ ተከትሎ በተፈጠረው ቀውስ ሳቢያ ሰኔ 1/1997 በመንግስት የተገደሉ ዜጎች ዛሬ 16ኛ ዓመት መታሰቢያቸው ነው።

በወቅቱ "ኢህአዴግ" ይህን መሰሉ አንባገነናዊ ተገባር የፈፀመው ስልጣኑን ለማስጠበቅ ፣ ስልጣኑን የሚያስጠብቀውም በመሳሪያ ኃይል እንጂ በህዝብ ድምፅ እንዳልሆነ የተቀናቃኝ ፖለቲካ ኃይሎች በተለያየ ጊዚያት ተናግረዋል።

ሰኔ 1 ቀን 1997 በግፍ በመንግስት የፀጥታ ኃይሎች የተገደሉ ዜጎች ለነፃነት፣ ለዴሞክራሲ፣ ለፍትህ፣ ለሀገራዊ አንድነት ዋጋ የከፈሉ እንደሆኑ ይነገርላቸዋል፤ በየዓመቱም በዚህ ቀን ይታሰባሉ።

ፖለቲከኞች ፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾ ይህን የሰኔ 1 ቀን 1997 ዓ.ም ክስተት ለሁሉም ትምህርት የሚሰጥ እና መቼም ቢሆን ሊደገም የማገባው ብዙ ትምህርትም ሰጥቶ ያለፈ እንደሆነ ይናግራሉ።

በወቅቱ (ሰኔ 1 ቀን 1997 ዓ.ም) በግፍ የተገደሉ ፣ የቆሰሉ፣ ለእስርና እንግልት የተዳረጉ ዜጎች ኢትዮጵያን ያስተዳደር በነበረው "ኢህአዴግ" በሚባለው ፓርቲ ወቅት ሲሆን ፓርቲው ከዓመት በፊት በኢትዮጵያ ምድር ህልውና እንዳይኖረው ተደርጎ፣ ከስሟል።

በውስጡ የነበሩ ድርጅቶችም ከአንዱ (#ህወሓት) በቀር አንድ ላይ ተዋህደው ውህድ ፓርቲ ፈጥረው ኢትዮጵያን እያስተዳደሩ ነው።

Video Credit : Biniyam Hirut
@tikvahethiopia
#LieutenantGeneralBachaDebele 

በሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የሠራዊት ግንባታ ሥራዎች ዋና አስተባባሪ ሌተናል ጄነራል ባጫ ደበሌ ለቢቢሲ ቃለምልልስ ሰጥተዋል።

ቃለምልልሱ በወቅታዊ የጦርነቱ ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነበር።

ሌ/ጄነራል ባጫ ደበሌ ህወሓት ባደራጀው ሰራዊት አዲስ አበባ ገብቶ ኢትዮጵያን እበትናለሁ በሚል ሂሳብ እስከ ሰሜን ሸዋ የተወሰኑ አካባቢዎች ድረስ ገብቶ እንደነበር ገልፀዋል።

" በመከላከል ማዳከም ከዚያም በማጥቃት ለመደምሰስ በሚለው መርህ መሰረት። ይህንን ኃይል ለተከታታይ አንድ ወር መከላከል አድርገናል። ለማጥቃት የሚያስችለንን ተገቢ ዝግጅት በመከላከል ውስጥ ሆነን አድርገናል። ሰሞኑን የማጥቃት እርምጃ ወስደናል " ብለዋል።

በተወሰደው የማጥቃት እርምጃ ሰሜን ሸዋ የነበረውን የጠላት ኃይል አባረናል ፤ በጋሸና፣ በደቡብ ወሎ፣ በወረ ኢሉ እንዲሁም በምሥራቅ ከጭፍራ አልፈን በዋናው መስመር በባቲ በኩል የነበረውም እንደዚሁ አባረናል ሲሉ ተናግረዋል።

ዛሬ አርብ ባቲም፣ ደሴም ኮምቦልቻም አንድ ላይ ይያዛሉ የሚል ግምት እንዳለ የተናገሩት ሌ/ጄነራሉ አሳውቀዋል።

እየታየ ያለው ውጤት ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ወደ ጦር ግንባር ከመሄዳቸውም ጋር እንደሚያያዝ እና የጠ/ሚኒስትሩ ወደዚያ መሄድ የሠራዊቱን የመስራት አቅም በከፍተኛ ደረጃ እንደጨመረው ጠቁመዋል።

በሌላ በኩል ከትላንት በስቲያ #ህወሓት በአማራ ክልል ተይዘው ከነበሩ ቦታዎች በታክቲካዊ ውሳኔ ሠራዊቱ ለቆ መውጣቱን ስለገለፀበት መግለጫ ተጠይቀው ምላሽ ሰጥተዋል።

ሌ/ጄነራል ባጫ ደበሌ፥ "ምን እንዲሉ ነው የሚጠበቀው ? በአቅማቸው በጉልበታቸው አይደለም እዚህ የደረሱት። በላኳቸው ሰዎች ጉልበትና አቅም ነው እዚህ የደረሱት። ስለዚህ ጌቶቻቸው ለማስደሰት ምን ይበሉ ? " ብለዋል።

አክለውም ፥ " እነሱ እኮ አዲስ አበባ ለመግባት በቀናት ሳይሆን ሰዓታት ነበር ሲቆጥሩ የነበሩት። አንዳንድ የመገናኛ ብዙኃን እኮ አዲስ አበባ ተከባለች፣ ሊገቡ ነው የሚል ዘገባ ሲያስተላልፉ ነው የነበሩት። እነዚህ ሰዎች ተሸነፍን ሊሉ አይችሉም " ሲሉ መልሰዋል።

ሌ/ጄነራል ባጫ ፥ ስለድርድር ሲነሳ "መንግስት የለም ጦርነቱ አልቋል፣ ከማን ጋር ነው የምንደራደረው" ብለዋል ሲሉ ያስታወሱ ሲሆን አሁን እነሱ ባልጠበቁት መንገድ የማጥቃት ጎርፍ ሲወስዳቸው ሊሉ የሚችሉት ይህንን ብቻ ነው ብለዋል።

" ለምን እንደድሮው ጻድቃን የሚባለው ወይም የእነሱ ሰዎች ወጥተው መግለጫ አይሰጡም? " ሱሉ የጠየቁት ሌ/ጄነራል ባጫ ፥ " ስለመኖራቸውም እጠራጠራለሁ፤ ሁለተኛ ደግሞ ያንን ለማድረግ ሐፍረት ይዟቸዋል። ሐፍረት የያዛቸው ስለጌቶቻቸው ነው። በዚህ ጉዳይ ትልልቆቹ ምዕራባዊያን ናቸው የሚያፍሩበት። ሊሉ የሚችሉት አልተሸነፍንም ለቀቅን ነው። መልሰን እናጠቃለን የሚል ቃል ለመግባት የተደረገ ነው " ብለዋል።

ሌ/ጄነራል ባጫ ፥ " በሳተላይት ይከታተሉናል ሲሉ ነበር። ስለዚህ ከየት ቦታ እንደወጡ በደንብ ያያሉ። ስለዚህ ተመትተው እንደወጡ እነሱ ቢክዱም ጌቶታቸው ያውቃሉ " ያሉ ሲሆን " ከአማራ ክልል ለቀን ወጣን ካሉ ከአፋር ክልልስ ይህንን ሁሉ መሬት እንዴት አድርገው ለቀቁ ? ጭፍራ፣ ቡርቃ፣ ጪፍቱ አፋር ናቸው። ይሄንን ሁሉ መሬት እንዴት አድርገው ነው የለቀቁት። አመኑም አላመኑም የሆነው ይሄ ነው " ብለዋል።

ሌ/ጄነራል ባጫ ደበሌ ፤ በቀጣይ የኢትዮጵያ ጦር ወደ ትግራይ ክልል መዲና #መቐለ የማምራት እቅድ ይኖረው እንደሆነ ተጠይቀው ፥ " ይህ ወታደራዊ ጉዳይ ነው። እኛ እዚህ ጋር እንቆማለን አንልም። ወታደራዊ ሁኔታው ነው የሚወስነው። ጦርነት በእርግጠኝነት የሚነገር ነገር አይደለም። የማይገመቱ ነገሮች (አንሰርቴይኒቲ) የሞላበት ነው። ስለዚህ በቀጣይ የሚፈጠረው ነገር ነው የሚወስነው። ነገር ግን እኛ አንቆምም " ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።

ጦሩ ህወሓት የያዛቸውን ቦታዎች ደረጃ በደረጃ እያስለቀቀ እና እየደመሰስ እንደሚቀጥል የተናገሩት ሌ/ጄነራል ባጫ ደበሌ ፤ " መቐለ ነው የምንቆመው የት ነው የምንቆመው ለሚለው፤ የምንቆም አይደለንም። አሁን ግን እቅዳችን እዚህ ድረስ ነው የሚል ነገር የለንም " ብለዋል።

የኢትዮጵያ ጦር ህወሓት የገባበት ገብቶ እስከሚያጠፋው ድረስ ይቀጥላል ሲሉ ተናግረዋል።

@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ሰኔ 1 ቀን 1997 ዓ/ም !

" ኢህአዴግ " ስልጣን ከያዘ በኃላ ለ3ተኛ ጊዜ የተካሄደውን #የ1997ቱ ሀገር አቀፋዊ ምርጫ ተከትሎ በተፈጠረው ቀውስ ሳቢያ ሰኔ 1/1997 በመንግስት የተገደሉ ዜጎች ዛሬ 17ኛ ዓመት መታሰቢያቸው ነው።

በወቅቱ "ኢህአዴግ" ይህን መሰሉ አንባገነናዊ ተገባር የፈፀመው ስልጣኑን ለማስጠበቅ ፣ ስልጣኑን የሚያስጠብቀውም በመሳሪያ ኃይል እንጂ በህዝብ ድምፅ እንዳልሆነ የተቀናቃኝ ፖለቲካ ኃይሎች በተለያየ ጊዚያት ተናግረዋል።

ሰኔ 1 ቀን 1997 በግፍ በመንግስት የፀጥታ ኃይሎች የተገደሉ ዜጎች ለነፃነት፣ ለዴሞክራሲ፣ ለፍትህ፣ ለሀገራዊ አንድነት ዋጋ የከፈሉ እንደሆኑ ይነገርላቸዋል፤ በየዓመቱም በዚህ ቀን ይታሰባሉ።

ፖለቲከኞች ፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾ ይህን የሰኔ 1 ቀን 1997 ዓ.ም ክስተት ለሁሉም ትምህርት የሚሰጥ እና መቼም ቢሆን ሊደገም የማገባው ብዙ ትምህርትም ሰጥቶ ያለፈ እንደሆነ ይናግራሉ።

በወቅቱ (ሰኔ 1 ቀን 1997 ዓ.ም) በግፍ የተገደሉ ፣ የቆሰሉ፣ ለእስርና እንግልት የተዳረጉ ዜጎች ኢትዮጵያን ያስተዳደር በነበረው "ኢህአዴግ" በሚባለው ፓርቲ ወቅት ሲሆን ፓርቲው ከ2 ዓመት በፊት በኢትዮጵያ ምድር ህልውና እንዳይኖረው ተደርጎ፣ ከስሟል።

በውስጡ የነበሩ ድርጅቶችም ከአንዱ (#ህወሓት) በቀር አንድ ላይ ተዋህደው ውህድ ፓርቲ ፈጥረው ኢትዮጵያን እያስተዳደሩ ነው።

Video Credit : Biniyam Hirut

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ETHIOPIA የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት በላከልን ባለ 7 ነጥብ የቋም መግለጫ በሰሜን ኢትዮጵያ ዳግም የተቀሰቀሰው ጦርነት ቆሞ ሰላማዊ ድርድር እንዲቀጥል ጠይቋል። ምክር ቤቱ በሶስተኛ ወገን አማካኝነት ግጭቱን በድርድር ለመፍታት ሲደረግ የነበረውን ቅድመ ዝግጅት በቅርበት ሲከታተል እንደነበረ የገለፀ ሲሆን የድርድር ሂደቱ ተቋርጦ ግጭት መቀስቀሱ እጅጉን እንዳሳሰበው አመልክቷል።…
#Ethiopia

" ጥቃቱን የጀመሩት የህወሓት ኃይሎች ናቸው " - የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት

ዳግም ያገረሸው ግጭት አሁንም ቀጥሎ በተለያዩ የሰሜን ኢትዮጵያ ክፍሎች ግጭቶች ስለመኖራቸው የሚገልፁ ሪፖርቶች አሉ።

ይህ ግጭት ዳግም እንዲያገረሽ ያደረገው ህወሓት በኢትዮጵያ ጦር ላይ ጥቃት በመክፈቱና ሰላም አሻፈረኝ በማለቱ እነደሆነ የኢፌዴሪ መንግስት መግለፁ ይታወሳል ፤ ህወሓት ግን ይህ ከመገለፁ ቀደም ብሎ ፌዴራል መንግስት ጥቃት እንደፈፀመበት እና የተኩስ አቁሙን እንደጣሰ በመግለፅ ክስ አቅርቦ ነበር።

ጥቃቱን መጀመሪያ ማን ፈፀመ ? በሚለው ላይ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ም/ቤት ዳግም ላገረሸው ጦርነት ምክንያት የሆነውን ጥቃት የከፈተው ህወሓት / TPLF እንደሆነ ያለውን አቋም አሳውቋል።

ለዚህም አሳማኝ ነው ያለውን ምክንያት አቅርቧል።

የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሰቢ ዶ/ር መብራቱ አለሙ ለቪኦኤ ሬድዮ የሰጡት ቃል ፦

" እሱ / #ህወሓት ባይጀምር እንዴት እስከ ቆቦ ድረስ ይወሩታል፤ እንዴት እስከ ወልዲያ ድረስ ይመጣሉ። በጋራ ምክር ቤቱ በኩል ብዙም እምነት ያለው ነገር አይደለም (ህወሓት ጦርነት ተከፈተብኝ የሚልው ክስ) ምክንያቱም መንግስት የሰላም አማራጭ አቅርቧል። መንግስት ብዙ ፈተናዎች አሉበት ፣ የሀገር ውስጥ ብዙ ችግሮች አሉ ፤ ከኑሮ ውድነቱ ጋር ተያይዞ፣ ከሸኔ እንቅስቃሴ ጋር በተለያዩ ቦታዎች ካሉ ክፍተቶች ጋር ተያይዞ ወደ ጦርነት ሊያስገባ የሚችለው ምንም ፍላጎት የለውም መንግስት። ስለዚህ ህወሓት በራሱ ጊዜ የቀሰቀሰው ነው እኛ እንደ ጋራ ምክር ቤት እይታችን። "

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ህወሓት ከሽብርተኛ ድርጅትነት #ተሰረዘ። የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ከሽብርተኛ ድርጅት እንዲሠረዝ ውሳኔ አሳለፈ፡፡ ምክር ቤቱ ዛሬ ባሄደው ልዩ ስብሰባ ህወሓትን ከሽብርተኛ መዝገብ ለማንሳት በቀረበለት የውሳኔ ሀሳብ ላይ ከተወያየ በኋላ በአብላጫ ድምፅ ውሳኔውን አፅድቋል። #ኤፍቢሲ @tikvahethiopia
#Tigray

" በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ተቋቁሞ ወደ ስራ እየገባ ነው " - ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል

ዛሬ የህወሓት ሊቀመንበር የሆኑት ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል በትግራይ ክልል ለሚገኙ መገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተው ነበር።

በዚህ መግለጫቸው በፕሪቶሪያው ስምምነት መሰረት በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ተቋቁሞ ወደ ስራ እየገባ መሆኑን አሳውቀዋል።

ዶ/ር ደብረፅዮን ፤ የፌዴራል መንግስት ህወሓትን ከሽብርተኝነት ፍረጃ መሰረዙ በህወሓት ስራ አስፈፃሚ አባል አቶ ጌታቸው ረዳ ፕሬዜዳንትነት የሚመራ ጊዜያዊ አስተዳደር ወደ ትግበራ ለመግባት ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ስለመግለፃቸው ከድምፂ ወያነ ቴሌቪዥን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

ዶ/ር ደብረፅዮን ህወሓት ከሽብርተኝነት መዝገብ ስለመሰረዙ ምን አሉ ?

" በዛሬው ዕለት ህወሓት ከሽብር መዝገብ ተሰርዟል። ስለሆነም ጊዜያዊ አስተዳደራችን ስራው የሚጀምርበት ሁኔታ ተሟልቷል።

#በጀት የማዘጋጀትም ይሁን ሌሎች #ከእስረኞች ጋር የተያያዙ ጉዳዮች የወንጀል ክሶችን በማንሳት እና ሌሎች ጉዳዮችን በተመለከተ በሁለቱም ወገን በኩል ግኝኑነት ተጀምሯል።

በመሆኑም በበኩላችን በጓድ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ጊዜያዊ አስተዳደራችን ስራዎቹ እንዲሳኩ ለማድረግ ሁሉንም አቅማችንን በማቀናጀት ከፍተኛ ርብርብ እናደርጋለን።

የትግራይ ህዝብም በሁሉም አቅሙ የጊዜያዊ አስተዳደራችን ደግፎ እንዲሰማራ ጥሪ እናቀርባለን። "

ዶ/ር ደብረፅዮን ስለ ጊዜያዊ አስተዳደሩ ምን አሉ ?

" የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደርን ለማፋጠን አሸባሪነት የሚለው ሳይነሳ ቀድመን ነው እየሰራን የመጣነው። ጊዜያዊ መንግስቱን ለማቋቋም በርካታ ስራዎች እየተከናወኑ መምጣታቸውን ሁሉም ሲከታተለው የነበረ ጉዳይ ነው።

ኮሚቴ ከማቋቋም ጀምሮ ሁሉም ጊዜያዊ አስተዳደሩን በተመለከተ አጀንዳው አድርጎ እንዲሰራ በውስጥም በውጭም መድረኮችን በማዘጋጀት ተሰርቷል።

ኮንፈረንስ በማዘጋጀት እና ከኮንፈረስን በኃላ ምርጫዎችን በማካሄድ ሊያካትታቸው የሚገባ ፈፃሚ አካላት እንዲመረጡ ተደርጓል።

በጊዜያዊ አስተዳደሩ #ህወሓት እና #ባይቶና ከፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የትግራይ ሰራዊት ፣ የትግራይ ምሁራን ተሳታፊ ሆነዋል። በጊዜያዊ አስተዳደሩ የሚሳተፉ አካላት ተሟልተን ለማዕከላዊ መንግስቱ አሳውቀናል። "

ዶ/ር ደብረፅዮን #ህወሓትን በተመለከተ ምን አሉ ?

" ድርጅታችን ህወሓት የትግራይ ግዛታዊ አንድነትን ለማረጋገጥ ሰላም የሰፈነባትና ብሔራዊ ክብሯ የተጠበቀች ትግራይን ለመገንባት ሁሉንም አቅሙን በማቀናጀት የቅድሚያ ቅድሚያ ሰጥቶ እንደሚታገልበት ማረጋገጥ እፈልጋለሁ። ዘላለማዊ ክብር ለጀግኖች ሰማዕታት!! "

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
አንድ ዓመት ስለደፈነው የፕሪቶሪያው ሰላም ስምምነት የኢትዮጵያ መንግሥት ፣ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፣ ህወሓት እና ሀገራት ምን አሉ ?

የኢትዮጵያ መንግሥት

የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ፤ የፕሪቶሪያው ግጭት የማስቆም ስምምነት ዋና ዉጤት " የጦር መሣሪያ ላንቃ መዘጋቱ " እንደሆነ አሳውቋል።

ሚኒስቴር ከግጭት ማቆሙ ስምምነት በኋላ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ መድረኮች የምትጠቀስበት ሁኔታ ካለፈው ዓመት የተለየ ሆኗል ብሏል።

ስምምነቱ ኢትዮጵያ በብዙ መንገድ ከተለያዩ ሀገሮች ጋር ያላትን ግንኙነት መለወጡን የግለፀው ሚኒስቴር መ/ቤቱ ኢትዮጵያ ከአሜሪካ፣ ከአየርላንድ እንዲሁም ከአውሮጳ ሕብረት/EU ጋር ያላትን ግንኙነት እንዲሻሻል ማድረጉን እንደ ማሳያ ገልጿል።

ስምምነቱ ለኢትዮጵያ ምን አስገኘ ለሚለው ጥያቄም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር " ሰላም አስገኝቷል " ሲሉ ምላሽ ሰጥቷል።

ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ፤ ምንም እንኳን በተደረሰው ስምምነት ግጭት በመቆሙ ሻክረው የነበሩ ግንኙነቶች አሁን መልካቸውን ቢቀይሩም የምልሶ ግንባታ እና የጦርነቱ ሰለባዎችን መልሶ በማቋቋም ረገድ እጥረት መኖሩን አልሸሸገም ሲል ዶቼ ቨለ ዘግቧል።

የትግራይ ክልላዊ መንግሥት ጊዜያዊ አስተዳደር

በአሁን ሰዓት ትግራይ ክልልን እያስተዳደረ የሚገኘው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር እና የስምምነቱ ፈራሚ ህወሓት በየፊናቸው የሰላም ስምምነቱን አንደኛ አመት አስመልክተው መግለጫ አውጥተዋል።

ጊዚያዊው አስተዳደሩ በመግላጫው ላይ የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ህዝቡን ለማጥፋት ሲካሄድ የነበረን ዘመቻ እንዲሁም እንደ ብሄር ትግራዋይ እንዲጠፋ የህዝቡ ባህል፣ ቋንቋና ታሪክ ከሰዎች ህሊና ሳይቀር እንዲሰረዝ የተጎነጎነ ሴራ እንዲገታ አድርጓል ብሏል።

ስምምነቱ ሁሉም ፍላጎቶች እና ወደ ጦርነት ያስገቡ ጠንቆች በተቻለ መጠን ሰላማዊና ሰላማዊ በሆነ መንገድ ብቻ ሊሳካ ይችላል የሚል በር መክፈቱን አመልክቷል።

ስምምነቱ አንድ አመት ቢሞላውም እስከ አሁን ድረስ ነፃ ያልወጣ ህዝብ ነፃ የማውጣት ፣ የተፈናቀለ ወደ ቄየው የመመለስ ፣ ህገ-መንግስታዊና ሉአላዊ የትግራይ ግዛት የማረጋገጥ ጉዳይ ፈፅሞ አልተነካም ፤ አሁንም ህዝቡ መከራ ውስጥ እየኖረ ነው ሲል ጊዜያዊ አስተዳደሩ አመልክቷል።

ጊዜያዊ አስተዳደሩ የፕሪቶሪያው የሰላም ውል በዓለም ማህበረሰብ ፊት የተፈፀመ ስምምነት እንደመሆኑ መጠን ፣ የዓለም ማህበረሰብ በአፈፃፀሙ ያሉ እንቅፋቶች በማስወገድና የትግራይ ህዝብ ኑሮ ወደ ነበረበት የመመለስ ህጋዊና ሞራላዊ ግዴታውን እንዲፈፅም ሲል ጥሪ አቅርቧል።

ህወሓት

ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ ( #ህወሓት ) በፊናው ባወጣው መግለጫ ስምምነቱ የዘላቂና አስተማማኝ ሰላም መሰረት መሆኑን ገልጿል።

ለስምምነቱ ተፈፃሚነት አባላቱና ደጋፊዎቹ በማሳተፍ በቁርጠኝነት እየታገለ መቆየቱንና ትግሉ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አመልክቷል።

" የስምምነቱ ፈራሚ የሆነው የኢትዮጵያ መንግስት በውሉ ላይ የተቀመጡ ወሳኝ መሰረታዊ አበይት ጉዳዮች በአግባቡ አልፈፀመም " ያለው ህወሓት " ይህንንም የዓለም ማህበረሰብ የሚያውቀው ሃቅ ነው " ሲል ገልጿል።

" በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት እስከ አሁነ የተገኙት ድሎች በማክበር ፤ የተቀሩት እንዲፈፀሙ የፌደራል መንግስት በውሉ መሰረት ሃላፊነቱ መፈፀም ይገባዋል ፤ ውሉ እንዲፈረም ሚና የነበራቸው ሁሉም አካላት ኢጋድ ፣ የአፍሪካ ህብረት ፣ የአሜሪካ መንግስት ፣ የአውሮፓ ህብረት ፣  ተሰሚነት ያላቸው የሰብአዊ መብት ተማጓቾችና የሚድያ ተቋማት እንዲሁም የዓለም ማህበረሰብ ሞራላዊና  ፓለቲካዊ ሃላፊነታቸው መወጣት ይገባቸዋል " ሲል ህወሓት በመግለጫው አስገንዝበዋል።

ሀገራት ምን አሉ ?

መቀመጫቸው አዲስ አበባ የሆኑ #የአስር_ሀገራት ኤምባሲዎች በኢትዮጵያ ለ2 ዓመታት ተካሂዶ በነበረው ግጭት ተሳትፈው የነበሩ ሁሉም ወገኖች የሰላም ስምምነቱን ሙሉ ለሙሉ ተግባራዊ እንዲያደርጉ እና አሉ ያሏቸውም ተግዳሮቶች በንግግር መፍትሄ እንዲያገኙ ጥሪ አድርግዋል።
- አውስትራሊያ፣
- ካናዳ፣
- ዴንማርክ፣
- ፊንላንድ፣
- ጃፓን፣
- ኔዘርላንድስ፣
- ኒውዚላንድ፣
- ኖርዌይ፣
- ስውዲን፣
- ዩናይትድ ኪንግደም/ዩኬ በጋራ ባወጡት መግለጫ፣ የፕሪቶሪያው ስምምነት ከተካሄደ ወዲህ በግጭቱ የተሳተፉ ሁሉም ወገኖች ሰላምን ለማምጣት ያደርጉትን ጥረት አድንቀዋል።

ስምምነቱ የተፈረመበት #አንደኛ_ዓመት ፣ የተመዘገቡ መልካም ውጤቶች የሚደነቁብት እንዲሁም ደግሞ ተግዳሮቶች እንዳሉ እና የተሟላና አስተማማኝ ሰላምን ለማረጋገጥ ጥረቶች በእጥፍ መቀጠል እንዳለባቸው ግንዛቤ የሚወሠድበት መሆኑን ኤምባሲዎቹ አመልክተዋል።

ጥቅምት 24/2013 ዓ.ም የጀመረው ደም አፋሳሹ ፣ እጅግ አውዳሚና አስከፊው መነሻውን ትግራይ አድርጎ ወደ አጎራባችን ክልሎች የተዛመተው ጦርነት ከ2 አመት በኃላ ህወሓትና የፌደራል መንግስት በደቡብ አፍሪካዋ የፕሪቶሪያ ከተማ ጥቅምት 24/2015 ዓ.ም በፈረሙት ግጭት ማቆም ጨምሮ በርካታ ጉዳዮች ባካተተ የሰላም ስምምነት ውል ጦርነቱ መቋጫ ማግኘቱ ይታወሳል ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ዘግቧል።
                  
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#TPLF #ህወሓት

ክልላዊ ፣ አገራዊ ፣ አህጉራዊ እና ዓለምአቀፋዊ ጉዳዮች ባካተቱ 6 ነጥቦች ላለፉት ከ41 ቀናት በላይ ስብሰባ መቀመጡን የገለፀው ህወሓት ዛሬ ባለ 6 ገፅ መግለጫ አውጥቷል።

ጥር 22/2016 ዓ.ም ባወጣው መገለጫ እንዳስታወቀው ረጅም ጊዚያት ወስዶ ያካሄደው የድርጅቱ የፓሊትና የማእከላይ ኮሚቴ  የግምገማ ፣ የሂስና የግለሂስ መድረክ ወደ ቀጣዩ ጉባኤ የሚያሸጋግሩ ወሳኔዎች የተወሰኑበት ነው ብሏል።

ህወሓት በመግለጫው  ፦
- ለትግራይ ህዝብ
- ለድርጅቱ አመራርና አባላት
- ለኢትዮጵያ ህዝቦችና ብሄር ብሄረሰቦች
- ለኤርትራ ህዝብ
- ለዓለም ማህበረሰብና ለትግሉ ደጋፊዎች እንዲሁም ሌሎችም አካላት መልእክት አስተላልፈዋል። 

ህወሓት በተለይ ለኢትዮጵያ ህዝቦችና ብሄር ብሄረሰቦች ባስተላለፈው መልእክት ፤ " ህወሓት ለትግራይ ፣ ለኢትዮጵያ ህዝቦችና ብሄር ብሄረሰቦች የሰላም ስትራቴጂክ አማራጭ ከመሆን በዘለለ በማንም ህዝብ ላይ ጥላቻ አንደሌለው አረጋግጣለሁ " ብሏል።

" ከኤርትራ ህዝብ የጋራ ጥቅም መሰረት ያደረግ የትግል አጋርነት ነበረን አጋርነቱና የጋራ ጥቅም መሰረት ያደረገ መደጋገፉ ይቀጥላል " ያለው ህወሓት " የኤርትራ ህዝብ የኤርትራ ሰራዊት በሃይል ከያዛቸው የትግራይ ግዛቶች ለቆ እንዲወጣ ጫና እንዲያሳድር የሚያስታውስ ጥሪ አስተላልፈዋል። 

ህወሓት " ለዓለም አቀፍ ማህበረሰብና ከትግላችን ደጋፊዎች " በሚል ባስተላለፈው መልእክት " የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ሙሉ በሙሉ እንዲተገበር ፣ ስምምነቱ መሰረት ያደረገ ውይይት እንዲካሄድ ፣ የትግራይ የግዛት አንድነት እንዲረጋገጥ ፣ ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው እንዲመለሱ ፣ የትግራይ መልሶ ግንባታ እንዲፋጠን ፣ ሰብአዊ ወንጀል የፈፀሙ በዓለም አቀፍ ህግ እንዲዳኙ እንዲደረግ የበኩላችሁ እንድትወጡ የህወሓት ማእከላይ ኮሚቴ ጥሪውን ያቀርባል " ማለቱ የመቐለ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ዘግቧል።    
                                       
@tikvahethiopia            
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray #TPLF የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የዛሬውን የሚኒስትሮች ምክር ቤት ውሳኔን አወደሱ። አቶ ጌታቸው የሚኒስትሮች ምክር ቤት ውሳኔ ሰላምን ለማጠናከር በትክክለኛው አቅጣጫ አንድ እርምጃ የተራመደ ነው ብለውታል። ዛሬ የሚኒስትሮች ም/ቤት ያሳለፈው " የኢትዮጵያ የምርጫ ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና የምርጫ ሥነ-ምግባር አዋጅን ለማሻሻል የቀረበ ረቂቅ…
#Update

ፓርላማው ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ ( #ህወሓት ) ዳግም ህጋዊ እውቅና ሊያገኝ የሚችልበትን / በድጋሚ እንዲመዘገብ የሚፈቅድለትን የአዋጅ ማሻሻያ አጽድቋል።

" የኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና የምርጫ ስነምግባር አዋጅን " የሚያሻሽለው የህግ ረቂቅ የጸደቀው በ2 የፓርላማ አባላት ተቃውሞ፣ በአንድ ድምጸ ተዐቅቦ፣ በአብላጫ ድምጽ ነው።

" በአመጽ እና በህገ-ወጥ መንገድ ሲንቀሳቀስ የነበሩ " የፖለቲካ ፓርቲዎችን " በልዩ ሁኔታ " እንዲመዘገቡ የሚያስችለው የህግ ማሻሻያ፤ የፖለቲካ ቡድኖቹ ሊያሟሉ የሚገባቸው መስፈርቶችን እና የምርጫ ቦርድን ኃላፊነት የዘርዘረ ነው።

የጸደቀው የአዋጅ ማሻሻያ ፥ " ኃይልን መሰረት ያደረገ የአመጻ ተግባር ላይ ተሰማርቷል " በሚል " ህጋዊ ሰውነቱ እንዲሰረዝ " የተደረገው ህወሓት #በድጋሚ እንዲመዘገብ የሚያስችሉ አንቀጾችን በውስጡ ይዟል።

" አንድ የፖለቲካ ቡድን ኃይልን መሰረት ያደረገ የአመጽ ተግባር ውስጥ የተሳተፈ እንደሆነ እና ይህንን ተግባር ማቆሙን እና ሕገ መንግስታዊ ዲሞክራሲያዊ ስርዓትን አክብሮ ለመንቀሳቀስ መስማማቱ በሚመለከተው የመንግስት አካል ከተረጋገጠ፣ የፖለቲካ ቡድኑ በልዩ ሁኔታ እንደ ፖለቲካ ፓርቲ ሊመዘገብ ይችላል " ሲል አዋጁ ደንግጓል።

#EthiopiaInsider
#TPLF

@tikvahethiopia