TIKVAH-ETHIOPIA
1.47M subscribers
56.1K photos
1.4K videos
202 files
3.79K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Gambella , #Akobo📍

" የኔትወርክና የመንገድ መሠረተ ልማት ባለመሟላቱ የሚፈጠሩ የፀጥታ ችግሮችን በፍጥነት ለመፍታት አዳጋች ሆኗል " - አቶ ኮንግ ጋትዮቴ

በጋምቤላ ክልል በአኮቦ ወረዳ ከደቡብ ሱዳን በሚነሱ የሙርሌ ታጣቂዎች ድንበር አቋርጠው ህብረተሰቡ ላይ ጉዳት እንዳያደርሱ ከፀጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት እየሰራ መሆኑን የወረዳዉ አስተዳደር አስታውቋል።

የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ኮንግ ጋትዮቴ እንዳሉት ከደቡብ ሱዳን የሚነሱ የሙሩሌ ጎሳ ታጣቂዎች በተለያዩ ጊዜያት ድንበር አቋርጠዉ በመግባት ጥቃት ሲፈፅሙ ቆይተዋል ብለዋል።

ታጣቂ ቡድኑ በሰዉ ህይወት ላይ ከሚያደርሰው ጉዳት ባለፈ ህፃናትንና የቁም እንስሳትን ሲዘርፉ እንደነበር ጠቅሰዉ በአሁኑ ወቅት ከክልሉ የጠጥታ አካላት ጋር በመቀኛጀትና የስጋት ቀጠናዎችን በመለየት መሰል ጥቃት እንዳይፈፀም እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

በወረዳዉ የኔትወርክና የመንገድ መሠረተ ልማት ባለመሟላቱ የሚፈጠሩ የፀጥታ ችግሮችን በፍጥነት ለመፍታት አዳጋች እንደሆነባቸዉ ገልፀዉ መንግስት እነዚህ መሠረተ ልማቶች ላይ ትኩረት ሊሰጥ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

በሌላ በኩል የክልሉ መንግስት በጥቃቱ ለተጎዱ እና ለተፈናቀሉ ከ2,500 በላይ ወገኖች በ2 ሚሊዮን ብር 600 ኩንታል በቆሎ በመግዛት ድጋፍ ማድረግ መቻሉን የክልሉ አደጋ መከላከል እና ምግብ ዋስትና ኤጀንሲ መግለፁን ከጋምቤላ ፕሬስ ሴክሬተሪያት ያገኘነው መረጃ ያሳያል

@tikvahethiopia
#Gambella

ትናንት ምሽት ላይ በጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ በተፈጠረ ግጭት የአንድ ሰው ህይወት ሲያልፍ አንድ ሰው ላይ የመቁሰል አደጋ መደረሱ ተገልጸ።

የክልሉ ፖሊስ ፤ በዩኒቨርሲቲው ውስጥ በክልል ፖሊስ እና በፌደራል ፖሊስ መካከል በተፈጠረ ግጭት የአንድ ሰው ህይወት ሲያልፍ በአንድ ሰው ላይ የመቁሰል አደጋ ደርሷል ሲል አሳውቋል።

በአሁኑ ሰዓት የአካባቢው ሠላም ወደነበረበት ተመልሷል፤ ግጭት ፈጥረዋልም የተባሉ ግለሰቦች በህግ ቁጥጥር ስር በማዋል ተገቢው ማጣራት እየተካሄደ ነው ሲል የክልሉ ፖሊስ ገልጿል።

ፖሊስ የግጭቱን መንስኤ እያጣራ እንደሆነም አሳውቋል።

ከተማዋ ሰላም መሆኗን እና ህብረተሰቡም ወደ ተለመደው የሰላም ሁኔታ መመለሱንም ገልጿል።

የጋምቤላ ክልል ፖሊስ ነዋሪዎች ረብሻና ሁከት ከሚፈጥሩ አንዳንድ ማህበራዊ የሚዲያ ገፆችና ያልተረጋገጠ መረጃ ከሚሰጡ ዘገባዎች እራሳቸውን እንዲጠብቁ አስገንዝቧል።

@tikvahethiopia
#Gambella

በጋምቤላ ክልል መዠንገር ዞን ፤ ሜጢ ከተማ ከፍርድ ቤት ቀጠሮ ወደ ማረሚያ ቤት 22 እስረኞችን ሲመልስ የነበረ የፖሊስ ተሽከርካሪ ተገልብጦ ከባድ አደጋ መድረሱ ተሰምቷል።

በአደጋው የአንድ እስረኛ ህይወት አልፏል።

አጠቃላይ በተሽከርካሪው 22 እስረኞችና 4 የፖሊስ አባላት (26 ሰዎች) የአደጋው ሰለባ ሲሆኑ በአደጋው የሞት፣ ከባድ ፣እና ቀላል ጉዳት ተመዝግቧል።

የመዠንገር ዞን ፀጥታ መምሪያ ለሸገር ኤፍ ኤም በሰጠው ቃል ፤ መኪናው ከፊት ለፊት ባጃጅ ገብቶበት እሱን አድናለው ሲል መገልበጡን ገልጾ ጉዳት የደረሰባቸው እስረኞች እና የፖሊስ አባላት ቴፒ ሆስፒታል ተወስደዋል።

ከእስረኞች መካከል ያመለጠ እንደሌለ ያሳወቀው ፀጥታ መምሪያው አንድ ታራሚ ህይወቱ እንዳለፈ ሌሎቹ ግን በሆስፒታል ህክምና ላይ እንደሚገኙ ገልጿል።

22ቱ ግለሰቦች በተለያየ ጥፋት ተጠርጥረው ማረሚያ የወረዱ መሆናቸውን የገለፀው የፀጥታ መምሪያው ከአዲስ አበባ የሚላክ " የስንዴ እርዳታ " ወደ ህዝብ ሳይደርስ መንገድ ላይ ሲሸጡ እና ለግል ጥቅም ሲያውሉ የነበሩ ሰዎች መኖራቸውን መጠቆሙን ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ዘግቧል።

@tikvahethiopia
#Gambella

ትናንት ከቀኑ 10 ሰዓት ገደማ በጋምቤላ ወረዳ ጎሊ በሚባል አካባቢ በተፈፀመ ጥቃት በእርሻ ሥራ ላይ የነበሩ 2 ሰዎች (አንድ ወንድ እና አንድ ሴት) ሲገደሉ 3 ሠዎች (2 ወንድ እና አንስ ሴት) ታፍነው መወሰዳቸውን የጋምቤላ ክልል አሳውቋል።

ክልሉ ለጥቃቱ የጋምቤላ ነፃነት ግንባር (ጋነግ) ተብሎ የሚጠራውን ቡድን እና በህ/ተ/ም/ቤት በአሸባሪነት የተፈረጀውን " ሸኔ " / እራሱን የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት እያለ የሚጠራውን የታጠቀ ቡድን ተጠያቂ አድርጓል።

የክልሉ መንግስት የፀጥታ ሀይሎች ጥቃት አድራሾቹ ላይ እርምጃ ለመውሰድ ክትትል እያደረጉ እንደሚገኝ ገልጾ ህብረተሰቡ ተገቢውን ትብብር እንዲያደርግ ጥሪ ማቅረቡን ከክልሉ ኮሚኒኬሽን የተገኘው መረጃ ያሳያል።

@tikvahethiopia
#Gambella 📍

ትላንት ምሽት በጋምቤላ ከተማ 01 ቀበሌ ኒዉላንድ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አካባቢ ተኩስ ተከፍቶ እንደነበር የክልሉ ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት አሳውቋል።

ፅ/ቤቱ ፤ ተኩስ ከፍቶ የነበረው ራሱን የጋምቤላ ነፃነት ግንባር (ጋነግ) ብሎ የሚጠራው ድርጅት ነው ብሏል።

" ቡድኑ ህዝብ የማሸበር ስራውን አጠናክሮ ቀጥሏል " ያለው ፅ/ቤቱ ትላንት ምሽት 3 ሰዓት ገደማ በ01 ቀበሌ በከፈተው ተኩስ በአንድ የመንግስት ልዩ ሀይል ላይ ጉዳት አድርሷል ሲል አመልክቷል።

መንግስት የፀጥታ ሀይሉን በማደራጀት የከፋ ጉዳት እንዳይደርስ የመከላከል ስራ እያከናወነ መሆኑን የጠቀሰው ፅ/ቤቱ ህብረተሰቡ ከፀጥታ ሀይሉ ጎን በመሆን ተገቢውን መረጃ እንዲሰጥ ጥሪ አቅርቧል።

@tikvahethiopia
#Gambella

ጋምቤላ በተኩስ ልውውጥ እየተናጠች ነው።

በጋምቤላ ክልል ዋና ከተማ " ጋምቤላ " ዛሬ ከማለዳ ጀምሮ ከፍተኛ የተኩስ ልውውጥ እየተደረገ መሆኑን እና ከፊል የከተማው ክፍል ውስጥ ታጣቂዎች እንደሚታዩ ነዋሪዎችን ዋቢ አድርጎ ቢቢሲ ዘግቧል።

ጋምቤላ ውስጥ ታጣቂዎች ዛሬ ሰኔ 07/2014 ዓ.ም. ከንጋት 11 ሰዓት ተኩል ጀምሮ ነው ተኩስ ከፈቱ የተባለው። እስካሁን ጥቃቱን የሰነዘሩት ታጣቂዎች እነማን መሆናቸው የታወቀ ነገር የለም።

የታጣቂዎቹ ጥቃት ኢላማ የርዕሰ መስተዳደሩን ጽ/ ቤት ለመቆጣጠር ያለመ ሳይሆን እንደማይቀር የከተማዋ ነዋሪዎች ገልጸዋል።

ሁለት የከተማዋ ነዋሪዎች እንዳሉት በዚሁ ክስተት ሳቢያ ፦
- የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች፣
- የንግድ ሥራዎች
- መደበኛ እንቅስቃሴዎች የተስተጓጎሉ ሲሆን ነዋሪዎችም በቤታቸው ዘግተው መቀመጣቸውን ተናግረዋል።

በክልሉ ርዕሰ መስተዳድሩ ቢሮ አካባቢም ከፍተኛ የተኩስ ድምጽ ላለፉት አራት ሰዓታት እየተሰሙ እንደሚገኙ አንድ በአቅራቢያው ያሉ ነዋሪ አክለዋል።  

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኡሞድ ኡጁሉ በከተማዋ ስለተከሰተው የተኩስ ልውውጥና አሁን ስላለው ሁኔታ " ምንም የምንሰጠው መረጃ የለም’ " ሲሉ መናገጋቸውን ቢቢሲ ዘግቧል።

በሌላ በኩል የጋምቤላ ቲክቫህ አባላት የላኳቸው መልዕክቶች ፦

📩 " Gambella lay cheger ale mesarya yetateku sewoch bezat eyegebu new tekus betam ale "

📩 " Here Gambella city upto now high fighting really we are worried please inform for concerned body "

📩 " እባካችሁ ጋምቤላ ሰላም አደለም "

በሌላ መረጃ የክልሉ መንግስት ፥ " በጋምቤላ ከተማ ያለውን አንፃራዊ ሰላም ለማደፍረስ እየተንቀሳቀሱ የሚገኙት የፀረ ሰላም ሀይሎችን ለመመከት የከተማው ማህበረሰብ ሳይረበሽ ከፀጥታ ሀይሉ ጎን እንዲሆን ጥሪ እናቀርባለን " ብሏል።

ዛሬ ከጠዋቱ 12:30 ጀምሮ የጠላት ጦር እና የመንግስት የፀጥታ ሀይል የተኩስ ልውውጥ እያደረጉ ናቸው። " ሲል ገልጾ ዝርዝር ዜናው ይገለፃል ብሏል።

ጠላት ሲል የጠራውን ኃይል በስም አልገለፀም።

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
TIKVAH-ETHIOPIA
#Gambella ጋምቤላ በተኩስ ልውውጥ እየተናጠች ነው። በጋምቤላ ክልል ዋና ከተማ " ጋምቤላ " ዛሬ ከማለዳ ጀምሮ ከፍተኛ የተኩስ ልውውጥ እየተደረገ መሆኑን እና ከፊል የከተማው ክፍል ውስጥ ታጣቂዎች እንደሚታዩ ነዋሪዎችን ዋቢ አድርጎ ቢቢሲ ዘግቧል። ጋምቤላ ውስጥ ታጣቂዎች ዛሬ ሰኔ 07/2014 ዓ.ም. ከንጋት 11 ሰዓት ተኩል ጀምሮ ነው ተኩስ ከፈቱ የተባለው። እስካሁን ጥቃቱን የሰነዘሩት ታጣቂዎች…
#Gambella

በጋምቤላ የሰዎች ህይወት ማለፉን አንድ የክልሉ ከፍተኛ ባለሥልጣን ዋቢ አድርጎ ቢቢሲ አስነብቧል።

በጋምቤላ ከተማ ውስጥ የፀጥታ ችግር መፈጠሩን ያረጋገጡት እኚሁ ባለስልጣን በዚህም የሰው ህይወት መጥፋቱንና የተጎዱ መኖራቸውን ተናግረዋል።

እሳቸው ቢያንስ ሁለት የፀጥታ ኃይሎች እንዲሁም ከታጣቂዎቹ የሦስቱ ህይወት ማለፉን ከሆስፒታል ምንጮቻቸው መረዳታቸውን ገልፀዋል።

" ለፌደራል መንግሥት አሳውቀናል። ከአቅራቢያ ወደ ከተማው ኃይል ለማሰማራት እየሞከሩ እንደሆነ ነግረውናል። እዚህ ያለው ኃይላቸው ግን ትንሽ ነው’ " ሲሉ አክለዋል።

በሌላ በኩል ለደኅንነታቸው ሲባል ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁት አንድ የከተማው ነዋሪ ከባሮ ወንዝ ተሻግሮ ያለው የከተማው ክፍል በታጣቂዎች ቁጥጥር ስለሆነ ከባሮ ማዶ ተሻግረው እንደሚገኙ ተናግረዋል።

" ከአራት ቀን በፊትም ተመሳሳይ ሙከራ ተደርጎ ነበር። ከዚህ በፊት በዚህ መጠን የታጣቂዎች እንቅስቃሴ አይተን አናውቅም ነበር " ሲሉ ነዋሪው አክለዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update በጋምቤላ ከተማ የተኩስ ልውውጡ መንግስት አሸባሪ ካለው ሸኔ ወታደሮች (እራሱን የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት እያለ የሚጠራው) እና የጋምቤላ ነፃነት ግንባር ጋር መሆኑን ክልሉ ገልጿል። " በጋምቤላ ከተማ ከጠዋቱ 12:30 ጀምሮ ሲካሄድ የነበረው የተኩስ ልውውጥ ያለማቋረጥ እስከ ረፋዱ 4 ሰዓት ከ20 ሲካሄድ ቆይቶ በአሁኑ ሰዓት ከተማው መጠነኛ መረጋጋት ይታያል " ሲል ክልሉ ገልጿል። ክልሉ…
#Update #Gambella

የጋምቤላ ክልል ፤ ጋምቤላ ከተማን ማረጋጋት መቻሉን አሳወቀ።

ክልሉ ፥ " ተኩስ ከፍተው በነበሩ የሸኔና የጋምቤላ ነፃነት ግንባር ላይ በፀጥታ አካላት በተወሰደ ጠንካራ እርምጃ ከተማዉን ማረጋጋት ተችሏል " ሲል አሳውቋል።

አክሎም በተወሰደዉ እርምጃ በታጣቂ ቡድኑ ላይ ከፍተኛ ሰበአዊና ቁሳዊ ኪሳራ ደርሷል ሲል አመልክቷል።

ክልሉ የከተማው ህብረተሰብ ከቤት ባለመውጣት ለፀጥታ ሀይሉ እያደረገ ላለው ትብብር ምስጋና አቅርቧል።

በከተማው ከጠዋቱ 12:30 ጀምሮ ያለማቋረጥ ለረጅም ሰዓት የተኩስ ልውውጥ ሲደረግ እንደነበር አስታውሶ በአሁኑ ሰዓት ተቆርጠው የቀሩ የቡድኑ አካላትን የማጥራት ስራ እየተከናወነ መሆኑን አስረድቷል።

" ታጣቂ ቡድኑን ሙሉ በሙሉ ለመደምሰስ በመንግስት ፀጥታ አካላት እየተወሰደ ያለዉ የማያዳግም እርምጃም ተጠናክሮ ይቀጥላል " ሲልም የክልሉ አስተዳደር አስታውቋል።

የደረሰው ጉዳት በቀጣይ እንደሚገለጽ ተገልጿል።

በሌላ በኩል ከጋምቤላ መልዕክት የላኩ የቲክቫህ አባላት ዛሬ ከጥዋት ጀምሮ በነበረው የተኩስ ልውውጥ በርካታ ታጣቂዎች መገደላቸው በአይናቸው መመልከታቸውንና በአንዳንድ የከተማው ቦታ የሞቱ ሰዎች አስክሬን ይታይ እንደነበር አስረድተዋል። በመንግስት የፀጥታ ኃይል በኩል የሞት ስለመኖሩም መስማታቸውን ገልፀዋል።

በሲቪል ሰዎች ላይ ስለደረሰ ጉዳት ግን ለጊዜው የሰሙት ነገር እንደሌላቸው አመልክተዋል።

ዛሬ በሆነው ደረጃ በከተማው የተኩስ ልውውጥ ሰምተው እንደማያውቁ የገለፁት የቤተሰብ አባላቶቻችን ታጣቂዎች ከተማ ድረስ እንኪደርሱ ቀደም ብሎ መከላከል ያልተቻለበት ሁኔታ ምርመራ ይፈልጋል ሲሉ አስገንዝበዋል።

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update #Gambella የጋምቤላ ክልል ፤ ጋምቤላ ከተማን ማረጋጋት መቻሉን አሳወቀ። ክልሉ ፥ " ተኩስ ከፍተው በነበሩ የሸኔና የጋምቤላ ነፃነት ግንባር ላይ በፀጥታ አካላት በተወሰደ ጠንካራ እርምጃ ከተማዉን ማረጋጋት ተችሏል " ሲል አሳውቋል። አክሎም በተወሰደዉ እርምጃ በታጣቂ ቡድኑ ላይ ከፍተኛ ሰበአዊና ቁሳዊ ኪሳራ ደርሷል ሲል አመልክቷል። ክልሉ የከተማው ህብረተሰብ ከቤት ባለመውጣት ለፀጥታ…
#Update #Gambella

የጋምቤላ ክልል ፕሬዜዳንት አቶ ኡሞድ ኡጁሉ በጋምቤላ ከተማ ተከስቶ የነበረው የፀጥታ ችግር ሙሉ በሙሉ መቆጣጠር መቻሉን ገለፁ።

ፕሬዝዳንቱ ይህን የገለፁት የከተማውን ወቅታዊ ሁኔታ በተመለከተ መግለጫ በሰጡበት ወቅት ነው።

" በክልሉ የሚገኙ የፀጥታ ሀይሎች ባካሄዱት ቅንጅታዊ ማጥቃት ከተማውን ሙሉ በሙሉ መቆጣጠር ተችሏል " ያሉት አቶ ኡሞድ " በጥቃቱ በጠላት በኩል ከፍተኛ ሰብዓዊና ቁሳዊ ኪሳራ ደርሷል ፤ ከወገን ጦር በኩልም መጠነኛ ጉዳት ደርሷል " ሲሉ ገልፀዋል።

አቶ ኡሞድ ፤ በጋምቤላ ከተማ በሚገኙ የመንግስት ተቋማት ላይ ምንም አይነት ጉዳት አለመድረሱን ገልፀው በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች የርዕሰ መስተዳድሩን ጽህፈት ቤት ተቆጣጥረዋል [ ታጣቂዎቹን ማለታቸው ነው ] በሚል የተናፈሰው ወሬ #ሀሰተኛ መሆኑን የኢትዮጵያ ህዝብ ሊገነዘብ ይገባል ብለዋል።

" ነዋሪዎች በአሁኑ ሰዓት በከተማው በአንዳንድ አካባቢ ተደብቆ የሚገኝ የጠላት ሀይል ካለ በአቅራቢያቸው ለሚገኝ የፀጥታ ሀይል ጥቆማ ይስጡ " ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ህብረተሰቡ አካባቢውን ነቅቶ እንዲጠብቅ በተለይም #ከምሽቱ_2_ሰዓት ጀምሮ በቤቱ በመቀመጥ ለሠላሙ ተባባሪ መሆን ይኖርበታልም ብለዋል።

የጋምቤላ ክልል ፕሬዜዳንት አቶ ኡሞድ ኡጁሉ " በጥቃቱ ህይወታቸውን ላጡና ጉዳት ለደረሰባቸው አካላት በክልሉ መንግስት እና ህዝብ ስም መጽናናትን እመኛለሁ " ማለታቸውን ከክልሉ ፕሬስ ሴክሬተሪያት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update #Gambella የጋምቤላ ክልል ፕሬዜዳንት አቶ ኡሞድ ኡጁሉ በጋምቤላ ከተማ ተከስቶ የነበረው የፀጥታ ችግር ሙሉ በሙሉ መቆጣጠር መቻሉን ገለፁ። ፕሬዝዳንቱ ይህን የገለፁት የከተማውን ወቅታዊ ሁኔታ በተመለከተ መግለጫ በሰጡበት ወቅት ነው። " በክልሉ የሚገኙ የፀጥታ ሀይሎች ባካሄዱት ቅንጅታዊ ማጥቃት ከተማውን ሙሉ በሙሉ መቆጣጠር ተችሏል " ያሉት አቶ ኡሞድ " በጥቃቱ በጠላት በኩል ከፍተኛ…
#Gambella | " ታጣቂዎቹ ከጋምቤላ ከተማ ውጭ ያሉ ቦታዎች ላይ ሊኖሩ ይችላሉ ፤ የት ቦታ ነው ያሉት የሚለውን ለማወቅ ጥናት እያደረግን ነው " - አቶ ኡጌቱ አዲንግ

ትላንት ታጣቂዎች ጋምቤላ ከተማን ለመቆጣጠር ጥቃት ከፍተው እንደነበር ነገር ግን በፀጥታ ኃይሎች በተወሰደው እርምጃ መክሸፉ ይታወቃል።

የክልሉ ፕረስ ሴክሬታሪያት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኡጌቱ አዲንግ ለሪፖርተር በሰጡት ቃል ፤ የክልሉ መንግስት ታጣቂዎቹ በከተማው ጥቃት ለመክፈት ዝግጅት እያደረጉ ስለመሆኑ መረጃ እንደነበረው ተናግረዋል።

ይህን ተከትሎ የክልሉ ፀጥታ ም/ቤት ሰኞ 5 ቀን 2014 ግምገማ ማድረጉንና የክልሉ መንግሥት በመረጃው ላይ ተመሥርቶ ጥቃቱን ለመመከት የተቀናጀ የፀጥታ ኦፕሬሽን ማድረጉን አስታውቀዋል፡፡

" ጥቃት ለመፈጸም እንደተዘጋጁ መረጃ ነበረን፡፡ በዚህ መረጃ ነው ወደ ኦፕሬሽን የተገባው፡፡ ዞሮ ዞሮ [ወደ ከተማው] ገብቷል ግን ቢገባም መመለሻ እንደሌለው ነው የነበረን ውይይት " ብለዋል።

" ጋምቤላ ከተማን በሙሉ ለመቆጣጠር ሙከራ ቢያደርጉም በተደረገው ትግል ከተማው ነፃ ሆኗል " ያሉት ኃላፊው ወደ ከተማዋ ከገቡ በኋላ በደረሰባቸው ጥቃት " በአንዳንድ ቦታዎች ተደብደቀው ወደ ቤቶች የገቡ " ታጣቂዎች በመኖራቸው የፀጥታ ኃይሉ ' ለቀማ ' ላይ ነው ሲሉ ገልፀዋል።

በንፁኃን ላይ ስለ ደረሰ ጉዳት በተመለከተ ፥ " ጦርነት ባለበት ሁሉ ሰው መሞቱ አይቀርም፡፡ ስለዚህ በወታደርም በሲቪሊያን ላይም ችግር ደርሷል፡፡ ቁጥሩን ገና አላጣራንም ስናጣራ እናሳውቃለን " ብለዋል።

ታጣቂዎቹ በክልሉ ከከተማው ውጭ ያሉ ቦታዎች ላይ ሊኖሩ እንደሚችሉ ጠቅሰው " የት ቦታ ነው ያሉት የሚለውን ለማወቅ ጥናት እያደረግን ነው " ብለዋል ለጋዜጣው።

#ሪፖርተር

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ጋምቤላ ክልል ፡ በመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች ከሕግ አግባብ ውጭ የተፈጸሙ የኃይል እርምጃዎች ሰኔ 7 ቀን 2014 ዓ.ም. በጋምቤላ ከተማ፣ ጋምቤላ ክልል ከጠዋት እስከ ምሽት የቀጠለ ግጭት እና የፀጥታ እና የደኅንነት ችግርን ተከትሎ ለአንድ ቀን የከተማዋ የመንግሥት አገልግሎቶች፣ የንግድ እንቅስቃሴዎች እና ሌሎችም አገልግሎቶች ተቋርጠው መዋላቸው ይታወሳል። ጥቃቱ በኦሮሞ ነጻነት ግንባር (በተለምዶ ኦነግ…
#Gambella

በጋምቤላ በዚህ ሳምንት ከተፈፀመው ጥቃት ጋር በተያያዘ ንፁሃን ዜጎች ላይ ከማዋከብ አንስቶ እስከ ግድያ የደረሰ ከዚህም በተጨማሪ የዝርፊያ ድርጊት መፈፀሙ መጠቆሙ ይታወሳል።

ክልሉ ካለው ነባራዊ ሁኔታ ጋር በተያያዘ ንፁሃን ሰለባ እንዳይሆኑ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እያደረገ መሆኑን መግለፁ አይዘነጋም።

በከተማው አንድ ወጣት እጁን ወደ ኃላ ታስሮ የፀጥታ ኃይል ልብስ በለበሱ እና ባለሰቡ አካላት በጥይት ሲደብደብ የሚያሳይ ቪድዮ መሰራጨቱ በርካቶችን አስዝኖም አቆጥቶም ነበር ፤ ይህን ተከትሎ ክልሉ በሰጠው መግለጫ ይህንን ጉዳይ በግልፅ አፍረጥርጦ ባይናገርም ከህግ ውጪ የሆነ ድርጊት የፈፀሙና የስነ- ምግባር ጉድለት ያለባቸው የፀጥታ አካላት እንዳሉ አረጋግጦ ህጋዊ እርምጃ መዉሰድ መጀመሩን አስታውቆ ነበር።

ትላንት ሪፖርተር ጋዜጣ ይዞት በወጣው ዘገባ ደግሞ ክልሉ አንድ ወጣት በጥይት የመደብደቡን ክስተት አረጋግጦ ፤ ከሕግ ውጪ ግድያ በፈጸሙ የፀጥታ ኃይሎች ላይ ዕርምጃ ተወስዷል ብሏል።

የጋምቤላ ክልል ኮሙዩኒኬሸን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኡጉት አዲንግ " የኦነግ ሸኔና የጋምቤላ ነፃ አውጪ ቡድን አባላት ለይቶ ሕጋዊ ዕርምጃ የመውሰዱ ጥረት ፈታኝ ነበር " ያሉ ሲሆን " በዚህ የተነሳ ጥንቃቄ ሳያደርጉ ወይም በእልህና በቁጣ ሰላማዊ ዜጎች ላይ ዕርምጃ የወሰዱ የፀጥታ አስከባሪዎች ነበሩ " ብለዋል።

#አንድ የልዩ ኃይልና #አንድ የመደበኛ ፖሊስን ጨምሮ ሁለት የፀጥታ አስከባሪዎች በሕገወጥ ግድያ ተጠርጥረው ተይዘዋል ሲሉ አሳውቀዋል።

ጥቃት የከፈቱት ታጣቂዎች ሲቭልም የለበሱ ስለነበሩ እንዲሁም አንዳንዶቹ የትጥቅ ልብሳቸው ቀይረው ከህብረተሰቡ ጋር መቀላቀላቸው ሁኔታዎች ፈታኝ አድርጎት እንደነበርም ለጋዜጣው ተናግረዋል።

@tikvahethiopia
#Gambella

• 2 ሰዎች ተገድለዋል።
• 1 ሰው ቆስሎ ሆስፒታል ህክምና ላይ ነው።
• 2 ህፃናት ታፍነው ተወስደዋል።

በጋምቤላ ከደቡብ ሱዳን የሚነሱ የ "ሙርሌ ጎሳ" ታጣቂዎች ድንበር አቋርጠው በመግባት ጥቃት አድርሰዋል።

በዲማ ወረዳ ኡኩጉ የስደተኛ መጠለያ ጣቢያ ላይ ድንበር ተሻግረው በመጡ የሙርሌ ታጣቂዎች በከፈቱት ተኩስ የ2 ሰው ህይወት ሲያልፍ አንድ ሰው ቆስሎ 2 ህፃናት በታጣቂዎች መወሰዳቸውን የክልሉ ፖሊስ አሳውቋል።

ታጣቂዎች ጥቃቱን የፈፀሙት ከትናንት በስቲያ ከምሽቱ 4:30 ላይ ሲሆን ክልሉ በአሁኑ ሰዓት ልዩ ኃይሉንና ሚሊሻ በመጠቀም ሰላምና ፀጥታ የማስከበር ስራውን እየሰራ መሆኑን አሳውቋል።

ጥቃት አድራሾች ላይ እርምጃ ለመውሰድም በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ ፖሊስ ገልጷል።

#ድንበሩ_ሰፊ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ተመሳሳይ ጥቃት እንዳይፈጸም መንግስት ከሚያደርገው ጥረት በተጓዳኝ ህብረተሰቡ በንቃት አካባቢውን እንዲጠብቅ ማሳሰቢያ ተላልፏል።

የጋምቤላ ፖሊስ ፥ በፀጥታ አካላት ከሚሰራው የመከላከል ስራ ጎን ለጎን የክልሉ መንግስት ከፌዴራል መንግስት ጋር በመሆን ለችግሩ ዘላቂ መፍትሄ ለማበጀት ከደ/ሱዳን መንግስት ጋር ውይይት እየተደረገ ነው ማለቱን ከክልሉ ፕሬስ ሴክሬተሪያት ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

@tikvahethiopia
#Gambella

በጎርፍ አደጋ ወገኖቻችን ተፈናቀሉ።

በጋምቤላ ክልል በ4 ወረዳዎች በደረሰ የጎርፍ አደጋ ከአራት ሺህ በላይ አባዎራና እማዎራ ወገኖቻችን ከመኖሪያ ቀያቸዉ ተፈናቅለዋል።

ከክልሉ አደጋ ስጋት አመራር በተገኘው መረጃ በሃገራችን ደጋማዉ አካባቢ በጣለዉ ከፍተኛ ዝናብ ምክንያት በላሬ፣ በመኮይ በዋንቱዋና በኢታንግ ልዩ ወረዳ በሚገኙ ቀበሌዎች ላይ የጎርፍ መጥለቅለቅ ተከስቷታ።

የጎርፍ መጥለቅለቅ ከደረሰባቸዉ 4 ወረዳዎች ዉስጥ አራት ሺህ አንድ መቶ ሰላሳ ዘጠኝ አባዎራና እማዎራ ከመኖሪያ ቀያቸዉ የተፈናቀሉ ሲሆን ለጊዜዉ ደረቃማ በሆኑ አካባቢዎች እንዲሰፍሩ ተደርጓል።

የደረሰው ጉዳት ዝርዝር ፦
- በኢታንግ ልዩ ወረዳ 2040 አባወራና እማወራ፣
- በላሬ ወረዳ 1000፣
- በዋንቱዋ ወረዳ 619፣
- በመኮይ 480 አባወራና እማወራ የተፈቀሉ ሲሆን በጂካዎ ወረዳም ከፍተኛ ጉዳት ደርሷል።

የጎርፍ አደጋዉ በቤት ዉስጥ ያሉ ቁሳቁሶች እንዲሁም በቁም እንስሳት ላይ ጉዳት አድርሷሳ።

በጎርፍ አደጋ ከቤት ንብረታቸዉ ለተፈናቀሉ ነዋሪዎች የአስቸኳይ ጊዜ እርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው የተገለፀ ሲሆን ከክልሉ መንግስትና ከሚመለከታቸዉ ባለድርሻ አካላት በመነጋገር አፋጣኝ ድጋፍ የሚደርስበት ሁኔታ ይመቻቻል ሲል የክልሉ አደጋ ስጋት አመራር አስታውቋል።

መረጃው ከክልሉ ኮሚኒኬሽን የተገኘ ነው።

@tikvahethiopia
#Gambella

" የአካባቢው ማህበረሰብ በተቻለው አቅም እራሱን እንዲጠብቅ አደራ እንላለን " - የጋምቤላ ክልል መንግስት

የሙርሌ ጎሳ ታጣቂዎች በጋምቤላ ክልል፤ ኑዌር ዞን በከፈቱት ተኩስ 3 ሰዎችን ሲገድሉ ፤ አንድ የ11 ዓመት ታዳጊ አፍነውን ወስደዋል።

የጋምቤላ ክልል መንግስት ኮሚኒኬሽን እንዳሳወቀው በቀን 26/01/2015 ዓ/ም ከቀኑ 12 ሰዓት ገደማ ላይ በኑዌር ዞን ፤ በማኮይ ወረዳ በሎንጆክ ቀበሌ የሙርሌ ታጣቂዎች ተኩስ ከፍተው 3 ሰዎችን ሲገድሉ፤ አንድ የ11 ዓመት ታዳጊ አፍነው ወስደዋል።

ይህ ድርጊት የተፈፀመበት ቦታ " ጎርፍ ካጠቃቸው " ቦታዎች አንዱ ሲሆን ህብረተሰቡን የማረጋጋት እና ታጣቂዎች ለመያዝ እየተሰራ መሆኑን ክልሉ አሳውቋል።

የክልሉ መንግስት ፤ የአካባቢው ማህበረሰብ በተቻለው አቅም እራሱን እንዲጠብቅ አደራ ብሏል።

የሙርሌ ጎሳ ታጣቂዎች በተደጋጋሚ ጊዜ ድንበር ጥሰው እየገቡ በኑዌር ዞን እና አኝዋሃ ዞን በሰው ህይወት ላይ አደጋ ሲያደርሱ እና በርካታ ከብቶችንም ዘርፈው ሲወስዱ ቆይተዋል።

@tikvahethiopia
ሰሞነኛው ዝናብ ...

በተለያዩ የሀገራችን አካባቢዎች ከሰሞኑን እየጣለ ያለው ዝናብ በሰው ህይወት እና በንብረት ላይ ጉዳት እያደረሰ ይገኛል።

#SNNPRS

በደቡብ ክልል ፥ ጎፋ ዞን ዑባ-ደብረፀሃይ ወረዳ ዛባ ቀበሌ በጣለው ከባድ ዝናብ በተከሰተ የጎርፍ አደጋ 21 ሰዎች መሞታቸውን ለማወቅ ተችሏል። በንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ደርሷል።

በህይወት የተረፉ ዜጎ በትምህርት ቤቶች ውስጥ እንዲጠለሉ የተደረገ ሲሆን ለችግሩ ዘላቂ መፍትሄ ለማፈላለግ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ስራ መገባቱ ተሰምቷል።

ተጎጂ ወገኖችን ለመደገፍም በዞኑ የአደጋ ጊዜ ዝግጁነት ማቋቋሚያ የባንክ ሂሳብ ቁጥር 1000511561276 ላይ ድጋፍ እንዲደረግ ተጠይቋል።

#Amhara

በአማራ ክልል፣ ደቡብ ወሎ ዞን ለገሂዳ ወረዳ 02 አዋተል ቀበሌ ሚያዚያ 27/2015 ዓ.ም ምሽት ለተከታታይ 30 ደቂቃ የጣለው በረዶ የቀላቀለ ዝናብ በእንስሳት፣ በሰብልና በመኖሪያ ቤቶች ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሷል።

በረዶ ቀላቅሎ የጣለው ዝናብ ከ37 ሄክታር መሬት በላይ የደረሱ ሰብሎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱ ተነግሯል።

#Gambella

በጋምቤላ ክልል ፤ በዲማ ወረዳና አጎራባች ወረዳዎች ከሚያዝያ 25 /2015 ዓ.ም ጀምሮ እየጣለ ባለው ሃይለኛ ዝናብ ምክንያት በተከሰተው ጎርፍ በሚሊየን የሚገመት ንብረት ላይ ጉዳት ደርሷል።

የጎርፍ አደጋው እስካሁን ባለው መረጃ በወረዳው ከ70 በላይ መኖሪያ ቤቶች በውሃ ያጥለቀለቀ ሲሆን በሰብል ላይም ጉዳት አድርሷል።

ጎርፉ በዲማ ከተማ ወንዝ ዳር የነበረውን የከተማ ንፁህ መጠጥ ውሃ መሳቢያ ጀነሬተርና ፖምፕ ግንብ ቤቱን ጨምሮ በሚሊዮን በሚገመት ንብረት ላይ ጉዳት ማድረሱን ታውቋል።

በዚህም ችግር ሳቢያ የከተማው ንፁህ መጠጥ ውሃ አገልግሎት መቆሙ ተነግሯል።

በተመሳሳይ በዲፕ (መርከስ) ቀበሌ የሚገኘው የእኩጉ ስደተኞች መጠለያ ጣብያና የአካባቢው ማህበረሰብ የንፁህ መጠጥ ውሃ አገልግሎት የሚሰጡ ሁለት መሳቢያ ጀነሬተሮች በጎርፍ መወሰዱ ታውቋል።

ከዚህ በተጨማሪም የአኮቦ ወንዝ እስከጫፉ ድረስ በመሙላቱ ዲማ ወረዳን ጨምሮ ሁለት አጎራባች ወረዳዎች የሚያገናኝ የአኮቦ ብረት ድልድይ ላይ ጉዳት ደርሷል።

በደረሰው አደጋ ድጋፍ የሚያስፈልጋቸው ወገኖች ለማገዝ የክልሉ መንግሥትን ጨምሮ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች የበኩላቸውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ ቀርቧል።

መረጃ ምንጮች ፦ የጎፋ ዞን ፣ የለገሂዳ እና የዲማ ወረዳ ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ናቸው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#NewsAlert በጋምቤላ ክልል የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በሁለት ቦታዎች እንዲሰጥ ተወሰነ። በጋምቤላ ክልል ሰሞኑን ተከስቶ በነበረው የፀጥታ ችግር ምክንያት የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በጋምቤላ ዩኒቨርስቲ እና በጋምቤላ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ እንደሚሰጥ የክልሉ መንግስት አስታውቋል። የክልሉ መንግሥት ፤ " በጋምቤላ ዩኒቨርስቲ ብቻ ሊሰጥ የነበረው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ሰሞኑን ተከስቶ በነበረው…
#Gambella

በጋምቤላ መምህራን ትምህርትና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የሚፈተኑ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ተፈታኝ ተማሪዎች " የጤና እክል " ገጥሟቸው እንደነበር የክልሉ የመንግስት አሳውቋል።

ተፈታኞቹ ትላንት ምሽት ከ1:30 ጀምሮ ወደ ጋምቤላ አጠቃላይ ሆስፒታል አቅንተው ተገቢው ህክምና እየተደረገላቸው ነው ተብሏል።

ተፈታኞቹ የገጠማቸው የጤና እክል መነሻው " የምግብ መመረዝ " አልያም " የተበላሸ ምግብ መብላት " መሆን አለመሆኑን በማጣራት ላይ ክልሉ አሳውቋል።

ሆስፒታል ከገቡ ተማሪዎች መካከል ለህይወት የሚያሰጋ የጤና እክል የደረሰባቸው እንደሌሉ የገለፀው ክልሉ አብዛኞቹ አገግመው ወደ ፈተና ማዕከላቸው መመለሳቸውን አመልክቷል።

በአሁኑ ሰዓትም ህክምና በመከታተል ላይ ያሉ ተፈታኞች እንደሚገኙ የተጠቆመ ሲሆን በህይወት ላይ የደረሰ ጉዳት እንደሌለ ክልሉ አሳውቋል።

" የተፈታኝ ወላጆች ልጆቻቸው በመልካም ጤንነት ላይ የሚገኙ በመሆናቸው እንዳይደናገጡ " ያለው የጋምቤላ ክልል " ምክንያቱ ምን እንደሆነ የህክምና ባለሙያዎች የሚሰጡትን መረጃ ለህዝብ ይፋ እናደርጋለን " ብሏል።

በጋምቤላ ክልል በተከሰተው የፀጥታ ችግር ምክንያት የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ እና በጋምቤላ መምህራን ትምህርትና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ እንዲሰጥ መወሰኑ አይዘነጋም።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ከኢሰመኮ ሪፖርት ፦ " ሰኔ 7 ቀን 2014 ዓ.ም. ከቀኑ 7፡00 ሰዓት በኋላ እንዲሁም ሰኔ 8 እና 9 ቀን 2014 ዓ.ም. በዋናነት በክልሉ የጸጥታ ኃይሎች በተወሰዱ እርምጃዎች " የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች እና መሣሪያ በቤታችሁ እንዳለ ተጠቁመናል፤ የደበቃችሁትን መሣሪያ አውጡ " በሚል ምክንያት ሴቶችና የአእምሮ ሕመምተኞችን ጨምሮ ቢያንስ 50 ሲቪል ሰዎች በተናጠል እና በጅምላ ከፍርድ ውጪ መገደላቸውን፣…
#Gambella

ንፁሃንን " መረጃ ሰጥታችኋል " በሚል በአቃቂ ሁኔታ #እንዲገደሉ ትዕዛዝ አስተላልፈዋል ፤ ግድያው ላይም ተሳትፈዋል ከተባሉ ተከሳሾች ውስጥ የጋምቤላ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የቀድሞ ዋና ኮሚሽነር አቡላ ኦባንግ በተከሰሱበት ክስ #ነጻ መባላቸው ተሰምቷል።

ሌሎች የቀድሞ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን አመራሮች እና የልዩ ኃይል አዛዦችን ጨምሮ 12 ተከሳሾች ግን የጥፋተኝነት ፍርድ ተላልፎባቸዋል።

ብይኑን የሰጠው የፌደራሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ የሕገ-መንግሥት እና በሕገ-መንግሥት ሥርዓቱ ላይ የሚፈጸሙ የወንጀል ጉዳዮች የሚመለከተው ችሎት ነው። 

ክስ ቀርቦባቸው የነበሩት እነማን ናቸው ?

የጋምቤላ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የቀድሞው ዋና ኮሚሽነር አቡላ ኦባንግ፣
የቀድሞው ም/ኮሚሽነር ቱት ኮር፣
የክልሉ ልዩ ኃይል የቀድሞ ዋና አዛዥ ዋና ኢንስፔክተር ኮንግ ሬክ
የክልሉ ልዩ ኃይል የቀድሞው ምክትል አዛዥ ዋና ኢንስፔክተር ኡጀዲ ባሬ እና የተለያዩ የፀጥታ አባላትን ጨምሮ አጠቃላይ 15 ተከሳሾች ናቸው።

ተከሳሾቹን ላይ የቀረበው ክስ ምንድነው ?

ሰኔ 7/2014 ዓ/ም በጋምቤላ ከተማ መንግሥት በአሸባሪ ቡድንነት የፈረጀው " ሸኔ " እና የጋምቤላ ነጻ አውጪ ግንባር (ጋነግ) በጋራ ሆነው ቀበሌ 03 በፌደራል ፖሊስ ካንፕ እና በክልሉ ልዩ ኃይል እንዲሁም በሌሎች ፀጥታ አካላት ላይ ድንገተኛ ተኩስ ከፍተው ነበር።

በኃላም ጥቃት አድራሾቹም በፀጥታ ኃይሎች ወደ መጡበት እንዲመለሱ ተደርጓል።

ከዚህ ክስተት በኋላ ግን ማንነታቸው የተለዩ 35 ሰዎች እና ማንነታቸው ያልተለዩ ሌሎች ንፁሃንን " #መረጃ_ሰጥታችኋል " በሚል በአሰቃቂ ሁኔታ ሕይወታቸው እንዲያልፍ  ትዛዝ ሰጥተዋል ፤ በግድያው ላይ የተሳተፉም አሉ የሚል ነው።

የክስ መዝገቡ የተከሳሾች የተሳትፎ ደረጃቸውን በዝርዝር አስቀምጧል።

ፍርድ ቤት ምን ውሳኔ አሳለፈ ?

ከ15ኛው ተከሳሽ ውጭ ሌሎቹ በማረሚያ ቤት ሆነው ጉዳያቸውን ሲከታተሉ ቆይተዋል።

ግለሰቦቹ የእምነት ክህደት ቃላቸውን ሰጥተዋል።

ዐቃቤ ህግ ምስክሮቹን አሰምቷል። ማስረጃዎቹን አቅርቧል።

ፍርድ ቤት ፦
° የጋምቤላ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የቀድሞው ዋና ኮሚሽነር አቡላ ኦባንግ፣
° ቀድሞው ም/ኮሚሽነር ቱት ኮር
° የክልሉ ልዩ ኃይል የቀድሞው ዋና አዛዥ ዋና ኢንስፔክተር ኮንግ ሬክ
° የክልሉ ልዩ ኃይል የቀድሞ ምክትል አዛዥ ዋና ኢንስፔክተር ኡጀዲ ባሬን ጨምሮ 13 ተሳሾች በተከሰሱበት ድንጋጌ እንዲከላከሉ ብይን ሰጥቷል።

ዛሬ በዋለው ችሎት 12 ተከሳሾች የዐቃቤ ሕግ ማስረጃን በበቂ ሁኔታ መከላከል አለመቻላቸው ተጠቅሶ የጥፋተኝነት ፍርድ ተላልፎባቸዋል።

የጋምቤላ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የቀድሞው ዋና ኮሚሽነር አቡላ ኦባንግ የዐቃቤ ሕግ ማስረጃን በተገቢው መከላከላቸው ተጠቅሶ ነጻ ተብለዋል።

ፍርድ ቤት ጥፋተኛ የተባሉ ተከሳሾችንና የዐቃቤ ሕግን የቅጣት አስተያየት ለመጠባበቅ ለሐምሌ 10/2016 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።

ከዚህ ቀደም የጋምቤላ ክልል ልዩ ኃይል የቀድሞ አባል ኮ/ል አቶሬ ጉር እና የጋምቤላ ፖሊስ ኮሚሽን የቀድሞ አባል ረ/ሳጅን ቾድ ቤንግን በተመለከተ ፍ/ቤቱ በቀረበባቸው ክስ ላይ በቂ ማስረጃ አለመሰማቱን ተገልጾ በነጻ እንዲሰናበቱ ተደርጓል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከኤፍቢሲ ነው ያገኘው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Gambella ንፁሃንን " መረጃ ሰጥታችኋል " በሚል በአቃቂ ሁኔታ #እንዲገደሉ ትዕዛዝ አስተላልፈዋል ፤ ግድያው ላይም ተሳትፈዋል ከተባሉ ተከሳሾች ውስጥ የጋምቤላ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የቀድሞ ዋና ኮሚሽነር አቡላ ኦባንግ በተከሰሱበት ክስ #ነጻ መባላቸው ተሰምቷል። ሌሎች የቀድሞ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን አመራሮች እና የልዩ ኃይል አዛዦችን ጨምሮ 12 ተከሳሾች ግን የጥፋተኝነት ፍርድ ተላልፎባቸዋል። …
#EHRC #Gambella

“ ቪዲዮው የቆየ ነው ፤ ከሁለት ዓመት በፊት ነው ” - የኢሰመኮ ጋምቤላ ክልል ጽሕፈት ቤት

ባለፉት ሳምንታት ውስጥ አንድ እጅግ በጣም አሰቃቂ ቪድዮ በማህበራዊ ሚዲያዎች ሲዘዋወር ቆይቷል።

እውነት ለመናገር በቪድዮ ላይ የሚታየው የጭካኔ ተግባር በቃላት የሚገለጽ አይደለም።

ቪድዮው የጋምቤላ ክልል የጸጥታ ልብስ የለበሱ አካላት ሰዎችን እጅግ በአሰቃቂ ሁኔታ በድንጋይ ጭምር ጭንቅላታቸውን እየፈጠፈጡ በጅምላ ሲገድሏቸው የሚያሳይ ለማየት የሚከብድ ዘግናኝ ቪዲዮ ነው።

ይህን ቪዲዮ የተመለከቱ በርካቶች ፣ “ እውነት እኛ ሀገር ነው ? እኛ ሀገር ከሆነስ ለዚህ ተግባር ተጠያቂነት እና ፍትሕ ተረጋግጧል ? ” በማለት በእጅጉ አዝነው ጠይቀዋል።

አብዛኛዎቹ ሰዎችም ቪዲዮው ከሰሞኑን የተፈጸመ ጥቃት አድርገውም የወሰዱ ነበሩ።

ቲክቫህ ኢትዮጵያም ለጉዳዩ ቅርብ ናቸው ያላቸውን አካላት ስለቪድዮው ጠይቋል።

ይህንን ቪዲዮ ኮሚሽናችሁ ተመልክቶት ነበር ? በማለት የጠየቃቸው የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ጋምቤላ ክልል ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አቤል አዳነ፣ “ ቪዲዮው የቆየ ቪዲዮ ነው። ከሁለት ዓመታት በፊት የነበረ ቪዲዮ ነው ” ብለዋል።

ሰኔ 7 / 2014 ዓ/ም “ የሸኔና ጋነግ ” ታጣቂዎች በጋምቤላ ክልል ገብተው ጥቃት እንደፈጸሙ አስታውሰዋል።

በኋላ “ የክልሉ ልዩ ኃይሎች ‘ ኦነግ ሸኔ ቀርተዋል ’ ብለው የጠረጠሯቸውን ሰዎች በየቤታቸው እየሄዱ፣ እዛው ፓሊስ ኮሚሽን አካባቢ ወስደው ግድያ ፈጽመውባቸዋል ” ነው ያሉት።

“ ይህንን ቪዲዮ ጨምረን ሌሎችንም ምርመራ አድርገን የምርመራውን ሪፓርት ይፋ አድርገናል በሰዓቱ ” ብለዋል።

የኮሚሽኑ አስተያዬት የተካተተበትን ሪፓርትም ልከዋል። 

ግድያውን የፈጸሙት አካላት በሕግ ፊት ተጠያቂ ተደርገው ይሆን ? በማለት ላቀረብንላቸው ጥያቄ “ በዚህ ጉዳይ ላይ ተጠርጥረው የታሰሩ ሰዎች አሉ ” ብለዋል።

ከፌደራል ፓሊስ ፣ ከፍትህ ሚኒስቴር የተውጣጣ አጣሪ መርማሪ ቡድንም ጋምቤላ መጥቶ ጉዳዩን እንደመረማረና ‘በጉዳዩ ላይ ተጠይቂ ናቸው’ ብሎ የሚያስባቸውን ሁሉ በህግ ቁጥጥር ስር እንዲውሉ ተደርጎ የፍርድ ሂደታቸው እየተካሄደ መሆኑን አስረድተዋል።

ከነዚህም ውስጥ በወቅቱ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር የነበሩትና ምክትላቸውን ጨምሮ ሌሎችም እንዳሉበት አክለዋል።

ትላንትና ከሰኔ 7 ቀን 2014 የጋምቤላ ክስተት ጋር በተያያዘ ንፁሃንን " መረጃ ሰጥታችኋል " በሚል በአቃቂ ሁኔታ #እንዲገደሉ ትዕዛዝ አስተላልፈዋል ፤ ግድያው ላይም ተሳትፈዋል የተባሉ ፦
➡️ የጋምቤላ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የቀድሞ አመራሮች ፣
➡️ የልዩ ኃይል አዛዦች (ዋናውና ምክትሉ)
➡️ የተለያዩ የጸጥታ አባላት
የጥፋተኝነት ፍርድ እንደተላለፈባቸው ፤ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን የቀድሞ ዋና ኮሚሽነር አቡላ ኦባንግ ግን በተከሰሱበት ክስ #ነጻ መባላቸው ይታወሳል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#Gambella : በጋምቤላ ክልል 4 ወረዳዎች የጎርፍ አደጋ ተከስቷል።

ከ16 ሺህ በላይ ነዋሪዎች ከመኖሪያ ቀያቸዉ ተፈናቅለዋል።

በሀገሪቱ ደጋማ አካባቢ በጣለው ከባድ ዝናብ ፦
- በጎግ፣
- በላሬ፣
- በጆርና
- በዋንቱዋ ወረዳዎች በሚገኙ ቀበሌዎች ላይ የጎርፍ መጥለቅለቅ ተከስቶ ነው ወገኖቻችን የተፈናቀሉት።

ተፈናቃዮቹን ለጊዜዉ ደረቃማ በሆኑ አካባቢዎች እንዲሰፍሩ ተደርጓል ተብሏል።

የጎርፍ አደጋዉ በቤት ዉስጥ ባሉ ቁሳቁሶች እንዲሁም በቁም እንስሳትና በሰብል ላይም ጉዳት ማድረሱን ገልፀዋል።

የጎርፍ መጥለቅለቁ በሚቀጥሉት ጊዜያት ከዚህ የከፋ ጉዳት ሊያስከትል ይችላል ተብሏል። ለዚህም ነዋሪዎች አስፈላጊውን ዝግጅትና ጥንቃቄ ሊያደርጉ እንዲያደርጉ የክልሉ አደጋ ስጋት ስራ አመራር አሳውቋል።

#GambellaRegionPressSec.

@tikvahethiopia
#Gambella

ከ6 አመት በላይ ጋምቤላ ክልልን ሲመሩ የቆዩት አቶ ኡሞድ ኡጁሉ ከስልጣናቸው ተነስተው አዲስ ፕሬዚዳንት ዛሬ ተሹሟል።

የክልሉ ምክር ቤት ዛሬ ወ/ሮ አለሚቱ ኡሞድን የክልሉ ፕሬዜዳንት አድርጎ ሾሟል።

ወ/ሮ አለሚቱ የዛሬው ሹመት እስኪሰጣቸው በኢፌዴሪ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የህፃናት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ በመሆን አገልግለዋል።

በክልሉ ም/ቤት " የአመራር ለውጥ ያስፈለገበት ምክንያት በሠላም እና ፀጥታ እንዲሁም በልማት ዘርፍ በርካታ ስራዎች ቢሰሩም የተቀመጡ አቅጣጫዎች ውስንነቶች በመታየታቸው ነው " ተብሏል።

የቀድሞው ፕሬዜዳንት አቶ ኡመድ ሌላ የፓርቲ ተልዕኮ እንደሚሰጣቸውም ተሰምቷል።

በሌላ በኩል ደግሞ ጋትሏክ ሮን (ዶ/ር) ምክትል ፕሬዝዳንት ሆነው ተሹመዋል።

@tikvahethiopia