TIKVAH-ETHIOPIA
1.5M subscribers
56.7K photos
1.41K videos
203 files
3.87K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የአስሩ ክልሎች እና የሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች ወቅታዊ የኮሮና ቫይረስ (COVID-19) ስርጭት ቁጥራዊ መረጃ ፦

#Afar

በቫይረሱ የተያዙ - 1,447
ያገገሙ - 231

#Amhara

በቫይረሱ የተያዙ - 3,427
ህይወታቸው ያለፈ - 35
ያገገሙ - 2,273

#BenishangulGumuz

በቫይረሱ የተያዙ - 1138
ያገገሙ - 382

#Harari

በቫይረሱ የተያዙ - 1,514
ህይወታቸው ያለፈ - 27
ያገገሙ - 748

#Oromia

በቫይረሱ የተያዙ - 9,602
ህይወታቸው ያለፈ - 67
ያገገሙ - 4,801

#SNNPRS

በቫይረሱ የተያዙ - 2,242
ህይወታቸው ያለፈ - 16
ያገገሙ - 1,717

#AddisAbaba

በቫይረሱ የተያዙ - 37,278
ህይወታቸው ያለፈ ድምር - አልተገለፀም
ያገገሙ ሰዎች ድምር - አልተገለፀም

#Tigray

በቫይረሱ የተያዙ - 5,433
ህይወታቸው ያለፈ - 27
ያገገሙ - 4,333

#Somali

በቫይረሱ የተያዙ - 1,376
ህይወታቸው ያለፈ - 26
ያገገሙ - 1,084

#Sidama

በቫይረሱ የተያዙ - 1,926
ህይወታቸው ያለፈ - 22
ያገገሙ - 1,576

#DireDawa

በቫይረሱ የተያዙ - 1,260
ህይወታቸው ያለፈ - 21
ያገገሙ - 1,086

#Gambela

በቫይረሱ የተያዙ - 954
ያገገሙ - 506
ህይወታቸው ያለፈ - አራት በኮሮና ተቋም፣ አምስት ከአስክሬን፣ አስራ አንድ ላብራቶሪ ውጤት በመጠበቅ

መስከረም 9/2013 ዓ/ም
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
መስከረም 19/2013 ዓ/ም

የኮቪድ-19 መረጃዎች፦

#Somali

በሱማሌ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 63 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 3 ሰዎች በኮቪድ-19 መያዛቸው ተረጋግጧል።

#BenishangulGumuz

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 207 የላብራቶሪ ምርመራ ተራደርጎ 17 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል።

#Amhara

በአማራ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 5,25 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 24 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። የ1 ሰው ህይወት አልፏል (ከወልዲያ ሆስፒታል)

#Sidama

በሲዳማ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 138 የላብራቶሪ ምርመራ የተደረገ ሲሆን 21 ሰዎች በኮቪድ-19 መያዛቸው ተረጋግጧል (17ቱ ከሀዋሳ ከተማ ናቸው)

#Harari

በሐረሪ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 189 የላብራቶሪ ምርመራ የተደረገ ሲሆን 92 ሰዎች በኮቪድ-19 መያዛቸው ተረጋግጧል።

#Tigray

በትግራይ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 505 የላብራቶሪ ምርመራ የተደረገ ሲሆን 46 ሰዎች በኮቪድ-19 መያዛቸው ተረጋግጧል። የ1 ሰው ህይወት አልፏል (ከመቐለ ህክምና ማዕከል)

#DireDawa

በድሬዳዋ 237 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 76 ሰዎች ላይ የኮሮና ቫይረስ ተገኝቷል።

#Oromia

በኦሮሚያ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 481 የላብራቶሪ ምርመራ የተደረገ ሲሆን 84 ሰዎች በኮቪድ-19 መያዛቸው ተረጋግጧል። የ2 ሰዎች ህይወት አልፏል።

#Gambella

በጋምቤላ ክልል ባለፉት 24 ሰዓታት በተደረገው የላብራቶሪ ምርመራ 3 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል።

#SNNPRS

በደቡብ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 451 የላብራቶሪ ምርመራ የተደረገ ሲሆን 24 ሰዎች በኮቪድ-19 መያዛቸው ተረጋግጧል።

@tikvahethiopiaBOT
መስከረም 21/2013 ዓ/ም

የኮቪድ-19 መረጃዎች ፦

#Somali

በሱማሌ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 75 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 4 ሰዎች በኮቪድ19 መያዛቸው ተረጋግጧል።

#BenishangulGumuz

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 201 የላብራቶሪ ምርመራ ተራደርጎ 41 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል።

#Amhara

በአማራ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 696 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 25 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል።

#DireDawa

በድሬዳዋ 195 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 76 ሰዎች ላይ የኮሮና ቫይረስ ተገኝቷል።

#Harari

በሐረሪ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 211 የላብራቶሪ ምርመራ የተደረገ ሲሆን 65 ሰዎች በኮቪድ-19 ተይዘዋል።

#Tigray

በትግራይ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 621 የላብራቶሪ ምርመራ የተደረገ ሲሆን 36 ሰዎች በኮቪድ-19 መያዛቸው ተረጋግጧል።

#Oromia

በኦሮሚያ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 652 የላብራቶሪ ምርመራ የተደረገ ሲሆን 89 ሰዎች በኮቪድ-19 መያዛቸው ተረጋግጧል። የ2 ሰዎች ህይወት አልፏል።

#AddisAbaba

በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት 24 ሰዓት 2,814 የላብራቶሪ ምርመራ የተደረገ ሲሆን 286 ሰዎች በኮቪድ-19 መያዛቸው ተረጋግጧል። የ2 ሰዎች ህይወት አልፏል።

#Gambella

በጋምቤላ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 88 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 10 ሰዎች ላይ ቫይረሱ ተገኝቷል፤ 7ቱ ኢትዮጵያውያን ፣ 3ቱ ቻይናውያን ናቸው።

#SNNPRS

በደቡብ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 793 የላብራቶሪ ምርመራ የተደረገ ሲሆን 70 ሰዎች በኮቪድ-19 መያዛቸው ተረጋግጧል።

@tikvahethiopiaBOT
TIKVAH-ETHIOPIA
#COVID19Ethiopia በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰዓት በተደረገው 6,916 የላብራቶሪ ምርመራ 890 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ሲረጋገጥ የ3 ሰዎች ህይወት አልፏል። በተጨማሪ በትላንትናው ዕለት 247 ሰዎች አገግመዋል። በአጠቃላይ በሀገራችን በኮቪድ-19 የተያዙ ሰዎች 76,988 የደረሱ ሲሆን የሟቾች ቁጥር 1,208 ደርሷል ፤ ከበሽታው ያገገሙ አጠቃላይ ሰዎች ቁጥር ደግሞ 31,677 ደርሷል። @t…
መስከረም 22/2013 ዓ/ም

የኮቪድ-19 መረጃዎች ፦

#Somali

በሱማሌ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 208 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 1 ሰው በኮቪድ-19 መያዙ ተረጋግጧል።

#BenishangulGumuz

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 120 የላብራቶሪ ምርመራ ተራደርጎ 23 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል።

#Amhara

በአማራ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 566 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 104 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል።

#DireDawa

በድሬዳዋ 168 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 67 ሰዎች ላይ የኮሮና ቫይረስ ተገኝቷል።

#Harari

በሐረሪ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 311 የላብራቶሪ ምርመራ የተደረገ ሲሆን 103 ሰዎች በኮቪድ-19 ተይዘዋል።

#Oromia

በኦሮሚያ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 451 የላብራቶሪ ምርመራ የተደረገ ሲሆን 135 ሰዎች በኮቪድ-19 መያዛቸው ተረጋግጧል። የ3 ሰዎች ህይወት አልፏል።

#AddisAbaba

በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት 24 ሰዓት 3,274 የላብራቶሪ ምርመራ የተደረገ ሲሆን 333 ሰዎች በኮቪድ-19 መያዛቸው ተረጋግጧል።

#Gambella

በጋምቤላ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 92 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 5 ሰዎች ላይ ቫይረሱ ተገኝቷል። ትላንት 2 ሰዎች አገግመዋል።

#SNNPRS

በደቡብ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 822 የላብራቶሪ ምርመራ የተደረገ ሲሆን 61 ሰዎች በኮቪድ-19 መያዛቸው ተረጋግጧል፤ የ2 ሰዎች ህይወት አልፏል።

@tikvahethiopiaBOT
ጥቅምት 1/2013 ዓ/ም

የኢትዮጵያ ኮቪድ-19 መረጃዎች ፦

#Somali

በሱማሌ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 142 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 7 ሰዎች በኮቪድ19 መያዛቸው ተረጋግጧል።

#BenishangulGumuz

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 104 የላብራቶሪ ምርመራ ተራደርጎ 39 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል።

#Amhara

በአማራ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 1,154 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 99 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። ከ99ኙ መካከል 64 ከምዕ/ጎጃም ዞን ፣ 16 ከባህር ዳር ከተማ ይገኙበታል።

#DireDawa

በድሬዳዋ 142 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 47 ሰዎች ላይ የኮሮና ቫይረስ ተገኝቷል።

#Tigray

በትግራይ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 468 የላብራቶሪ ምርመራ የተደረገ ሲሆን 19 ሰዎች በኮቪድ-19 መያዛቸው ተረጋግጧል።

#Oromia

በኦሮሚያ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 471 የላብራቶሪ ምርመራ የተደረገ ሲሆን 169 ሰዎች በኮቪድ-19 መያዛቸው ተረጋግጧል።

#AddisAbaba

በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት 24 ሰዓት 3,913 የላብራቶሪ ምርመራ የተደረገ ሲሆን 365 ሰዎች በኮቪድ-19 መያዛቸው ተረጋግጧል። የ6 ሰዎች ህይወት አልፏል።

#Harari

በሐረሪ ባለፉት 24 ሰዓት 120 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 53 ሰዎች ላይ ቫይረሱ ተገኝቷል።

#SNNPRS

በደቡብ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 645 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 50 ሰዎች ላይ ቫይረሱ ተገኝቷል።

#Sidama

በሲዳማ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 184 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 18 ሰዎች ላይ ቫይረሱ ተገኝቷል።

@tikvahethiopiaBOT
ጥቅምት 4/2013 ዓ/ም

የኢትዮጵያ ኮቪድ-19 መረጃዎች ፦

#Somali

በሶማሌ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 146 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ በቫይረሱ መያዙ የተረጋገጠ ሰው አልተገኘም።

#BenishangulGumuz

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 85 የላብራቶሪ ምርመራ ተራደርጎ 27 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል።

#Amhara

በአማራ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 765 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 76 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። የ2 ሰው ህይወት አልፏል (1 ከእንጅባራ ህክምና ማዕከል፣ 1 ከሃይቅ)

#Oromia

በኦሮሚያ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 579 የላብራቶሪ ምርመራ የተደረገ ሲሆን 102 ሰዎች በኮቪድ-19 መያዛቸው ተረጋግጧል። የ2 ሰዎች ህይወት አልፏል።

#DireDawa

በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ባለፉት 24 ሰዓት በተደረገው 142 የላብራቶሪ ምርመራ 54 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል።

#Harari

በሐረሪ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት በተደረገው 94 የላብራቶሪ ምርመራ 13 ሰዎች በቫረረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል።

#SNNPRS

በደቡብ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 1304 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 55 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል።

#AddisAbaba

በአ/አ ባለፉት 24 ሰዓት 3,246 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 308 ሰዎች በኮቪድ-19 መያዛቸው ተረጋግጧል፤ የ2 ሰዎች ህይወት አልፏል።

* ያልተካከቱ የክልል ሪፖርቶችን ቆይት ብላችሁ ይህንኑ ፖስት ተመልከቱ !

@tikvahethiopiaBOT
#SNNPRS

በደ/ብ/ብ/ሕ/ክ/ መንግስት የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ከዛሬ ታህሳስ 07 ቀን 2013 ዓ/ም ጀምሮ መሰጠት ተጀመሯል።

ፈተናው ለ3 ተከታታይ ቀን ይሰጣል።

አጠቃላይ 292,769 ተማሪዎች ለፈተናው ተቀምጠዋል።

በፀጥታ ችግር ምክንያት ፈተና የማይሰጥባቸው ጣቢያዎች ቢኖሩም እንደ ጣቢያ በጣቢያቸው አይፈተኑም እንጂ በፈተና የሚቀመጡ ተማሪዎች አቅራቢያ ወዳለው ወደ ሌሎች ፈተና ጣቢያዎች ሄደው እንዲፈተኑ ሁኔታዎች መመቻቸቱ የክልሉ ትምህርት ቢሮ ገልጿል።

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#SNNPRS

በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት ተራዝሞ የነበረው የ2012 ዓ/ም 8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና በሰላማዊ ሁኔታ መጠናቀቁን የደቡብ ክልል ትምህርት ቢሮ አስታወቀ፡፡

በደቡብ ኦሞ ዞን አንድ ተማሪ ለወንድሙ ለመፈተን ሞክሮ እጅ ከፍንጅ ተይዞ ከመታሰሩ ውጭ ፈተናው ከኩረጃ በነፃ ሁኔታ መጠናቀቁን ቢሮ አሳውቋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ከጸጥታ ጋር ተያይዞ በኮንሶ፣ ማሎኮዛ ወረዳ ፣ በአሌ ልዩ ወረዳ እና በቤንቺ ሼኮ ዞን ጉራ ፈርዳ ወረዳ የሚገኙ ትምህርት ቤቶች በአቅራቢያቸው በሚገኙ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎቻቸውን አስፈትነዋል።

በጉራጌ ዞን እነርኖር ወረዳ ከመዋቅር ጥያቄ ጋር ተያይዞ 494 ተማሪዎች ፈተና ላይ እንዳይቀመጡ መደረጉ ተገልጿል።

በአጠቃለይ በ3,782 የመፈተኛ ጣቢያዎች ወደ 292,769 ተማሪዎች ፈተና ወስደዋል።

ምንጭ፦ የደቡብ ክልል ትምህርት ቢሮ
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#SNNPRS

በደቡብ ክልል እስካሁን ወደ ትምህርት ቤት ያልሄዱ አንድ ሚሊዮን የሚጠጉ ተማሪዎች አሉ።

እነዚህን ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታ የመመለስ ንቅናቄ እየተካሄደ መሆኑን የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታውቋል።

ከ9 ወራት በኋላ የገፅ ለገፅ ትምህርት ቢጀመርም ተማሪዎች የሚጠበቀውን ያህል በትምህርት ገበታቸው ላይ አልተገኙም ብሏል ቢሮው።

አሁን እየተካሄደ ያለው ንቅናቄ ቤት ለቤት በመንቀሳቀስ ተማሪዎች ከሰኞ ጀምሮ ወደ ትምህርት ቤት እንዲመለሱ ለማድረግ ያለመ ነው።

* በደቡብ ክልል በዘንድሮው የትምህርት ዘመን 4 ሚሊዮን 200 ሺህ ተማሪዎችን ለመቀበል ከታቀደው ውስጥ 77 ነጥብ 3 በመቶ ተፈፅሟል። ቀሪውን በንቅናቄው ለማሳካት እየተሰራ ነው ተብሏል።

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#SNNPRS

በካፋ ዞን ዴቻ ወረዳ ጉንድራ ገራ ቀበሌ ከሰሞኑ የጣለውን ከባድ ዝናብ ተከትሎ የወረደው በረዶ ከ7 መቶ 80 ሄክታር በላይ ማሳ ላይ በነበሩ ቋሚና ዓመታዊ ሠብሎችና የቤት እንስሳት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱን የዞኑ አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት አስታውቋል።

በጉዳቱ ሳቢያ ለችግር ለተጋለጡ ወገኖች ሠብዓዊ ድጋፍ የማድረስ ሥራ መጀመሩ ተገልጿል።

መጋቢት 8 ቀን 2013 ዓ.ም በዴቻ ወረዳ ጉንድራ ገራ ቀበሌ የጣለውን ከባድ ዝናብ ተከትሎ የወረደው በረዶ ከ 6 መቶ 31 ሄክታር በላይ ማሳ ላይ የነበሩ ቡና ፣ ኮረሪማና እንሠትን የመሳሰሉ ቋሚ ሠብሎች ላይ ጉዳት ሲያደርስ ከ1 መቶ 53 ሄክታር በላይ በሆነ ማሳ ላይ የነበረ የበቆሎ ችግኝን ሙሉ በሙሉ ከጥቅም ውጭ አድርጓል፡፡

በጉዳቱ ሳቢያም 312 እማወራና አባወራዎች ሥር የሚተዳደሩ ከ1 ሺ 5 መቶ 60 በላይ ሠዎች ለችግር ተዳርገዋል፡፡

በ780 የቀንድ ከብቶችና 556 የጋማ ከብቶች ላይም በረዶው ጉዳት አድርሷል ፡፡

በአካባቢው የጣለው በረዶ ከዚህ ቀደም ተከስቶ የማያውቅና ከባድ ነበረ ነው ተብሏል።

አደጋው በጉንድራ ገራ ብቻ ሣይሆን በጉንድራ ሸላ ቀበሌ ላይ የተከሰተ በመሆኑ ሠብዓዊ ድጋፍ ለማድረስ የሚያስችል የአደጋውን መጠን የመለየት ሥራ እየተሰራ ነው ተብሏል።

ምንጭ፦ ደ.ሬ.ቴ.ድ
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
#SNNPRS : የ8ኛ ክፍል ማለፊያ ውጤት ይፋ ተደረገ።

የደቡብ ክልል ትምህርት ቢሮ የ2013 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል ማለፊያ ውጤት ይፋ አድርጓል።

በ2013 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በክልሉ ሁሉም የ8ኛ ክፍል ማጠናቀቅቂያ ፈተና በ16 ዞኖችና በ7 ልዩ ወረዳዎች ተሰጥቷል ። ለፈተናው ከተመዘገቡት 237,116 ተማሪዎች 234,790 ፈተናውን ወስደዋል፡፡

በዚህም የ8ኛ ክፍል ማለፊያ ነጥብ ፦
- ለወንዶች 42 ፣
- ለሴቶች 41
- ለአይነ ስውራንና መስማት ለተሳናቸው ተማሪዎች ደግሞ 40 ሆኖ በክልሉ ትምህርት ቢሮ ማኔጅመንት ተወስኗል።

ለዚህ ውሳኔ እንደ መነሻ በ2012 ዓ/ም ኮቪድ - 19 ወረርሽኝ ባሳደረው ጫና በወቅቱ 7ኛ ክፍል የነበሩ ተማሪዎች 2ኛ ሴሜስተር ሳይማሩ ወደ 8ኛ ክፍል መዛወራቸውንና በክልሉ አንዳንድ አከባቢዎች የተፈጠረውን የፀጥታ ችግር ከግንዛቤ ውስጥ በማስገባት እንደሆነም ተመላክቷል።

ምንጭ ፡ የደቡብ ክልል ትምህርት ቢሮ

@tikvahethiopia
#SNNPRS : የደቡብ ክልል አዲስ መንግስት ምስረታ እየተካሄደ ነው።

6ኛው ዙር የደቡብ ብሄሮች ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ክልል ምክር ቤት መስራች ጉባኤ በመካሄድ ላይ ይገኛል።

በጉባኤው የአዲሱን ምክር ቤት አፈ ጉባኤዎች ፣ርዕሰ መስተዳደር እና የክልሉን መንግስት የካቢኔ አባላት ይሰየማሉ፣ የክልሉን አስፈጻሚ አካላት ስልጣን እና ተግባር ለመወሰን የወጣውን ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ ይፀድቃል ፤ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አባላትን መወከል የእለቱ አጀንዳዎች ናቸው።

Credit : የደቡብ ክልል ኮሚኒኬሽን

@tikvahethiopia
#SNNPRS

በደቡብ ክልል መሳሪያ የታጠቀ ግለሰብ በ5 ቀናት ውስጥ እንዲያስመዘግብ ጥሪ ቀረበ።

ይህ ጥሪ የተላለፈው በወቅታዊ ጉዳይ ላይ የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ትናንት ያካሔዱትን ውይይት መድረክ ተከትሎ ነው።

በዚህም መሰረት ማንኛውም የጦር መሳሪያ የታጠቀ አካል ከዛሬ ከጥቅምት 26 ቀን ጀምሮ እስከ ጥቅምት 30 ቀን 2014 ዓ.ም ባሉት ተከታታይ ቀናት በአካባቢው በሚገኙ የፖሊስ ጣቢያዎች ቀርቦ ማስመዝገብ ይኖርበታል ተብሏል።

ከዚህ በተጨማሪ ማንኛውም #መታወቂያ የሚሰጥ አካል አዲስ መታወቂያ መስጠት አልያም የመታወቂያ እድሳት ማካሔድ ክልክል መሆኑ ተገልጿል።

አስቸጋሪ ሁኔታ ቢፈጠር እና መታወቂያ ማግኘት ግዴታ ሆኖ ከተገኘ ግን የክልሉ የአስቸኳይ ጊዜ መምሪያ እዝ አውቆት ውሳኔ ሊሰጥበት ይችላል ተብሏል።

መረጃው ከደቡብ ክልል ኮሚኒኬሽን ያገኘነው ነው።

@tikvahethiopia
#SNNPRS

ከፌደራል የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ዕዝ መምሪያ የሚተላለፉ መመሪያወች እንደተጠበቁ ሆነው÷ የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል መንግስት በክልሉ ውስጥ ተግባራዊ የሚደረጉ የክልከላ መመሪያዎች አውጥቷል፡፡

ክልከላዎቹም ፦

1. በክልሉ ውስጥ ባሉ አካባቢወች ማንኛውም ባለሁለት እግር ተሽከርካሪ ከቀኑ 12፡00 ሰዓት በኋላ እንቅስቃሴ ማድረግ የተከለከለ ነው።

2. ማንኛውም የህዝብ ማመላለሻ ተሸከርካሪ ባለ ሶስት እግርን ጨምሮ ከምሽቱ 2፡00 በኃላ ማንቀሳቀስ የተከለከለ ነው።

3. የምርት ዕንቅስቃሴ እንዳይስተጓጎል የጭነት መኪኖች በየኬላው ጥብቅ ፍተሻ እየተደረገባቸው እንዲንቀሳቀሱ የፈቀድላቸው ሆኖ ከረዳቱና ካሽከርካሪው ውጪ መጫን የተከለከለ ነው።

4. ከፀጥታ አካላት ውጪ ማንኛውም እግረኛ በክልሉ ውስጥ ከምሽቱ 3፡00 ሰዓት በኋላ መንቀሳቀስ የተከለከለ ነው።

5. ከጤና ተቋማት፣ከነዳጅ ማደያዎች፤ከፖሊስ ጣብያ ውጪ ማንኛውም አገልግሎት ሰጪ ተቋም ከምሽቱ 3፡00 በኋላ አገልግሎት መስጠት አይችሉም።

6. ማንኛውም ባለ ሁለት እግር ተሸከርካሪ እና አሽከርካሪ የመንግስትን ጨምሮ ከቀን 29/2/2014 ጀምሮ እስከ 3/3/2014 ዓ.ም ድረስ በአቅራብያቸው ባለው የፖሊስ ተቋም ቀርበው መመዝገብ አለባቸው።

#ሼር #Share

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የቀጠለ👇 ከየካቲት ወር መጀመሪያ እስከአሁን የተከሰቱ የእሳት አደጋዎች፦ #AmharaRegion 📍 - በወልድያ በ06 ቀበሌ " ጎልጎታ " ተብሎ በሚታወቀው ሰፈር የካቲት 18 ለ19/2014 ዓ.ም አጥቢያ ሌሊት በደረሰ የእሳት አደጋ ባልና ሚስትን ህጻን ልጃቸው ጨምሮ ለሞት ሲዳርግ 3 ሰዎችን በቃጠሎ ለቁስለት ዳርጓል። - በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን በደላንታ ወረዳ በ016 ቀበሌ ልዩ ቦታው ሸንቦቆ…
የቀጠለ👇

#SNNPRS📍

- በስልጤ ዞን በ " ዳሎቻ ወረዳ " ውስጥ መንስዔው ባልታወቀ ምክያት በተከሰተ አደጋ የሳር ክዳን ቤቶች ሙሉ በቃጠሎ ወድመዋል፡፡

- በስልጤ ዞን በሚቶ ወረዳ " ግርንዚላ ሸፎዴ " ቀበሌ ምክንያቱ ባልታወቀ ድንገተኛ የእሳት ቃጠሎ ሶስት ህፃናት ህይወታቸው ስያልፍ ሁለት የሳር ክዳን ቤቶች ሙሉ በሙሉ መውደማቸው ተገልጿል።

- በስልጤ ዞን ዳሎቻ ወረዳ ውስጥ "በጅገና ላሾ ቀበሌ" ቀጠና-2 ጃፈር-1 ልማት ቡድን ምክንያቱ ያልታወቀ የእሳት አደጋ ከ1ሚሊየን 320ሺህ ብር በላይ የሚገመት ንብረት አውድሟል፡፡ 18 የቤተሰብ አባላትም ተፈናቅለዋል።

- በሀዲያ ዞን በምሻ ወረዳ ኤራ ጌሜዶ ቀበሌ መጋቢት 4 ቀን ምክንያቱ ባልታወቀ የእሳት አደጋ ምክንያት 22 ቤቶች ከነሙሉ ቁሳቁሳቸዉ ወድመዋል። በቃጠሎዉም 11 አባወራዎች ከቤት ንብረታቸዉ ተፈናቅለዋል።

- በነጭ ሳር ብሔራዊ ፓርክ ተከስቶ የነበረው የእሳት ቃጠሎ ከ1 ቀን በኋላ በቁጥጥር ስር መዋሉ ተገልጿል።

#OromiaRegion📍

- በባሌ ብሔራዊ ፓርክ የተነሳ እሳት ለአራት ቀናት ከቆየ በኋላ በቁጥጥር ስር መዋሉ ተገልጿል። የእሳቱ መነሻና የደረሰው ጉዳት በግልጽ አልተቀመጠም።

- ትላንት ማታ በጅማ ከተማ 'ቢሺሼ' እየተባለ በሚጠራ አከባቢ በተነሳው የእሳት አደጋ በአከባቢው የሚገኙ የልብስና የሸቀጣሸቀጥ ሱቆች ሙሉ ለሙሉ በሚባል መልኩ ወድመዋል። የእሳቱ መነሻና ያደረሰው የጉዳት መጠን እስካሁን በውል አልታወቀም።

NB : ከላይ የተዘረዘሩት የእሳት አደጋዎች በ ቲክቫህ ኢትዮጵያ @tikvahethmagazine በኩል ከመላው ሀገሪቱ ክፍል ከየካቲት ወር 2014 ዓ/ም አንስቶ እስከ ዛሬ ለቤተሰቦቻች የተላኩ መረጃዎች ብቻ ናቸው፤ መረጃዎቹ በመንግስት ተቋማት በኩል አልፈው ሪፖርት የተደረጉ ናቸው።

@tikvahethiopia
#SNNPRS

የደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ክልል መግለጫ አውጥቷል።

የክልሉ መንግስት በመግለጫው ትላንት ሚያዝያ 20/2014 ዓ/ም በስልጤ ዞን በወራቤ ከተማ እና በሳንኩራ ወረዳ ላይ በሀይማኖት ተቋማት ላይ ያነጣጠረ ጥቃት መፈፀሙን ገልጿል።

የተፈፀመው ጥቃት ለዘመናት ተቻችለው እና ተከባብረው በኖሩ የልዩ ልዩ እምነት ተከታይ ህዝቦች ላይ የሚፈጥረው አሉታዊ ተጽዕኖ ከፍተኛ ነው ብሏል።

" ሀይማኖትን ሽፋን በማድረግ በጽንፈኛ ሀይሎች የሚደርሰውን ጥቃት አልታገስም " ያለው የክልሉ መንግስት በስልጤ ዞን የተጀመረው ጥቃት ወደ ሌሎች የክልሉ አካባቢዎች እንዳይዛመት ሰላም ወዳዱ የክልሉ ህዝብ ከመንግስት ጎን በመሆን የአካባቢውን ሰላም ማስጠበቅ ይኖርበታል ብሏል።

(ዝርዝር መግለጫው ከላይ ተያይያዟል)

@tikvahethiopia
#SNNPRS

አንደኛ በመኸር ዝናብ መዛበት ሁለተኛ በግጭት ምክንያት የሚፈናቀሉ ሰዎች መጨመር በደቡብ ክልል የተረጂዎችን ቁጥር ጨምሯል።

የደቡብ ክልል የአደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን እንደሚለው፤ አሁን ላይ በደቡብ ክልል 3.3 ሚሊዮን ሰዎች ለከፋ ረሃብ / የምግብ ዋስትና ችግር ሊጋለጡ ይችላሉ ሲል ተንብዩዋል።

የከፋ ለሆነ የምግብ ችግር ሊጋለጡ ይችላሉ የተባሉት ከዚህ ቀደም የምግብ ችግር ኖሮባቸው በሴፍቲኔት መርሃ ግብር ሲደገፉ የነበሩ (917 ሺህ)፣ በግጭት የተፈናቀሉ (122 ሺ) ፣ በመኸር ዝናብ መጥፋት ምርት ያላገኙ (2.3 ሚሊዮን) ነዋሪዎች ናቸው።

በደቡብ ክልል የከፋ የምግብ እጦት ካለባቸው አካባቢዎች አንዱ የኮንሶ ዞን ህፃናት እና እናቶች ለከፋ ጉዳት መዳረጋቸውን ነዋሪዎች እየተናገሩ ነው።

በዞኑ አብዛኛው አካባቢዎች የእርዳታ አቅርቦት እየደረሰ እንዳለሆነ ነዋሪዎች ይገልፃሉ።

አንድ የኮልሜ ክላስተር ነዋሪ ፦

" ምንም አይነት እየመጣ አይደለም። ምንም አይነት ድጋፍ አላገኘንም። እኛ መጠበቅ ካለብን መንግሥት እንዲደርስልን ነው። ከሞት እንዲታደገን ነው። በገንዘብም ቢሆን መንግሥት እንዲረዳንና ከዚህ ዓመት ቢያሻግረን ብለን ነው የምንማፀነው። "

ሌላ ነዋሪ ፦

" አንደኛ ዝናብ ጠፋ ፣ በዛ ላይ የከብት ሳርም የለም። በመንግስት በኩል የሚደረግ እርዳታም የለም " ብለዋል።

የኮንሶ ዞን የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ ከፈኔ ቲጫኖ በዞኑ ካላት ተረጂዎች እስካሁን ድጋፍ ያገኙ ግማሽ እንኳን እንደማይሆኑ ተናግረዋል።

በተለይ ደግሞ ከሀምሌ ወር ጀምሮ የምግብ ድጋፍ ፈላጊው ሊጨምር እንደሚችል ገልፀዋል።

ያንብቡ : https://telegra.ph/SNNPRS-07-21

#ዶቼቨለ

@tikvahethiopia
#SNNPRS #GurageZone

" ሰዎች ለምን የክልልነት ጥያቄ ትደግፋላችሁ በሚል እየታሰሩ ናቸው " - ነዋሪዎች

" ህዝቦችን ለማጋጫት ስራ የሚሰሩ አካላት አሉ በዚህ ምክንያት የተለያዩ የስራ ኃላፊዎች ጭምር በቁጥጥር ስር ውለዋል " - የደቡብ ክልል ፖሊስ

በደቡብ ክልላዊ መንግስት ጉራጌ ዞን ከክልልነት ጥያቄ ጋር በተያያዘ በርካታ ሰዎች እየተሰሩ መሆናቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች በመግለፅ ላይ ይገኛሉ።

እየታሰሩ ከሚገኙት መካከል በዞኑ በኃላፊነት ቦታ ያሉ ጭምር መሆናቸው ተጠቁሟል።

ትላንት ምሽት ለቪኦኤ ሬድዮ ቃላቸውን የሰጡ አቶ በላቸው ገብረማርያን የተባሉ በግብርና ስራ የሚተዳደሩ የዞኑ ነዋሪ ካለፈው ቅዳሜ አንስቶ 13 ሰዎች እንደታሰሩ ከነዚህ ውስጥ ልጃቸውም እንደሙገኝበት ገልፀዋል። እሳቸውንም ፖሊስ እያፈላለገ መሆኑን አመልክተዋል።

እስሩ እየተካሄደ ያለው ለምን " የክልልነት ጥያቄ ትደግፋላችሁ " በሚል እንደሆነ አንዳችም ወንጀል እንዳልተፈፀመ ተናግረዋል።

አንድ የወልቂጤ ነዋሪ ደግሞ ወንድማቸው ለወቅታዊ ስበስባ ተብሎ ተጠርቶ መታሰሩን ገልፀዋል።

የደቡብ ክልል ፖሊስ የዞን ስራ ኃላፊዎች ጨምሮ ቁጥራቸው ያልተገለፀ ሰዎች መታሰራቸውን የደቡብ ክልል ፖሊስ አረጋግጧል።

የደቡብ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አለማየሁ ማሞ ለሬድዮ ጣቢያው ተከታዩን ቃል ሰጥተዋል ፦

" ... ማንም ሰው ዴሞክራሲያዊ ጥያቄ በአግባቡ በስርዓት መጠየቅ መነጋገር፣ መወያየት፣ መወሰን መብቱ ነው ነገር ግን ተቀጥረው ህዝቦችን ለማጋጫት ስራ የሚሰሩ አካላት አሉ በዚህ ምክንያት ነው የተለያዩ የስራ ኃላፊዎች ጭምር በቁጥጥር ስር የዋሉት። ምርመራ እየተጣራባቸው ነው። አሁን በአካባቢው የተለየ የፀጥታ ችግር የለም "

ያንብቡ : https://telegra.ph/VOA-08-24

@tikvahethiopia
#SNNPRS #SouthWestEthiopia

የ8ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ።

የደቡብ ክልል እና የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል የ8ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ይፋ መሆኑ ዛሬ ተገልጿል።

በሁለቱ ክልሎች ውሳኔ መሰረት የማለፊያ ነጥብ ፦

👉 ለወንዶች 41፣
👉 ለሴቶች 40 እና
👉 ለአይነ ስውራን 39 ሆኖ ተወስኗል።

በዚህ መሰረት ፦ በ2014 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በሁለቱም ክልሎች ለፈተና ከተቀመጡ ከ257 ሺህ በላይ ተማሪዎች 187 ሺህ 500 በላይ ተማሪዎች ወደቀጣይ ክፍል የሚያሳልፋቸውን ውጤት አምጥተዋል።

ለፈተና ከተቀመጠው አጠቃላይ ተማሪ ቁጥር ሲታይ ከ73 በመቶ በላይ ተማሪዎች አልፈዋል።

በተለየ መልኩ ከጸጥታ ጋር በተያያዘ በአሉታዊ ጫና ውስጥ ሆነው የተማሩና ለፈተና የተቀመጡ የደራሼ ልዩ ወረዳ ተማሪዎችን ውጤት በተለየ መልኩ ታይቷታ።

በዚህም መሰረት ፦

👉 ለወንዶች 39፣
👉 ለሴቶች 38 እና
👉 ለአይነ ስውራን 37 ሆኖ ተወስኗል።

የሁለቱ ክልሎች ተማሪዎች ውጤታቸውን ከነገ ጀምሮ መውሰድ ይችላሉ ተብሏል።

የደራሼ ልዩ ወረዳ ተማሪዎች ግን ውጤታቸው በእጅ የሚሰራ በመሆኑ የ1 ሳምንት ጊዜ ዘግይቶ ይደርሳል እስከዛው በትዕግስት እንዲጠባበቁ መልዕክት ተላልፏል።

#ENA

@tikvahethiopia
ሰሞነኛው ዝናብ ...

በተለያዩ የሀገራችን አካባቢዎች ከሰሞኑን እየጣለ ያለው ዝናብ በሰው ህይወት እና በንብረት ላይ ጉዳት እያደረሰ ይገኛል።

#SNNPRS

በደቡብ ክልል ፥ ጎፋ ዞን ዑባ-ደብረፀሃይ ወረዳ ዛባ ቀበሌ በጣለው ከባድ ዝናብ በተከሰተ የጎርፍ አደጋ 21 ሰዎች መሞታቸውን ለማወቅ ተችሏል። በንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ደርሷል።

በህይወት የተረፉ ዜጎ በትምህርት ቤቶች ውስጥ እንዲጠለሉ የተደረገ ሲሆን ለችግሩ ዘላቂ መፍትሄ ለማፈላለግ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ስራ መገባቱ ተሰምቷል።

ተጎጂ ወገኖችን ለመደገፍም በዞኑ የአደጋ ጊዜ ዝግጁነት ማቋቋሚያ የባንክ ሂሳብ ቁጥር 1000511561276 ላይ ድጋፍ እንዲደረግ ተጠይቋል።

#Amhara

በአማራ ክልል፣ ደቡብ ወሎ ዞን ለገሂዳ ወረዳ 02 አዋተል ቀበሌ ሚያዚያ 27/2015 ዓ.ም ምሽት ለተከታታይ 30 ደቂቃ የጣለው በረዶ የቀላቀለ ዝናብ በእንስሳት፣ በሰብልና በመኖሪያ ቤቶች ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሷል።

በረዶ ቀላቅሎ የጣለው ዝናብ ከ37 ሄክታር መሬት በላይ የደረሱ ሰብሎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱ ተነግሯል።

#Gambella

በጋምቤላ ክልል ፤ በዲማ ወረዳና አጎራባች ወረዳዎች ከሚያዝያ 25 /2015 ዓ.ም ጀምሮ እየጣለ ባለው ሃይለኛ ዝናብ ምክንያት በተከሰተው ጎርፍ በሚሊየን የሚገመት ንብረት ላይ ጉዳት ደርሷል።

የጎርፍ አደጋው እስካሁን ባለው መረጃ በወረዳው ከ70 በላይ መኖሪያ ቤቶች በውሃ ያጥለቀለቀ ሲሆን በሰብል ላይም ጉዳት አድርሷል።

ጎርፉ በዲማ ከተማ ወንዝ ዳር የነበረውን የከተማ ንፁህ መጠጥ ውሃ መሳቢያ ጀነሬተርና ፖምፕ ግንብ ቤቱን ጨምሮ በሚሊዮን በሚገመት ንብረት ላይ ጉዳት ማድረሱን ታውቋል።

በዚህም ችግር ሳቢያ የከተማው ንፁህ መጠጥ ውሃ አገልግሎት መቆሙ ተነግሯል።

በተመሳሳይ በዲፕ (መርከስ) ቀበሌ የሚገኘው የእኩጉ ስደተኞች መጠለያ ጣብያና የአካባቢው ማህበረሰብ የንፁህ መጠጥ ውሃ አገልግሎት የሚሰጡ ሁለት መሳቢያ ጀነሬተሮች በጎርፍ መወሰዱ ታውቋል።

ከዚህ በተጨማሪም የአኮቦ ወንዝ እስከጫፉ ድረስ በመሙላቱ ዲማ ወረዳን ጨምሮ ሁለት አጎራባች ወረዳዎች የሚያገናኝ የአኮቦ ብረት ድልድይ ላይ ጉዳት ደርሷል።

በደረሰው አደጋ ድጋፍ የሚያስፈልጋቸው ወገኖች ለማገዝ የክልሉ መንግሥትን ጨምሮ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች የበኩላቸውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ ቀርቧል።

መረጃ ምንጮች ፦ የጎፋ ዞን ፣ የለገሂዳ እና የዲማ ወረዳ ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ናቸው።

@tikvahethiopia