TIKVAH-ETHIOPIA
1.43M subscribers
55.4K photos
1.39K videos
199 files
3.72K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
በሩዋንዳው #ጄኖሳይድ ወቅት የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ምን አደረገ ? ከ800 ሺህ እስከ 1 ሚሊዮን የሚደርሱ ሰዎች ባለቁበት የሩዋንዳ የዘር ጭፍጨፋ ወቅት የዓለም መሪዎች ምንም እንኳን ስለ ዘር ጭፍጨፋው (ጄኖሳይድ) ቢያውቁም ጣልቃ አልገቡም ነበር። ለረጅም ጊዜ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ' ጄኖሳይድ ' የሚለውን ቃል ከመጠቀም ተቆጥቦ ነበር ፤ ይህም #በአሜሪካ ጫና እንደሆነ ይነገራል። አሜሪካም…
ሚዲያ የሩዋንዳውን የዘር ጭፍጨፋ (ጄኖሳይድ) እንዴት አቀጣጠለ ?

በ100 ቀናት ከ800,000 እስከ 1,000,000 ቱትሲዎችና ለዘብተኛ የሚባሉ ሁቱዎች ባለቁበት የሩዋንዳው የዘር ጭፍጨፋ/ጄኖሳይድ ሚዲያዎች ከፍተኛ ድርሻ ነበራቸው።

እንዴት ?

- ራዲዮ-ቴሌቭዥን ሊብሬስ ዴስ ሚልስ ኮሊንስ (RTML) እንዲሁም መንግታዊው ' ሬድዮ ሩዋንዳ ' በቱትሲዎች ላይ በመላ ሀገሪቱ ጥላቻ እንዲፈጠርና የሩዋንዳ ጄኖሳይድ እንዲፈፀም ዋና አቀጣጣይ ነበሩ።

- RTML ሚዲያ በወቅቱ በብዙ ወጣቶች ዘንድ ተደማጭነት የነበረው ነው። ጣቢያው በወጣቶች ዘንድ እጅግ የሚወደዱ ሙዚቃዎችን እያስተላለፈ #በመሃል ያቋርጠውና ቱትሲዎችን በመጥቀስ " እነዚያ ሰዎች እጅግ ቆሻሻ ቡድን ናቸው " የሚሉ አዋራጅና ቀስቃሽ መልዕክቶችን ያስተላልፋል። በስርጭቶቹ ውስጥ "#በረሮዎች" እና "#እባቦች" የሚሉ ቃላት በተደጋጋሚ ጥቅም ላይ ያውላል።

- RTML ሚያዚያ 6 /1994 ፕሬዜዳንት ጁቬናል ሃብያሪማና የነበሩበት አውሮፕላን ተመቶ ሲወድቅ በቅድሚያ ድርጊቱን የፈፀመው RPF ነው ብሎ የፈረጀ እና ንፁሃንን ለጭፍጨፋ ያመቻቸ ሚዲያ ነው።

- በጭፍጨፋው ወቅት ጨፍጫፊዎቹ በአንድ እጃቸው ሬድዮ በአንድ እጃቸው ደግሞ #ቆንጨራ ይዘው ነበር ሲንቀሳቀሱ የነበሩት። በዚህም ወቅት RTML እና ሬድዮ ሩዋንዳ ቱትሲዎች እና እነሱን የሚሸሽጉ ሁቱዎች እንዲገደሉ ያሉበትን አድራሻ ጭምር ሲገልጹ ነበር።

- ሚዲያዎቹ ጎረቤት በጎረቤቱ ላይ እንዲነሳ እና ቱትሲ የሚባሉትን በጠቅላላ እንዲያጠፏቸው ሲሰብኩ ነበር። በዚህም ብዙዎቹ ሁቱዎች የገዛ ጎረቤታቸውን አንዳንዶቹ ከቱትሲ ጋር የተዛመዱ #ዘመዶቻቸውን ጭምር ጨፍጭፈዋል።

- ሚዲያዎቹ የተለያዩ አነሳሽ ቃላቶች በመጠቀም ቱትሲዎች #እንዲጠሉ#እንዲገደሉ ሰዎችን ሲያበረታቱ ነበር። ትንንሽ ልጆች ፣ ታዳጊዎች ሳይቀሩ በራሳቸው ወገን #ጥላቻ እንዲሞሉ አድርገዋል።

- የሁቱ ሚዲያዎች በቀደመው ጊዜ #ቱትሲዎች ሀገሪቱ ውስጥ ትልቅ ስፍራ ይዘው በነበረበት ወቅት " በደል ፈፅመዋል " በማለትና " የሀገሪቱ ችግሮች እነሱናቸው እስከመጨረሻ ካልጠፉ በቀር ምንም መፍትሄ የለም " በማለት ሁቱዎችን ይቀሰቅሱ ነበር።

በነገራችን ላይ ከጭፍጨፋው ጅማሮ #በፊትም የሀገሪቱ መንግሥት ሚዲያዎችን በመጠቀም ሰፊ የሆነ የጥላቻ ፕሮፖጋዳንዳ ሲሰራ ቆይቷል።

በተለይ ቱትሲዎችን ከRPF ኃይል ጋር በማገናኘት ሁቱዎች ውስጣቸው በከፍተኛ ጥላቻ ታውሮ የገዛ ወገናቸውን እንዲጨፈጭፉ ሰርቷል።

አጠቃላይ በሰው ልጅ ታሪክ ውስጥ የታየ እጅግ  አስከፊው የዘር ጭፍጨፋ የአንድ ሌሊት ውጤት አልነበረም፤ በሂደት የመጣ እንጂ።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
Rwandan genocide
Apr 7, 1994 – Jul 15, 1994

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ከኢሰመኮ ሪፖርት ፦ " ሰኔ 7 ቀን 2014 ዓ.ም. ከቀኑ 7፡00 ሰዓት በኋላ እንዲሁም ሰኔ 8 እና 9 ቀን 2014 ዓ.ም. በዋናነት በክልሉ የጸጥታ ኃይሎች በተወሰዱ እርምጃዎች " የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች እና መሣሪያ በቤታችሁ እንዳለ ተጠቁመናል፤ የደበቃችሁትን መሣሪያ አውጡ " በሚል ምክንያት ሴቶችና የአእምሮ ሕመምተኞችን ጨምሮ ቢያንስ 50 ሲቪል ሰዎች በተናጠል እና በጅምላ ከፍርድ ውጪ መገደላቸውን፣…
#Gambella

ንፁሃንን " መረጃ ሰጥታችኋል " በሚል በአቃቂ ሁኔታ #እንዲገደሉ ትዕዛዝ አስተላልፈዋል ፤ ግድያው ላይም ተሳትፈዋል ከተባሉ ተከሳሾች ውስጥ የጋምቤላ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የቀድሞ ዋና ኮሚሽነር አቡላ ኦባንግ በተከሰሱበት ክስ #ነጻ መባላቸው ተሰምቷል።

ሌሎች የቀድሞ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን አመራሮች እና የልዩ ኃይል አዛዦችን ጨምሮ 12 ተከሳሾች ግን የጥፋተኝነት ፍርድ ተላልፎባቸዋል።

ብይኑን የሰጠው የፌደራሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ የሕገ-መንግሥት እና በሕገ-መንግሥት ሥርዓቱ ላይ የሚፈጸሙ የወንጀል ጉዳዮች የሚመለከተው ችሎት ነው። 

ክስ ቀርቦባቸው የነበሩት እነማን ናቸው ?

የጋምቤላ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የቀድሞው ዋና ኮሚሽነር አቡላ ኦባንግ፣
የቀድሞው ም/ኮሚሽነር ቱት ኮር፣
የክልሉ ልዩ ኃይል የቀድሞ ዋና አዛዥ ዋና ኢንስፔክተር ኮንግ ሬክ
የክልሉ ልዩ ኃይል የቀድሞው ምክትል አዛዥ ዋና ኢንስፔክተር ኡጀዲ ባሬ እና የተለያዩ የፀጥታ አባላትን ጨምሮ አጠቃላይ 15 ተከሳሾች ናቸው።

ተከሳሾቹን ላይ የቀረበው ክስ ምንድነው ?

ሰኔ 7/2014 ዓ/ም በጋምቤላ ከተማ መንግሥት በአሸባሪ ቡድንነት የፈረጀው " ሸኔ " እና የጋምቤላ ነጻ አውጪ ግንባር (ጋነግ) በጋራ ሆነው ቀበሌ 03 በፌደራል ፖሊስ ካንፕ እና በክልሉ ልዩ ኃይል እንዲሁም በሌሎች ፀጥታ አካላት ላይ ድንገተኛ ተኩስ ከፍተው ነበር።

በኃላም ጥቃት አድራሾቹም በፀጥታ ኃይሎች ወደ መጡበት እንዲመለሱ ተደርጓል።

ከዚህ ክስተት በኋላ ግን ማንነታቸው የተለዩ 35 ሰዎች እና ማንነታቸው ያልተለዩ ሌሎች ንፁሃንን " #መረጃ_ሰጥታችኋል " በሚል በአሰቃቂ ሁኔታ ሕይወታቸው እንዲያልፍ  ትዛዝ ሰጥተዋል ፤ በግድያው ላይ የተሳተፉም አሉ የሚል ነው።

የክስ መዝገቡ የተከሳሾች የተሳትፎ ደረጃቸውን በዝርዝር አስቀምጧል።

ፍርድ ቤት ምን ውሳኔ አሳለፈ ?

ከ15ኛው ተከሳሽ ውጭ ሌሎቹ በማረሚያ ቤት ሆነው ጉዳያቸውን ሲከታተሉ ቆይተዋል።

ግለሰቦቹ የእምነት ክህደት ቃላቸውን ሰጥተዋል።

ዐቃቤ ህግ ምስክሮቹን አሰምቷል። ማስረጃዎቹን አቅርቧል።

ፍርድ ቤት ፦
° የጋምቤላ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የቀድሞው ዋና ኮሚሽነር አቡላ ኦባንግ፣
° ቀድሞው ም/ኮሚሽነር ቱት ኮር
° የክልሉ ልዩ ኃይል የቀድሞው ዋና አዛዥ ዋና ኢንስፔክተር ኮንግ ሬክ
° የክልሉ ልዩ ኃይል የቀድሞ ምክትል አዛዥ ዋና ኢንስፔክተር ኡጀዲ ባሬን ጨምሮ 13 ተሳሾች በተከሰሱበት ድንጋጌ እንዲከላከሉ ብይን ሰጥቷል።

ዛሬ በዋለው ችሎት 12 ተከሳሾች የዐቃቤ ሕግ ማስረጃን በበቂ ሁኔታ መከላከል አለመቻላቸው ተጠቅሶ የጥፋተኝነት ፍርድ ተላልፎባቸዋል።

የጋምቤላ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የቀድሞው ዋና ኮሚሽነር አቡላ ኦባንግ የዐቃቤ ሕግ ማስረጃን በተገቢው መከላከላቸው ተጠቅሶ ነጻ ተብለዋል።

ፍርድ ቤት ጥፋተኛ የተባሉ ተከሳሾችንና የዐቃቤ ሕግን የቅጣት አስተያየት ለመጠባበቅ ለሐምሌ 10/2016 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።

ከዚህ ቀደም የጋምቤላ ክልል ልዩ ኃይል የቀድሞ አባል ኮ/ል አቶሬ ጉር እና የጋምቤላ ፖሊስ ኮሚሽን የቀድሞ አባል ረ/ሳጅን ቾድ ቤንግን በተመለከተ ፍ/ቤቱ በቀረበባቸው ክስ ላይ በቂ ማስረጃ አለመሰማቱን ተገልጾ በነጻ እንዲሰናበቱ ተደርጓል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከኤፍቢሲ ነው ያገኘው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Gambella ንፁሃንን " መረጃ ሰጥታችኋል " በሚል በአቃቂ ሁኔታ #እንዲገደሉ ትዕዛዝ አስተላልፈዋል ፤ ግድያው ላይም ተሳትፈዋል ከተባሉ ተከሳሾች ውስጥ የጋምቤላ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የቀድሞ ዋና ኮሚሽነር አቡላ ኦባንግ በተከሰሱበት ክስ #ነጻ መባላቸው ተሰምቷል። ሌሎች የቀድሞ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን አመራሮች እና የልዩ ኃይል አዛዦችን ጨምሮ 12 ተከሳሾች ግን የጥፋተኝነት ፍርድ ተላልፎባቸዋል። …
#EHRC #Gambella

“ ቪዲዮው የቆየ ነው ፤ ከሁለት ዓመት በፊት ነው ” - የኢሰመኮ ጋምቤላ ክልል ጽሕፈት ቤት

ባለፉት ሳምንታት ውስጥ አንድ እጅግ በጣም አሰቃቂ ቪድዮ በማህበራዊ ሚዲያዎች ሲዘዋወር ቆይቷል።

እውነት ለመናገር በቪድዮ ላይ የሚታየው የጭካኔ ተግባር በቃላት የሚገለጽ አይደለም።

ቪድዮው የጋምቤላ ክልል የጸጥታ ልብስ የለበሱ አካላት ሰዎችን እጅግ በአሰቃቂ ሁኔታ በድንጋይ ጭምር ጭንቅላታቸውን እየፈጠፈጡ በጅምላ ሲገድሏቸው የሚያሳይ ለማየት የሚከብድ ዘግናኝ ቪዲዮ ነው።

ይህን ቪዲዮ የተመለከቱ በርካቶች ፣ “ እውነት እኛ ሀገር ነው ? እኛ ሀገር ከሆነስ ለዚህ ተግባር ተጠያቂነት እና ፍትሕ ተረጋግጧል ? ” በማለት በእጅጉ አዝነው ጠይቀዋል።

አብዛኛዎቹ ሰዎችም ቪዲዮው ከሰሞኑን የተፈጸመ ጥቃት አድርገውም የወሰዱ ነበሩ።

ቲክቫህ ኢትዮጵያም ለጉዳዩ ቅርብ ናቸው ያላቸውን አካላት ስለቪድዮው ጠይቋል።

ይህንን ቪዲዮ ኮሚሽናችሁ ተመልክቶት ነበር ? በማለት የጠየቃቸው የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ጋምቤላ ክልል ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አቤል አዳነ፣ “ ቪዲዮው የቆየ ቪዲዮ ነው። ከሁለት ዓመታት በፊት የነበረ ቪዲዮ ነው ” ብለዋል።

ሰኔ 7 / 2014 ዓ/ም “ የሸኔና ጋነግ ” ታጣቂዎች በጋምቤላ ክልል ገብተው ጥቃት እንደፈጸሙ አስታውሰዋል።

በኋላ “ የክልሉ ልዩ ኃይሎች ‘ ኦነግ ሸኔ ቀርተዋል ’ ብለው የጠረጠሯቸውን ሰዎች በየቤታቸው እየሄዱ፣ እዛው ፓሊስ ኮሚሽን አካባቢ ወስደው ግድያ ፈጽመውባቸዋል ” ነው ያሉት።

“ ይህንን ቪዲዮ ጨምረን ሌሎችንም ምርመራ አድርገን የምርመራውን ሪፓርት ይፋ አድርገናል በሰዓቱ ” ብለዋል።

የኮሚሽኑ አስተያዬት የተካተተበትን ሪፓርትም ልከዋል። 

ግድያውን የፈጸሙት አካላት በሕግ ፊት ተጠያቂ ተደርገው ይሆን ? በማለት ላቀረብንላቸው ጥያቄ “ በዚህ ጉዳይ ላይ ተጠርጥረው የታሰሩ ሰዎች አሉ ” ብለዋል።

ከፌደራል ፓሊስ ፣ ከፍትህ ሚኒስቴር የተውጣጣ አጣሪ መርማሪ ቡድንም ጋምቤላ መጥቶ ጉዳዩን እንደመረማረና ‘በጉዳዩ ላይ ተጠይቂ ናቸው’ ብሎ የሚያስባቸውን ሁሉ በህግ ቁጥጥር ስር እንዲውሉ ተደርጎ የፍርድ ሂደታቸው እየተካሄደ መሆኑን አስረድተዋል።

ከነዚህም ውስጥ በወቅቱ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር የነበሩትና ምክትላቸውን ጨምሮ ሌሎችም እንዳሉበት አክለዋል።

ትላንትና ከሰኔ 7 ቀን 2014 የጋምቤላ ክስተት ጋር በተያያዘ ንፁሃንን " መረጃ ሰጥታችኋል " በሚል በአቃቂ ሁኔታ #እንዲገደሉ ትዕዛዝ አስተላልፈዋል ፤ ግድያው ላይም ተሳትፈዋል የተባሉ ፦
➡️ የጋምቤላ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የቀድሞ አመራሮች ፣
➡️ የልዩ ኃይል አዛዦች (ዋናውና ምክትሉ)
➡️ የተለያዩ የጸጥታ አባላት
የጥፋተኝነት ፍርድ እንደተላለፈባቸው ፤ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን የቀድሞ ዋና ኮሚሽነር አቡላ ኦባንግ ግን በተከሰሱበት ክስ #ነጻ መባላቸው ይታወሳል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia