TIKVAH-ETHIOPIA
1.39M subscribers
54.7K photos
1.37K videos
198 files
3.64K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia - የፀጥት ችግር እና ግጭት - አንበጣ መንጋ ጉዳት - የኮሮና ቫይረስ ተፅእኖ - የትግራይ ክልል ችግር ተደማምረው ኢትዮጵያ ውስጥ ከ12.5 ሚሊዮን በላይ ታዳጊዎች እና ህፃናት የአስቸኳይ ጊዜ እርዳታ ፈላጊዎች እንዳደረጋቸው ተገለፀ። ይህን የገለፁት UNICEF የኢትዮጵያ ቢሮ እና የስውዲን ኤምባሲ ዛሬ በጋራ በሰጡት መግለጫ ነው። መግለጫው ትኩረቱን ያደረገው በኢትዮጵያ ውስጥ ስላለው…
ቁጥራዊ መረጃ #ኢትዮጵያ

ከUNICEF እና ከስውዲን ኤምባሲ መግለጫ :

- 23.5 ሚሊዮን በተያዘው ዩፈረንጆች ዓመት #ሰብዓዊ_እርዳታ የሚፈልጉ ኢትዮጵያውያን ቁጥር (በረብሻ እና ግጭት፣ አንበጣ መንጋ፣ በኮቪድ-19 ወረርሽኝ፣ የትግራይ ጦርነት ተዳምሮ)

- ከ23.5 ሚሊዮን መካከል 12.5 ታዳጊዎች እና ህፃናት እርዳታ ፈላጊ ናቸው።

- ከ700 ሺህ በላይ ህፃናት እና ታዳጊዎች በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ከመኖሪያ ቀያቸው የተፈናቀሉ።

- 6 ሺህ ህፃናት በትግራይ ጦርነት ምክንያት ከቤተሰቦቻቸው ጋር የተለያዩ እና መገናኘት ያልቻሉ (እስካሁን ባለው ብቻ)

- 192.7 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር እስከ አመቱ መጨረሻ በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች ያለውን ችግር ለመደገፍ UNICEF የሚያስፈልገው ተጨማሪ ገንዘብ።

- 70 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ፥ ከእአአ 2011 አንስቶ ስውዲን በUNICEF በኩል በኢትዮጵያ ለሚሰራው ስራ ያደረገችው ድጋፍ።

- 350 ሺህ ትግራይ ውስጥ ለረሃብ ፣ የከፋ ችግር ተጋልጠዋል የተባሉ ሰዎች ቁጥር።

@tikvahethiopia
#Humanity❤️

ይህ የሆነው በአሜሪካ ሀገር ሚኒሶታ ነው።

በሚኒሶታ በሚገኝ #ፈጣን_መንገድ ላይ አንድ አሽከርካሪ መንገድ ስቶ ወጥቶ ከመብራት ፖል ጋር ተጋጭቶ እዛው መኪና ውስጥ እያለ መኪናው በከፍተኛ እሳት መያያዝና መንደድ ይጀምራል።

በመንገዱ ሲጓዙ የነበሩ አሽከርካሪዎች ይህን አይተው አላለፉም።

መኪናቸውን አቁመው ከሚነደው መኪና ውስጥ አሽከርካሪውን ለማውጣትና ለማዳን ርብርብ ጀመሩ።

ከእሳት ነበልባል ጋር #እየታገሉ ፤ በሹፌሩ በር በኩል ያለውን መስታወት ሰብረው ከብዙ እልህ አስጨራሽ ትግል በኃላ አሽከርካሪውን በእሳት ተያይዞ ከሚነደው መኪና ውስጥ በህይወት አወጡት።

በኃላም ወደ ሆስፒታል እንዲወሰድ አደረጉ።

አሽከርካሪው ላይ ምንም አይነት የከፋ ጉዳት አልደረሰበትም ተብሏል።

ከከፍተኛ እሳት ጋር ተጋፍጠው የሰው ህይወት ለማትረፍ ርብርብ ሲያደርጉ ከነበሩት አንዱ ከድር ቶላ ይባላል። (ጥቁር ጁንስ ሱሪ በነጭ ጫማ ያደረገው)

ወደ ስራ እየሄደ በነበረበት ሰዓት ነው ይህ ክስተት ያጋጠመው።

ከድር የነፍስ አድን ስራውን ፥ " በህይወቴ እጅግ በጣም አስፈሪው ቅጽበት ነበር። ይህንን መቼም ቢሆን አልረሳውም ሁሌም ቢሆን አስታውሰዋለሁ " ሲል አስረድቷል።

አሽከርካሪው በህይወት እንዲተርፍ ቦታው ላይ የነበሩ ሁሉም ሰዎች ላደረጉት ፍጹም #ሰብዓዊ ተግባርና ርብርብ ፈጣሪን አመስግኗል።

የነበረውን የህይወት አድን ርብርብ የሚያሳይ ቪድዮ ከድር ቶላ መኪና ላይ በነበረ የዳሽቦርድ ካሜራ የተቀረጸ ነው።

Video Credit : Kadir Tolla / ከድር ቶላ

#TikvahFamily

@tikvahethiopia