TIKVAH-ETHIOPIA
1.5M subscribers
56.7K photos
1.41K videos
203 files
3.87K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia - የፀጥት ችግር እና ግጭት - አንበጣ መንጋ ጉዳት - የኮሮና ቫይረስ ተፅእኖ - የትግራይ ክልል ችግር ተደማምረው ኢትዮጵያ ውስጥ ከ12.5 ሚሊዮን በላይ ታዳጊዎች እና ህፃናት የአስቸኳይ ጊዜ እርዳታ ፈላጊዎች እንዳደረጋቸው ተገለፀ። ይህን የገለፁት UNICEF የኢትዮጵያ ቢሮ እና የስውዲን ኤምባሲ ዛሬ በጋራ በሰጡት መግለጫ ነው። መግለጫው ትኩረቱን ያደረገው በኢትዮጵያ ውስጥ ስላለው…
ቁጥራዊ መረጃ #ኢትዮጵያ

ከUNICEF እና ከስውዲን ኤምባሲ መግለጫ :

- 23.5 ሚሊዮን በተያዘው ዩፈረንጆች ዓመት #ሰብዓዊ_እርዳታ የሚፈልጉ ኢትዮጵያውያን ቁጥር (በረብሻ እና ግጭት፣ አንበጣ መንጋ፣ በኮቪድ-19 ወረርሽኝ፣ የትግራይ ጦርነት ተዳምሮ)

- ከ23.5 ሚሊዮን መካከል 12.5 ታዳጊዎች እና ህፃናት እርዳታ ፈላጊ ናቸው።

- ከ700 ሺህ በላይ ህፃናት እና ታዳጊዎች በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ከመኖሪያ ቀያቸው የተፈናቀሉ።

- 6 ሺህ ህፃናት በትግራይ ጦርነት ምክንያት ከቤተሰቦቻቸው ጋር የተለያዩ እና መገናኘት ያልቻሉ (እስካሁን ባለው ብቻ)

- 192.7 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር እስከ አመቱ መጨረሻ በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች ያለውን ችግር ለመደገፍ UNICEF የሚያስፈልገው ተጨማሪ ገንዘብ።

- 70 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ፥ ከእአአ 2011 አንስቶ ስውዲን በUNICEF በኩል በኢትዮጵያ ለሚሰራው ስራ ያደረገችው ድጋፍ።

- 350 ሺህ ትግራይ ውስጥ ለረሃብ ፣ የከፋ ችግር ተጋልጠዋል የተባሉ ሰዎች ቁጥር።

@tikvahethiopia