TIKVAH-ETHIOPIA
1.39M subscribers
54.7K photos
1.37K videos
198 files
3.64K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
" 53 በመቶ የሚሆኑት ኢትዮጵያውያን አዲስ አበባን የፌደሬሽን ምክር ቤት አባል ለማድረግ በአብላጫነት ይደግፋሉ " - የአፍሮባሮሜትር ጥናት

(በኢዮብ ትኩዬ)

66 በመቶ ኢትዮጵያውያን የጠቅላይ ሚኒስትር የሥልጣን ዘመን እንዲገደብ እንደሚሹ መመላከቱን ቲክቫህ ኢትዮጵያ #አፍሮባሮሜትር ይፋ ካደረገው ጥናት ተረድቷል።

የዳሰሳ ጥናቱ ከላይ ከተጠቀሰው የገደብ ፍላጎት በተጨማሪ 67 በመቶ ኢትዮጵያውያን የሕገ መንግሥቱን መሻሻል እንደሚፈልጉ፣ ነገር ግን የራስን ዕድል በራስ የመወሰንና በባንዲራው ያለውን አርማ በተመለከተ የሕዝቡ አስተያየት እንደተከፋፈለ ያስረዳል።

በጥናቱ ቁልፍ ግኝቶች መሠረት፦

- 67 በመቶ ኢትዮጵያውያን የሕገ መንግሥቱን መሻሻል የሚደግፉ፣ 16 በመቶዎቹ  ሕገ መንግሥቱ  ሙሉ ለሙሉ እንዲወገድ፣ እንዲሁም ቀሪዎቹ 16 በመቶዎቹ ደግሞ አሁን ባለበት እንዲቀጥል የሚፈልጉ ናቸው።

- በ2012 ዓ.ም ከተካሄደው የአፍሮባሮሜትር ዳሰሳ ጥናት አንጻር፣ በዚህ ጥናት ሕገ መንግሥቱ እንዲቀየር የደገፉ በአምስት በመቶ ብልጫ አላቸው። 

ይህንኑን ብልጫ በተመለከተ የተቀመጠውና ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተው የጥናቱ ግራፋዊ መግለጫ፣ በ2020 69 በመቶቹ፣ በ2023 67 በመቶ የሚሆኑት ዜጎች ሕገ መንግሥቱ መሻሻል እንዳለበት፣ በ2020 18 በመቶ፣ በ2023 16 በመቶዎቹ ዜጎች ሕገ መንግሥቱ ባለበት እንዲቀጥል እንዲሁም በ2020 11 በመቶ፣ በ2030 16 በመቶዎቹ ዜጎች ደግሞ ሕገ መንግሥቱ በአዲስ ይቀየር ብለው እንደሚስማሙ ያስረዳል።

- የተጠቆሙ የሕገ መንንግሥት ማሻሻያዎችን በተመለከተ፣ 67 በመቶ የሚሆኑት ኢትዮጵያዊያን ከአማርኛ በተጨማሪ ሌሎች የሥራ ቋንቋዎችን ለፌደራል መንግሥት እንዲደረግ፣ 66 በመቶዎቹ የጠቅላላ ሚኒስትር የሥልጣን ዘመን እንዲገደብ እንዲሁም በ2012 ዓ.ም 35 በመቶ፣ በአሁኑ ጥናት ደግሞ 53 በመቶ የሚሆኑት ኢትዮጵያውያን አዲስ አበባን የፌደሬሽን ምክር ቤት አባል ለማድረግ በአብላጫ ይደግፋሉ።

በዚህም 67 በመቶ የሚሆኑት ዜጎች ተጨማሪ የሥራ ቋንቋዎች ለሕገ መንግሥቱ እንደሚያስፈልግ፣ 30 በመቶ የሚሆኑት አያስፈልግም ብለው እንደሚቃወሙ እንዲሁም 4 በመቶ የሚሆኑት ደግሞ ከመቃወሙም ከመደገፉም እንዳልሆኑ የጥናቱ ገላጭ ግራፍ ያስገነዝባል።

ገላጭ ግራፉ አክሎም፣ 66 በመቶ የሚሆኑ ዜጎች የጠቅላይ ሚኒስትር የሥልጣን ገደብ እንዲደረግ፣ 27 በመቶዎቹ ደግሞ መገደቡን እንደሚቃወሙ እንዲሁም 7 በመቶ የሚሆኑት ከመደገፉም ከመቃወሙም እንዳልሆኑ ያሳያል።

በተጨማሪም 54 በመቶ የሚሆኑት ዜጎች አዲስ አበባን የፌደሬሽኑ አባል ማድረግን እንደደሚደግፉ፣ 34 በመቶዎቹ እንደሚቃወሙ፣ 12 በመቶዎቹ ደግሞ ከመቃወሙም ከመደገፉም እንዳልሆኑ በግራፍ ተቀምጧል።

እንዲሁም፣ 46 በመቶ የሚሆኑት ዜጎች የራስን ዕድል በራስ የመወሰን አንቀጽ 39ኝን ለማስወገድ እንደሚደግፉ፣ 47 በመቶዎቹ እንደሚቃወሙ፣ 7 በመቶዎቹ ደግሞ ከመቃወሙም ሆነ ከመደገፉ ጎራ እንዳልሆኑ ተመላክቷል።

በተጨማሪም፣ 29 በመቶ የሚሆኑ ዜጎች በባንዲራ መሀል ላይ ያለውን ብሔራዊ አርማ ማስወገድን እንደሚደግፉ፣ 62 በመቶዎቹ እንደሚቃወሙ እንዲሁም 9 በመቶዎቹ ደግሞ ከመደገፉም ከመቃወሙም ጎራ እንዳልሆኑ የጥናቱ ግራፍ ያስረዳል።

ጥናቱ የተካሄደው በ2,400 ቃለ መጠይቆች፣ ዕድሚያቸው 18 ከዚያ በላይ የሆኑ ኢትዮጵያውያንን በማሳትፍ እንደሆነ፣ ከግንቦት 17 እስከ ሰኔ 15 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ መረጃው እንደተሰባሰበ፣ የናሙናው መጠን በአገር አቀፍ ደረጃ የተሰራና የስህተት ኅዳጉ +/-2 በመቶ፣ የአስተማማኝነት ደረጃው 95 በመቶ እንደሆነ ተመላክቷል።

#ቲክቫህኢትዮጵያ

@tikvahethiopia
' ቤቲንግ ' ሊታገድ ነው ?

ከሰሞኑን በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ " ቤቲንግ " ሊታገድ መሆኑን የሚገልፁ በትክክል ምንጫቸው ያልተገለፁ ፅሁፎች ሲሰራጩ ተስተውሏል።

ብሄራዊ ሎተሪ አስተዳደር ግን እየተሰራጩ ያሉት መልዕክቶች ፍፁም ስህተት ናቸው ብሏል በማህበራዊ ትስስር ገፁ ዛሬ ባወጣው ማሳሰቢያ።

" ' አንዳንድ ግለሰቦች በማህበራዊ ሚዲያ ቤቲንግ ሊዘጋ ነው ' በማለት የሚያሰራጩት መልእክት ፍጹም ስህተት መሆኑን እንገልፃለን " ያለው አስተዳደሩ " የስፖርት ውርርድ ጨዋታዎችም ሆነ  ሎተሪን   በተመለከተ ማንኛውም መረጃ ከብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር ብቻ ማግኘት እንደሚገባ አመልክቷል።

ከዚህ ቀደም ከ ' ቤቲንግ / ስፖርታዊ ውርርድ / ' ጋር በተያያዘ ፤ የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር #እንዲታገድ እየሰራ መሆኑን አሳውቆ እንደነበር ይታወሳል።

ሚኒስቴር መ/ቤቱ  ፤ ከታዲጊዎች እና ወጣቶች ስብዕና ግንባታ እንዲሁም በተለያየ መንገድ ከሚያስከትላቸው ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ቀውሶች አንጻር ነው ዘርፉ #ሊታገድ ይገባል በሚል እየሰራ እንደሆነ አሳውቆ የነበረው።

የስፖርት ውርርድ ' ቁማር ነው ' ብሎ የሚያምነው ይኸው የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር መ/ቤት ፤ በተለያየ ጊዜ ሰርቻቸዋለሁ ባላቸው የዳሰሳ ጥናቶች ቤቲንግ ለወጣቱና ለታዳጊው ዘርፈ ብዙ አደጋ የደቀነ መሆኑን አመላካች መሆኑን ፤ ቁማር ታዳጊዎችን ይሁን አዋቂ ሰዎችን ወዳልተፈለገ መንገድ ሊወስድ የሚችል ማህበራዊ ቀውስ እንደሆነና ማንኛውም ሰው ሰርቶ የመለወጥ እሳቤውን የሚያቀጭጭ፣ ቤተሰብን ጭምር ወደ መበተን ሊያደርስ የሚችል ጉዳይ መሆኑን አስገንዝቦ ነበር።

ወጣቶች እና ታዲጊዎች ለቤቲንግ ውርርድ ሲሉ ያላቸውን ነገር በሙሉ እስከማውጣት ይደርሳሉ ፤ ወጣቶች ስራን ከመስራት ይልቅ በአቋራጭ መክበር እንዲያስቡ በማድረግ ምርት እና ምርታማነትን የሚቀንስ ተግባር ነው የሚልው መ/ቤቱ ቤቲንግ እንዲታገድ ፍቃድ ለሚሰጡት የንግድ ሚኒስቴር እና የብሄራዊ ሎተሪ አስተዳደር ተቋማት አስፈላጊውን የግንዛቤ እና የማሳወቅ ስራ ቢሰራም ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን አስተዋፅኦ ባለማድረጋቸው ለውሳኔው መዘግየት ዋነኛ ምክንያት መሆኑን ገልጾ ነበር።

የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ቤቲንግ እንዲታገድ ብርቱ እንቅስቃሴ ማድረግ መጀመሩን ካሳወቀ ወራት ቢቆጠርም እስካሁን በጉዳዩ ላይ አዲስ ነገር የለም።

የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር ግን በ ' ቤቲንግ ' ኮሚሽን (15%) በሚሊዮን የሚቆጠር ብር ያስገኛል (ለሀገር) ፣ በርካታ ሰው በተለይ ሴቶችን ቀጥሯል ፣ ለማህበራዊ ጉዳይ ከገቢው ያውላል ፣ ቤት ይከራያል ፣ ገንዘብ ኢኮኖሚ ውስጥ እንዲንቀሳቀስ ያደርጋል ... ይህ ሁሉ ጥቅሞቹ ናቸው ብሎ ያምናል።

" ቤቲንግ " አትራፊ እንደሆነ የሚገልጸው አስተዳደሩ " ጨዋታ " እንጂ " ቁማር " አይደለም ብሎ ያምናል። በስርዓት እንዲመራም መመሪያዎችን አውጥቶ እየሰራ እንደሆነና " እኛ ጨዋታውን አቅርበናል ፤ ተጫዋቹ ደግሞ በኃላፊነት መጫወት አለበት " ባይ ነው።

ማህበራዊ ቀውስ ያመጣ እንደሆነ ኃላፊነት ያለባቸው አካላት አጥንተው ከጉዳቱ ጥቅሙ ያመዝናል በሚል ከሚታገድ በህግ እንዲመራና የማይገባቸው ሰዎች እንዳይጫወቱ ክትትል  ቢደረግ የተሻለ መሆኑ ታምኖበት እየተሰራ እንደሆነ በከወራት በፊት ገልጿል።

ከሰሞኑን በማህበራዊ ሚዲያ ላይ " ከጥር 3 ጀምሮ ቤቲንግ ይታገዳል " የሚሉ ምንጫቸው ያልተረጋገጠ መረጃዎች በስፋት ሲሰራጩ የነበረ ሲሆን የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር ይህ ፍፁም የተሳሳተ ነው ፤ ማንኛውም ቤቲንግ / የስፖርት ውርርድ ነክ መረጃ የሚገኘው ከኔው ነው እንጂ ከሌላ አይደለም ሲል አስገንዝቧል።

#ቲክቫህኢትዮጵያ

@tikvahethiopia
" ኢትዮጵያ የ ' ብሪክስ ' ቡድንን የተቀላቀለችው በዋናነት በወቅታዊ የፖለቲካና ኢኮኖሚያዊ ማዕቀቦች ጫና ነው " - የኢትዮጵያ ኢኮኖሚክስ ማህበር የባለሙያዎች ዳሰሳ

ከ5 ሺህ 500 በላይ የኢኮኖሚ ባለሙያዎችን ያቀፈው የኢትዮጵያ ኢኮኖሚክስ ማህበር ‘ የኢትዮጵያ ብሪክስ ቡድንን መቀላቀል ጥቅም እና ስጋት ’ን የፈተሸ የባለሙያዎች ዳሰሳ አድርጎ በዋና መስሪያ ቤቱ ይፋ አድርጓል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በአካል ተገኝቶ በተከታተለው በዚህ ዳሰሳ የማህበሩ የምርምርና ፖሊሲ ትንተና ዳይሬክተር ደግዬ ጎሹ (ዶ/ር)፤ " በዳሰሳው 233 የኢኮኖሚ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል " ብለዋል።

የግኝቱ ዋነኛ ነጥቦች ፦

- ከተሳታፊዎች መካከል :

* 49% የሚሆኑ ባለሙያዎች ኢትዮጵያ የብሪክስ ቡድንን የተቀላቀለችው በፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ማዕቀቦች ተገፍታ ነው ብለዋል።

* 47% የሚሆኑት አዳጊ ኢኮኖሚ ስላላት ነው ብለዋል።

* 45.5% የጂኦፖለቲካዊ ምክንያቶችን አንስተዋል።

* 41% እና 39% እንደቅደም ተከተላቸው ከምዕራባውያን ጋር የግንኙነት መሻከር እና የውጭ ምንዛሪ እጥረትን በገፊ ምክንያትነት ጠቅሰዋል።

" ይሄ ትንሽ ተቃርኖ አለው። መንግስት የሚለው በራሳችን በጎ ተግባሯ (merits) ነው ይላል፤ ያመለከተችው በተፅዕኖዎቹ ነው፤ ለምን እንደተቀበሏት አይታወቅም። በእርግጥ ብሪክስ የተቀበላቸው ሀገራት በምን መስፈርት እንደገቡ ማንም አያውቀም " ሲሉ ዶ/ር ደግዬ ግኝቱን አስረድተዋል።

- ከተሳታፊ ባለሙያዎች ውስጥ ኢትዮጵያ ብሪክስን በመቀላቀሏ ከጉዳቱ ጥቅሙ ያመዝናል ያሉት 51% ሲሆኑ 25% የሚሆኑት በተቃራኒው እንደሚሆን ገምተዋል።

- #ዶላርን ከግብይት ስርዓት ውጪ ለማድረግ ስለተያዘው የብሪክስ ዕቅድ በተመለከተ ይሳካል የሚሉት ብዙኀኑ ቢሆኑም ይህ እንዲሳካ እስከ 15 ዓመታት ይፈጃል ያሉት 67% ናቸው።

ዳሰሳው ሌላኛው የተመለከተው ጉዳይ ኢትዮጵያ ብሪክስን በመቀላቀሏ ከምዕራባውያን ወገኖች ስለምታጣቸው ጥቅሞች እና ስለሚኖሩት ጫናዎች ነው።

በዚህም፦

* ብድር እና ድጋፎችን ለማግኘት ትቸገራለች ወይም ትከለከላለች የሚሉ ባለሙያዎች 56% ናቸው።

* 43% የሚሆኑት በሂደት ላይ ለሚገኙ ፕሮጀክቶች ገንዘብ ለማሰራጨት ትቸገራለች ብለዋል።

* 40% የሚሆኑት የብር የመግዛት አቅም እንዲዳከም ግፊት ይደረግባታል ብለዋል።

- ጫናዎችን በተመለከተ 66% የሚሆኑት ከምዕራባውያን ዘርፈ ብዙ ጫናዎችን ሲገምቱ፣ በአባላቱ መካከል የእርስ በእርስ የፖለቲካ ፍላጎት ግጭቶች እንዲሁም የብሪክስ ልማት ባንክ የሆነው " ኒው ዲቨሎፕመንት ባንክ " አቅም ውስንነት በተከታይነት ስጋቶች ሆነው ተቀምጠዋል።

የባለሙያዎች ዳሰሳው ያስቀመጣቸው ምክረ ሃሳቦች ፦

የኢኮኖሚ ባለሙያዎቹ ኢትዮጵያ በምዕራባውያን ቁጥጥር ስር ከሚገኙት ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት እንዲሁም ከብሪክስ ጋር መስራት ግዴታዋ እንደሆነ ገልፀው፤ ለረጅም ዓመታት ከምዕራባውያን ጋር ከነበራት ትስስር አሁን እንደተፃራሪ ወደሚታየው ብሪክስ ቡድን ስትገባ የሁለቱን አሰላለፍ ጥቅምና ጉዳት በትኩረት ለይቶ መንቀሳቀስ ትኩረት እንደሚፈልግ ተገልጿል።

እስከዛሬ ከምዕራባውያን የሚገኙ ጥቅሞችን ማካካስ ካልቻለ ተግዳሮቱ ይበዛል። የዶላርን የበላይነት መቀነስና ለንግድ የራሳቸውን ኖቶች መጠቀም የሚለውም ለኢትዮጵያ የውጭ ምንዛሪ እጥረት የባሰ ራስምታት ስለሚሆን ከአባል ሀገራቱ የሚኖረውን አንድነትና ልዩነት በአግባቡ መፈተሽ ይገባል።

ባለሙያዎች በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አስተማማኝነት ላይ ጥያቄ ያነሱ ሲሆን ከብሪክስ አባል ሀገራት ጋር የሚያሰራ የፋይናንስ ስርዓት ለመፍጠር መልሶ ማደራጀት ይፈልጋል ብለዋል።

#ቲክቫህኢትዮጵያ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የሶማሊያ ካቢኔ በነገው ዕለት አስቸኳይ ስብሰባ እንደተጠራ ተሰምቷል። አስቸኳይ ስብሰባው ፤ ዛሬ በሶማሌላንድ (ሶማሊያ ሶማሌላንድን እንደ ሰሜናዊ ክልሏ ነው የምትቆጥራት) እና በኢትዮጵያ መካከል ተደርጓል ስለተባለው ስምምነት በተመለከተ ተወያይቶ ውሳኔ ለማሳለፍ ነው ተብሏል። ከዚሁ ከነገው አስቸኳይ የካቢኔ ስብሰባ ዝግጅት ጋር በተያያዘ #በአሁን_ሰዓት በሶማሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት…
#Ethiopia 🤝 #Somaliland

" ታሪክ እየተሰራ ነው " - አሊ ሀሰን ሞሃመድ

ኢትዮጵያ እስካሁን በይፋ ከሶማሌላንድ ጋር በተፈረመው የትብብር ስምምነት የባህር በር ለመጠቀም እና የባህር ኃይል ቤዝ እንዲኖራት በምላሹ ደግሞ የ " ሶማሌላንድን " የነፃ ሀገርነት እውቅና እንደምትሰጥ አንዲትም ቃል #አልተናገረችም

የሶማሌላንዱ ፕሬዜዳንት ግን ከስምምነቱ በኃላ ኢትዮጵያ ለሶማሌላንድ የነፃ ሀገርነት ውቅና እንደምትሰጥ በምላሹ የባህር በር እና የባህር ኃይል እንዲኖራት 20 ኪሎሜትር መሬት በሊዝ እንደምትሰጥ ገልጸዋል።

የራስ ገዟ ሶማሌላንድ ባለስልጣናትም ተመሳሳይ መረጃዎችን ሰጥተዋል።

ለአብነት አሊ ሀሰን ሞሃመድ የኢንፎርሜሽን ሚኒስትር ፤ " ታሪክ እየተሰራ ነው " ብለዋል።

ኢትዮጵያ በሊዝ የ20 ኪሎሜትር የባህር በር ተጠቃሚ እንድትሆን በምላሹ ደግሞ #እውቅና እና የኢኮኖሚ እድገት እንደምትሰጥ ገልጸዋል።

" ይህ ጨዋታ ቀያሪ፤ ትልቅ ትርጉም ያለው ስምምነት ነው " ያሉት ባለስልጣኑ " ትልቅና ደፍረትን የሚጠይቅ እርምጃ ነው ፤ ወደፊት ለሶማሌላንድ እና ኢትዮጵያ የብሩህ አድማስ በሮችን የሚከፍት ነው " ብለዋል።

ይህንኑ የአሊ ሀሰን ሞሀመድ ሃሳብን ሞባረክ ታኒ የተባሉት የፕሬዜዳንቱ ዋና ፀሐፊ ተጋርተውታል።

በሌላ በኩል ፤ ሶማሊያ እንደራሷ አንድ ግዛት የምታያት " ሶማሌላንድ " ከኢትዮጵያ ጋር ተፈራረመች ስለተባለው የመግባቢያ ስምምነት በተመለከተ ነገ ካቢኔዎቿ አስቸኳይ ስብሰባ ተቀምጠው ውሳኔ ያሳልፋሉ ተብሏል።

ለነገው አስቸኳይ ስብሰባ ዝግጅት ዛሬ ምሽት በጠቅላይ ሚኒስትሩ ቢሮ ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ምክትላቸው እና ከፍተኛ የካቢኔ አባላት የተገኙበት ሰብሰባ ሲደረግ አምሽቷል።

የሶማሊያ ባለስልጣናትም የመግባቢያ ስምምነቱ ክፉኛ እንዳስቆጣቸው ተነግሯል።

የሶማሊያ የማዕድን እና ነዳጅ ሚኒስትሩ አብዲሪዛቅ ሞሀመድ ፤ " ሶማሊያ አትከፋፈልም ፤ በሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነታችን አንደራደርም " ብለዋል።

ሚኒስትሩ ፤ " ኢትዮጵያ ከግዛት (ክልል) አስታዳዳሪ ጋር ወደብን ለመከራየት / ወታደራዊ ስምምነት (MOU) ማድረግ እንደማትችል በደንብ አድርጋ ታውቃለች ይህ ስልጣን ሙሉ በሙሉ የፌዴራላዊ ሶማሊያ መንግሥት ነው ፤ ኢትዮጵያ የግዛት አንድነታችንን የሚጥስ ተግባር መፈፀም አትችልም " ሲሉ ገልጸዋል።

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የዛሬውን " ታሪካዊ " የተባለ የትብብር ስምምነት መፈረሙን ተከትሎ " ኢትዮጵያ #ቀይ_ባህርን የመጠቀምና በዛውም የማልማት ፍላጎት ከሶማሌላንድ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈርሟል " ሲሉ አብስረዋል።

ዶክተር ዐቢይ፤ " እኛ ያሉንን ሃብቶች የመጋራት ፣ የመካፈልና በጋራ የመልማት ፍላጎት እንጂ ማንንም በኃይል የማስገደድ ፍላጎት የለንም ስንል የነበረው ሃሳብ በተግባር ታይቷል " ሲሉም ነው ያሳውቁት።

#ቲክቫህኢትዮጵያ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የሶማሊላንድ ካቢኔ አስቸኳይ ስብሰባ ተጠራ። የራስ ገዟ ሶማሊላንድ ምክትል ፕሬዜዳንት አብዲራህማን ሳይሊች የሶማሊላንድን ካቢኔ ለነገ አስቸኳይ ስብሰባ ጠርተዋል። ይኸው የተጠራው አስቸኳይ ስብሰባ ዛሬ በሶማሊያ መንግሥት ካቢኔ እና የፌዴራል ምክር ቤቶች ለተደረገው አስቸኳይ ስብሰባ #ምላሽ የሚሰጥ እንደሆነ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከሶማሊላንድ ንግድ እና ቱሪዝም ሚኒስትር አብዲረሺድ ኢብራሂም ያገኘው…
#Update

ራስ ገዟ ሶማሊላንድ የሶማሊያ መንግሥትን አስጠነቀቀች።

ከኢትዮጵያ ጋር የተፈረመውን የመግባቢያ ስምምነት ለማደናቀፍም ይሁን ለመቃረን የሚሞክር ማንኛውም ግለሰብ ይሁን አካል ላይ እርምጃ ወስዳለሁ ብላለች።

የራስ ገዟ ሶማሌላንድ" የሚኒስትሮች ምክር ቤት " ዛሬ አስቸኳይ ስብሰባ አድርጎ ነበር።

ከስብሰባው በኃላ ባወጣው ባለ 8 ነጥብ የአቋም መግለጫ ፦

- ምክር ቤቱ እ.ኤ.አ. ጥር 1/2024 በአዲስ አበባ የተፈርመውን የመግባቢያ ስምምነት በሙሉ ድጋፍ አፅድቆ እንደተቀበለውና እንደሚያደንቅ ገልጿል።

- ምክር ቤቱ ኢትዮጵያ " ለሶማሌላንድ ሪፐብሊክ " ሉዓላዊነት እውቅና የሰጠች የመጀመሪያ ሀገር በመሆኗ ምስጋናውን አቅርቧል።

NB. (የኢትዮጵያ መንግሥት ባወጣው መግለጫ ፤ ስምምነቱ በሂደት ሶማሌላንድ ዕውቅና ለማግኘት የምታደርገውን ጥረት በተመለከተ የኢትዮጵያ መንግስት በጥልቀት አጢኖ አቋም እንደሚወስድበት መግለፁ ይታወቃል)

- ምክር ቤቱ ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ሶማሌላንድ ምድሯን፣ አየሯን እና ባህሯን ሙሉ በሙሉ የምትቆጣጠር ነፃ ሀገር ናት ብሏል። በተጨማሪም " በሶማሌላንድ ሪፐብሊክ " ሕገ መንግሥት መሠረት " የሶማሌላንድ ሪፐብሊክ " ከማንኛውም ብሔራዊ ጥቅሟን ከሚያስጠብቅና ከሚጣጣም አካል ጋር ስምምነት የማድረግ ሥልጣን አላት ብሏል።

- ምክር ቤቱ ፤ " በሶማሌላንድ ሪፐብሊክ " እና በኢትዮጵያ ፌደራላዊ መንግስት መካከል የተደረገውን የመግባቢያ ስምምነት አስመልክቶ የሶማሊያ መንግስት የሰጠውን መግለጫ እና ድርጊት በጽኑ አውግዟል። የሶማሊያ መንግስት በመሰል ጉዳዮች ከመሳተፍ እንዲቆጠብ አስጠንቅቋል።

- ምክር ቤቱ ከሶማሊያ የወጡት መግለጫዎች " በሶማሌላንድ ሪፐብሊክ " እና በሶማሊያ መንግስት መካከል ከዚህ ቀደም የተደረጉ ስምምነቶችን የሚጻረር መሆኑን ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ይወቅልኝ ብሏል።

- ምክር ቤቱ ፤ " በሶማሌላንድ ሪፐብሊክ " እና በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ሪፐብሊክ መንግስታት መካከል የተፈረመውን የመግባቢያ ስምምነት ለማደናቀፍ ወይም ለመቃወም ለሚሞክር ማንኛውም ግለሰብ ወይም አካል ላይ ጥብቅ እርምጃ እንደሚወስድ ማስጠንቀቂያ ሰጥቷል።

- ምክር ቤቱ የሶማሌላንድ ህዝብ ለተፈረመው የመግባቢያ ሰነድ ላደረገው ደማቅ አቀባበል እና ድጋፍ ያለውን አድናቆት ገልጿል።

- ምክር ቤቱ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ሪፐብሊክን አርአያነት በመከተል በዓለም ዙሪያ ያሉ መንግስታት " ለሶማሌላንድ ሪፐብሊክ " እውቅና ለመስጠት ድፍረት እና ጥበብ እንዲያሳዩ አሳስቧል። ይህን መሰሉ ዕውቅና ለአህጉራዊ መረጋጋት፣ ለደህንነት እና ለአፍሪካ ቀንድ የዴሞክራሲ መርሆች መሻሻል አስተዋጽኦ እንደሚያደርግ አጽንኦት ሰጥቷል።

ሶማሊላንድ ላለፉት ሶስት አስርት ዓመታት እራሷን እንደ አንድ ነፃ ሀገር የምትቆጥር ሲሆን የራሷ ህገመንግስት፣ የመገበያያ ገንዘብ፣ የፀጥታ ኃይል፣ ፓስፖርት፣ ራሱን የቻለ የፖለቲካ ስርዓት አላት። እስከዛሬ ግን ዓለም አቀፍ እውቅና ማግኘት አልቻለም። ሶማሊያ እንደ አንድ የራሷ ግዛት ነው የምታያት።

#ቲክቫህኢትዮጵያ

@tikvahethiopia
#ስጋ

የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ሰይድ እንድሪስ የ2016 ዓ/ም የገና በዓል ዝግጅትን በተመለከተ ምን አሉ ?

* ሰሞኑን የተለያዩ ኦፕሬሽኖች ሰርተናል። 200 ቤቶች አካበቢ ለማየት ሞክረን ከዛ ውስጥ በ30 ቤቶች ሕገ ወጥ ስጋ የተገኘበት ሁኔታ ነው የተፈጠረው።

* 15 ቤቶች ሙሉ ለሙሉ #አንዲታሸጉ ያደረግንበት ፣ ሌላ ተጨማሪ 10 ቤቶች ደግሞ ሕገ ወጥ (ሀሰተኛ) የስጋ ምርመራ ሰነድ ይዘው ህብረተሰቡን እያታለሉ ሥጋ ሲሸጡ የነበሩበት ሁኔታ መኖሩን ያዬንበት ሂደት አለ።

* አጠቃላይ ባደረግነው ሂደት 1,500 ኪሎግራም ሕገ ወጥ በሦስት ቀናት ውስጥ ተሰብስቦ እዚህ መጥቶ እንዲወገድ የተደረገበት ሂደት አለ። 

* ባደረግነው ዳሰሳ #የሕገወጥ እንስሳት እርድ አለ። ከዚያ ውጪ ግን በእምነትም ይሁን በባህላችን ባዕድ የሆኑ እንስሳት ታርደው ወደ ገበያ የቀረቡበት ሂደት የለም። የተያዘው ሥጋ፦
- የበሬ ፣
- የፍዬል
- የበግ ፣ ግን በሕገ ወጥ መንገድ የታረደ ነው።

* የበሬ ስጋ የአንድ (1) ኪሎ ዋጋ ከ550 እስከ 570 ብር በዕለቱ ሽያጭ ይከናወናል። በአራት መስኮቶች የበግ እና የፍየል ስጋም ሽያጭ ይከናወናል። የበግ ስጋ በ500 ብር ፣ የፍየል በ510 ብር በኪሎ ግራም ለበዓሉም ለመደበኛ ቀናትም የሚያቀርቡበት በዚህ ደረጃ ተዘጋጅቷል።

" የባዕድ እንስሳት / #አህያ ስጋ እየተሸጠ ነው " ሲባል በነበረው ጉዳይ ምን ተባለ ? ያንብቡ👇
https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-01-05

#ቲክቫህኢትዮጵያ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የራስ ገዟ ሶማሌላንድ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው ስብሰባ ሶማሌላንድ ዓለም አቀፍ ስምምነቶችን የመፈፀም መብትን የሚደግፍ እና የሶማሊያን መንግሥት ጣልቃ ገብነትን ውድቅ የሚያደርግ ውሳኔ አሳልፏል። ሶማሌላንድን የራሴ አካል ናት የምትለውን ሶማሊያ እያቀረበች ያለውን የይገባኛል ጥያቄ #ውድቅ በማድረግም "የሶማሌላንድ ሪፐብሊክ ሉዓላዊነትና ነጻነቷ የተረጋገጠ ነው " ብሏል። የሶማሊያው…
#Update

ራስ ገዟ ሶማሌላንድ የሁለትዮሽ ስምምነት ለማድረግ " የሶማሊያ ፍቃድ "አያስፈልገኝም ፤ አልጠይቅምም " አለች።

ከሶማሊያ ተነጥላ ሶስት አስርት ዓመታት እንደሆናት የገለፀችው ሶማሌላንድ፤ ሶማሊያ የምታቀርበው " የኔ አካል ናት " የሚለው የባለቤትነት ጥያቄ ፍፁም ሀሰት ነው ስትል ገልጻለች።

የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክን በሶማሊላንድ የወደብ ተጠቃሚ ለማድረግ የተፈረመው የመግባቢያ ስምምነት አንድ ሀገር ከሌላ ሀገር ጋር ከሚደርገው #የሊዝ_ኮንትራቶች የተለየ አለመሆኑን አመልክታለች።

ራስ ገዟ ሶማሌላንድ ፤ ሶማሊያ የመግባቢያ ስምምነቱን በተመለከተ ያየዘችውን አቋም እና ያወጣቻቸውን መግለጫዎች ሁሉ #ውድቅ አድርጋለች።

ከዚህ ባለፈ ሶማሌላንድ የሁለትዮሽ ስምምነቶችን ለማድረግ የሶማሊያን ፈቃድ ትፈልጋለች የሚባል ማንኛውም ሀሳብ ፍፁም ውሸት ነው ስትል ገልጻለች።

ሶማሊላንድ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከበርካታ ሀገራት ጋር የራሷን ነጻ የሆነ ግንኙነት ስታደርግ እንደነበርና አሁንም የምትቀጥል መሆኑን ገልጻ ከአሁኑ የመግባቢያ ስምምነት በፊት በርካታ ዓለም አቀፍ እና የሁለትዮሽ ስምምነቶችን በተሳካ ሁኔታ መፈፀሟን አስታውሳለች።

ከእነዚህ ከተፈፀሙ ዓለም አቀፍ እና የሁለትዮች ስምምነቶች መካከል አንዳቸውም ከሶማሊያ ፈቃድ አልተጠየቁም ወይም አልተቀበሉም ብላለች።

ሶማሌላንድ ባለፉት 33 ዓመታት የሶማሌላንድ እና የሶማሊያ #ተቃራኒ ሁኔታዎችን ብዙ ይናገራሉ ስትልም ገልጻለች።

ሶማሌላንድ ፤ በአፍሪካ ቀንድ የበለፀገ ዲሞክራሲ እና የመረጋጋት ምልክት ሆና የውስጥ ጉዳዮቿን፣ አስተዳደሯን እና ምርጫዋን ያለአለም አቀፍ ድጋፍ በብቃት በመምራት ላይ እንደሆነች አመልክታችለች።

" ሀገራችን እና የባህር ዳርቻዋ ያለማቋረጥ / በወጥነት ከዘረፋ፣ ከሽብርተኝነት እና ከሽፍታነት የፀዱ ናቸው። " ስትል አክላለች።

በአንፃሩ ሶማሊያ ላለፉት 33 ዓመታት ከውስጥ ሽኩቻ፣ ሙስና እና ሽብርተኝነት ጋር ስትታገል፣ በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ዘንድ በተደጋጋሚ " የወደቀች / የከሸፈች ሀገር " ስትባል እንደነበር እና ለራሷ ጥበቃ የዓለም አቀፍ ሰላም አስከባሪ ሃይል ያስፈለጋት ሀገር መሆኗን ሶማሌላንድ ገልጻለች።

" ሶማሊያ ብዙ ጊዜ ' ብርቅዬ አፍሪካዊ ተአምር ' እየተባለች በሚነገርላት በሶማሌላንድ ላይ ያልተገባ አረዳድ እንዲኖር ከማድረግና መሠረተ ቢስ የባለቤትነት ጥያቄ ከማቅረብ ይልቅ፣ የራሷን ቤት ብታስተካክል ይመረጣል " ብላለች።

" እርግጥ ነው፣ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በሁለቱ አካላት መካከል ያለውን ከፍተኛ ልዩነት ይገነዘባል " ያለችው ሶማሌላንድ " እኛ ለአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ሰላምና መረጋጋት የምናደርገውን አስተዋጽኦ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የሚያደንቀው ነው " ስትል ገልጻለች።

ሶማሌላንድ እንደፈለገችው በነፃነት ዓለም አቀፍ ግንኙነት የመመሥረት ሉዓላዊ መብቷን ከማስጠበቅ ወደ ኋላ ባትልም፣ ከሶማሊያ ጋር እንደ #ጎረቤት ገንቢ ውይይት ለማድረግና ሰላማዊ በሆነ መንገድ አብሮ ለመኖር ቁርጠኛ ነኝ ብላለች።

ሶማሊያ ፤ እንደ አንድ የራሷ ግዛት በምትቆጥራት ሶማሌላንድ እና በኢትዮጵያ መካከል የተፈረመውን ስምምነት " ዋጋቢስ " በማለት ውድቅ ያደረገች ሲሆን የኢትዮጵያ ድርጊት ሉዓላዊነቴን ፣ ግዛታዊ አንድነቴ የሚዳፈር ነው ብላለች።

የሀገሪቱ ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሞሀሙድም ስምምነቱን ተከትሎ ወደ ተለያዩ ሀገራት እና ተቋማት ጋር በመደወል ውይይት አድርገዋል።

በአሁን ሰዓት ደግሞ በኤርትራ ይፋዊ ጉብኝት እያደረጉ ሲሆን የግብፅ ፕሬዜዳንት አብዱል ፈታህ አልሲሲም ወደ ግብፅ መጥተው የስራ ጉብኝት እንዲያደርጉ ጥሪ ማቅረባቸው ተሰምቷል።

#ቲክቫህኢትዮጵያ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#EOTC ዛሬ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ በወቅታዊ ጉዳይ ላይ መግለጫ ሰጥተው ነበር። ብፁዕነታቸው በመግለጫቸው ፤ " በዚህ ወቅት ቤተክርስቲያኗ የተለያዩ ፈተናዎች ገጥመዋታል ፤ በየግል በተለያዩ አባቶች፣ በተለያዩ መንገዶች በሚሰበኩ ስብከቶች ፣ በሚፈጠሩ ሁኔታዎች ፣ ለምን ? እንዴት ? ዝም አልሽ ቤተክርስቲያን በሚልም ትልቅ ፈተና ላይ ነች " ብለዋል። ቤተክርስቲያን…
#EOTC

" ኮብልለው አልሄዱም፣ ኮብላይም አይደሉም ! "

ብፁዕ አቡነ አብርሃም ምን አሉ ?

- ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶክተር) ኮብልለው አልሄዱም፣ ኮብላይም አይደሉም። ለእውነት እና ለፅድቅ ለቤተክርስቲያናቸው አንገታቸውን ከሚሰጡ አባቶች አንዱ እንጂ የሚሸሹ የሚኮበልሉ ፣ የሚደበቁ የወንጀል ሰው ሊሆኑ አይችሉም። አይደሉምም።

- ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ በቅዱስ ፓትርያርኩ ፍቃድ፣ እንደ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት አውቆት ለአገልግሎት ቤተክርስቲያን ሊባርኩ ታቦታት ይዘው አስፈቅደው ሰሜን አሜሪካ ሄደዋል። ይሄ ደግሞ ዛሬ ብቻ ሳይሆን በየጊዜው ነው የሚሄዱት።

- ቆም ብላችሁ አድምጡ ! እናተ ለፖለቲካችሁ ብዙ እንደምትሉ ብዙ እንደምታስቡ ሁሉ እኛም ለሰማያዊ መንግሥታችን እንቆማለን ፤ ለምድራዊ መንግሥታችን እንገዛለን በሃይማኖት እስካልመጣብን ድረስ በሃይማኖት ከመጣ ግን መገዛት አይደለም አትገዙ ብለን እናውጃለን። ግን ግድሉ አንልም፣ ተገዳደሉ አንልም፤ ቤተክርስቲያን ቃሏ ስላልሆነ። አትገዙ ግን ትላለች አሁን ግን እዚህ አልደረስንም። ቤተክርስቲያን እያስተማረች ያለችው ሰላምን፣ ፍቅርን ብቻና ብቻ ነው።

- ያለ ስም ስም መስጠት ይሄ ማህበራዊ ሚዲያ በሚባለው ንፋስ ፣ ምንም ጭብጥ በሌለው ሃይማኖታዊውን ሰው ሃይማኖታዊ አይደለም፤ ለቤተክርስቲያን የሚሰራውን ፣ለሀገር የቆመውን ኮበለለ ፣ ከዳ የሚባል ደካማ አስተሳሰብ የቤተክርስቲያን ህልውና አያናግም።

- " ደግሞ ሰምተናል አባ ጴጥሮስ ፣ አባ አብርሃም ... ተለውጠዋል ዝም ብለዋል አድር ባይ ሆነዋል የሚለውን ፤ ከሃይማኖት ውጭ ሌላ ማደሪያ የለንም። ለኛ ማደሪያችን መዋያችን ሃይማኖታችን ናት "

- ለመንግስትን እንደ መንግስት እንድንገዛው መፅሀፍ ቅዱስ ያስገድደናልም በሃይማኖታችን እስካለመጣ ድረስ ሃይማኖታችንም ለመንግስት እንድንገዛ ያስገድደናል።

- ከዚህ ውጭ ከውስጥ የምንሰራውን በይፋ እንዲህ ነው ብለን አናወራም በሚል ዝም ብለናል።

- የወሬ ገበያ ያለው ሰው ሁሉ የወሬ ገበያው እንዲደራ ዛሬ አባ አብርሃም ፣ አባ ጵጥሮስ አልተናገሩም በሚል ሌላ ስም ልስጥ ቢል የሱ ወሬ እንጂ የኛ አይደለም።

- አባ ጴጥሮስ ሆኑ አባ አብርሃም ስራቸውን የሚሰሩት በሃይማኖታቸው መሰረት ብቻ ነው።

#ቲክቫህኢትዮጵያ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#EOTC

ብፁዕ አቡነ አብርሃም ምን አሉ ?

- በዓለ ጥምቀቱን ለማክብረ በመንግሥት ዘንድ ቤተክርስቲያን ይሄን ትበል ፣ አለበለዚያ እንዲህ አይደለም የሚሉ መልዕክቶች ደርሰውናል።

- ቤተክርስቲያን ሰላሟን ታውጃለች።

- አሉ አሉ እየተባሉ ስለተነገሩ ንግግሮች እና ግለሰቦች፣ ጳጳሳት እና ሊቃነጳጳሳት ከሆኑ በቅዱስ ሲኖዶስ ታያለች፣ ትመክራለች ታስተምራለች። ህግ አላት በህጓ መሰረት ትገስፃላች። ከዚህ ውጭ ሱሪ በአንገት አውጣው የሚባል ነገር ቤተክርስቲያን አትሸከምም አትቀበለም።

- ሰላሟን እያወጀች፣ ሰላሟን እየሰበከች በሰላም መንገድ ትጓዛለች።

- ሁል ጊዜ ቤተክርስቲያን መሞትን ስራዬ ብላው ይዛ ኖራለች ወደፊትም ሞት ከሆነ በሰላም ለመቀበል ዝግጁ ናት።

- " ይሄን ካደረግሽልኝ ይሄን አደርግልሻለሁ " የሚል መደራደሪያ የላትም ፣ ሊኖራትም አይችልም። ድርድሯ ሰላምና ሰላም ብቻ ነው።

- እኔ ያልኩሽን አድርጊ የሚል በቀኝም ይሁን በግራ ፤ ከገዢውም ክፍል ይሁን እገዛለሁ የሚል ሃሳብ ቢመጣ ያን ተቀብላ የማስተናገድ አቅምም ብቃትም የላትም።

- የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች፣ በዓሉ ዓለም አቀፍ ስለሆነ የተለያየ እምነት ያላችሁ ልጆች ፣ የሌላ እምነት ተከታይ ሆናችሁ በዓሉ በዓላችን ነው የምትሉ፣ የምትደግፉ በዓሉን እራሳችሁ አክባሪዎች ፣እራሳችሁ የፀጥታው አስተናጋጆች የሰላም መሪዎች ሆናችሁ በዓሉ በሞቀና በደመቀ ሁኔታ እንዲከበር ቤተክርስቲያን መልዕክት ታስተላልፋለች።

- የፀጥታ አካላት ትላንት እንዲህ ተብያለሁ ይሄ እንደገና በተቃውሞ ካልታወጀልኝ በስተቀር ይሄን አላደርግም የሚለውን አስተሳሰብ ትቶ ህግን በህግ ስርዓትን በስርዓት ለመፈፀም አእምሮውን አስፍቶ የተሻለ ስራ እንዲሰራ ቤተክርስቲያን መልዕክቷን ታስተላልፋለች።

- ሌላው ሌላው ችግር በመድረክ ዙሪያ፣ ማነው ጥፋተኛ ? ምን አስቦ ነው ? ምን ብሎ ነው ? የሚለውን ቅዱስ ሲኖዶስ የሚመክርበት የሚዘክርበት፣  የሚገሰፀውን የሚገስፅበት ፣ ከቀኖና የወጣውን ከቀኖና ወጥተሃል የሚልበት የራሱ ስርዓት ስላለው ለህጉ እንተወዋለን።

- " ይሄን በሉ ይሄን አድርገ፣ ይሄን ካላደረጋችሁ ይሄን አናደርግም " የሚባል መያዣ ነገር ቤተክርስቲያን አስተናግዳ አታውቅም ፤ ወደፊትም አታስተናግድም።

- እገሌ እገሌ ባልልም ቤተክርስቲያን ቤተክርስቲያን ናት በዓሉም የህዝብ ነው ይሄን መያዣ አናድረግም ችግሩ ችግር ሳይሆን እንዲፈታ ይደረግ በመልካም ነገር በዓሉን በሰላም እናክብር ብለው የተናገሩ መሪዎች አሉ በዚህ አጋጣሚ ሊደነቁ ይገባል። ከመሪዎች የሚጠበቀው ይሄ ነው። ችግርን እንዴት እንፍታው ችግርን እንዴት እናስወግደው ፣ ሰላም እንዴት እናስፍን ነው መባል ያለበት።

- በየሄድንበት " ደግሞ ለኦርቶዶክስ፣ ለተዋሕዶ ቤተክርስቲያን " ቃሉም ይከብዳል በየቢሮው ስንሄድ ቢያንስ አይሆንም አይባልም " ያንን ያንን ያርሙ " ይላሉ።

- " ኦርቶዶክስ ሃገር ናት ፣ ለሀገር ዋልታ ናት፣ ምሰሶ ናት አምድ ናት ይሄን ታሪክ አይክደውም። ዘመን ቢያስረጃትም ዘመን ቢጥላትም ዘመን ያነሳታል።

- ዛሬም ሲደረግላት እያመሰገነች ነው። ለሀገር ሰላም ማድረግ ያለባትን እያደረገች ነው ፤ በየመስሪያ ቤቱ ስንሄድ " ደግሞ ለኦርቶዶክስ " የሚለው ቃል ሊታረም ይገባል።

- ቤተክርስቲያን ትከበር ፣ በቤተክርስቲያን ውስጥም #በሃይማኖት_ስም እንደፈለገ የሚዋኙ ሰዎች ቆም ብለው ያዳምጡ፣ የሚናገሩትንም ይመርምሩ ፣ ሃይማኖታዊ ቃል ነው አይደለም ይበሉ ከሃይማኖታዊ ቃል ውጭ የሆነው ሁሉ የእኛ #አይደለም

#ቲክቫህኢትዮጵያ
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#EOTC ብፁዕ አቡነ አብርሃም ምን አሉ ? - በዓለ ጥምቀቱን ለማክብረ በመንግሥት ዘንድ ቤተክርስቲያን ይሄን ትበል ፣ አለበለዚያ እንዲህ አይደለም የሚሉ መልዕክቶች ደርሰውናል። - ቤተክርስቲያን ሰላሟን ታውጃለች። - አሉ አሉ እየተባሉ ስለተነገሩ ንግግሮች እና ግለሰቦች፣ ጳጳሳት እና ሊቃነጳጳሳት ከሆኑ በቅዱስ ሲኖዶስ ታያለች፣ ትመክራለች ታስተምራለች። ህግ አላት በህጓ መሰረት ትገስፃላች። ከዚህ…
#EOTC

" ሀገራችን ሰላም ትሁን፤ የሃይማኖት ሰዎች እንደ ሃይማኖት እናስብ፣ እንደ ሃይማኖት እንናገር፣ አላስፈላጊ ጀግንነትን እንርሳው " - ብፁዕነታቸው

ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ምን አሉ ?

- የማይደፈር ሲደፈር አይተናል፤ ቤተክርስቲያን ስትደፈር ዝም አንልም።

- " ፖለቲካው የፖለቲካው መስመር ሲደፈር ዝም እንደማይል ሁሉ እኔም ደግሞ የመጀመሪያዋም የመጨረሻዋም ህይወቴም ማንነቴም ክብሬም ቤተክርስቲያኔ ስለሆናች እሷ ስትደፈር ዝም አልልም። እናገራለሁ፤ የመጣውን በፀጋ ለመቀበል ዝግጁ ነኝ "

- ከዚህ በፊት ለመንግሥት ችግር ካለ እዚህ ጠቅላይ ቤተክህነት ውስጥ ንገሩን ብለናቸዋል። እኛ እናርማለን፣ እኛው እናስተካክላለን፣ አላስፈላጊ እርምጃ አትውሰዱ ብለናቸዋል። ትላንት ግን ከቤተክህነት የሚወጣው በሙሉ ይፈተሻል ዛሬም፣ የሚወጣ መኪና በሙሉ ይፋተሻል፤ የሚገባው ግን አይፈተሽም። የሚገባውን የኛ ዘበኞች ይፈትሹ ይሆናል፤ የመንግሥት ወታደሮች ግን አይፈትሹም። አንዱ ሌላ ነገር ይዞ ገብቶ ሲወጣ ፈታሹ ሌላ ነገር ይዞ ተብሎ የቤተክርስቲያን ስም እና ክብር ቢዋረድ ማነው ኃላፊው?

- ምንድነው የተፈለገው? ከቤተክርስቲያን ምንድነው የሚወጣው? መድፍ ነው? መሳሪያ ነው? አከፋፋይ ናት ቤተክርስቲያኒቱ? አትታመንም? መንግሥትን ያስጮኸ ነገር አለ እኛም የጮህንበት ከመንግስት በፊት፤ ግለሰቦችን ስለተናገሩት ንግግር የማይባል ተብሏል እያልን እኛ ነን የጮህን ይሄ የቤተክርስቲያን ቋንቋ አይደለም ብለን ነበር፤ መግለጫ ለመስጠት ተዘጋጅተን ነበር መንገዱን ስናየው መጠላለፊያ እንጂ ከፅድቅ ስላልሆነ ነው ዝም ያለነው። የፅድቅ ሲሆን ገፍተን ነው የምንወጣው።

- ከቤተክህነት ምንድነው የሚወጣው ? ከተፈለገ መባል ያለበት ጥርጣሬ አለን ቤተክህነት ውስጥ ይባላል፤ እንዲህ አይነት ነገር ቢወጣ ኃላፊነቱ የናተ ነው ጠብቁ ነው ልንባል የሚገባው ወይም ሰው እንሥጣችሁ የሚያንሳችሁ ከሆነ ቤተክርስቲያኒቱን እንዳያስወቅስ ነው መባል ያለበት እንጂ ቤተክርስቲያን የማትታመን ሆነ ከትላንት ጀምሮ እስካሁን እኛ መሪዎቹ በማናውቀው ፈታሽ በር ላይ ቆሞ መፈተሽ ድፍረት ነው። ቤተክርስቲያኒቱን ህልውናዋን መፈታተን ነው። አቅሟንም መፈትን ነው ተገቢ አይደለም።

- መደፋፈሩ በዝቷል፤ መንግስትም ቤተክርስቲያኒቱን ይደፍራል አልፎ ይሄዳል።

- እንደ ግለሰብ በስሜት የሚናገሩ ሰዎች ይኖራሉ። ቤተክርስቲያኒቱን መድፈር አዳጋ ነው። ለሃይማኖቱ የማይሞት የለም፣ ከዚህ በፊት ብዙዎች ሞተዋል፤ ተከባብረን እንኑር ለሰላም እንኑር።

- ካህን ነው ሲሉት ሌላ ነጭ ለባሽ ይሆናል፣ ነጭ ለባሽ ነው ሲሉት ካህን ሆኖ ይገኛል፤ የቤተክርስቲያን መሪ ነው ሲሉት የፖለቲካ መሪ ሆኖ ይገኛል፤ የፖለቲካ መሪ ሲሉት ቀዳሽ ሆኖ ይገኛል ምን አመጣው ይሄን ቀጥ ብለን እንቁም። ደሃ ሲበደል ተበደለ እንበል ሲታሰር ፍቱ እንበል፤ እያልን ነው እኮ፤ መንግሥትን ፍቱ እያልን እንመካከራለን ይፈታል ለዚህ ደግሞ እናመሰግናለን።

- በሃይማኖት ጉዳይ አንደራደርም።

- ካህን ካህን ይሁን፣ ወታደርም ወታደር ይሁን ሌላውም እራሱን ይሁን በሚያስተሳስረን ነገር ተሳስረን ጥላቻና ሁከትን፣ ሽብርና አላስፈላጊ ነገርን እናርቅ።

- ካላስፈላጊ #ጎጠኝነት#ዘረኝነት እንራቅ።

- ሀገራችን ሰላም ትሁን የሃይማኖት ሰዎች እንደ ሃይማኖት እናስብ፣ እንደ ሃይማኖት እንናገር፣ አላስፈላጊ ጀግንነትን እንርሳው። አላስፈላጊ ሙገሳንም እንርሳው። ካላስፈላጊ ሙገሳ አስፈላጊ በሆነ ወቀሳና ለመጨረሻው መከራ እራሳችንን እናዘጋጅ።

ያንብቡ፦ https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-01-12-2

#ቲክቫህኢትዮጵያ

@tikvahethiopia
" ለገንዘብ ተብሎ በግብረሰዶማውያን እና በስደተኞች ጥገኝነት ጥየቃ (asylum) ጉዳይ ሀገሪቱ ያላት ፖሊሲ አይቀየርም " - ሀንጋሪ

በመጪው ሰኔ የአውሮፓ ፓርላማ ምርጫ ይደረጋል ተብሎ እቅድ ተይዟል።

ከምርጫው ጋር ተያይዞ ስለ ግብረሰዶማውያን እና ስለስደተኞች እንዲሁም ስለሌሎች ጉዳዮች የሀንጋሪው ጠቅላይ ሚኒስትር ቪክቶር ኦርባን ከአንድ የሀገር ውስጥ ሬድዮ ጣቢያ ጋር ቃለምልልስ አድርገው ነበር።

በዚህም ወቅት ፤ ብዙ የአውሮፓ ፖለቲከኞች ይህንን ወቅት እንደምንም ብለው መትረፍ ይፈልጋሉ ብለዋል።

" ምርጫ በሌለበት ጊዜ ማስመሰል ትችላላችሁ " ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፤ " ምርጫ ሲደረግ ግን ከህዝቡ ጋር መነጋገር አለባችሁ። ነገር ግን ሰዎች ብራስልስ ውስጥ የሚጠቀሙትን የሌቦች ቋንቋ አይረዱም። የህዝብን ቋንቋ መናገር መጀመር አለብን " ሲሉ ተናግረዋል።

ንግግራቸውን ቀጠል አድርገው፤ " የአውሮፓ ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ኡርሱላ ፎን ደር ሌየን ፤ የብራሰልስ አካላት በሃንጋሪውያን ላይ ያላቸውን ነገር ማለትም ስደተኞችን ወደ ሀገር ውስጥ እንደማናስገባ እና የግብረሰዶማውያን አክቲቪስቶችን ወደ ትምህርት ተቋማት እንዲገቡ እንደማንፈቅድ በመጨረሻ አምነዋል " ብለዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፤ " የግብረሰዶማውያን ፕሮፓጋንዲስቶችን ወደ ትምህርት ቤቶቻችን እንድናስገባ እንዲሁም ስደተኞችን ወደ ሀገራችን እንድናስገባ የሚያደርግ በዓለም ላይ ምንም አይነር ገንዘብ የለም " ሲሉ አስረግጠው ተናግረዋል።

ለገንዘብ ተብሎ በግብረሰዶማውያን እና በስደተኞች ጥገኝነት ጥየቃ (asylum) ጉዳይ ሀገሪቱ ያላት ፖሊሲ እንደማይቀየር የሀገሪቱ መንግሥት አሳውቋል።

የአውሮፓ ህብረት ከግብረሰዶማውያን እና ከስደተኞች መብት እንዲሁም #ከአካዳሚክ_ነፃነት ጋር በተያያዘ ብዙ ለሀንጋሪ ሊሰጥ የሚገባውን ብዙ ቢሊዮን ዩሮ (20 Billion EUR) ይዞባታል።

እ.ኤ.አ. ከ2010 ጀምሮ በስልጣን ላይ የሚገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር ኦርባን ግብረሰዶማዊነትን እና የፆታ ለውጥን በትምህርት ቤቶች ውስጥ #ሊያስተዋውቁ ይችላሉ የሚባሉ ነገሮችን የሚከለክል ህግ በ2021 አጽድቀዋል።

ህጉ ከገንዘብ ቅጣት እስከ እስር ቤት መወርወር ያደርሳል።

ይህ ህግ የፀደቀው ህፃናትን ከ " ከግብረሰዶማውያን ፕሮፓጋንዳ " መጠበቅ በማስፈለጉ ሲሆን በዚህ ህግ ምክንያት ከአውሮፓ ህብረት ጋር አለመግባባት ውስጥ እንዲገቡ አድርጓቸዋል። የአውሮፓ ህብረቱም ከዚህና ከሌሎች ጉዳዮች ጋር በተያያዘ 20 ቢሊዮን ዩሮ ገንዘብ ይዞባታል።

#ቲክቫህኢትዮጵያ
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኢትዮጵያ " በነዳጅ የሚሰሩ አውቶሞቢሎችን ወደ ሀገር ውስጥ ማስገባት እንደማይቻል ይታወቅ " - የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር በነዳጅ የሚሰሩ አውቶሞቢሎች ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገቡ ቢከለከልም " ይሄን አልሰማንም " ያሉ ሰዎች የነዳጅ ተሽከርካሪዎችን ገዝተው ወደ ሀገር እያመጡ ይገኛሉ ተብሏል። ይህ የተሰማው የትራንስፖርት እና ሎጀስቲክስ ሚኒስትሩ ዓለሙ ስሜ በዛሬው እለት በህዝብ ተወካዮች…
#AddisAbaba

በህዝብ ትራንስፖርት የሚጠቀሙ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች በስራ መግቢያ እና መውጫ ሰዓት ፦
* እንዳይቸገሩ ፣
* መንገድ ላይ ሰልፍ ተሰልፈውም ጊዜያቸው እንዳይጠፋ ፣
* ባሰቡበት ሰዓት በህዝብ ትራንስፖርት ያሰቡበት ቦታ እንዲደርሱ በተለየ ሁኔታ ለተወሰነ ሰዓት የግል ተሽከርካሪዎች እንዳይንቀሳቀሱ #ለመገደብ እየተሰራ ይገኛል። ይህ በቅርብ ተግባራዊ ይደረጋል ተብሏል።

የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር ምን አለ ?

ዓለሙ ስሜ (ዶክተር) ፦

" በአዲስ አበባ በትራንስፖርት የሚሄደው ህዝብ አገልግሎቱን በአግባቡ የማያገኝበት ፣ ባሰበበት ሰዓት ተነስቶ ባሰበው ሰዓት የፈለገው ቦታ እንዳይደርስ የሚያደርጉ ሶስት ምክንያቶች አሉ።

1ኛ. የህዝብ ትራንስፖርት የተሽከርካሪ እጥረት ነው።

2ኛ. የመንገድ መዘጋጋት ነው።

3ኛ. የስምሪት እና የተሽከርካሪ ማናጅመት አለመዘመን ነው።

በነዚህ ሶስት ጉዳዮች እየሰራን ነው።

የተሽከርካሪ ቁጥር ለመጨመር በየዓመቱ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በአንድ ጊዜ ብዙ ሰዎች የሚጭኑ ማስ ትራንስፖርት ተሽከርካሪዎች እየገዛ ወደ አገልግሎት እያስገባ ነው። ዘንድሮም እየተሰራ ነው። በዓለም ባንክ በርካታ ተሽከርካሪዎች ተገዝተው ለአዲስ አበባ ከተማ እንዲሰጡ እየተሰራ ነው።

የመንገድ መዘጋትን በተመለከተ መንገዶቻችን የተወሰኑ ናቸው። ሀገሪቱ ካላት ተሽከርካሪ በአብዛኛው አዲስ አበባ ውስጥ ነው ያሉት። ይሄን ችግር ለመቅረፍ ስራዎች እየተሰሩ ነው።

አንደኛው ለህዝብ ጭነት ተሽከርካሪዎች የተለየ መንገድ ፣የተለየ መስመር ማበጀት ነው እሱም ተበጅቶ እየተሰራ ነው ያለው። ግን በቂ አይደለም።

ሁለተኛው በተለይ በስራ መውጫና መግቢያ ሰዓት #የተወሰኑ ሌሎች ተሽከርካሪዎችን እንዳይንቀሳቀሱ የመገደብና ህዝብን የሚጭኑ አውቶብስ ቶሎ ቶሎ እንዲመላለስ ማድረግ ነው። ከተሽከርካሪ እጥረት መንገድ ላይ የሚቆመውን ህዝብ ባለው ተሽከርካሪ ቶሎ ለመጫን መንገድ ክፍት የሚሆንበት #ሰዓቶችን መርጠን ጥናቱ አልቋል ወደ ስራ በቅርቡ ይገባል።

ስለዚህ በስራ መውጫና መግቢያ ሰዓት የግል መኪና ተጠቃሚዎች የሚገደቡበት ሁኔታ ይፈጠራል። ይሄም የግል መኪና ተጠቃሚዎች ወደህዝብ የትራንስፖርት አማራጭ እንዲገቡ የማስገደድ ሁኔታ ይመጣል። ይህ ለህዝብ አውቶብስ መንገድ ይከፈታል፣ ነዳጅ ይቆጠባል፣ የአየር ብክለትን ይቀንሳልም። ይህን አሰራር በቅርብ ተግባራዊ እናደርጋለን።

የአውቶብሶች መነሻ እና መድረሻ ሰዓታቸው እንዲታወቅ በቴክኖሎጂ የማስደገፍ ስራ ከዓለም ባንክ ጋር እየተሰራ ነው። ይህም ስራ ካለቀ ከዚህ ጋር ያሉት ችግሮች ይፈታሉ። "

#ቲክቫህኢትዮጵያ
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba በህዝብ ትራንስፖርት የሚጠቀሙ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች በስራ መግቢያ እና መውጫ ሰዓት ፦ * እንዳይቸገሩ ፣ * መንገድ ላይ ሰልፍ ተሰልፈውም ጊዜያቸው እንዳይጠፋ ፣ * ባሰቡበት ሰዓት በህዝብ ትራንስፖርት ያሰቡበት ቦታ እንዲደርሱ በተለየ ሁኔታ ለተወሰነ ሰዓት የግል ተሽከርካሪዎች እንዳይንቀሳቀሱ #ለመገደብ እየተሰራ ይገኛል። ይህ በቅርብ ተግባራዊ ይደረጋል ተብሏል። የትራንስፖርት…
የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር ምን አለ ?

ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) ፦

- በነዳጅ የሚሰራ #አዲስ ሆነ #አሮጌ የግል አውቶሞቢል መኪና ወደ ሀገር ማስገባት አይቻልም። ሀገር ውስጥ የሚገጣጠሙ ኤሌክትሪክ ብቻ እንዲሆኑ አቅጣጫ ተቀምጧል።

- የነዳጅ አውቶሞቢል ተሽከርካሪዎች ከአምና ጀምሮ ወደ ሀገር እንዳይገቡ ታግዷል። ግን እስከ ቅርብ ጊዜ በተለያየ መልኩ የሚገቡ ነበሩ። ለምሳሌ ፦ ከውጭ #ተመላሽ ዳይስፖራ ተብሎ እነሱ ላይ ተፈፃሚ አይሆንም ነበር፤ እነሱ የነዳጅ ሲያስገቡ አይከለከሉም ነበር። ይህ ግን አሁን ላይ አይሰራም። የግል አውቶሞቢል በማንኛውም ምክንያት በዳይስፖራ ሰበብም ይሁን በምንም ሁኔታ እንዲገባ አይፈቀድም።

- የመኪና አስመጪዎች የኤሌክትሪክ አውቶሞቢል ብቻ ነው ማስገባት የሚችሉት።

- በጣም ያረጁ መኪናዎች ከአገልግሎት እንዲወጡ አዋጅ ወጥቷል። ህግም ወጥቶ መኪናዎች መስጠት የሚችሉት አገልግሎት በእድሜያቸው ልክ እንዲሆንና እድሜያቸው ከአገልግሎት ዘመናቸው ውጭ የሆነ ከገበያ ውና ከአገልግሎት እንዲወጡ የሚሄዱበት ሁኔታ እየተሰራ ነው።

- በተለይ አዲስ አበባ ትንንሽ ሰዎችን ከሚጭኑ ታክሲዎች ይልቅ በአንድ ጊዜ በርካታ ሰዎችን የሚጭኑ ብዝሃ ትራንስፖርት እየተበረታቱ ነው። በሂደት አዲስ አበባ ውስጥ እንደሌሎች ያደጉ ከተሞች 10 እና 12 ሰዎች የሚጭኑ ሚኒባስ ታክሲዎች ከአገልግሎት እየወጡ እንዲሄዱ ይደረጋል። ይህ መጨናነቁንም ፣ ብክለቱን ከከተማ ያስወጣል።

- የብዝሃ ትራንስፖርትን በማሳደግ የተሽከርካሪ ቁጥር ለመቀነስም ታስቧል። የብዝሃ ተሽከርካሪዎች በኤሌክትሪክ የሚሰሩ እንዲሆንም እየተደረገ ነው። አዲስ አበባ በቅርብ የሚገዛቸው ባሶች የኤሌክትሪህ ይሆናሉ።

- ከዚህ በኋላ የመኪና ሰሌዳ ዝም ብሎ አይሰራጭም። አስመጪዎች ሰሌዳ እየወሰዱ / በብዛት እየገዙ ድንበር አካባቢ ሄደው አዲስ / አሮጌ መኪና ላይ በመግጠም እንደነባር ህጋዊ መኪና እያሽከረከሩ የሚገቡበት ሁኔታ አለ። የተራጋ አሰጣቱን ለመቆጣጠር ይሰራል።

- በአዲስ አበባ የፓርኪንግ ቦታ በቅርብ ኖሮ መንገድ ላይ መኪና እንዳይቆም ለማድረግ እየተሰራ ነው። በከተማው በ2 ኪሎ ሜትር አቅራቢያ ፓርኪንግ ካለ ባልተፈቀደ ቦታ ማቆም እንዳይቻል አስገዳጅ ስራ እየተሰራ ነው።

- የአዲስ አበባ ከተማ የህዝብ ትራንስፖርት ተጠቃሚዎች በስራ መውጫና መግቢያ ሰዓት እንዳይቸጉሩና ባሰቡት ሰዓት ያሰቡበት እንዲደርሱ፣ ሰልፍ ተሰልፈው መንገድ ላይ እንዳይቆሙ ለማድረግና የህዝብ ትራንስፖርት በፍጥነት እንዲመላለስ የግል መኪና ተጠቃሚዎች እንቅስቃሴ እንዲገደቡ ይደረጋል። ይህ የሚሆንበት ሰዓቶችም ተለይተው ተመርጠዋል። በቅርቡ ተግባራዊ ይደረጋል።

#ቲክቫህኢትዮጵያ

@tikvahethiopia
" የተስፋፋዉ የሙስና ሰንሰለት ሙሉ በሙሉ የሀብታም ልጅ በገንዘቡ ፤ የባለስልጣንም ልጅ በስልጣኑ ስራ እንዲቀጠር ሲያደርገው ሌላው የድሀ ልጅ ከስራ ውጭ አድርጎታል ! " - ነዋሪዎች (ከሰሞኑን በሚዛን አማን በነበረ ህዝባዊ ውይይት ላይ የተነሳ)

#ቲክቫህኢትዮጵያ

@tikvahethiopia
#IOM

" እ.ኤ.አ ከ2014 እስከ 2023 ቢያንስ 63,285 ሰዎች ሞተዋል / የገቡበት አይታወቅም " - IOM

እ.ኤ.አ. ከ2014 እስከ 2023 ባለው ጊዜ ውስጥ ቢያንስ 63,285 ሰዎች በዓለም ላይ ባሉ ስደተኞች በሚጓዙበት መስመር ህይወታቸውን አጥተዋል ወይም ጠፍተዋል።

አብዛኞቹ ህይወታቸውን ያጡት ደግሞ በውሃ መስጠም ምክንያት ነው።

እንደ ዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት (አይኦኤም) ሪፖርት መሰረት 28,854 ሰዎች የሞቱት እና የት እንደገቡ ያልታወቀው በሜዲትራኒያን ባህር ላይ ነው።

ከተመዘገቡት የሟቾች ቁጥር ወደ 60 በመቶ የሚጠጋው ከመስጠም ጋር የተያያዘ ሲሆን ከየት እንደሆነ ከተለዩት ውስጥ ደግሞ ከአንድ ሶስተኛ በላይ የሚሆኑት በግጭት ውስጥ ካሉ ሀገራት ማለትም ፦
- አፍጋኒስታን፣
- ማይንማር፣
- ሶሪያ
- #ኢትዮጵያ የሄዱ ናቸው።

ከባለፉት አስርት ዓመታት ውስጥ ለስደተኞች በጣም ገዳይ እና የከፋ የነበረው 2023 ሲሆን 8,541 ሞት ተመዝግቧል።

ዓመቱ በሜዲትራኒያን ባህር በከፍተኛ ሁኔታ ሞት የጨመረበትም ነው።

እጅግ በርካታ አፍሪካውያን የተሻለ ኑሮ ፍለጋ በሚል በህገወጥ መንገድ እጅግ አስከፊ በሆነ መንገድ ወደ #ሊቢያ ሄደው በባህር ተጉዘው አውሮፓ ለመግባት በሚያደርጉት ጥረት የባህር ሲሳይ ሆነው ቀርተዋል።

እንደ ዓለም አቀፍ ተቋማት መረጃ ፥ አስከፊው ጉዞ አድርገው እድለኛ ሆነው በህይወት ዛሬም ድረስ መረጋጋት ወደሌላት #ሊቢያ የሚገቡ ከሆነ እገታ ፣ ስቃይ ፣ ድብደባ  አለፍ ሲልም ግድያ ሊፈፀምባቸው ይችላል።

በኃላም በባህር ጉዞ ከሊቢያ አውሮፓ ለመግባት በሚያደርጉት ጉዞ ህይወታቸውን ያጣሉ።

#ቲክቫህኢትዮጵያ
@tikvahethiopia
#ኢንተርን

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ኢንተር ሀኪሞች ከስራ ሰዓትና ክፍያ ጋር በተያያዘ ቅሬታ እንዳላቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

ኢንተርን ሀኪሞቹ ምን አሉ ?

“ ከጥቂት ዓመታት በፊት የሆስፒታሉ የኢንተርን ሀኪሞች የሥራ ሰዓት ወደ 24 ሰዓታት ዝቅ እንዲል ተደርጎ ነበር።

ነገር ግን የኮሌጁ ግለሰብ / #ዳይሬክተር ሲቀየር በራሱ ውሳኔ የራሱን መላምት በመፍጠር መልሶ ወደ 36 ሰዓታት ከፍ አድርጎታል።

ይህን ውሳኔ ተከትሎ የሥራ ሰዓት ከዚህ በፊት ሴኔቱ በወሰነው መሠረት ይሁንልን ብለን ጠየቅን። ይህንንም በመጠየቃችን የተበሳጨው የዲፓርትመንት አስተባባሪ ፦
• ከቀዶ ጥገና፣
• ከህፃናት፣
• ከማህፀንና የፅንስ ዲፓርትመንት ጋር መከረ። እነዚህ ዲፓርትመንቶች አስገድደውን ሥራ ጀመርን።

የሥራ ሰዓታችን እንዲስተካከል በተደጋጋሚ ጠየቅን።

በዲፓርትመንት ደረጃ እየተሰበሰቡ ' ከዚህ በኋላ ይህን ጥያቄ የሚያየሳ ሀኪም እስከ ዲሲሚሳል ድረስ እንቀጣቸዋለን ' አሉ። ከዚህ በተጨማሪ የቀን ሥራ ሰዓታትን በአንድ ሰዓት ከፍ እንዲል ከነበረው ሕግ ውጪ ሆነብን።

ያንን ሁሉ ችለን ደመወዝ ይከፈለናል ብለን ብንጠብቅም ሳይከፈለን መጋቢት 14/2016 ዓ/ም 10ኛ ሳምንታት ጨርሰናል። ” የሚል ቅሬታ አቅርበዋል።

ለተነሳው ቅሬታ ምላሽ እንዲሰጡን በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የህክምና ሳይንስ ኮሌጅና አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ቺፍ ኤክሴኩይቲቭ ዳይሬክተር ዶ/ር አይንሸት አዳነን ጠይቀናል።

ምን አሉ ?

ዶ/ር አይንሸት ፥ “ የሰዓት ጭማሪ ለሚለው እኔ ባለኝ መረጃ መሠረት የተጨመረ ነገር የለም። ከድሮው የተቀየረ አሰራር የለም። እኔ ባለኝ መረጃ መሠረት እነርሱን #ያስፈራራቸው_ሰው_የለም ” ብለዋል።

Q. ቲክቫህ ኢትዮጵያ የኢንተርን ሀኪሞች የሥራ ሰዓት ስንት ተብሎ ነው የተወሰነው ? ሲል ጥያቄ አቅርቧል።

ዶ/ር አይንሸት አዳነ ፦

“ በክሬዲት ደረጃ ይህን ያህል የትርፍ  ፤ ይህን ያህል የመደበኛ ተብሎ የተቀመጠ ነገር የለም።

ለበርካታ አመታት ሲሰራበት ከነበረው መንገድ የተለየ እነርሱ ጋ የተጨመረ ነገር የለም። ”

Q. ዩኒቨርሲቲው 36 ሰዓታት የነበረውን የሥራ ሰዓት ወደ 24 ሰዓታት ዝቅ እንዳደረገ መረጃዎች ያሳያሉ ፣ ሀኪሞቹም ወደ 24 ሰዓት ዝቅ ተደርጎ የነበረ ወደ 36 ሰዓት ከፍ እንዳለባቸው ገልጸዋል ፣ እርስዎ ደግሞ የተወሰነ ሰዓት እንደሌለ እየገለጹ ነው ለዚህስ ያለዎት ማብራሪያ ምንድን ነው ? ስንል ጠይቀናል።

ዶ/ር አይንሸት አዳነ ፦

“ የሆነ ጊዜ ጫናው ስለበዛ በኢንተርን ሀኪሞች ጥያቄ ተነሳና ዲፓርትመንቶች ራሳቸው ከኢንተርን ሀኪሞች ጋር ውይይት አድርገው (የተወሰኑ ዲፓርትመንቶች እንዲያውም ሙሉ አይደለም) አምነውበት ወደ ተግባር ተገባ። አሳማኝ ስለሆነ የሥራ ጫናው።

ይሁን እንጂ ለተወሰነ ወራት ተግባራዊ ከተደረገ በኋላ አድረው በሚወጡትና ተተኪ ሆነው በሚገቡት ኢንተርን ሀኪሞች መካከል የርክክብ ክፍተት መፈጠሩ የጤና አገልግሎት ላይ ተፅዕኖ ስላመጣ፣ የኢንተርን ሀኪሞች ተመርቀው ሲወጡ የተሟላ እውቀት እንዳይቀስሙ ያደርጋል በሚል ወደ ነበረበት ይመለስ ተብሎ ተመልሷል። ”

Q. ‘ደመወዝ አልተከፈለንም’ ሚለው የሀኪሞቹን ቅሬታስ?

ዶ/ር አይንሸት አዳነ ፦

“ ሀኪሞቹ አጠያየቃቸው ልክ አልነበረም።

ኦረንቴሽን እንዲሰጣቸው በደብዳቤ ጭምር ቢጠሩም መገኘት አልቻሉ።

‘ይህ ካልተደረገልን (ቅሬታው ምላሽ ካላገኘ) ሥራ አንገባም’ በማለታቸውና ሳምንቱን ሙሉ ከሥራና ት/ት ገበታ ባለመገኘታቸው የሕክምና ትምህርት ቤቱ ባሳለፈው ውሳኔ፣ የ3 ወራት ደመወዝ ነው የተቀጡት። ያለ ደመወዝ እንዲሰሩ ነው የህክምና ት/ቤቱ የወሰነው። ”

#ቲክቫህኢትዮጵያ
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
🇪🇹 የፖለቲካ ፓርቲዎች ምን ይላሉ ? 🇪🇹

" ... አሁንም ቢሆን ለያዥ እና ገናዥ አስቸጋሪ የሆነው የመንግስት አቋም ነው " - መረራ ጉዲና (ፕሮፌሰር)

የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ( #ኦፌኮ ) ሊቀመንበር መረራ ጉዲና (ፕ/ር) በሀገራችን ጉዳይ ላይ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጋር ቆይታ አድርገዋል።

Q. በተለያዩ ቦታዎች ያለውን የጸጥታው ችግር እንዴት ትገመግሙታላቹ ? መፍትሄውስ ምንድን ነው ?

ፕ/ር መረራ ጉዲና ፦

" ብሔራዊ እርቅ እና ብሔራዊ መግባባት የሚባለውን እኮ ከኢህአዴግ መጀመሪያ ዓመት ጀምሮ እስከ 30 ዓመታት ስንጠይቅ ቆይተናል።

አሁንም ቢሆን መልክ አልይዝ እያለ ያስቸገረው / ለያዥና ለገናዥ አስቸጋሪ የሆነው የመንግስት አቋም ነው።

ስልጣንን በMonopoly መያዝ ከንጉሱ ዘመን ጀምሮ እንደ ባህል ተይዟል። አሁንም ቀጥሏል። የኢትዮጵያ መሪዎች ከዛ አልወጣ አሉ። ውጤቱ ደግሞ የታወቀ ነው። 

ደርግ ወጣቶችን ጨፍልቆ ነው የሄደው ፤ ኢህአዴግ ለ27 ዓመታት አገሪቱን ቀላል ያልሆነ ቀውስ ውስጥ ከቷት ነው ጡረታ የወጣው ፤ ብልጽግናም በባሰ መንገድ ይህንኑ ሁኔታ እየተከተለ ነው።

የኢትዮጵያ ጸጥታ ሁኔታ ' ከድጡ ወደ ማጡ ' ተብሎ የሚገለጽበት ደረጃ ላይ ነው።  መፍትሄው ቁጭ ብሎ መወያዬት ነው።

ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን #ከመገዳደል ፓለቲካ ወደ #መደራደር ፓለቲካ ማምጣት እጅግ በጣም አስፈላጊ ነው። "

Q. በየጊዜው የንጹሐን ሕይወት በግፍ እየተቀጠፈ ነው። ከቦታ ቦታ ተንቀሳቅሶ መስራትም የሞት ጊዜን እንደማፋጠን ሆኖ ይስተዋላል።  መፍትሄ እንዲመጣ ምን እየሰራችሁ ነው ?

ፕ/ር መረራ ጉዲና፦

" ለ30 ይሁን ለ6ቱ ዓመታት በዴሞክራሲ የሚደረገው ለውጥ በተለይ ዴሞክራሲያዊ ምህዳርን እንዲያሰፉ ደጋግመን ስንጠይቅ ነበር።

አሁንም ያን መጠየቅ ቀጥለናል። ሜዳው / ምህዳሩ ግን በተቃራኒው እየጠበበ፣ አስቸጋሪ ሁኔታዎች በአገሪቷ ላይ እየተንሰራፉ የመጡበት ሁኔታ ነው ያለው።

ምህዳሩ ካልሰፋ፣ ለዴሞክራሲ የሚደረገው ትግል መልክ ካልያዘ፣ ወጣቱንም ወደ ጫካ እየተገፋ የትም አያደርሰንም። "

Q. ከመንግስት የሚደርስባችሁ ጫና ምንድን ነው ?

ፕ/ር መረራ ጉዲና ፦

" ከኦነግ ቀጥሎ ከፍተኛ ጫና ያለበት የእኛ ፓርቲ ነው።

ለምሳሌ የዛሬ 4 ዓመት ከ200 በላይ ቢሮዎች ነበሩን፤ አሁን ያሉን 3 ብቻ ናቸው። አባሎቻችን #ግድያ እና #እስራት ይፈጸምባቸዋል። 

ለምሳሌ ፦ የምሥራቅ ወለጋ የቢሮ ኃላፊ ከተወሰደ የት እንደገባ አላወቅንም 2 ዓመታት ሊሆነው ነው።

የምሥራቅ ሸዋ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላችን ለዚያውም የዩኒቨርሲቲ የሕግ መምህር ታስሯል።

አምቦ 4 ወጣቶች ታስረው 2 ሳምንታት ሆኗቸዋል። "

Q. #ብልሹ_አሰራርና #ሙስናን በተመለከተ ኢትዮጵያ በምን ደረጃ ትገኛለች ? መፍትሄውስ ?

ፕ/ር መረራ ጉዲና ፦

" በኢትዮጵያ ታሪክ የተለዬ/የከፋ የሙስና ደረጃ ነው ያለው።

መንግስትና ተቋማቱ የአንድ ቡድን ጉዳይ አስፈጻሚ ሆነው ሲዋቀሩ እንዲህ አይነት ሁኔታዎች ይፈጠራሉ።

አሁንም መንግስት ተጠያቂነት ባለው መንገድ እንደገና ካልተዋቀረ በስተቀር፣ ከዚህ በሽታ የምንወጣበት መንገድ ያለ አይመስለኝም።

Q. የኑሮ ውድነቱ ሕዝቡን በእጅጉ አማሮታል። ፓርቲያችሁ ለመንግስት ያላችሁ ግምገማን ቢያጋሩ ?

ፕ/ር መረራ ጉዲና ፦

" ዜጎች እጅግ አስቸጋሪ ፣ ፈታኝ ሁኔታ ላይ ደርሰዋል።

መንግስት አስፈላጊ እርምጃ እንዲወስድ በተደጋጋሚ ተይቀናል።

መንግስት ግን ጆሮ ያለው አይመስልም። ችግሩ ግን እጅግ በጣም ፈታኝ ነው። "

Q. በቀጣዩ ሀገራዊ ምርጫ ተመራጭ ሆኖ ለመቅረብ ዝግጅት እያደረጋችሁ ነው ?

ፕ/ር መረራ ጉዲና ፦

" የፓለቲካ ምህዳር ለማግኘት የመገዳደል ፓለቲካው እንዲቆም እየጠየቅን ነው። ምርጫ ከዚያ በኋላ የሚመጣ ነው።

ለነፃና ፍትሃዊ ምርጫ አስቻይ የሆነ ሁኔታ ኢትዮጵያ ውስጥ የለም።

ትልልቆቹ አማራና ኦሮሚያ ክልሎች ጦርነት ውስጥ ናቸው። በዚህ ሁኔታ ምን አይነት ምርጫ እንደሚካሄ የምናየው ነው። መደራጀቱን ቀጥለናል። "

#TikvahEthiopiaFamilyAA

#ቲክቫህኢትዮጵያ
#የፖለቲካ_ፓርቲዎች_ምን_ይላሉ?

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የግንቦት 2016 ዓ/ም የርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የማጠቃለያ መግለጫ ተሰጥቷል። በዚሁ መግለጫ ቅዱስ ሲኖዶስ ፥ " በመላው ሀገራችን በተፈጠሩ ግጭቶች፣ አለመግባባቶችና የሰላም ዕጦት በርካታ የሰው ሕይወት መጥፋትና የንብረት ውድመት እንደቀጠለ በመሆኑ በእጅጉ እናዝናለን " ብሏል። ጉዳዩ የሚመለከታቸው ሁሉም ባለድርሻ አካላት ከግጭትና ከጥፋት ድርጊት ተቆጥበው የተፈጠረውን…
#Update

ቅዱስ ሲኖዶስ በምልዓተ ጉባኤው የብፁዕ አቡነ ልቃስን የአውደምህረት ንግግር ከቤተክርስቲያኒቱ ቀኖና አስተምህሮት ውጭ የሆነ ፣ ቅዱስ ሲኖዶስንም ሆነ ቤተክርስቲያንን የማይወክል ነው ሲል ውሳኔ አሳለፈ።

ንግግራቸው ቤተክርስቲያንን #ዋጋ_እያስከፈላት መሆኑና በቤተክርስቲያንና መንግሥት መካከል የነበረውን ግንኙነት እንዳሻከረው ተመላክቷል።

ቅዱስ ሲኖዶስ ፥ ብጹዕ አቡነ ሉቃስ የምስራቅ አውስትራሊያ እና በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ፅ/ቤት የገዳማት አስተዳደር መምሪያ የበላይ ኃላፊ ሊቀጳጳስ ታህሳስ 19 / 2016 ዓ/ም በአሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ እና አካባቢው ሀገረ ስብከት በሜሪላንድ ከተማ ሐመረብርሃን ቅዱስ ዮሐንስ ወቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን በዓለ ንግስ ላይ ታቦተ ህጉ በቆመበት እንዲሁም ምእመናን በተሰበሰቡበት ቤተክርስቲያንን የማይመጥንና የቅዱስ ሲኖዶስን ልዕልና ብሎም የአባትነትን ክብር ዝቅ በሚያደርግ ሁኔታ አንድን ጠቅላይ ሚኒስትር ፦
° " #ግድሉ "
° " #ዘርህ_ይጥፋ "
° " #የአድማ_ብተና_ይበትንህ " በማለት መናገራቸውን ገልጿል።

ይህ ንግግራቸው ፦
➡️ ቤተክርስቲያኒቱን የማይወክል፣
➡️ ከቀኖና ቤተክርስቲያን ውጭ የሆነ፣
➡️ ቅዱስ ሲኖዶስን የማይወክል፣
➡️ ለዘመናት ጸንቶ የቆየውን የአባቶች ክብር ዝቅ የሚያደርግ፣
➡️ የቅዱስ ሲኖዶስን ልዕልና ዝቅ የሚያደርግ፣
➡️ ከህገ ኦሪትም ሆነ ከቃለ ወንጌል ያፈነገጠ ንግግር እንደሆነ ቅዱስ ሲኖዶስ ገልጿል።

የብፁዕ አቡነ ሉቃስን ጨምሮ አንዳንድ አባቶች በተለያየ ቦታ የሚያስተለልፏቸው መልዕክቶች ቤተክርስቲያንን ለትችት እየዳረገ እንዲሁም ዋጋ እያስከፈለ ነው ተብሏል።

በቀጣይ የመግለጫ አሰጣጥ እና የትምህርተ ወንጌል አሰጣጥ ገዢ ህገ ደንብ ተዘጋጅቶ ለጥቅምት 2017 ዓ/ም ምልዓተ ጉባኤ እንዲቀርብ ተወስኗል።

ከዛሬ ጀምሮ በመላው ዓለም ያሉ አህጉረ ስብከት ስህተት እንዳይፈጸም ቁጥጥርና ክትትል እንዲያደርጉ ያን ሳያደረጉ ቀርተው የተሳሳቱ እና ከቀኖና ቤተክርስቲያን ያፈነገጡ ትምህርቶች አውደምህረት ላይ ቢተላለፉ በኃላፊነት እንደሚያስጠይቅ ጥብቅ መመሪያ እንዲተላለፍ ተወስኗል።

#ቲክቫህኢትዮጵያ
#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ቅዱስ ሲኖዶስ በምልዓተ ጉባኤው የብፁዕ አቡነ ልቃስን የአውደምህረት ንግግር ከቤተክርስቲያኒቱ ቀኖና አስተምህሮት ውጭ የሆነ ፣ ቅዱስ ሲኖዶስንም ሆነ ቤተክርስቲያንን የማይወክል ነው ሲል ውሳኔ አሳለፈ። ንግግራቸው ቤተክርስቲያንን #ዋጋ_እያስከፈላት መሆኑና በቤተክርስቲያንና መንግሥት መካከል የነበረውን ግንኙነት እንዳሻከረው ተመላክቷል። ቅዱስ ሲኖዶስ ፥ ብጹዕ አቡነ ሉቃስ የምስራቅ አውስትራሊያ…
#ሙሉ_ቃል

ቅዱስ ሲኖዶስ ስለ ብፁዕ አቡነ ሉቃስ ምን አለ ?

" ' ግደሉ ብሎ ' ማወጅ ቤተክርስቲያኒቱን የማይወክል እና ቅዱስ ሲኖዶስን የማይመጥን ንግግር ነው " - ቅዱስ ሲኖዶስ

ቅዱስ ሲኖዶስ ያሳለፈውን ውሳኔ ያቀረቡት ብፁዕ አቡነ አብርሃም ናቸው።

ብፁዕ አቡነ አብርሃም በንባብ ያሰሙት ፦

" በአሁኑ ሰዓት ላይ ትልቅ ተግዳሮትና የፈተና ምንጭ በመሆን ቤተክርስቲያናችንን ዋጋ እያስከፈሏት ያሉትን የአንዳንድ አባቶች መግለጫ እና የአውደ ምህረት ትምህርቶች እንደ አብነት በመጥቀስ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በሰፊው ተወያይቷል።

በውይይቱ የተለዩ ዋና ዋና ነጥቦች ፦

- አብዛኛው የአውደ ምህረት ስብከቶቻችን ከትምህርተ ወንጌል ይልቅ የነገር እና የደረቅ ትችት መድረክ እየሆኑ መምጣታቸው ፤

- በተለይም በመዋቅር ውስጥ የስራ መደብ የሌላቸው ተዘዋዋሪ " #ሰባኪ_ነን_ባዮች " የወገንተኝነት እና የፖለቲካ ትችትን እንደ ተከታይ ማፍሪያ በመቁጠር በሚዘሩት ፍጹም ከቃለ ወንጌል የራቀ ዘር ቅድስት ቤተክርስቲያንን ዋጋ እያስከፈላት መሆኑ ፤ ይህን ለመከላከል ጥረት በሚያደርጉ አህጉረ ስብከት ላይ ትልቅ የመልካም አስተዳደር ችግር እየተፈጠረ መሆኑ ፤

- በተለይም ብጹዕ አቡነ ሉቃስ የምስራቅ አውስትራሊያ እና በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ፅ/ቤት የገዳማት አስተዳደር መምሪያ የበላይ ኃላፊ ሊቀጳጳስ ታህሳስ 19 / 2016 ዓ/ም በሀገረ አሜሪካ በዋሽንግተን ዲሲ እና አካባቢው ሀገረ ስብከት በሜሪላንድ ከተማ ሐመረብርሃን ቅዱስ ዮሐንስ ወቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን በዓለ ንግስ ላይ ታቦተ ህጉ በቆመበትና ምእመናንም በተሰበሰቡበት እንደ ቀኖና ቤተክርስቲያን ዕለቱን አስመልክቶ ተገቢውን ትምህርተ ወንጌል ከመስጠት ይልቅ ቤተክርስቲያንን የማይመጥን እና የቅዱስ ሲኖዶስን ልዕልና ብሎም የአባትነትን ክብር ዝቅ በሚያደርግ ሁኔታ አንድን የተከበረ ጠቅላይ ሚኒስትር ፦

° " #ግድሉ "
° " #ዘርህ_ይጥፋ "
° " #የአድማ_ብተና_ይበትንህ " የሚሉ ህገወጥ እና ክብረነክ የሆኑ ንግግሮች በመናገር በፈጸሙት ያልተገባ ተግባር በቤተክርስቲያኒቱ እና በመንግስት መካከል የነበረውን ግንኙነት በማሻከር ቤተክርስቲያንን ብዙ ዋጋ እያስከፈላት ከመሆኑ በላይ ለዘመናት ጸንቶ የቆየውን የአባቶችን ክብር እና የቅዱስ ሲኖዶስን ልዕልና ዝቅ ያደረገ ተገቢነት የሌለው አድርጎት መሆኑን፤

- ክብር ይግባውና ጌታችን፣ አምላካችን መድሃኒታችን ኢያሱስ ክርስቶስ በማትዮስ ወንጌል ምዕራፍ አምስት ቁጥር ሰላሳዘጠኝ ላይ እንደተናገረው " እኔ ግን እላችኋለሁ ጉንጭህን በጥፊ ለሚመታህ ሁሉ ሁለተኛውን ደግመህ አዙርለት " ብሎ ያስተማረውን አብነት አድርጋ አትግደል የሚለውን ህገ ኦሪት አጽንታ እያስተማረች እስካሁን ድረስ ጸንታ በቆየችው እናት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አውደምህረት ላይ " ግደሉ " ብሎ ማወጅ ቤተክርስቲያኒቱን የማይወክልና ቅዱስ ሲኖዱስን የማይመጥን ንግግር መሆኑን ፤

- ልክ እንደ አቡነ ሉቃስ ፈጽሞ ጫፍ የረገጠ ባይሆንም ሌሎችም #አንዳንድ_አባቶች በተለያዩ ቦታዎች ያስተላለፏቸው መልዕክቶች አግባብነት የሌላቸውና ቤተክርስቲያንን ለትችት የዳረጉ መሆናቸውን ምልዓተ ጉባኤው በዝርዝር ገምግሟል።

ውሳኔ ፦

1ኛ. ብጹዕ አቡነ ሉቃስ የምስራቅ አውስትራሊያ እና በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ፅህፈት ቤት የገዳማት አስተዳደር መምሪያ የበላይ ኃላፊ ሊቀጳጳስ ታህሳስ 19 ቀን 2016 ዓ/ም በሀገረ አሜሪካ በዋሽንግተን ዲሲ እና አካባቢው ሀገረ ስብከት በሜሪላንድ ከተማ ሐመረብርሃን ቅዱስ ዮሐንስ ወ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን አውደምህረት ላይ " ግደሉ ፣ ዘርህ ይጥፋ፣ የአድማ ብተና ይበትንህ " ... ሌሎች ከቀኖና ቤተክርስቲያን ውጭ የሆኑ ንግግሮች ቤተክርስቲያኒቱንም ሆነ ቅዱስ ሲኖዶስን የማይወክል ከቤተክርስቲያኒቱ አስተምህሮ እና ቀኖና ውጭ የሆነ ከህገ ኦሪትም ሆነ ከቃለ ወንጌል ያፈነገጠ ንግግር መሆኑ ፤

2ኛ. በቀጣይም እንዲህ አይነት ተመሳሳይ ስህተት #በብዑጽነታቸው ሆነ በአንዳንድ አባቶች ሰባክያን ወንጌል እንዳይደገም ተፈጽሞም ቢገኝ ተገቢው የእርምት ውሳኔ ለመስጠት ይቻል ዘንድ የመግለጫ አሰጣጥ እና የትምህርተ ወንጌል አሰጣጥ አስመልክቶ ገዢ የሆነ ህገ ደንብ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት አገልግሎት መምሪያ እና በሊቃውንት ጉባኤ በኩል ተዘጋጅቶ ለጥቅምት 2017 ዓ/ም ምልዓተ ጉባኤ እንዲቀርብ ፤

3ኛ. ይህ ውሳኔ ከተወሰነበት ዕለት ጀምሮ በመላው ዓለም የሚገኙ አህጉረ ስብከት ተመሳሳይ ስህተት እንዳይፈጸም ተገቢውን ቁጥጥር እና ክትትል እንዲያደርጉ ፤ ከክትትል እና ከቁጥጥር ጉድለት ምክንያት በየትኛውም የቤተክርስቲያኒቱ አውደምህረት ላይ ለሚተላለፉ የተሳሳቱና ከቀኖና ቤተክርስቲያን ያፈነገጡ ትምህርቶች እና ንግግሮች በኃላፊነት የሚያስጠይቅ መሆኑን ለሁሉም ሀገረ ስብከት በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት በኩል ጥብቅ መመሪያ እንዲተላለፍ በማለት ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል።

ይህ ሙሉ ቃል የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ ነው። "

#ቲክቫህኢትዮጵያ

@tikvahethiopia
#Ethiopia #UAE

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ ማዕከላዊ ባንክ የተፈራረሙት ስምምነት ምንድነው ?

1ኛ. በኢትዮጵያ ብር እና የተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ (UAE) ድርሀም መካከል የምንዛሬ ልውውጥ ለማድረግ ተስማምተዋል።

ይህ ስምምነት 46 ቢሊዮን የኢትዮጵያ ብር እና 3 ቢሊዮን UAE ድርሃም በማዕከላዊ ባንክ በኩል ለመቀያየር / ለመለዋወጥ ያመቻችላቸዋል።

ዓላማው ፦
° በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የፋይናንስ እና የንግድ ትብብርን ለመደገፍ ነው።
° ድንበር ተሻጋሪ ግብይቶችን የበለጠ ውጤታማ እና ቀልጣፋ ለማድረግ ነው።

2ኛ. ኢትዮጵያ እና የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ/UAE በራሳቸው ገንዘብ (በብር እና ድርሃም) ለመገበያየት የመግባቢያ ስምምነት (MoU) ተፈራርመዋል።

ዓላማው ፦
° የንግድ ልውውጦችን በራሳቸው (በሁለቱ ሀገራት ገንዘብ) ለማድረግ ምቹ ሁኔታዎችን ይፈጥራል።
° የፋይናንስ እና የባንክ ትብብርን ያጠናክራል።
° የፋይናንስ ገበያዎችን ያዳብራል።
° የሁለትዮሽ ንግድን ያመቻቻል።
° የቀጥታ ኢንቨስትመንት ያበረታታል።
° የሙያ እና መረጃ ልውውጥ እንዲኖር ያመቻቻል።

3ኛ. የክፍያ እና የመልዕክት መለዋወጫ ስርዓቶችን ለማገናኘት የመግባቢያ ስምምነት (MoU) ተፈራርመዋል።

ዓላማው ፦
° ድንበር ተሻጋሪ የገንዘብ ልውውጦችን ውጤታማነት ያሳድጋል።
° በፋይናንሺያል ቴክኖሎጂ እና በማዕከላዊ ባንኮች ዲጂታል ምንዛሬዎች ላይ ትብብር እንዲደረግ ይረዳል።
° በክፍያ መድረክ አገልግሎቶችና በኤሌክትሮኒክ ስዊች በኩል ትብብር ያደርጋሉ። በክፍያ ስርዓቶቻቸው በኩል ኢቲስዊች እና ዩኤኢስዊች እንዲሁም በመልእክት መላላኪያ ስርዓቶች በሀገራቱ የቁጥጥር መስፈርቶች በማገናኘት ትብብር ያደርጋሉ።

የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ (UAE) በአሁን ሰዓት ጠንካራ ከሚባሉ የኢትዮጵያ ወዳጅ ሀገር አንዷ ናት።

ሁለቱም የ #BRICS+ አባል ሀገራት እንደሆኑም ይታወቃል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ያሰባሰበው ከብሔራዊ ባንክ እና ከተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ ማዕከላዊ ባንክ ነው።

#ቲክቫህኢትዮጵያ

@tikvahethiopia