TIKVAH-ETHIOPIA
1.39M subscribers
54.7K photos
1.37K videos
198 files
3.64K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
"ኢትዮጵያን በዚህ ሰአት #እያደማት ያለው ከአብራኳ የወጣ #እውቅና ፈላጊ የፌስቡክ አክቲቪስት እና የዩትዩብ ጡረተኛ ዜጋዋ ነው።"

©አዲሲቷ ኢትዮጵያ እኔ ነኝ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አክሱም ዩኒቨርሲቲ‼️

አክሱም ዩኒቨርሲቲ ግጭት እንዳይፈጠርና የመማር ማስተማር ሂደቱ ሰላማዊ እንዲሆን  አስተዋጽዖ ላበረከቱ አካላት #እውቅና ተሰጠ።

ዩኒቨርሲቲው በእስከ ዛሬው የመማር ማስተማር ሂደት ውስጥ ግጭት ያልተፈጠረበትና ተማሪዎች በሰላም ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ በማድረግ ምሳሌ መሆን ችሏል።

ይህ እንዲሆን የበኩላቸውን ላበረከቱ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ነው ዛሬ እውቅና የተሰጣቸው።

እውቅና የተሰጣቸው የሃይማኖት አባቶች፣ የአገር ሽማግሌዎች፣ የዞኑና የከተማው የተማሪዎች የወጣቶች ኮማንድ ፖስት፣ የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ እንዲሁም የአካባቢው ነዋሪዎች መሆናቸው ታውቋል።

ዩኒቨርሲቲው በሶስት ካምፓሶች የሚማሩ ከ14 ሺህ በላይ ተማሪዎች ሲኖሩት ከነዚህ መካከል አራት ሺዎቹ ዘንድሮ የገቡ ናቸው።

ምንጭ፦ ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የሶማሊያ ካቢኔ በነገው ዕለት አስቸኳይ ስብሰባ እንደተጠራ ተሰምቷል። አስቸኳይ ስብሰባው ፤ ዛሬ በሶማሌላንድ (ሶማሊያ ሶማሌላንድን እንደ ሰሜናዊ ክልሏ ነው የምትቆጥራት) እና በኢትዮጵያ መካከል ተደርጓል ስለተባለው ስምምነት በተመለከተ ተወያይቶ ውሳኔ ለማሳለፍ ነው ተብሏል። ከዚሁ ከነገው አስቸኳይ የካቢኔ ስብሰባ ዝግጅት ጋር በተያያዘ #በአሁን_ሰዓት በሶማሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት…
#Ethiopia 🤝 #Somaliland

" ታሪክ እየተሰራ ነው " - አሊ ሀሰን ሞሃመድ

ኢትዮጵያ እስካሁን በይፋ ከሶማሌላንድ ጋር በተፈረመው የትብብር ስምምነት የባህር በር ለመጠቀም እና የባህር ኃይል ቤዝ እንዲኖራት በምላሹ ደግሞ የ " ሶማሌላንድን " የነፃ ሀገርነት እውቅና እንደምትሰጥ አንዲትም ቃል #አልተናገረችም

የሶማሌላንዱ ፕሬዜዳንት ግን ከስምምነቱ በኃላ ኢትዮጵያ ለሶማሌላንድ የነፃ ሀገርነት ውቅና እንደምትሰጥ በምላሹ የባህር በር እና የባህር ኃይል እንዲኖራት 20 ኪሎሜትር መሬት በሊዝ እንደምትሰጥ ገልጸዋል።

የራስ ገዟ ሶማሌላንድ ባለስልጣናትም ተመሳሳይ መረጃዎችን ሰጥተዋል።

ለአብነት አሊ ሀሰን ሞሃመድ የኢንፎርሜሽን ሚኒስትር ፤ " ታሪክ እየተሰራ ነው " ብለዋል።

ኢትዮጵያ በሊዝ የ20 ኪሎሜትር የባህር በር ተጠቃሚ እንድትሆን በምላሹ ደግሞ #እውቅና እና የኢኮኖሚ እድገት እንደምትሰጥ ገልጸዋል።

" ይህ ጨዋታ ቀያሪ፤ ትልቅ ትርጉም ያለው ስምምነት ነው " ያሉት ባለስልጣኑ " ትልቅና ደፍረትን የሚጠይቅ እርምጃ ነው ፤ ወደፊት ለሶማሌላንድ እና ኢትዮጵያ የብሩህ አድማስ በሮችን የሚከፍት ነው " ብለዋል።

ይህንኑ የአሊ ሀሰን ሞሀመድ ሃሳብን ሞባረክ ታኒ የተባሉት የፕሬዜዳንቱ ዋና ፀሐፊ ተጋርተውታል።

በሌላ በኩል ፤ ሶማሊያ እንደራሷ አንድ ግዛት የምታያት " ሶማሌላንድ " ከኢትዮጵያ ጋር ተፈራረመች ስለተባለው የመግባቢያ ስምምነት በተመለከተ ነገ ካቢኔዎቿ አስቸኳይ ስብሰባ ተቀምጠው ውሳኔ ያሳልፋሉ ተብሏል።

ለነገው አስቸኳይ ስብሰባ ዝግጅት ዛሬ ምሽት በጠቅላይ ሚኒስትሩ ቢሮ ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ምክትላቸው እና ከፍተኛ የካቢኔ አባላት የተገኙበት ሰብሰባ ሲደረግ አምሽቷል።

የሶማሊያ ባለስልጣናትም የመግባቢያ ስምምነቱ ክፉኛ እንዳስቆጣቸው ተነግሯል።

የሶማሊያ የማዕድን እና ነዳጅ ሚኒስትሩ አብዲሪዛቅ ሞሀመድ ፤ " ሶማሊያ አትከፋፈልም ፤ በሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነታችን አንደራደርም " ብለዋል።

ሚኒስትሩ ፤ " ኢትዮጵያ ከግዛት (ክልል) አስታዳዳሪ ጋር ወደብን ለመከራየት / ወታደራዊ ስምምነት (MOU) ማድረግ እንደማትችል በደንብ አድርጋ ታውቃለች ይህ ስልጣን ሙሉ በሙሉ የፌዴራላዊ ሶማሊያ መንግሥት ነው ፤ ኢትዮጵያ የግዛት አንድነታችንን የሚጥስ ተግባር መፈፀም አትችልም " ሲሉ ገልጸዋል።

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የዛሬውን " ታሪካዊ " የተባለ የትብብር ስምምነት መፈረሙን ተከትሎ " ኢትዮጵያ #ቀይ_ባህርን የመጠቀምና በዛውም የማልማት ፍላጎት ከሶማሌላንድ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈርሟል " ሲሉ አብስረዋል።

ዶክተር ዐቢይ፤ " እኛ ያሉንን ሃብቶች የመጋራት ፣ የመካፈልና በጋራ የመልማት ፍላጎት እንጂ ማንንም በኃይል የማስገደድ ፍላጎት የለንም ስንል የነበረው ሃሳብ በተግባር ታይቷል " ሲሉም ነው ያሳውቁት።

#ቲክቫህኢትዮጵያ

@tikvahethiopia