TIKVAH-ETHIOPIA
1.39M subscribers
54.7K photos
1.37K videos
198 files
3.64K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ስጋ

የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ሰይድ እንድሪስ የ2016 ዓ/ም የገና በዓል ዝግጅትን በተመለከተ ምን አሉ ?

* ሰሞኑን የተለያዩ ኦፕሬሽኖች ሰርተናል። 200 ቤቶች አካበቢ ለማየት ሞክረን ከዛ ውስጥ በ30 ቤቶች ሕገ ወጥ ስጋ የተገኘበት ሁኔታ ነው የተፈጠረው።

* 15 ቤቶች ሙሉ ለሙሉ #አንዲታሸጉ ያደረግንበት ፣ ሌላ ተጨማሪ 10 ቤቶች ደግሞ ሕገ ወጥ (ሀሰተኛ) የስጋ ምርመራ ሰነድ ይዘው ህብረተሰቡን እያታለሉ ሥጋ ሲሸጡ የነበሩበት ሁኔታ መኖሩን ያዬንበት ሂደት አለ።

* አጠቃላይ ባደረግነው ሂደት 1,500 ኪሎግራም ሕገ ወጥ በሦስት ቀናት ውስጥ ተሰብስቦ እዚህ መጥቶ እንዲወገድ የተደረገበት ሂደት አለ። 

* ባደረግነው ዳሰሳ #የሕገወጥ እንስሳት እርድ አለ። ከዚያ ውጪ ግን በእምነትም ይሁን በባህላችን ባዕድ የሆኑ እንስሳት ታርደው ወደ ገበያ የቀረቡበት ሂደት የለም። የተያዘው ሥጋ፦
- የበሬ ፣
- የፍዬል
- የበግ ፣ ግን በሕገ ወጥ መንገድ የታረደ ነው።

* የበሬ ስጋ የአንድ (1) ኪሎ ዋጋ ከ550 እስከ 570 ብር በዕለቱ ሽያጭ ይከናወናል። በአራት መስኮቶች የበግ እና የፍየል ስጋም ሽያጭ ይከናወናል። የበግ ስጋ በ500 ብር ፣ የፍየል በ510 ብር በኪሎ ግራም ለበዓሉም ለመደበኛ ቀናትም የሚያቀርቡበት በዚህ ደረጃ ተዘጋጅቷል።

" የባዕድ እንስሳት / #አህያ ስጋ እየተሸጠ ነው " ሲባል በነበረው ጉዳይ ምን ተባለ ? ያንብቡ👇
https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-01-05

#ቲክቫህኢትዮጵያ

@tikvahethiopia