TIKVAH-ETHIOPIA
1.39M subscribers
54.7K photos
1.37K videos
198 files
3.64K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ሱዳን

አብደላ ሃምዶክ #የሱዳን ጠቅላይ ሚኒስትር በመሆን በትናንትናው እለት ተሹመዋል። ሌተናል ጄነራል አብደል ፈታህ አብደልራህማን ቡርሃን አዲስ የተቋቋመው የሱዳን ሉአላዊ ምክር ቤት መሪ በመሆን መሾማቸውን ተከትሎ ነው አብደላ ሃምዶክ ጠቅላይ ሚኒስትር በመሆን የተሾሙት።

እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር ከ2011 ጀምሮ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ኢኮኖሚስት በመሆን ሲያገለግሉ የነበሩት አብደላ ሀምዶክ ከሚሰሩበት አዲስ አበባ ወደ ካርቱም በማቅናት በትናንትናው እለት ቃለ መሃላ ፈጽመዋል።

ምንጭ:- ቢቢሲ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ሱዳን_ያስተናገደቻቸው_ሰልፎች

በዳቦ ዋጋ መናር ምክንያት ፕሬዝዳንት ኦማር ሀሰን አልበሽር ከስልጣን እንዲነሱ ያደረገው የሱዳን አብዮት 2ተኛ ዓመቱ በተለያዩ ስሜቶች እየታሰበ ነው፡፡

ከዛሬ 2 ዓመት ወዲህ ፕሬዝዳንት አልበሽርን በመጣል አዲስ የሽግግር መንግስት የተቋቋመ ሲሆን ወታደሩንና ሲቪሉን የሚወክሉ መሪዎች ሀገሪቱን እያስተዳደሩ ነው፡፡

ዛሬ ካርቱምን ጨምሮ በሱዳን የተለያዩ ከተሞች በተካሔዱ ሰልፎች በአንድ ወገን አብዮቱን የሚደግፉ አካላት በሌላ በኩል ደግሞ ተቃዋሚዎችም ድምጻቸውን አሰምተዋል፡፡

አብዮቱን በመደገፍ ሰልፍ የወጡ ሰልፈኞች የአብዮቱ ዓላማ ግን መስመሩን መሳቱን በመጥቀስ ቁጣቸውን አሰምተዋል፡፡

የኑሮ ውድነት እና የኢኮኖሚ ቀውስን በመቃወም ከሁለት ዓመት በፊት አብዮት ቢፈነዳም እነዚህን ችግሮች ከመቅረፍ አንጻር አብዮቱ ምንም አልፈየደም በሚል የተቃውሞ ድምጾች ተስተጋብተዋል፡፡

በሱዳን ያለው የኑሮ ውድነት ፣ ከፍተኛ የዳቦ እጥረት እና የሀገሪሩ ኢኮኖሚያዊ ቀውስ እንደቀጠሉ ናቸው፡፡

ከአብዮቱ በተቃራኒ በመቆም የፕሬዝዳንት አልበሽርን መንግሥት በመደገፍ አደባባይ የወጡም አሉ፡፡ እነዚህ አካላት የአልበሽር ስርዓት እንዲመለስ የሚፈልጉ ናቸው፡፡

ያም ሆነ ይህ ታዲያ የሀገሪቱ ሉኣላዊየሽግግር መንግስት ሊቀ መንበር በአብዮቱ 2ኛ ዓመት ላይ ትኩረት ያደረጉ መልዕክቶችን አስተላልፈዋል፡፡

የሀገሪቱ የጦር ኃይሎች ዋና አዛዥ እና የሉኣላዊ ሽግግር ምክር ቤት ሊቀ መንበር አብዱልፈታህ አል-ቡርሃን ፣ የአልበሽር አገዛዝ የተወገደበትን ሁለተኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ ባስተላለፉት መልዕክት ሰራዊቱ በአብዮቱ የተገኙ ውጤቶችን እንደሚያስጠብቅ ተናግረዋል።

አል ቡርሃን በትዊተር ሱዳናውያንን እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል፡፡

ምንጭ፦ አል ዓይን (AlAIN)

@titikvahethiopia
#Egypt #Ethiopia #Sudan

በሕዳሴ ግድብ ዙሪያ በኢትዮጵያ፣ ሱዳን እና ግብፅ መካከል የሚደረገው ድርድር በሚቀጥለው #እሁድ ታህሳስ 25 ቀን 2013 ዓ.ም እንደሚቀጥልም አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ገልፀዋል።

አምባሳደሩ ይህን የገለፁት በሰጡት ሳምንታዊ መግለጫ ላይ ነው።

ከታላቁ ህዳሴው ግድብ ድርድር ራሷን አግልላ የነበረችው #ሱዳን ወደ ድርድሩ እንደምትመለስ በቅርቡ ይፋ ማድረጓ ይታወቃል፡፡

አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በሰጡት መግለጫ ላይ ያነሷቸውን ሌሎች ጉዳዮች በዚህ ማግኘት ትችላላችሁ : telegra.ph/ALAIN-12-29 (መረጃውን አዘጋጅቶ ያሰራጨው አል ዓይን ኒውስ ነው)

@TIKVAHETHIOPIA @TIKVAHETHIOPIABOT
#GERD🇪🇹

"...የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የምትገነባው ሙሌት አካሂዳ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት ነው" - ፕ/ር ያዕቆብ አርሳኖ

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር እና የዓባይ ውሃ ጉዳይ ተመራማሪ ፕሮፌሰር ያዕቆብ አርሳኖ ፥ ኢትዮጵያ ታላቁን የህዳሴ ግድብ የምትገነባው ሙሌት አካሂዳ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት በመሆኑ የሙሌት ጉዳይ ብዙ የሚያነጋግር እንዳልሆነ ገለፁ።

ፕሮፌሰር ያዕቆብ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ በሰጡት ቃል፤ ሁለተኛው ዙር የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የውሃ ሙሌት ጉዳይ ኢትዮጵያውያን እና የዓለምን ፖለቲከኞች ቀልብ በእጅጉ የሳበ ክስተት ነው ብለዋል።

በተለይ ግብጽና ወደግብጽ ተለጥፋ ያልተገባ ጭቅጭቅ ውስጥ የምትገኘው #ሱዳን በተነዙ የሐሰት ፕሮፓጋንዳዎችና እና አሳሳች መግለጫዎች የተነሳ የህዳሴው ግድብ ሁለተኛው እርከን ሙሌት በተጋነነ ወሬ ውስጥ ነበር ሲሉ ገልፀዋል።

መታወቅ የነበረበትም ሆነ አሁንም መታወቅ ያለበት ጉዳይ #ኢትዮጵያ ታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የምትገነባው ሙሌት አካሂዳ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት መሆኑ ነው ሲሉ አስገንዝበዌ።

ይህ እንደሚሆን ደግሞ በኢትዮጵያ መንግስት ጥናት እና ዲዛይን ፣ በድርድሩ ሂደት ፣ በግድቡ ግንባታ ስራና በየጊዜው በሚወጡ በኢትዮጵያ መንግስት መግለጫዎች መገለጹን አስታውሰዋል።

#ኢፕድ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ፌልትማን ዳግም ኢትዮጵያ ሊመጡ ነው። የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ጄፍሪ ፌልትማን ነገ ለሁለት ቀናት ጉብኝት ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት አሳውቋል። የጉዞአቸው ዓለማ ሰሜን ኢትዮጵያ እየተካሄድ ያለው ግጭት አሳሳቢነቱ እየጨመረ በመምጣቱ መሆኑን ሚኒስቴሩ አሳውቋል። ፌልትማን ወደ ሀገራችን ኢትዮጵያ ሲመጡ ይህ ለሶስተኛ ጊዜ ነው የሚሆነው ከዚህ ቀደም…
ፎቶ ፦ ፌልትማን ኢትዮጵያ ገብተዋል።

የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ የሆኑት ጄፍሪ ፌልትማን ዛሬ ኢትዮጵያ (አዲስ አበባ) ገብተዋል፤ ወደ ኢትዮጵያ ከገቡ በኃላም ከሙሳ ፋኪ ማሃመት ጋር ተገናኝተው መክረዋል።

የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ማሃማት ፌልትማንን በይፋዊ የትዊተር ገፃቸው ጄፍሪ ፌልትማንን በቢሯቸው ተቀብለው በ #ኢትዮጵያ እና #ሱዳን ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ መምከራቸውን አሳውቀዋል።

Credit : Moussa Faki Mahamat (Twitter)

@tikvahethiopia
#ETHIOPIA #SUDAN

ዛሬ #ኢትዮጵያ ሀገራችን ከጎረቤት ሀገር #ሱዳን ጋር የአቋም መፈተሻ ጨዋታዋን እያደረገች ትገኛለች።

ይህ ጨዋታ እየተካሄደ የሚገኘው የሁለቱም ሀገራት ብሄራዊ ቡድኖች በአፍሪካ ዋንጫ ለመካፈል ባቀኑባት ካሜሮን ሀገር ነው።

የሀገራችን የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከቀናት በፊት በትልቁ የአፍሪካ የእግር ኳስ ውድድር የአፍሪካ ዋንጫ ላይ ለመሳተፍ ከውድድሩ ቀደም ብሎ ወደ ካሜሮን አቅንቷል።

ቡድናችን ካሜሮን ከደረሰ በኃላ በየዕለት ልምምድ እየሰራ ውድድሩ እስኪጀመር እየተጠባበቀ ይገኛል። ዛሬ አቋሙን የሚፈትሽበት ጨዋታ እያደረገ ነው።

ሀገራችን በተወከለችበት ትልቁ የአፍሪካ የእግር ኳስ ውድድር መድረክ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላትም ወደ ስፍራው ከብሄራዊ ቡድኑ ጋር ያቀኑ ሲሆን በስፖርት ገፃችን ላይ መረጃዎችን ያካፍላሉ።

የቲክቫህ ስፖርት ገፅ ፦ https://t.me/+VvwzStMNcNHmhK0x

@tikvahethsport
በሱዳን 2 ሰዎች ተገደሉ።

ጎረቤት ሀገር #ሱዳን በተቃውሞ መናጧን የቀጠለች ሲሆን ትላንት እሁድ በተደረገ የተቃውሞ ሰልፍ የ2 ሰዎች ህይወት ማለፉን ለማወቅ ተችሏል።

በኦምዱርማን እንዲሁም በካርቱም በሀገሪቱ የተደረገውን መፈንቅለ መንግስት በመቃወም ሰልፍ አካሂደዋል።

የሱዳን የዶክተሮች ማዕከላዊ ኮሚቴ በትላትናው ሰልፍ የሁለት ሰዎች ማለፉን ሪፖርት ያደረገ ሲሆን አንደኛው ሟች ትላንት አንዱ ደግሞ ዛሬ ነው የተገለፀው።

ተቃውሞ ከተነሳ ጀምሮ እስካሁን ድረስ የተገደሉ ሰዎች 63 ደርሷል።

@tikvahethiopia
ከዓለም ዙሪያ ፦

➡️ #አሜሪካ - በኒውዮርክ የተቃውሞ ሰልፍ ተካሂዷል። ሰልፉ በመሳሪያ የገዙ ጥቃቶችን ለማውገዝ የተካሄደ ነው። ሰልፉ የተካሄደው አንድ ወጣት በቴክሳስ ሮብ በሚሰኝ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት 19 ህፃናት ተማሪዎችን እና 2 መምህራንን በአሰቃቂ ሁኔታ ከገደለ ከቀናት በኃላ ነው።

➡️ #ስፔን - በሰሜናዊ ስፔን ላ ሪዮጃ ክልል በባዮዲዝል ማምረቻ ፋብሪካ ላይ በደረሰ ፍንዳታ ቢያንስ 2 ሰዎች መሞታቸው ሪፖርት ተደርጓል።

➡️ #የመን - በየመን አደን ከተማ ሰዎች በሚበዙበት በተጨናነቀ ገበያ ላይ በደረሰ ፍንዳታ በትንሹ 4 ሰዎች ሲሞቱ በርካቶች መቁሰላቸው ታውቋል፤ እስካሁን ለጥቃቱ ኃላፊነት ወስዳለሁ ብሎ ብቅ ያለ የለም።

➡️ #ሱዳን - ከወራት በፊት በሱዳን የተካሄደውም ወታደራዊ መፈንቅለ መንግስት ተከትሎ የተነሳው ተቃውሞ አሁንም ያልበረደ ሲሆን ትላንትና በሺዎች የሚቆጠሩ ተቃዋሚዎች በካርቱም ጎዳናዎች ላይ ተቃውሞ አሰምተዋል። የጥቅምቱ መፈንቅለ መንግስት ሀገሪቱን ወደ ፖለቲካዊ ቀውስ አስገብቷል።

➡️ #ጣልያን - የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ማሪዮ ድራጊ የሩሲያው ፕሬዜዳንህ ፑቲን አሁን ላይ በዓለም የሚየው የምግብ ችግር "በሩሲያ ላይ የተጣለው ማዕቀብ ነው " ብለው እንደነገራቸው ተናግረዋል። የሩስያ እና ዩክሬን ጦርነት ከጀመረ አንስቶ ምዕራባውያን ሀገራት ሩስያ ላይ እጅግ ከፍተኛ የሚባሉ ማዕቀቦችን እየጣሉ እንደሆነ ይታወቃል። ለእነዚህ ማዕቀቦችም ሩስያ ምላሽ ከመስጠት ወደኃላ አላለችም።

➡️ #ቱርክ #ፈረንሳይ - የቱርክ ፕሬዜዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ከፈረንሳይ ፕሬዜዳንት ኢማኑኤል ማክሮን የስውዲን እና ፊንላንድ ለNATO አባልነት ባቀረቡት ማመልከቻ፣ በዩክሬን ሩስያ ጦርነት፣ በቀጠናዊ ጉዳዮች እና በሌሎችም ጉዳዮች ላይ ተገናኝተው መክረዋል።

@tikvahethiopia
ከዓለም ዙሪያ 🌍

➡️ #ሶማሊያ ፦ በሶማሊያ እየተባባሰ ያለው የድርቅ ሁኔታ ለምግብ እጦት እና ለውሃ እጥረት የተጋለጠው ህዝብ ቁጥር 8 ሚሊየን ሊደርስ ይችላል የሚል ከፍተኛ ስጋትን ፈጥሯል። አሁን ላይ በሀገሪቱ ያለው ድርቅ በገጠር 66 ወረዳዎችና ሰፊ አካባቢዎች ክፉኛ መቷል።

➡️ #ዩክሬን ፦ ዩክሬን በጦርነቱ ምክንያት 243 ህጻናት መሞታቸውን እና 444 ህፃናት መቁሰላቸውን አረጋግጫለሁ ስትል አስታውቃለች።

➡️ #ግብፅ ፦ የግብፅ ፍርድ ቤት በቀድሞው የፕሬዚዳንት እጩ አብደል ሞኒም አቡል ፎቱህ እና በሙስሊም ወንድማማች ቡድን ውስጥ ያሉ ታዋቂ ግለሰቦችን " የሀሰት ዜና በማሰራጨት " እና መንግስትን ለመገልበጥ አሲረዋል በሚል በእስራት እንዲቀጡ ወስኗል። አቡል ፎቱህ 70 ዓመታቸው ሲሆን የ15 አመት እስራት ተፈርዶባቸዋል፣ መሐመድ አል-ካሳስ የአቡል ፎቱህ " Strong Egypt Party " ምክትል ኃላፊ የ10 ዓመት እስራት ተፈርዶባቸዋል፣ እንዲሁም የ15 አመት እስራት የተፈረደባቸው የወንድማማችነት የቀድሞ የበላይ መሪ ማህሙድ ኢዛት ሲሆኑ እሳቸው ቀደም ሲልም በሌሎች ክሶች የእድሜ ልክ እስራት ተፈርዶባቸው ነበር።

➡️ #ሱዳን ፦ የሱዳኑ ወታደራዊ መሪ ጄኔራል አብደል ፈታህ አል ቡርሃን ጥቅምት 25 የተደረገውን መፈንቅለ መንግስት ተከትሎ ተጥሎ የነበረውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መነሳቱን አሳውቀዋል። ቡርሃን " የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን በአገር አቀፍ ደረጃ ተነስቷል " ብለዋል።

➡️ #ሩስያ ፦ የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ የዩክሬን #ዶንባስ ግዛትን ነፃ ማውጣት ለሞስኮ ምንም ቅድመ ሁኔታ የሌለው ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ መሆኑን ገልፀው ሌሎች ግዛቶች የወደፊት ዕጣ ፈንታቸውን ለራሳቸው መወሰን አለባቸው ብለዋል።

#ቲአርቲ #AJ #ኤፒ #SNTV

@tikvahethiopia
#China

ኢትዮጵያ ፣ ኤርትራ እና ሱዳን ስለ ቻይና-ታይዋን ጉዳይ ምን አሉ ?

#ኢትዮጵያ

ሀገራችን ኢትዮጵያ የሰሞኑን የቻይና-ታይዋን ጉዳይ የተከሰተውን ውጥረት በትኩረት እየተከታተለች መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ አለም ለኢዜአ ተናግረዋል።

አምባሳደር መለስ ፤ ኢትዮጵያ ለረጅም ዓመታት ስታራምድ የቆየችውን የአንድ ቻይና ፖሊሲ አቋሟን እንዳጸናች መሆኑን ተናግረዋል።

" የኢትዮጵያ የአንድ ቻይና ፖሊሲ አቋም ዛሬ የተጀመረ አይደለም ያሉት " አምባሳደር መለስ፤ " ከቻይና ጋር በነበረን ግንኙነት ሁሉ የኢትዮጵያ መንግስታት አፅንተው የያዙት አቋም ነው " ብለዋል።

አሁንም ቢሆን ኢትዮጵያ ለ #አንድ_ቻይና ፖሊሲ ፅኑ አቋም አላት ያሉ ሲሆን ፖሊሲውን ኢትዮጵያ አባል የሆነችባቸው የተመድና የአፍሪካ ህብረት የሚያራምዱት አቋም መሆኑን ገልፀዋል።

#ሱዳን

ሱዳን ለአንድ ቻይና መርህ ድጋፏን እንደምትሰጥ አሳውቃለች። ታይዋንም የቻይና ግዛት አካል መሆኗን ገልጻለች።

ሱዳን ፤ ቻይና ሉዓላዊነቷን እና የግዛት አንድነትዋን በመጠበቅ ረገድ የምታደርገውን እንቅስቃሴ እንደምትደግፍም አስታውቃለች።

#ኤርትራ

ኤርትራ የአሜሪካ አፈጉባዔ ወደ ታይዋን ያደረጉት ጉዞ ከዓለም አቀፍ ህግና መርህ ያፈነገጠ ነው ብላለች።

የአፈጉባኤዋ ድርጊት የቻይና መንግስት ሉዓላዊነት ደንቦችን እና ድንጋጌዎች እንዲሁም " የአንድ-ቻይና " ፖሊሲ የሚጻረር እና የቻይናውያን ውህደት ሂደትን የሚያደናቅፍ ነው ስትል ገልፃለች።

ኤርትራ፤ አሜሪካ ቻይናን ለመቆጣጠርና ለመያዝ ጥረት እያደረገች ነው ብላ ድርጊቱ አጸያፊ ነው ብላለች።

#CGTN #ENA #AlAIN #Shabait

@tikvahethiopia
ፎቶ፦ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ት ዐቢይ አሕመድ እና ልዑካቸው ለስራ ጉብኝት #ሱዳን፤ ካርቱም ገብቷል።

የስራ ጉብኝቱ ለአንድ ቀን እንደሆነ ተገልጿል።   

የሱዳን ሪፐብሊክ የሽግግር ሉዓላዊነት ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ጄኔራል አብደል ፈታሕ አል ቡርሃን ለጠቅላይ ሚኒስትሩ እና ልዑካቸው አቀባበል አድርገውላቸዋል።

Photo Credit : PMOEthiopia

@tikvahethiopia
#ኤርትራ #ሱዳን

የጎረቤት ሀገር ሱዳን ሉዓላዊ ምክር ቤት ምክትል ፕሬዜዳንት የሆኑት ጄነራል ሞሀመድ ሃምዳን ደጋሎ (ሄመቲ) ዛሬ ሰኞ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ወደ #ኤርትራ፣ አስመራ ማቅናታቸው ተሰምቷል።

ሄሜቲ በአስመራ ቆይታቸው ከፕሬዜዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ጋር በሁለቱ ሀገራት የሁለትዮሽ ግንኙነት እና በሁሉም መስክ ግንኙነታቸውን ማሳደግና ማጎልበት በሚችሉበት ሁኔታ ላይ ይፋዊ ውይይት ያደርሉ ተብሏል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የሱዳን ውጊያ 6ኛ ቀኑን ይዟል። በተዋጊዎቹ ኃይሎች መካከል ለ2ኛ ጊዜ ትላንት የ24 ሰዓታት ለሰብዓዊት ተኩስ ለማቆም ሙከራ ተደርጎ የነበር ቢሆንም ሳይሳካ ቀርቶ ውጊያው ቀጥሎ እንደነበር ተሰምቷል። የተኩስ አቁም እንዲደረግ የተሞከረው ዜጎቻቸውን ከሱዳን ለማስወጣት እየጣሩ ባሉ ሀገራት ግፊት መሆኑን አልጀዚራ ዘግቧል። ዛሬም በሱዳን የተለያዩ ከተሞች ውጊያ መኖሩ በተለይ በካርቱም የፕሬዜዳንቱ ቤተመንግስት…
#ሱዳን

" ቤተሰቦቻችን ስላሉበት ሁኔታ ለማወቅ አልቻልንም ፤ጭንቀት ላይ ነን "

በሱዳን እየተካሄደ ያለው ውጊያ ዛሬ 6ኛ ቀኑን መያዙ ይታወቃል።

በሱዳን ያሉ ቤተሰቦቻችን ያሉበትን ሁኔታ ለማወቅ ካርቱም ወዳለው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ስልክ ብንደውልም ምላሽ አላገኘንም ሲሉ እዚህ ኢትዮጵያ የሚገኙ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት መልዕክት ልከዋል።

በሱዳን ያሉ ቤተሰቦቻቸውን ለማግኘት ባለመቻላቸው እንደተጨነቁ የገለፁት እንዚሁ አባላት ፤ ማንን መጠየቅ እንዳለብን ግራ ገብቶናል ይህ ጉዳይ የሚመለከተው አካል ምላሽ ሊሰጠን ይገባል ብለዋል።

ለበርካታ ኢትዮጵያውያን ሁለተኛ ቤት በሆነችው ሱዳን ውስጥ ኢትዮጵያውያን ለስራ እና በቋሚነት ለኑሮ እንደሚገኙ ይታወቃል።

የሰሞኑ የሱዳን ውጊያ ደግሞ እዛ ያሉትን ብቻ ሳይሆን እዚህ ያሉ ቤተሰቦችንም ጭምር ጭንቀት ውስጥ ጥሏል።

ከትላንት በስቲያ በሱዳን የኢትዮጵያ ኤምባሲ ፤ በሱዳን እየተካሄደ ባለው ውጊያ በርካታ ሲቪሎች ለጉዳት መዳረጋቸውና ህይወትም እየተቀጠፈ መሆኑን በመግለፅ ከእነዚህ መካከል #ኢትዮጵያውያን እንደሚገኙበት መረጃዎች እንደደረሱት አሳውቋል።

ኤምባሲው ምን ያህል ኢትዮጵያውያን እንደሞቱ እና እንደተጎዱ በዝርዝር ባይገልፅም ይህን አስቸጋሪ ጊዜ ለማለፍ ኢትዮጵያዊን የተቻላቸውን ሁሉ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አሳስቧል።

መረጃ ለመለዋወጥ እና ለምክክር የኤምባሲው ባልደረባ የሆኑትን አቶ ነጅብ አብደላ በስልክ ቁጥር +249911646547 ማነጋገር እንደሚቻልም ገልጿል።

@tikvahethiopia
#ሱዳን #ኢትዮጵያ

የሱዳን ጋዜጦች የኢትዮጵያን ጦር የተመለከተ ሀሰተኛ ዜናዎች ሲያሳራጩ ነበር።

የተሰራጨው ዜና ምን ነበር ?

ከትላንት ምሽት ጀምሮ የሱዳን ሚዲያዎች በተለይም በ " አልሱዳኒ ጋዜጣ " የኢትዮጵያ ጦር በሱዳን ላይ ጥቃት ከፍተ የሚሉ ሀሰተኛ መረጃዎች ሲያሰራጩ ነበር።

አል ሱዳኒ ፤ በትናንትናው እለት የኢትዮጵያ ጦር በታንክ፣ በታጠቁ ተሽከርካሪዎች እና በብዙ እግረኛ ወታደሮች በመታገዝ በ " አልፋሽቃ አል-ሱግራ " ላይ ወረራ እና ጥቃት ፈጽሟል ፤ የሱዳን ጦርም ጥቃቱን በመመከተ ከፍተኛ ኪሳራ አድርሷል ሲል ነው ሀሰተኛ መረጃ ያሰራጨው።

ይህንን ዜናም በርካቶች ወዲያውኑ ሲቀባበሉት እና ለብዙሃኑ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚ ሲያዳርሱ ነበር።

ይህ መሰል ዜና እንዲሰራጭ ያደረገው የ " አልሱዳኒ " ጋዜጠኛ በትክክለኛ የፌስቡክ ገፁ የተሰራጨው ዜና ትክክል እንዳልሆነ በመግለፅ አንባቢውን ይቅርታ ጠይቋል።

" ዜናው እውነት አይደለም " ያለው ይኸው ጋዜጠኛ " ወረራም አልነበረም ፣ በሱዳንና በኢትዮጵያ ጦር መካከልም ግጭት አልነበረም " ብሏል።

የሰራው ሀሰተኛ ዜና በተፈጠረው ግራ መጋባትና መደናገር እንዳዘነ ይኸው ጋዜጠኛ በማህበራዊ ትስስር ገፁ ፅፏል።

ሱዳን እጅግ በጣም ሰፊ የኢትዮጵያ መሬትን በኃይል ተቆጣጥራው እንደምትገኝ ይታወቃል። ይህን ያደረገችውም በትግራይ ክልል ጦርነት መነሳቱን እንደ አጋጣሚ በመጠቀም ነበር።

ከዚህ በኃላም ኢትዮጵያ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው የድንበር ውዝግብ በጠረጴዛ ዙሪያ በሰላም እና በንግግር መፈታት እንዳለበት በተደጋጋሚ አቋሟን ስትገልፅ ቆይታለች።

ከሰሞኑን በሱዳን የውስጥ ኃይሎች መካከል በተፈጠረው ጦርነት ሳቢያ ሱዳን ከገባችበት ከፍተኛ ትርምስ እንድትወጣ ለማድረግ ኢትዮጵያ ሁሉን አቀፍ ድጋፍ እንደምታደርግ አሳውቃለች።

ግጭት ውስጥ ያሉት የሱዳን ኃይሎችም ግጭት እንዲያረግቡ የሰላም ጥሪ ያቀረበችው ኢትዮጵያ ላለው ችግር አፍሪካዊ መፍትሄ ለመስጠት አዲስ አበባ በሯ ሁሌም ክፍት መሆኑን አቋሟን ገልጻለች።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update RSF የግብፅ ወታደሮችን ለቀይ መስቀል አስረከበ። የሱዳን ጦርነት በጀመረበት ወቅት በጄነራል መሐመድ ሃምዳን ደጋሎ የሚመራው የሱዳን ፋጥኖ ደራሽ (RSF) ኃይል እንደማረካቸው የገለፃቸውን የግብፅ ወታደሮችን ዛሬ ጥዋት ለዓለም አቀፉ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ማስረከቡን አሳውቋል። RSF ለቀይ መስቀል ያስረከባቸው የግብፅ ወታደሮች በማራዊ ጦር ሰፈር የነበሩና ላለፉት 5 ቀናት ይዞ ያቆያቸው ናቸው…
#ሱዳን

የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል / RSF የ72 ሰዓታት ተኩስ አቁም ማድረጉን አውጇል።

ይህን ያደረገው የዒድ አልፈጥር በዓልን ምክንያት በማድረግ እና ዜጎች ከግጭት ቀጠና እንዲወጡ የሰብዓዊ ኮሪደር ለማመቻቸት በተጨማሪም ከቤተሰቦቻቸው ጋር እንዲገናኙ ለማድረግ መሆኑን ገልጿል።

ምንም እንኳን RSF ይህን ቢልም በሱዳን በተለይም በካርቱም በዛሬው የዒድ አልፈጥር በዓል ዕለት ግጭት መቀጠሉ ፣ ከተማዋ በከባባድ መሳሪያዎች ድምፅ እየተናወጠች ስለመሆኑ ለማወቅ ተችሏል።

RSF የሱዳንን ጦር በአስከፊ ጥቃቶችን እየፈፀመ ነው በሚል ከሷል።

ከሱዳን ጦር በኩል በዓሉን ምክንያት በማድረግ የተኩስ አቁም ለማድረግ ሃሳብ ይኖር እንደሆነ የታወቀ ነገር እንደሌለ አልጀዚራ ዘግቧል።

ባለፉት ቀናት ለሁለት ጊዜ ተኩስ አቁም ለማድረግ ተሞክሮ ምንም አልተሳካም።

በሱዳን እየተካሄደ ያለው ጦርነት በከተሞች ውስጥ እየተደረገ በመሆኑ በርካቶች ከቤታቸው ለመንቀሳቀስ ተቸግረዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#IOM እንደ ዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት መረጀ በመቶዎች የሚቆጠሩ የቱርክ ዜጎችን ጨምሮ ከ3,500 በላይ ሰዎች በሱዳን ያለውን ከባድ ጦርነት ሸሽተው በመተማ በኩል ወደ ኢትዮጵያ ገብተዋል። ከሚያዚያ 21 እስከ 25 ባለው ጊዜ ውስጥ ከ3500 በላይ የሆኑ የ35 ሀገራት ዜጋ  ስደተኞች ተመዝግበዋል። ከተመዘገቡት አጠቃላይ ስደተኞች መካከል ከ40 በመቶ በላይ የቱርክ ዜጎች ሲሆኑ፣ ኢትዮጵያውያን 14…
#ኢትዮጵያ #ሱዳን #መተማ

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ፤ በሱዳን እየተካሄደ ያለውን ጦርነት በመሸሽ በየቀኑ ከአንድ ሺህ በላይ የሚሆኑ የተለያዩ ሀገራት ዜጎች ድንበር አቋርጠው ወደ #ኢትዮጵያ እየገቡ እንደሆነ አሳውቋል።

ይህ ቁጥር አሁንም እየጨመረ ነው ብሏል።

እስካሁን በሱዳን ጦርነት ምክንያት #በመተማ በኩል ወደ ኢትዮጵያ የገቡ ዜጎች ቁጥርም በአጠቃላይ ከ12 ሺ በላይ መድረሱ ተመላክቷል።

ሱዳን እና ኢትዮጵያ በሚዋሰኑበት ምዕራብ ጎንደር ዞን መተማ በኩል ሕይወታቸውን ለማትረፍ ወደ ኢትዮጵያ እየገቡ ካሉት መካከል አብዛኞቹ ኢትዮጵያውያን ሲሆኑ የሌሎች አገራት ዜጎች እንደሚገኙበት የመንግሥታቱ ድርጅት መሥሪያ ቤት መረጃን ዋቢ በማድረግ ቢቢሲ ዘግቧል።

@tikvahethiopia
#ሱዳን

የሱዳን ተፋላሚ ኃይሎች ባለፈው ሳምንት በአሜሪካ እና ሱዑዲ አረቢያ አደራዳሪነት የተኩስ ማቆ ስምምነት ላይ ማድረሳቸው ቢነገርም እንደ ከዚህ በፊቶቹ ስምምነቶች ሁሉ ተጥሶ ካርቱም ትላትናም በፍንዳታ ስትናጥ መዋሏን ቪኦኤ ዘግቧል።

የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ከሰኞ ምሽት ለአራት ሩብ ጉዳይ ይጀምራል የተባለና ለሰባት ቀናት የሚቆይ ነበር።

ተኩስ ኡቅም ላይ ተደረሰ በተባለ በደቂቃዎች ውስጥ የአየር ድብደባ እና የተኩስ ልውውጥ እንደነበር የዓይን እማኞች ተናግረዋል። በሰሜን ካርቱም ውጊያ ሲካሄድ፣ ከካርቱም በሥተ ምስራቅ ደግሞ የአየር ድብደባ እንደነበር ዘገባው ጠቁሟል።

በአንዳንድ የካርቱም ክፍሎች ደግሞ፣ የሚያስጨንቅ ጸጥታ ሰፍኖ እንደነበር እና ነዋሪዎቹም የሰላም ስምምነቱ ውጊያውን ያስቆማል በሚል ተስፋ አድርገው እንደነበር ተነግሯል።

ነዋሪዎች ሕይወት አድን ርዳታ እንዲደርስ እና ወደ ጦር አውድማነት ከተቀየረችው ካርቱም በሕይወት ለመውጣት እንደሚሹም ታውቋል ሲል ቪኦኤ በዘገባው ገልጿል።

እስካሁን ድረስ ከ1,000 በላይ ሰዎች የሞሩ ሲሆን ከሚሊዮን በላይ የሚሆኑት ከመኖሪያቸው ተፈናቅለዋል። 250 ሺሕ የሚሆኑትን ደግሞ #ኢትዮጵያን ጨምሮ የተሻለ ሰላም እናገኛለን ወዳሉባቸው ጎረቤት አገራት ሸሽተዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የግብፁ መሪ ምን አሉ ? የግብፁ ፕሬዜዳንት አብዱል ፈታህ አልሲሲ ከሶማሊያው ፕሬዝዳንት ጋር የሁለቶሽ ምክክር ካደረጉ በኃላ በጋራ ሆነው መግለጫ ሰጥተው ነበር። በዚህም ወቅት የግብፁ መሪ ፤ " የአረብ ሊግ ቻርተር በሉዓላዊነታቸው እና በግዛታቸው ላይ ጥቃት የሚደርስባቸውን የአረብ ሀገራት እንድንከላከል ያስገድደናል " ሲሉ ተደምጠዋል። " ግብፅ በሶማሊያ ደህንነት ላይ ምንም አይነት ስጋት እንዲፈጠር…
ራስ ገዟ ሶማሌላንድ ስለ ግብፅ ምን አለች ?

" በስምምነቱ ዙሪያ የሚነሱ ማንኛውንም የውጭ #ጣልቃገብነቶችን እንቃወማለን " - ሶማሌላንድ

ዛሬ የራስ ገዟ ሶማሌላንድ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሯ በኩል መግለጫ አውጣለች። በዚህ መግለጫም ስለ ለሰሞነኛው የግብፅ ሁኔታ ምላሽ ሰጥታለች።

ምን አለች ?

ሶማሌላንድ ፤ ከግብፅ ጋር ያላትን ታሪካዊ ግንኙነት ከፍ አድርጋ እንደምትመለከት ገልጻ በአፍሪካ ቀንድ መረጋጋት ላይ ያላትን ስጋትም እውቅና እንደምትሰጥ ገልጻለች።

" ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከተከሰቱ ክስተቶች አንፃር ቀጠናዊ ጉዳዮችን በውይይት እና በትብብር ለመፍታት ያለኝን ቁርጠኝነት በድጋሚ አረጋግጣለሁ " ብላለች።

ይሁን እንጂ በሶማሌላንድ ሪፐብሊክ እና በ #ኢትዮጵያ 🇪🇹 መካከል ከተፈረመው የመግባቢያ ስምምነት (MoU) በኋላ የሚነሱ ማንኛውንም አይነት የውጭ #ጣልቃገብነቶችን እንድምትቃወም በድጋሚ አረጋግጣለች።

በመግለጫዋ ፤ " የሶማሌላንድ ሪፐብሊክ እንደ አንድ ሉዓላዊ ሀገር በተቋቋሙ ዓለም አቀፍ ማዕቀፍ ውስጥ ያሉትን ሁሉንም ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቶች አከብራለሁ " ስትል ገልጻለች።

" ሁሉም ፍላጎት ያላቸው አካላት ቀጠናዊ መረጋጋትን እና ገንቢ አጋርነትን በማስፈን ላይ እንዲያተኩሩ አበረታታለሁ " ያለችው ሶማሌለንድ ፤ " በዚህ መንፈስም #ግብፅ በቅርብ ጎረቤቶቿ እንደ ፦
* #ሱዳን
* #ሊቢያ
* #ጋዛ ያሉ ግጭቶችን ለመፍታት ዲፕሎማሲያዊ አቅጣጫዋን እንድትቀይር እናበረታታታለን " ብላለች።

" እነዚህ አካባቢዎች (ሱዳን፣ ሊቢያ፣ ጋዛ) በአሁኑ ጊዜ ጉልህ ከሆኑ ተግዳሮቶች ጋር #እየታገሉ ነው ፤ እናም የግብፅ ገንቢ ተሳትፎ ለዘላቂ ሰላም እና ደህንነት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያደርጋል ብለን እናምናለን " ስትል ገልጻለች።

የሶማሌለንድ መንግሥት በአፍሪካ ቀንድ ሰላምና ልማትን ለማስፈን ከሁሉም ሀገራት ጋር ዲፕሎማሲያዊ ውይይቶችን እና ትብብርን ያደርጋል ስትል አሳውቃለች።

" የጋራ ጂኦፖለቲካዊ አካባቢያችንን ሁኔታ ለማሻሻል ከግብፅ እና ከሌሎች ተባባሪዎች ጋር #በመከባበር እና #በጋራ_ጥቅም ላይ የተመሰረተ ገንቢ ግንኙነትን ለመፍጠር እንሰራለን " ስትል ገልጻለች።

@tikvahethiopia