TIKVAH-ETHIOPIA
1.43M subscribers
55.4K photos
1.39K videos
199 files
3.72K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#አሳዛኝ_ዜና⬇️

በሶማሊያ የፑንትላንድ የንግድ ከተማ በሆነችው ቦሳሶ ውስጥ ሦስት #ኢትዮጵያዊያን #በአይሲስ ታጣቂዎች #ሲገደሉ ቢያንስ አንድ መቁሰሉ ተዘገበ።

ስለጥቃቱ በቀዳሚነት የወጡ ዘገባዎች እንዳመለከቱት ታጣቂዎቹ በርካታ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች ይኖሩበታል በሚባለው ሳንቶስ ተብሎ በሚጣራው የከተማዋ ክፍል ውስጥ ባገኟቸው አራት ኢትዮጵያዊያን ላይ #ተኩስ ከፍተው ነው ጥቃቱን የፈፀሙት።

አንድ ስማቸውን ያልጠቀሱ የአካባቢው ባለስልጣን ኢትዮጵያዊያኑ በተፈፀመባቸው ጥቃት መገደላቸውንና መቁሰላቸውን ለቢቢሲ ሲያረጋግጡ፤ አፍቃሬ አይኤስ የሆነ ቡድንም በትዊተር ገጹ ላይ ስለጥቃቱ አስፍሯል።

ኢትዮጵያን ጨምሮ ከተለያዩ ሃገራት የኤደን ባህረ ሰላጤን በትናንሽ ጀልባዎች በማቋረጥ ወደ የመንና የመካከለኛው ምሥራቅ ሃገራት በህገ ወጥ መንገድ ለመሻገር የሚፈልጉ ስደተኞች #የቦሳሶን የባህር በር ይጠቀማሉ።

በአካባቢውም በመቶዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች እንደሚገኙ ተገልጿል።

እነዚህ በጥቃቱ የሞቱትና የቆሰሉት ኢትዮጵያዊያንም በህገ ወጥ አዘዋዋሪዎች አማካይነት ባህሩን ተሻግረው በጦርነት ወደ የምትታመሰው #የመን ለመጓዝ በቦታው የነበሩ ስደተኞች እንደሆኑ ይታመናል።

አይሲስ ከቅርብ ወራት ወዲህ በጉልህ የሚታዩ በርካታ ጥቃቶችን በሶማሊያ ውስጥ እየፈፀመ ሲሆን በተለይ ደግሞ በፑንት ላንድ ግዛት ውስጥ የአይኤስ ቡደን ከሌሎች አካባቢዎች በበለጠ ሰፊ እንቅስቃሴ ያደርጋል ተብሎ ይታመናል።

ፑንትላንድ በሰሜን ሶማሊያ የምትገኝ ከፊል ራስ ገዝ የሆነች ግዛት ናት።

ምንጭ፦ BBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ቆም ብለን …

በርካታ የአለም ሀገራት የማህበራዊ ሚዲያ ቴክኖሎጂን በኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና በፖለታካዊ ዘርፎች ለተጎናጸፉት ውጤት ሁነኛ መሳሪያ አድርገው እየተጠቀሙበት ነው፡፡ በተቃራኒው ከነበሩበት የእድገት ሂደት እና ከሰላማዊ ህይወት አሽቆልቁለው ማንም አካል አትራፊ ወዳልሆነበት በእርስ በርስ #ጦርነት ሀገራቸውን #አፍርሰው ለዜጎቻቸው ሞት፣ በረሀብ አለንጋ መቀጣት፣ ለወረርሽኝና  ስደት መዳረግ እጣፈንታቸው እንዲሆን የጥላቻና የሀሰት መረጃዎች ሚና ከፍተኛ እንደሆነ በተለያዩ የአለም አቀፍ ሚዲያዎች ይፋ እየተደረገ ነው፡፡

በሚወርድባቸው የከባድ ጦር መሳሪያ ወደ ፍርስራሽነት በመቀየር ላይ ያሉትና እስካሁን #መቋጫ መፍትሄ ያላገኘው የመካከለኛው መስርቅ የቅድመ ስልጣኔ ምድር የነበረችው ሀገረ #ሶሪያን እና ለኢትዮጵያ የቅርብ ጎረቤት በሚባል አቅራቢያ የምትገኘው #የመን በምሰሌነት ተጠቃሾች ናቸው፡፡

ኢትዮጵያም ለዜጎቿ ህይወት የሚበጁ ዘርፈ ብዙ ጥቅሞችን ዘመኑ ከፈጠረው የማህበራዊ ሚዲያ ቴክኖሎጂ መጠቀም የምትችልበት ምቹ ሁኔታዎች እየሰፋ ቢመጡም በተቃራኒው በቴክኖሎጂው በሚሰራጩ የሀሰት ወሬዎች፣ ብሄርን ወይም  ሃይማኖትን መሰረት ያደረጉ የጥላቻ መረጃዎች ያለገደብ የሚለቀቅበት ሁኔታ አመዝኖ የስጋት ምንጭ  እየሆነ መጥቷል፡፡

ማህበራዊ ሚዲያ የሆነ ቡድን ወይም አካል መነሻው ምን እንደሆነ ለማወቅ በሚያዳግት መልኩ በስሜታዊነት የሚፈረጅበት፣ የጥላቻ መረጃዎች  እየተፈበረኩ በተቀናበሩ ፎቶዎች የሚቀርብበት፣ በሀገሪቱ ለረጅም ጊዜያት ጸንተው ለነበሩ የመቻቻልና የአብሮነት እሴቶችን ለሚንዱ የጥላቻ መረጃዎች መጫዎቻ ሜዳ ሲሆን ይስተዋላል፡፡

በማህበራዊ ሚዲያ እየተሰራጨ ባሉ የሀሰትና የጥላቻ መረጃዎች በሀሪቱ ላይ እየፈጠሩ ባለው ችግርና መፍትሄው ላይ  ውይይት ባለፈው ሳምንት በአዲስ አበባ ተካሂዷል፡፡

በመድረኩ ላይም ሀገራችን ከማህበራዊ ሚዲያ ምን አተረፈች? በማለት በጥያቄ ሀሳባቸውን ማካፈል የጀምሩት በቀድሞው የኢፌዲሪ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት የማህበራዊ ሚዲያ ዘርፍ  ቡድን መሪ  አቶ በቀለ እውነቱ በማህበራዊ ሚዲያ የሚተላለፉ መረጃዎች ለህብረተሰቡ ከሚሰጡት ጠቀሜታ ይልቅ  ጉዳቱ እየበዛ  ነው ያሉት፡፡

ለመልካም ነገር የተጠቀሙ የአለም ሀገራት ፈለግ በመከተል ቢሰራበት በርካታ  ተግባራትን  በቀላሉ ለመከውንና አማራጭ  የመሆን  አቅም ያለው  ቴክኖሎጂ ነው ያሉት አቶ በቀለ “እኛም እያደረሰ ያለውን ጉዳት በመቀነስ እውቀት ለሚጨምሩና ኑሮን ለሚያቀሉ ተግባራት ማዋል ላይ ጠንክሮ መስራት ያስፈልጋል’’ ብለዋል፡፡

በሀገሪቱ ሚዲያውን እየተጠቀመ ያለው ቢያንስ መጻፍና ማንበብ የሚችል የህብረተሰብ ክፍል ነው የሚሉት ባለሙያው መረጃን በመመልከትም ሆነ ሀሳቡን  ተቃውሞና ደግፎ የሚሳተፈው አካል ለበጎ ተግባር የመጠቀም ሂደት ገና አልዳበረም በማለትም  ትዝብታቸውን ገልጸዋል፡፡

በማህበራዊ ገጾች የሚተላለፉ መረጃዎችን የማመዛዘን አቅም ማዳበር ይጠይቃል  የሚሉት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አቢዮት ባዬ፤ በአሁኑ ወቅት የሀገሪቱ የኢንተርኔት አገልግሎት ተጠቃሚዎች ቁጥር 17 ሚሊዮን ባላይ መድረሱንም ጠቁመዋል፡፡

ቀደም ሲል ሃሳብን በነጻነት መግለጽ ባለመረጋገጡ ሰዎች በሀገሪቱ የዴሞክራሲ ባህል እንዲዳብርና መብት እንዲከበር ማንነታቸውን በመደበቅ በስውር የማህበራዊ ሚዲያ ገጽ ከፍተው ለዴሞክራሲ መጎልበት የሚሰሩበት ወቅት እንደነበር ነው ዋና ዳይሬክተሩ የተናገሩት።

ከሞላ ጎደል ነገሮች በተስተካከሉበት በአሁኑ ወቅት ሀሳብን በነጻነት ለመግልጽ ምቹ በሆነት ዘመን በተቃራኒው ሀሰተኛ መረጃዎችን አቀናብሮ በማሰራጨት ዴሞክራሲን የሚያቀጭጭ፣ ብሄርን ከብሄር ወይም በሃይማኖቶች መካካል ቅራኔና ግጭት ለመፍጠር እየተሰራ ይታያል ይላሉ። ለሀገር ሰላምና አንድነትም ስጋት እየሆነ ይገኛል ነው ብለዋል፡፡

ሀሰተኛ ወሬዎችን እያጋነነ የሚያሰራጨው አካል ምን ፍላጎት ቢኖረው ነው? ለምን ይነግረኛል? ብሎ እራስን በመጠይቅና መረጃውን ከሌሎች ታማኝ ምንጮች በማጣራት ማረጋገጥ እንደሚያስፈልግም ነው ዶከትር አቢዮት  የገለጹት፡፡

የጥላቻ መረጃዎችን የሚለቁ አካላት አላማቸው ለበርካታ የቴክኖሎጂው ተጠቃሚዎች መልእከታቸውን መበተን በመሆኑ ሀሳቡን ደግፎ ወይም ተቃውሞ ምላሽ ባለመስጠት የድርጊቱ ፈጻሚዎችን አንድም እራሳቸውን ከሀሰት መረጃ እንዲያርሙ ወይም የተከታይነት ተጽኖ ማመናመን እንደሚገባም ባለሙያው መክረዋል፡፡

በሌላ ሰው ወይም ተቋም ስም ሀሰተኛ የማህበራዊ ገጽ በመክፈት የፈጠራ ወሬን ተዓማኒነት በሌላቸው ፎቶዎች በማቀናበር ሀገርንና ዜጎችን አደጋ ላይ የሚጥል መረጃዎችን የሚያስተላልፉ አካላትን ለማስቆም እንደሀገር ቆም ብለን ማሰብ አያስፍልገንም? በማለት ሀሳባቸውን በጥያቄ ያነሱት የሀይማኖት አባት ሀጂተሸለ ኪሮ እንዳሉት ወጣቱ ትውልድ የሀገሩን አንድነትና ሰላም አስጠብቆ ማስቀጠል አለበት ፡፡

“ማህበራዊ ሚዲያ በብሄሮችና በሃይማኖቶች መካካል የጥላቻ ወሬ መርጨት  ብቻ አይደለም” የሚሉት ሌላው  የሃይማኖት አባት አባ መላከሂወት ወልደየሱስ  በአንድ ቤተ እምነት ውስጥ ጭምር የአሉባልታና የሀሰት መረጃዎችን በማሰራጨት የመተማመንና የመከባበር  ባህልን እየሸረሸረ ነው ብለዋል፡፡

በርካታ የመረጃ አማራጮች መኖር መልካም አጋጣሚ መሆኑን የነገሩን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲት መምህር ዶክተር ጌታቸው ድንቁ፤ መረጃዎች ሁሉ እውነተኛና ጠቃሚ ባለመሆናቸው ተፈትሸውና ተለይተው መወሰድ እዳለባቸው ይመክራሉ፡፡

“በአሁኑ ወቅት በማህበራዊ ሚዲያ የሚቀርቡ መረጃዎች፤ የበሰለ የፖለቲካ ሀሰብን ከማቅረብ ይልቅ የአንድ ግለሰብን ወይም ቡድንን ስሜትና የጥላቻ መረጃ የሚቀርቡበት ሜዳ ሆኗል” የሚሉት ዶክተር ጌታቸው ህብረተሰቡ ስጋቱን እየተረዳው መምጣቱን ነው የተናገሩት።

መደበኛ የመገናኛ ብዙሃን ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ መሻሻሎችና አማራጭ የህዝብ የመረጃ ምንጭ እየሆነ ቢመጣም ለበርካታ አመታት “ለገዢው ሃይል  የሚዘምር” ነበር ይላሉ።

ዶክተር ጌታቸው እንደሚሉት በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለህብረተሰቡ የማስተማር፤ በቁጥር እያደገ በመጣው የኤፍ ኤምና ቴሌቭዥን መገናኛ ዘዴዎች መንግስት መረጃዎችን በፍጥነት መስጠትን በመፍትሄነት መጠቀም ግድ ይላል። ማንነቱን ያልገለጸ አካልን ጓደኛ ማድረግም ሆን መከትል እንደማያስፍልግም በማስረዳት፡፡

የድሬ ትዩብ መስራች እና ስራ አስኪያጅ አቶ ቢኒያም ነገሰ  ፌስ ቡክ የመጠቀሚያ ቴክኖሎጂውን በየጊዜው ይበልጥ ቀላልና ባለብዙ አማራጭ እያደረገው መምጣቱ በሀገሪቱ እየመጣ ያለውን አደጋ ያባብሰዋል የሚል ስጋት ነው ብለዋል።

አቶ ቢኒያም  “በድሬ ትዩብ ስም በተከፈት የሀሰተኛ  ገጽ ላይ በተለቀቀ የአንድ ድርጅት ስም ማጥፋት መረጃ እኛን ጥፋተኛ ሊያደርግ የነበረን ድርጊት የፌስቡክ ባለቤት ጋር በአካል በመሄድ ሀሰተኛ መሆኑን በማስረዳት የኛን ትክክለኛ ገጽ በማረጋገጥ ከችግሩ ዳን” በማለት በተሞክሮነት አንስተዋል፡፡

አሁን በሀገሪቱ  በማህበራዊ ሚዲያ ዘርፍ የሚስተዋለውን ችግር ከመሰረቱ ለመፍታት ጥናት ላይ የተመሰረትና ቴክኖሎጂውን በአግባቡ በመጠቀም ብሎም ውጤት ካስመዘገቡ  ሀገራ ተሞክሮ መውሰድ እንደሚያስፈልግ ነው የተናገሩት፡፡

የጥላቻ ሀሳቦችን የሚያንጸባርቁ  ገጾችን የሚከላከል አንድ ተቋም በማቋቋምና በቂ እውቀት ያላቸው ባለሞያዎችን መድቦ መስራት ይገባልም ነው ያሉት፡፡

ፌስቡክ በአፍሪካ ያለውን አገልግሎት
#update በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ላይ ከጅቢቲ ወደ የመን በማምራት ላይ ሳሉ በሰጠሙት ሁለት ጀልባዎች ውስጥ ከተጫኑት #ኢትዮጵያውያን ናቸው ከተባሉ ስደተኞች መካከል #የሞቱት ቁጥር ወደ 52 ከፍ ማለቱ ተነገረ። ዓለም አቀፉ የስደተኞች ጉዳይ ድርጅት በምህጻሩ IOM እንዳስታወቀው የህይወት አድን ሠራተኞች ከሁለቱ ጀልባዎች ተጨማሪ አስከሬኖችን በማግኘታቸው ትናንት 43 የነበረው የሟቾቹ ቁጥር ዛሬ ወደ 52 ከፍ ብሏል። 16 ሰዎች ከአደጋው መትረፋቸውን ድርጅቱ አስታውቋል። በአደጋው የሞቱት ሰዎች ትክክለኛ ቁጥር እስካሁን በግልጽ አልታወቀም። ድርጅቱ አንደኛዋ ጀልባ 130 ሰዎችን አሳፍራ ነበር የሚል እምነት አለው። የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ያነጋገረው አንድ ከአደጋው የተረፈ የ15 ዓመት ወጣት ቁጥራቸው 80 ከሚሆን ኢትዮጵያውያን ጋር በአንደኛው #ጀልባ ተጭኖ እንደነበር ገልጿል። የጀልባዋ ነጂ ሞተሩ ከባድ #ችግር እንዳጋጠመው ከተናገረ በኋላ ጀልባዋ መስመጠም መጀመሯን እርሱ ግን ከባህር ውስጥ በጅቡቲ የባህር ጠረፍ ጠባቂ #ተጎትቶ መውጣቱን ወጣቱ ተናግሯል። ጦርነት እየተካሄደባት ቢሆንም ወደ #የመን የሚደረገው ስደት እንደቀጠለ ነው።

ምንጭ፦ የጀርመን ድምፅ ሬድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ያማል---እጅግ በጣም ያማል‼️

በዚህ ሳምንት #የመን ርዕሠ-ከተማ #ሰነዓ ውስጥ በሁለት ትምሕርት ቤቶች አቅራቢያ በተጣለ #ቦምብ 14 ህጻናት መገደላቸዉን የተመድ #የህጻናት መርጃ ድርጅት ዩኒሴፍ አወገዘ።

የድርጅቱ የመካከለኛ ምሥራቅ እና የሰሜን አፍሪቃ ክፍል ሃላፊ ጊርት ካፔላሬ እንዳሉት ህጻናትን መግደል እና አካለቸዉን ማጉደል የህጻናትን መብቶች የሚጻረሩ እጅግ ከባድ ወንጀሎች ናቸው። እርምጃው ወላጆችም ልጆቻቸውን ወደ ትምሕርት ቤት እንዳይልኩ የሚያደርግ መሆኑን ጠቅሰዋል። በጥቃቱ ሌሎች 16 ተማሪዎች ጉዳት ደርሶባቸዋል። አብዛናዎቹ እድሜያቸው ከ9 ዓመት በታች ነው። #ሰንአ ሆስፒታል የህክምና እርዳታ ከሚደረግላቸው ክፉኛ ከተጎዱት ውስጥ በአስጊ ሁኔታ ላይ የሚገኙም እንዳሉ ገልጸዋል።

ባለፈው እሁድ የየመን አማጽያንን የሚወጋው ሳዑዲ መራሹ ህብረት ሰንአ ውስጥ በመኖሪያ አካባቢዎች ላይ ባካሄደው የአየር ድብደባ ቢያንስ 11 ሰላማዊ ሰዎች መገደላቸውን በኢራን ይደገፋሉ የሚባሉት የሁቲ አማጽያን ተናግረዋል። እንደ አማጽያኑ ከተገደሉት አብዛኛዎቹ ተማሪዎች ናቸው።

Via የጀርመን ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፎቶ: #ቀይ_ባሕርን አቋርጠው ወደ ሳውዲ አረቢያ እና #የመን በጀልባ በመጓዝ ሳሉ የመገልበጥ አደጋ ደርሶባቸው ህይወታቸው ላለፈ 70 ገደማ #ኢትዮጵያውያን ወጣቶች #የመታሰቢያ መርሐግብር በኣፅቢ ከተማ ተካሄደ። ከሟቾቹ ውስጥ ቢያንስ አርባ አንዱ ከትግራይ ክልል አፅቢ ወንበርታ ወረዳ የተነሱ ነበሩ።

Via #ELU
@tsegabwolde @tikvahethiopia
😢#የመን Yemen is seeing the world's worst humanitarian crisis, according to the #UN.

https://telegra.ph/Yemen-07-15
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
15 ኢትዮጵያውያን ባህር ላይ ሞቱ!

ከዘጠና በላይ ስደተኞችን አሳፍራ #ከጅቡቲ ወደ #የመን በመጓዝ ላይ የነበረች የአሳ ማስገሪያ ጀልባ በመሰባበሯ ለጠና ረሃብና ጥም መጋለጣቸውንና አንዳንዶቹም በተስፋ መቁረጥ ጭምር ራሳቸውን ወደ ባህሩ ወርውረው ለሕልፈት መዳረጋቸውን ዓለም አቀፉ የፍልሰተኞች ድርጅት /IOM/ አስታወቀ።

Via #VOA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#የመን

ትናንት - ራሱን የደቡብ የሽግግር ምክር ቤት (southern transitional council) ብሎ የሚጠራው የየመን ተገንጣይ ቡድን በተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች ድጋፍ ኤደንን ተቆጣጠረ -- #ዛሬ-በሳዑዲ አረቢያ ትዕዛዝ እና ዛቻ ጥሎ መውጣት ጀመረ።

Via #EshetBekele
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከዓለም ዙሪያ ፦

➡️ #አሜሪካ - በኒውዮርክ የተቃውሞ ሰልፍ ተካሂዷል። ሰልፉ በመሳሪያ የገዙ ጥቃቶችን ለማውገዝ የተካሄደ ነው። ሰልፉ የተካሄደው አንድ ወጣት በቴክሳስ ሮብ በሚሰኝ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት 19 ህፃናት ተማሪዎችን እና 2 መምህራንን በአሰቃቂ ሁኔታ ከገደለ ከቀናት በኃላ ነው።

➡️ #ስፔን - በሰሜናዊ ስፔን ላ ሪዮጃ ክልል በባዮዲዝል ማምረቻ ፋብሪካ ላይ በደረሰ ፍንዳታ ቢያንስ 2 ሰዎች መሞታቸው ሪፖርት ተደርጓል።

➡️ #የመን - በየመን አደን ከተማ ሰዎች በሚበዙበት በተጨናነቀ ገበያ ላይ በደረሰ ፍንዳታ በትንሹ 4 ሰዎች ሲሞቱ በርካቶች መቁሰላቸው ታውቋል፤ እስካሁን ለጥቃቱ ኃላፊነት ወስዳለሁ ብሎ ብቅ ያለ የለም።

➡️ #ሱዳን - ከወራት በፊት በሱዳን የተካሄደውም ወታደራዊ መፈንቅለ መንግስት ተከትሎ የተነሳው ተቃውሞ አሁንም ያልበረደ ሲሆን ትላንትና በሺዎች የሚቆጠሩ ተቃዋሚዎች በካርቱም ጎዳናዎች ላይ ተቃውሞ አሰምተዋል። የጥቅምቱ መፈንቅለ መንግስት ሀገሪቱን ወደ ፖለቲካዊ ቀውስ አስገብቷል።

➡️ #ጣልያን - የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ማሪዮ ድራጊ የሩሲያው ፕሬዜዳንህ ፑቲን አሁን ላይ በዓለም የሚየው የምግብ ችግር "በሩሲያ ላይ የተጣለው ማዕቀብ ነው " ብለው እንደነገራቸው ተናግረዋል። የሩስያ እና ዩክሬን ጦርነት ከጀመረ አንስቶ ምዕራባውያን ሀገራት ሩስያ ላይ እጅግ ከፍተኛ የሚባሉ ማዕቀቦችን እየጣሉ እንደሆነ ይታወቃል። ለእነዚህ ማዕቀቦችም ሩስያ ምላሽ ከመስጠት ወደኃላ አላለችም።

➡️ #ቱርክ #ፈረንሳይ - የቱርክ ፕሬዜዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ከፈረንሳይ ፕሬዜዳንት ኢማኑኤል ማክሮን የስውዲን እና ፊንላንድ ለNATO አባልነት ባቀረቡት ማመልከቻ፣ በዩክሬን ሩስያ ጦርነት፣ በቀጠናዊ ጉዳዮች እና በሌሎችም ጉዳዮች ላይ ተገናኝተው መክረዋል።

@tikvahethiopia
" በ5 ወር 27,800 ሰዎች ከአፍሪካ ቀንድ ወደ የመን ተሻግረዋል " - IOM

እንደ ተመድ የስደተኞች ኤጀንሲ (IOM) ፤ ባለንበት በዚህ ዓመት 2022 (እኤአ) /በ5 ወር/ ቢያንስ 27,800 ሰዎች ከአፍሪካ ቀንድ በጦርነት ወደምትታመሰው ወደ #የመን ተሻግረዋል ፤ ይህ ደግሞ በ2021 ሙሉ ዓመት ከተደረጉት ጉዞዎች ሁሉ የሚበልጥ ነው። (በ2021 ዓመት 27,700 ነበር)

IOM በዚህ ደረጃ ቁጥሩ ከፍ እንዲል ካደረጉት ምክንያቶች መካከል የCOVID-19 እንቅስቃሴ ገደቦች መቃለላቸው ፣ የበለጠ ምቹ የአየር ሁኔታ መኖር እንዲሁም በኢትዮጵያ ያለው የፀጥታ ሁኔታ እና ድርቅ ይጠቀሳሉ ብሏል። (አብዛኞቹ ስደተኞች ከኢትዮጵያ መሆናቸው ተጠቅሷል)

IOM በቅርቡ ከየመን ወደ ኢትዮጵያ በፍቃደኝነት የሚመለሱ በሺዎች የሚቆጠሩ ስደተኞችን ለመደገፍ የ7.5 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ድጋፍ ጠይቋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ግን ከኢትዮጵያና ከሶማሊያ በሺህ የሚቆጠሩ ስደተኞች በየመን በኩል ወደ መካከለኛው ምስራቅ ለመድረስ በማሰብ አደገኛውን የኤደን ባህረ ሰላጤ ያቋርጣሉ።

ስደተኞቹ በዋናነት ዓላማቸው ወደ የመን ሰሜናዊ ጎረቤት ወደሆነችው #ሳዑዲ_አረቢያ ለመድረስ ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#IOM በጅቡቲ የባህር ዳርቻ የ38 ሰዎች አስክሬን ተገኘ። በጀልባ መስጠም አደጋ የህፃናትን ጨምሮ አጠቃላይ 38 ሰዎች ሞተው አስክሬናቸው መገኘቱን የዓለም አቀፉ የስድተኞች ድርጅት አሳውቋል። 6 ሰዎች የገቡበት ያልታወቀ ሲሆን ሳይሞቱ እንዳልቀረ ተነግሯል። ከሞት የተረፉ 22 ሰዎች በጅቡቲ እርዳታ እየተደረገለቸው ይገኛል። @tikvahethiopia
" 38 #ኢትዮጵያውያን ፍልሰተኞች ህይወታቸው አልፏል " - በጅቡቲ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ

በጅቡቲ የባህር ዳርቻ ፍልሰተኞችን አሳፍራ ወደ #የመን በመጓዝ ላይ በነበረች ጀልባ ላይ በደረሰ የመስጠም አደጋ 38 ኢትዮጵያውያን ፍልሰተኞች ህይወታቸውን እንዳጡ በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አሳውቋል።

ትላንትና ሰኞ በጅቡቲ ሰሜን ምስራቅ " #ጎዶሪያ " በሚባል የባህር ዳርቻ አቅራቢያ ስልሳ (60) ኢትዮጵያውያን ፍልሰተኞችን አሳፍራ ወደ #የመን ትጓዝ የነበረች ጀልባ ላይ በደረሰው የመገልበጥ አደጋ የ38 ፍልሰተኞች ሕይወታቸውን አጥተዋል።

በጅቡቲ የኢፌዴሪ ሚሲዮንም አደጋው ከደረሰ በኋላ ወደ ስፍራው በመጓዝ የአደጋውን መንስኤ በማጣራት ላይ እንደሚገኝ ተገልጿል።

ኤምባሲው ፥ በየዓመቱ ከ200 ሺህ የሚበልጡ ፍልሰተኞች ከጅቡቲ ባህር ዳርቻ የኤደን ባህረ ሰላጤ በመነሳት መካከለኛው ምስራቅ አገራት ለመድረስ በየብስና በባህር አደገኛ ጉዞ ያደርጋሉ ብሏል።

ባለፉት አምስት ዓመታት #በጀልባ_መስመጥ አደጋ ብቻ የ189 ዜጎቻችን ሕይወት እንዳለፈ ጠቁሟል።

በየጊዜው የሚደርሰው አደጋ እንዳለ ቢሆንም የፍልሰተኞቹ ቁጥር ግን አሁንም #እየጨመረ እንደሆነ ገልጿል።

ዜጎች በህገ ወጥ #ደላሎች የሀሰት ስብከት በመታለል ውድ ሕይወታቸውን አደጋ ላይ ጥለው በዚህ አደገኛ የጉዞ መስመር ከመንቀሳቀስ እንዲቆጠቡ አስጠንቅቋል።

የፍትህ አካላት ሕገ ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎችን #ከገጠራማ የአገራችን አካባቢዎች ዜጎችን በመመልመል ለስደት በሚዳርጓቸው ግለሰቦች ላይ ተገቢውን እርምጃ እንዲወስዱ በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አሳስቧል።

@tikvahethiopia