TIKVAH-ETHIOPIA
1.39M subscribers
54.7K photos
1.37K videos
198 files
3.64K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#ETHIOPIA 3 ጉዳዮች ከዛሬው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አስቸኳይ ስብሰባ ፦ 1ኛ. የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ከዛሬ የካቲት 8/2014 ጀምሮ ቀሪ የሚሆንበት የውሳኔ ሃሳብ በ63 ተቃውሞ፣ በ21 ድምፀ ታአቅቦ፣ በአብላጫ ድምፅ ፀድቋል። 2ኛ. የመንግስት ሰራተኞች ጡረታ ለመደንገግ የቀረበ ረቂቅ አዋጅ በሁለት ድምጸ ተአቅቦ በአብላጫ ድምጽ እና የግል ድርጅቶች ሰራተኞች ጡረታ ለማደንገግ የቀረበውን ረቂቅ…
#መንግሥት እና የ #ግል ሠራተኞች ጡረታን ለመደንገግ የቀረበው አዋጅ ምን ይዟል ?

ለመንግሥት ሠራተኞች ፦

• የተሻሻለው የጡረታ ዐዋጅ የጡረታ ዕድሜን ጣራ ' 60 ዓመት ' እንዲሆን እና ጡረተኛው በሕይወት ሳለ የሚያገኘው የጡረታ መጠን ሲያልፍ ለትዳር አጋር 50 በመቶ የጡረታው ተጠቃሚ እንዲሆን ይፈቅዳል።

• የፖሊስና መከላከያ መዋጮ ከግለሰቡ የሚደረገው ሌሎች የግልና የመንግሥት ሠራተኞች እንደሚያዋጡት 7 በመቶ ሆኖ ከመንግሥት አካል የሚደረግለት መዋጮ ግን ወደ 33 በመቶ ከፍ እንዲል ተደርጓል።

ለግል ድርጅቶች ሠራተኞች ፦

• በድርጅቶች ምክንያት ሳይዋጣ የቀረን ገንዘብ በሦስት ወር ውስጥ ገቢ ካልተደረገ በቀጥታ ድርጅቱ ካለው ማንኛውም የባንክ አካውንት ገቢ እንዲደረግበት ያስገድዳል።

• የግል ድርጅት ባለቤቶች በድርጅቱ ሠራተኛ ሆነው በጡረታ ማዕቀፉ ውስጥ እንዳይገቡ አዋጁ አግዷል።

• ከ10 ዓመት በላይ ያገለገለ ሠራተኛ ዕድሜው ለጡረታ በሚደርስበት ጊዜ የዕድሜ ልክ ጡረታ ተከፋይ እንዲሆን አዋጁ ይፈቅዳል።

• የሚሰበሰበው የጡረታ መዋጮም ወደ ኢንቨስትመንት በማስገባት ገቢን ማሳደግ ለጡረተኞች የክፍያ ማሻሻያ የሚያደርግበትን እድል ይፈጥራል።

• አንድ አሰሪ የ ግል ድርጅት ፍቃዱን በሚያድስበት ወቅት የሠራተኞቹን መዋጮ ካላስገባ ፍቃዱ የማይታደስበት አስገዳጅ አንቀጽም ተካቷል።

#ኤፍቢሲ

@tikvahethiopia