TIKVAH-ETHIOPIA
1.43M subscribers
55.4K photos
1.39K videos
199 files
3.72K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ዲላ ዩኒቨርሲቲ⬆️የነባር ተማሪዎች የምዝገባ ቀን ላልተወሰነ ጊዜ መራዘሙን ተቋሙ ዛሬ ባወጣው ማስታወቂያ ገልጿል። 25/01/2011

@tsegabwolde @tikvahethiopia
አስቸኳይ‼️ከዚህ በታች የተዘረዘሩት ዩኒቨርሲቲዎች የ2011 ዓ.ም. የተማሪዎች የምዝገባ ቀን በድጋሜ መራዘሙን በይፋዊ #ፌስቡክ ገፃቸው እና በተቋማቸው ግቢ ውስጥ በለጠፉት ማስታወቂያ ላይ ገልፀዋል፦

. አክሱም ዩኒቨርሲቲ
. ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ
. ዲላ ዩኒቨርሲቲ
. ጎንደር ዩኒቨርሲቲ
. ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ
. አዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ
. ወልዲያ ዩኒቨርሲቲ
. ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ
. ወለጋ ዩኒቨርሲቲ
. ጅማ ዩኒቨርሲቲ
. ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ(esp.)
. ሀረማያ ዩኒቨርሲቲ
. ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ
. ወሎ ዩኒቨርሲቲ
. ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ
. አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ
. አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ
. አምቦ ዩኒቨርሲቲ

ማሳሰቢያ፦ የተለወጠ ወይም የተሳሳተ መረጃ ካለ በፍጥነት አሳውቃችኋለሁ ወይም ማስተካከያ ሰጥበታለሁ።

#ETHIOPIA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ይኸው ዜናው⬆️

ዶክተር አብይ - ሊቀ መንበር
አቶ ደመቀ - ምክትል ሊቀ መንበር

ምንጭ፦etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ወ/ሮ ሙፈሪያት በምርጫው ላይ አልተሳተፉም። የኢህአዴግ ለቀ መንበር ዶክተር አብይ አህመድ እና ምክትል ሊቀ መንበር አቶ ደመቀ መኮንን ሆነው ተመርጠዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ኢህአዴግን በአመራርነት ለመምራት #እጩዎች ሆነው የቀረቡት፦

▪️ዶክተር ዐቢይ አህመድ ከኦዴፓ
▪️አቶ ደመቀ መኮንን ከአዴፓ
▪️ዶ/ ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ከህወሓት

ድምፅ በመስጠት 177 ሰው ተሳትፏል፡፡
ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ከተሰጠው ድምፅ 176 ድምፅ አግኝተዋል፡፡ አቶ ደመቀ መኮንን ደግሞ 149 ድምፅ በማግኘት በምክትል ሊቀመንበር ሆነው ተመርጠዋል፡፡ ዶክተር ደብረ ፅዮን ገ/ሚካኤል ለምክትል ሊቀመንበርነት ቀርበው 15 ድምፅ አግኝተዋል፡፡

የደኢህዴን ሊቀመንበር የሆኑት ወ/ሮ ሙፈሪያት ካሚል በምርጫው አለመሳተፋቸው ተመልክቷል፡፡
ምርጫውን የሚመራ 12 አስመራጭ ኮሚቴ ተሰይሞ የምርጫ ሂደቱ ተከናውኗል፡፡

©etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የመግቢያ ጊዜ⬇️

የ2011 የትምህርት ዘመን የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የመግቢያ ጊዜ በትምህርት ፍኖተ- ካርታ ውይይት ምክንያት #መራዘሙን የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ።

በአዲሱ የትምህርት ፍኖተ-ካርታ በሚደረገው ውይይት ምክንያት የ2011 ዓ.ም የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ጊዜ ላልተወሰነ ጊዜ መራዘሙን የሚኒስቴሩ የኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር ወይዘሮ #ሀረግ_ማሞ አስታውቀዋል።

መንግሥት በቅርቡ አዲስ ባዘጋጀው ረቂቅ የትምህርት ፍኖተ-ካርታ ላይ የተጀመረው ውይይት ላይ ተጨማሪ ግብዓት ማሰባሰቢያ ውይይት ስለሚደረግ ቀደም ብሎ ተላልፎ የነበረው የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ጥሪ መራዘሙን ዳይሬክተሯ አስታውቀዋል።

ዩኒቨርሲቲዎች ከመምህራኖቻቸው እና ከአስተዳደር ሠራተኞቻቸው ጋር በረቂቅ ፍኖተ-ካርታው ላይ ውይይት አድርገው ሲያበቁ ከጥቅምት ወር መጀመሪያ አንስቶ እንደ የዩኒቨርሲቲዎቹ መርሀ-ግብር የተማሪዎች መግቢያ ጥሪ ይደረጋል ተብሎ የቆየ ቢሆንም ውይይቱ እየተካሄደ በመሆኑ ምክንያት ላልተወሰነ ጊዜ ተራዝሟል።

ባለፉት ሁለት ወራት ውይይት ሲደረግበት የቆየው የትምህርት ፍኖተ-ካርታ ረቂቅ ጥናት ግብዓት ማሰባሰብ ሂደት ከአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ማኅበረሰብ አባላት ጋርም በዛሬው ዕለት በመላ አገሪቱ ውይይት እየተደረገበት ይገኛል።

በመሆኑም ውይይቱ ሲጠናቀቅ በማዕከል በኩል ለሁሉም የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች #ጥሪ እንደሚደረግ ተናግረዋል።

በአገር አቀፍ ደረጃ የተዘጋጀው የትምህርትና ስልጠና ፍኖተ-ካርታ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ ያለመ ሲሆን ለተግባራዊነቱ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር #ውይይት እየተደረገ መሆኑ ይታወቃል።

ምንጭ፦ ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
etv zena live! የ11 ኛው የኢህአዴግ ጉባኤ ማጠቃለያ መርሃ ግብር!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ማስታወሻ📌የሀዋሳ ከተማ ነዋሪዎች ነገ በሀዋሳ አለም አቀፍ ስታዲየም የኢህአዴግን ድርጅታዊ ጉባኤ መጠናቀቅን አስመልክቶ ልዩ መርሃ ግብር ተዘጋጅቷል። ሁላችሁም #ተጋብዛችኋል!

ከጥዋቱ 2 ሰዓት ጀምሮ!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ⬆️የነባር ተማሪዎች የምዝገባ ቀን ላልተወሰነ ጊዜ መራዘሙን ተቋሙ ዛሬ ባወጣው ማስታወቂያ ገልጿል። 25/01/2011

@tsegabwolde @tikvahethiopia
🕊ናዲያ ሙራድ🕊

የ2018 የኖቤል #የሰላም ሽልማት አሸናፊ!

ከናዲያ በተጨማሪ ዶክተር ዴኒስ ሙክዌጊ የ2018 የኖቤል የሰላም አሸናፊ ሆኗል!

ለሰላም ለከፈሉት መስዕዋትነት በቻናሉ ስም እናመሰግናቸዋለን!
#NOBEL2018
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ናዲያ ሙራድ🕊 በፈረንጆቹ 2014 በሃገሯ #ኢራቅ በጽንፈኛው ታጣቂ ቡድን #አይ_ኤስ ታግታ የቆየችና #የወሲብ ጥቃት ሰለባ የሆነች ወጣት ናት። ከቡድኑ እገታ ከወጣች በኋላም ይህን መሰሉ #ጥቃት እንዲቆምና በጦርነት ቀጠና ውስጥ የሚገኙ #ሴቶችን ለመታደግ ጥረት ስታደርግ ቆይታለች። ናዲያ ላደረገችው ጥረት የዘንድሮው የኖቤል #የሰላም ሽልማት አሸናፊ ሆናለች።
.
.
እኔ ግሌ እስካሁን ድረስ በህይወቴ ውስጥ ካየኋቸው እና ታሪካቸውን ከሰማሁ ድንቅ ሰዎች አንዷ ናት። ከእርሷ ጥንካሬን፣ ተስፋ አለመቁረጥን፣ ሰላም ወዳድ መሆንን፣ ለሰው ልጅ መኖርን ተምሪያለሁ! ዛሬ ይህን አጋጣሚ ተጠቅሜ ለናዲያ ያለኝን ትልቅ ክብር ለመገልፀ እወዳለሁ!
.
.
🕊🕊🕊ናዲያ ሙራድ🕊🕊🕊
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ዶክተር ዴኒስ የ2018 የኖቤል የሰላም አሸናፊ!
ዶ/ር ዴኒስ🕊ኮንጓዊው የማህጸን ስፔሻሊስት ዶክተር #ዴኒስ_ሙክዌጊ የዘንድሮው የኖቤል #የሰላም ሽልማት አሸናፊ ነው። በጦርነት ወቅት የሚደርስ #የወሲብ ጥቃትን ለማስቆም ባደረጉት አስተዋጽኦ ሽልማቱን ያገኙት። ኮንጓዊው ዶክተር የዚህ ሰለባ ለሆኑ ሴቶች ህክምና በሚሰጥ ክሊኒክ ውስጥ ህክምና በመስጠት የሚፈጸመው የወሲብ ጥቃት እንዲቆም ሲታገሉ መቆየታቸው ተገልጿል።

ዶክተር ዴኒስ ለሰላም ላደረጉት ትልቅ ስራ በቻናላችን ስም እናመሰግናቸዋለን!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የኢህአዴግ ጉባኤ ሀዋሳ⬇️

የኢህአዴግ አጋር ድርጅቶች በድርጅቱ ስራ አስፈፃሚና ምክር ቤት ውስጥ እንዲሳተፉ በ11ኛው የኢህአዴግ ጉባዔ ላይ ተወሰነ።

የአጋር ድርጅቶች ሊቀመናብርትና ምክትል ሊቀመናብርት በቀጥታ በኢህአዴግ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ እንዲሳተፉ ተወስኗል።

እንዲሁም የአጋር ድርጅቶቹ አምስት የስራ አስፈፃሚ አባላት በኢህአዴግ ምክር ቤት እንዲሳተፉም ነው ጉባዔው #ውሳኔ ያስተላለፈው።

የጉባዔውን መጠናቀቅ አስመልክቶ መግለጫ የሰጡት አቶ ፍቃዱ ተሰማ፥ የአጋር ድርጅቶቹ የሚሳተፉት #ያለድምፅ መሆኑን ተናግረዋል።

አጋር ድርጅቶቹን ወደ ሀገራዊ መድረክ ለማምጣትና አንድ ሀገራዊ ፓርቲ ለመመስረት በጥናትና እውቀት ላይ ተመስርቶ ውይይት በማድረግ ወደ ኢህአዴግ የመቀላቀሉ ሂደት እንዲጠናቀቅ ጉባዔው ለኢህአዴግ ምክር ቤት ውክልና ሰጥቷል።

ጉባዔው በህግ የበላይነት መከበር ፣ በልማት ስራዎች፣ በወጣቶችና ሴቶች ተጠቃሚነት ላይም ከመቼውም ጊዜ በተሻለ እንዲሰራ አቅጣጫ ማስቀመጡ ተገልጿል።

ከጎረቤት ሀገራት ጋር የተጀመረው የዲፕሎማሲ ስራም ብሄራዊ ጥቅምን በሚያስጠብቅ መልኩ ተጠናከሮ ይቀጥላል ተብሏል።

በየአካባቢው አየተስተዋለ ያለው መፈናቀልና ሰብዓዊ መብት ጥሰት በምንም መልኩ ድርጀቱ እንደማይታገስም አቶ ፍቃዱ በመግለጫቸው አመልክተዋል።

ለዚህም የፀጥታ አካላት ተገቢውን #እርምጃ እንዲወስድ አቅጣጫ እንደተቀመጠም ነው የጠቆሙት።

የተጀመረውን ሀገራዊ ለውጥ ለማስቀጠል የመንግስት ተቋማት ሪፎርም እንዲደረግ ስምምነት ላይ መደረሱ ተነግሯል።

በተለይ ዴሞክራሲያዊ ስርዓቱን የሚያሰፉ ገለልተኛና ወገንተኝነታቸው ለህዝብ የሆኑ ተቋማት ለመገንባት የሪፎርም ስራዎች በአፋጣኝ
ተግባራዊ እንዲሆኑ ጉባዔው አሳስቧል።

ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ኢህአዴግ‼️ በየአካባቢው አየተስተዋለ ያለው #መፈናቀልና ሰብዓዊ መብት #ጥሰት በምንም መልኩ ኢህአዴግ እንደማይታገስ ተመለከተ። ለዚህም #የፀጥታ_አካላት ተገቢውን #እርምጃ እንዲወስዱ አቅጣጫ ተቀምጧል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
*አስቸኳይ የሰብዓዊነት ተግባር ላይ ይሳተፉ*

(ሼር ይደረግ!)

ከቤኒሻንጉል #ለተፈናቀሉ ከ90 ሺህ በላይ ኢትዮጵያዊያን ወገኖቻችን በህይወት ለመድረስ የአዲስ አበባ እና የአካባቢው ነዋሪዎች የእርዳታ ማስተባበሪያ መርሐ ግብር በመልካም ሁኔታ እየሔደ ነው።

የፊታችን ሰኞ እና ማክሰኞ መስከረም 28 እና 29 በሀገር ፍቅር ቴአትር ከሚሰበሰበው እርዳታ #በተጨማሪ ቅዳሜና እሁድ ብቻ ለሚመቻቸው ወገኖቻችን ከዚህ በታች ባሉ ግዚያዊ መሰብሰቢያ ጣቢያዎች ያዘጋጃችሁትን እርዳታ እያስመዘገባችሁ መለገስ ትችላላችሁ።

ለማስታወስ ያህልም የእርዳታ አይነቶቹን በድጋሚ እናስታውቃለን።

#የማይበላሹ_ምግቦች
መኮረኒ
ሩዝ
ፉርኖ ዱቄት
ዘይት
ሴሪፋም /ፋፋ/
ብስኩት /ጋቤጣ/

#የንጽህና_ቁሳቁሶች
ሳሙና
ኦሞ
ሳኒታይዘር
የሴቶች ንጽህና መጠበቂያ /ሞዴስ/

#አልባሳት
ብርድ ልብስ
ነጠላ ጫማ
የተለያዩ አልባሳት (ያገለገሉም ቢሆን)
በመሆኑም ከዚህ በታች በተቀመጡት ተጨማሪ አድራሻዎች ቅዳሜና እሁድን ብቻ የቻሉትን በአቅራቢያዎ መለገስ ይችላሉ።

🔹ሜክሲኮ ኬኬር ህንፃ ~0911219235 ቦሌ ኤድና ሞል ዝቅ ብሎ ምስራቅ በር ስጋ ቤት @Blen Sahlu

🔹ኮልፌ እና 18 ማዞሪያ ፍቅሩ አብጤ +251911319571

🔹ሰባተኛ የአማኑኤል ታክሲ መያዣ 0911793475 ደንበል ጀርባ ከ ላፓሪዝያን ፊት ለፊት ሶሎሞን ሞባይል +251912634363 @Solomon Mengesha

🔹ፒያሳ ማስታወቂያ ሚንስቴር አካባቢ ተስፋዬ ለማ ~+251912914748
ለበለጠ መረጃ መሐመድ ካሳ ወይንም ያሬድ ሹመቴን በ0930 36 52 44 ማግኘት ይችላሉ።

ጫካ ያደሩ ህፃናትና እናቶች፤ አረጋውያንና ደካሞች ከምንም በላይ "የኢትዮጵያዊያን ያለህ!" እያሉ ነው።

#ሰብዓዊነት_ይቅደም !!

(ከአንድ ግዜ በላይ ሼር በማድረግ ማህበራዊ ኃላፊነትዎን ይወጡ!)

ከያሬድ ሹመቴ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አፋልጉን⬆️

"ዘቢባ በሽር ትባላለች ያደረገችው ቢጫ ሻርብ የለበሰችውም እንዲሁ 22 አካባቢ ባቡር ውስጥ ገብታ #ጠፍታብናለች ያያችኋት ሰዎች ተባበሩን። 0936959633 , 0911131844 ቤተሰቦቿ ነን"

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ⬆️የነባር ተማሪዎች የምዝገባ ቀን ላልተወሰነ ጊዜ መራዘሙን ተቋሙ ዛሬ ባወጣው ማስታወቂያ ገልጿል። 25/01/2011

@tsegabwolde @tikvahethiopia
አስቸኳይ መረጃ‼️

በሀዋሳ ከተማ በመካሄድ ላይ ያለው የኢህአዴግ 11ኛ ድርጅታዊ ጉባዔ በሠላም መጠናቀቁን በማስመልከት በሲዳማ ብሔር ባህላዊ ጫዋታ ( #በቄጣላ) እንደሚበሰር ተገለፀ።

"ሀገራዊ አንድነት ለሁለንተናዊ ብልፅግና" በሚል መሪ ቃል ከመስከረም 23-25/2011 ዓ.ም በሀዋሳ ከተማ በመካሄድ ላይ ያለው የኢህአዴግ 11ኛው ድርጅታዊ ጉባዔ በድል መጠናቀቁን ለማብሠር ነገ ቅዳሜ መስከረም 26/2011 ዓ.ም. በሀዋሳ ዓለም አቀፍ ስታዲየም የኢህአዴግ ሊቀመንበርና የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትሪ ዶ/ር #ዐቢይ_አህመድ እና የግንባሩ ምክትል ሊቀመንበርና የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሪ አቶ #ደመቀ_መኮንን ጨምሮ የየሁሉም ክልሎች ርዕሳኔ መስተዳድሮች፣ የእህትና አጋር ድርጅቶች አመራሮች እንዲሁም የኢህአዴግ 11ኛው ድርጅታዊ ጉባዔ ተሳታፊ አባላትና ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት በሀዋሳ ዓለም አቀፍ ስታዲየም ከጧቱ 1:00 ጀምሮ የቄጣላ ትዕይንት ከታዬ በኋላ ጉባዔው በይፋ ይዘጋል።

በመሆኑም በተባለው ሰዓት በቦታው ተገኝታችሁ ትዕይንቱን እንድትከታተሉ የሲዳማ ዞን አስተዳደር ጥሪውን ያቀርባል።

መስከረም25/2011 ዓ.ም
ሀዋሳ,ሲዳማ

ምንጭ፦ የሲዳማ ዞን ባህል፣ ቱሪዝም እና መንግስ ኮሚኒኬሽን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ለሚመለከታቹ‼️

(ከፂዮን ግርማ)

ለመምከር አይደለም-የተሰማችኝን ለማካፈል ነው። ዕድሜ ብዙ ነገር ያስተምራል። በዕድሜያችን ላይ የሚጨምረው ሰዓትና የተጓዝንበት ሂደት ለሚቀጥለው ጊዜ #ስህተት እንዳንሠራ ሊታደገን ይገባል።

ጤናማ ባልሆነ ውድድርና #በብሽሽቅ ውስጥ፤ ከተወዳዳሪውና ከተበሻሻቂው ውጪ በማያውቀው ነገር በፅኑ #የሚጎዳ አካል (ሕዝብ) አለ።

ከችግርና ችጋር ጋር እየታገለ ምንም በማያውቀው ነገር ድንገት መከራ የሚወርድበትን አካል ለመታደግ የምታስፈልገው ነገር “ትንሽ” ናት "ጨዋ" #ቃላትን መጠቀም።

ስድብ፣ ማዋረድና ማንቋሸሽ ከታከለበት ውድድርና በብሽሽቅ ወጥቶ በሐሳብና በጉዳይ ላይ ብቻ ያተኮረ አስተያየት መስጠት። #በጨዋ ቋንቋ እየታገዙ የሐሳብ ድርና ማግን መሸመን ከልካይ አይኖረውም።

አንደበታችን ለበጎ፣ ጣቶቻችንን ደግሞ #ለመልካም ሥራ እናውላቸው። ተመልሰን #ለማንመጣባት ምድር መጥፎ ነገር ጥለን አንለፍ። #ጤናማ የአደባባይ ላይ ክርክርና የውይይት ባህልን እናዳብር፣ #ቴክኖሎጂን ከመጥፎ ነገር ይልቅ ለጥሩ ነገር እንጠቀም። እጆቻችንን #ለስድብ አናታትራቸው።

#ሼር - በፌስቡክ ገፃቹ ላይ!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ወ/ሮ ሙፈርያት በምርጫው አልተወዳደሩም – ከምርጫ ራሳቸውን #አላገለሉም። ሦስት ሰው ተጠቆመ።

በዚህም መሠረት፦
🔹ዶ/ር ዓቢይ አህመድ በአቶ ሚሊዮን ማቴዎስ
🔹አቶ ደመቀ መኮንን በአቶ ለማ መገርሳ፣
🔹ዶ/ር ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል በአቶ ገዱ አንዳርጋቸው ለእጩነት ተጠቆሙ።

በዶ/ር ደብረጽዮን ጥቆማ የሕወሓት እጩነት ተቃውሞ አቅርበው ነበር። ይሁን እንጂ በእጩነት #ይወዳደሩ የሚል በርካታ አባል #የድጋፍ ድምጽ ሰጠ። በምስጢር በጽሁፍ ነው ድምጽ ተሰጠው።

ምንጭ፦ ጋዜጠኛ ጌጡ ተመስገን
@tsegabwolde @tikvahethiopia