TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.82K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ናዲያ ሙራድ🕊 በፈረንጆቹ 2014 በሃገሯ #ኢራቅ በጽንፈኛው ታጣቂ ቡድን #አይ_ኤስ ታግታ የቆየችና #የወሲብ ጥቃት ሰለባ የሆነች ወጣት ናት። ከቡድኑ እገታ ከወጣች በኋላም ይህን መሰሉ #ጥቃት እንዲቆምና በጦርነት ቀጠና ውስጥ የሚገኙ #ሴቶችን ለመታደግ ጥረት ስታደርግ ቆይታለች። ናዲያ ላደረገችው ጥረት የዘንድሮው የኖቤል #የሰላም ሽልማት አሸናፊ ሆናለች።
.
.
እኔ ግሌ እስካሁን ድረስ በህይወቴ ውስጥ ካየኋቸው እና ታሪካቸውን ከሰማሁ ድንቅ ሰዎች አንዷ ናት። ከእርሷ ጥንካሬን፣ ተስፋ አለመቁረጥን፣ ሰላም ወዳድ መሆንን፣ ለሰው ልጅ መኖርን ተምሪያለሁ! ዛሬ ይህን አጋጣሚ ተጠቅሜ ለናዲያ ያለኝን ትልቅ ክብር ለመገልፀ እወዳለሁ!
.
.
🕊🕊🕊ናዲያ ሙራድ🕊🕊🕊
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አሜሪካ የተሳተፈችባቸው ጦርነቶች ...

በ21ኛው ክፍለ ዘመን የዓለም ኃይል እንደሆነች የሚነገርላት አሜሪካ በበርካታ ሀገራት ውስጥ በተደረጉ ጦርነቶች እጇን አስገብታለች።

በጥቂቱ...

#አፍጋኒስታን

አል-ቃይዳ መስከረም 11 ቀን 2001 በአሜሪካን ላይ ጥቃት ከሰነዘረ በኋላ አሜሪካ ታሊባንን ከስልጣን ለማስወገድ አሜሪካ የአፍጋኒስታንን ወረራ መርታለች። 20 ዓመታት የዘለቀ እጅግ ዋጋ ያስከፈለ ጦርነት ነበር። በመጨረሻ ግን ታሊባን ወደቦታው ተመለሰ። አሜሪካም ጓዛን ጠቅልላ ወጣች።

#ኢራቅ

በፕሬዚዳንት ጆርጅ ቡሽ ዘመን አሜሪካ እ.ኤ.አ. በ 2003 ኢራቅን በመውረር ሳዳም ሁሴን ከሥልጣን አስነስታለች። በኢራቅ ጦርነት በርካቶች አልቀዋል፣ ከፍተኛ ውድመት ደርሷል። ኢራቅ ዛሬም አስተማማኝ ሙሉ ሰላም የላትም። ለዳግም ግንባታም ደፋ ቀና እያለች ነው።

#የድሮን_ጥቃቶች

አሜሪካ ሽብርን ለመዋጋት በሚል በፓኪስታን፣ የመን፣ ሱማሊያ፣ ሊቢያ የድሮን ጥቃቶችን ፈፅማለች (አሜሪካ ከፍተኛ የሰራዊት ቁጥር አላሰፈረችም)።

እነሊቢያ፣የመን፣ ሱማሊያ በጦርነት ምስቅልቅላቸውን አውጥቶት ዛሬም ማገገም ያልቻሉ ለደህንነት አስጊ ሀገራት ሆነው ቀርተዋል።

#ሊቢያ

የአሜሪካና የአውሮፓ አጋሮች እኤአ በ 2011 በሊቢያ የአየር ዘመቻ ከፍተው ነበር ፤ ጥቃቱ ሙአመር ጋዳፊ በአረብ አብዮት ለመቃወም በተነሳሱ ተቃዋሚዎች ላይ የደረሰውን ግፍ ለመከላከል በሚል ነው ፤ የእነ አሜሪካ መዘቻ ጋዳፊን አወረደ ፣ ሊቢያ ግን ወደ ትርምስና ቀውስ ገባች፤ ዛሬም እዛው ናት።

አሜሪካ እጇን ባስገባችባቸው ሀገራት ትክክለኛ ውሳኔ እንደሆነ የምትሞግት ሲሆን በምታካሂዳቸው ዘመቻዎች ከሽብር ጥቃት ዜጎቿን መከላከል /የሀገሯን ደህንነት ማስጠበቅ እንደቻለች በተለያየ ጊዜ ታነሳለች።

@tikvahethiopia
አሜሪካ የተሳተፈችባቸው ጦርነቶች ...

#Repost

በ21ኛው ክፍለ ዘመን አሜሪካ በበርካታ ሀገራት ውስጥ በተደረጉ ጦርነቶች እጇን አስገብታለች።

በጥቂቱ...

#አፍጋኒስታን

አል-ቃይዳ መስከረም 11 ቀን 2001 በአሜሪካን ላይ ጥቃት ከሰነዘረ በኋላ አሜሪካ ታሊባንን ከስልጣን ለማስወገድ አሜሪካ የአፍጋኒስታንን ወረራ መርታለች። 20 ዓመታት የዘለቀ እጅግ ዋጋ ያስከፈለ ጦርነት ነበር። በመጨረሻ ግን ታሊባን ወደቦታው ተመለሰ። አሜሪካም ጓዟን ጠቅልላ ወጣች።

#ኢራቅ

በፕሬዚዳንት ጆርጅ ቡሽ ዘመን አሜሪካ እ.ኤ.አ. በ 2003 ኢራቅን በመውረር ሳዳም ሁሴን ከሥልጣን አስነስታለች። በኢራቅ ጦርነት በርካቶች አልቀዋል፣ ከፍተኛ ውድመት ደርሷል። ኢራቅ ዛሬም አስተማማኝ ሙሉ ሰላም የላትም። ለዳግም ግንባታም ደፋ ቀና እያለች ነው።

#ሊቢያ

የአሜሪካና የአውሮፓ አጋሮች እኤአ በ 2011 በሊቢያ የአየር ዘመቻ ከፍተው ነበር ፤ ጥቃቱ ሙአመር ጋዳፊ በአረብ አብዮት ለመቃወም በተነሳሱ ተቃዋሚዎች ላይ የደረሰውን ግፍ ለመከላከል በሚል ነው ፤ የእነ አሜሪካ መዘቻ ጋዳፊን አወረደ ፣ ሊቢያ ግን ወደ ትርምስና ቀውስ ገባች፤ ዛሬም እዛው ናት።

#ሶሪያ

አሜሪካ ከሌሎች አጋሮቿ ጋር ሆና በሶሪያ ጦርነት ውስጥም እጇ ያለበት ሲሆን በሶሪያ የሚንቀሳቀሱ የበሽር አል አሳድ ተቃዋሚዎችን ለማጥፋት በምትወስደው እርምጃ የሶሪያ ከተሞች ክፉኛ አውድማለች።

#የድሮን_ጥቃቶች

አሜሪካ ሽብርን ለመዋጋት በሚል በፓኪስታን፣ የመን፣ ሱማሊያ፣ ሊቢያ የድሮን ጥቃቶችን ፈፅማለች (አሜሪካ ከፍተኛ የሰራዊት ቁጥር አላሰፈረችም)።

እነሊቢያ፣የመን፣ ሱማሊያ ጦርነት ምስቅልቅላቸውን አውጥቶት ዛሬም ማገገም ያልቻሉ ለደህንነት አስጊ ሀገራት ሆነው ቀርተዋል።

@tikvahethiopia
#Russia

የሩስያ የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ተቆጣጣሪ ቡድን የዩክሬን ግጭትን አስመልክቶ ሀሰተኛ መረጃዎችን እያሰራጩ ነው ባላቸው የብሪቲሽ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (#ቢቢሲ) እና የራዲዮ ሊብሪቲ ድረ-ገጾች ላይ ገደብ ጥሏል።

ሩስያ የምዕራባውያን ሚዲያዎች ፤ በውጭ ሀገራት ጦርነት ለምሳሌ እንደ #ኢራቅ ባሉ እና በሙስና እጃቸው ያለባቸው የገዛ የራሳቸው ሀገራት መሪዎች ተጠያቂ ማድረግ ሳይችሉ በከፊል እና ብዙ ጊዜ ፀረ-ሩሲያ የሆነ አመለካከትን ለዓለም ያስተላልፋሉ ስትል በተደጋጋሚ ስትወቅስ ቆይታለች።

ከዩክሬን ጋር በተያያዘ የሩስያ ባለስልጣናት "ወረራ" ሚለውን ቃል የማይጠቀሙ ሲሆን የምዕራባውያን ሚዲያዎች ዩክሬን ውስጥ በሩሲያኛ ተናጋሪ ህዝቦች ላይ የሚፈፀመውን " የዘር ማጥፋት ወንጀል " ሪፖርት እንደማያደርጉ ይናገራሉ።

ሩስያ ምዕራባውያን ሚዲያዎች ላይ ገደብ ከመጣሏ በፊት ምዕራባውያኑም በሩስያ ሚዲያዎች ላይ የተለያዩ ገደቦችን ጥለዋል።

ለአብነት ዩናይትድ ኪንግደም በሩስያ የሚደገፈው " ራሺያ ቱዴይ " ቴሌቪዥን ዩናይትድ ኪንግደም ውስጥ እንዳይታይ አግዳዋለች።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የአሜሪካ ወረራ ... የቀድሞ የአሜሪካ መሪ ኢራቅን ለመውረር ትዕዛዝ ከሰጡ ዛሬ እሁድ 20 ዓመት ደፈነ። የቀድሞ ፕሬዝዳንት ጆርጅ ቡሽ ኢራቅን ለመውረር ትዕዛዝ ከሰጡ ዛሬ 20 ዓመት ሞልቶታል። የዛሬ 20 አመት ጦርነቱ ሲጀመር አስደንጋጭ እና አስፈሪ የቦምብ ጥቃት ዘመቻ ባግዳድን አቀጣጥሏት ነበር። በዚህ ወረራ የአሜሪካ ጦር በስልጣን ላይ የነበረውን የሳዳም ሁሴን መንግስት አፍርሶ ሳዳምን ከስልጣን…
#ኢራቅ

ዛሬ የቀድሞ #የአሜሪካ ፕሬዜዳንት ቡሽ ኢራቅ ላይ ወረራ እንዲፈፀም ካዘዙ 20 ዓመት የሞላው ሲሆን በወቅቱ ለወራር ምክንያት የተባለው ኢራቅ ውስጥ አለ የተባለው የጅምላ ጨራሽ የጦር መሳሪያ ነው።

ነገር ግን ይህ " አለ " የተባለው የጅምላ ጨራሽ መሳሪያ አልተገኘም።

እኤአ በ2003 ወረራው ከመፈፀሙ ከወራት በፊት በወቅቱ የኢራቅ ፕሬዜዳንት የነበሩት እና ከወራራው በኃላ #በስቅላት የተገደሉት ሳዳም ሁሴን በተመድ ጠቅላላ ጉባኤ (መስከረም 19/2002) ላይ እንዲህ ሲሉ ተናግረው ነበር ፦

" ኢራቅ ከኒውክሌር፣ ኬሚካል እና ባዮሎጂካል መሳሪያዎች ሁሉ የጸዳች መሆኗን ከዚህ በፊት አውጃለሁ።

#የአሜሪካ_አስተዳደር የመካከለኛው ምስራቅን ዘይት ለመቆጣጠር ኢራቅን ለማጥፋት ይፈልጋል ፤ ይህን ተከትሎ ፖለቲካውን እንዲሁም የመላው ዓለምን የዘይት / ነዳጅ እና የኢኮኖሚ ፖሊሲዎች ይቆጣጠራል። "

@tikvahethiopia
#ኢራቅ

የኢራቅ ፓርላማ #ግብረሰዶም / የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን ከ10 እስከ 15 ዓመት በሚደርስ እስር የሚቀጣ አዲስ ሕግ አርቅቋል።

በአዲሱ ሕግ መሠረት ጾታቸውን የቀየሩ ሰዎች ከ1 እስከ 3 ዓመት ሊታሰሩ ይችላሉ።

በአዲሱ ሕግ ፦

➡️ የግብረሰዶም / የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን የሚያበረታቱ፣ የሚያስተዋውቁ፤

➡️ ሴተኛ አዳሪነትን የሚያራምዱ፤

➡️ ጾታ ለመቀየር ቀዶ ህክምና የሚያደርጉ ዶክተሮችን፤

➡️ " ሆን ብለው " እንደ #ሴት የሚሆኑ ወንዶች እና " በሚስት መለዋወጥ " ላይ የተሠማሩ ሰዎች እስራት ይጠብቃቸዋል ፤ ዘብጥያም ይወርዳሉ።

የሕጉ ዓለማ ፥ " የኢራቅን ማህበረሰብ ከሞራል ዝቅጠትና ግብረ ሰዶማዊነት ከሚያደርሰው አደጋ ለመጠበቅ ነው " ተብሏል።

ረቂቁ መጀመሪያ ላይ ግብረሰዶማውያን #በሞት እንዲቀጡ የሚል የነበረው ቢሆንም በአሜሪካ እና በአውሮፓ ሀገራት ከፍተኛ ተቃውሞ መሻሻሉ ነው የተሰማው።

የኢራቅ ፓርላማ አባል የሆኑት አሚር አል-ማሙሪ ፥ " አዲሱ ሕግ #ኢስላማዊ እና ማህበረሰባዊ እሴቶችን የሚቃረኑ ልዩ ጉዳዮችን ለመዋጋት ትልቅ እርምጃ ነው " ብለዋል።

#አሜሪካ በውጭ ጉዳይ መ/ ቤቷ በኩል ሕጉን ፤ " ለሰብአዊ መብትና ነፃነት ጠንቅ ነው " በማለት ሕጉን ተቃውማለች።

" ሕጉ የኢራቅን ኢኮኖሚ የሚያቀዛቅዝ እና የውጭ ኢንቨስትመንትን የመሳብ አቅምን ያዳክማል" ብላለች።

የምዕራቡ ዓለም ሀገራት ሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶችም ሕጉን ተቃውመዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመረጃው ምንጮች #ቢቢሲ እና #ሮይተርስ መሆናቸውን ይገልጸል።

@tikvahethiopia