الزواج في الإسلام /ትዳር በኢስላም
22.6K subscribers
359 photos
16 videos
7 files
912 links
﴿وَمِنْ آيَاتِهِ أَنْ خَلَقَ لَكُم مِّنْ أَنفُسِكُمْ أَزْوَاجًا لِّتَسْكُنُوا إِلَيْهَا وَجَعَلَ بَيْنَكُم مَّوَدَّةً وَرَحْمَةً﴾

ለማንኛዉም አስተያየት☞☞ @Tidarbaislam_bot
ለይ ያድርሱን

ለጥያቄ ☞☞ t.me/Hayatbintkedir
Download Telegram
💌::::::::::እውነተኛ ፍቅር:::::::::::💌

🍃:::::ክፍል 3⃣

#የከድጃ ሀብት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መጣ፡፡ በውክልና እሷ ዘንድ በኮሚሽን መቀጠር ከቻሉ ሰዎች መካከል ሙሀመድ (ሰዐወ) አንዱ ነበር፡፡ ወጣቱ ትሁት ሰው አክባሪ የሰውን ገንዘብ ያለ ሀቁ የማይፈልግ ታታሪ ቸር ስራውን ወዳድ በመሆኑ ከድጃ ጋር #ከተቀጠረ ጀምሮ ከመካ ከተማ ርቆ በመሄድ እየነገደ ገንዘቧን በእጥፍ አሳደገው፡፡ በዚህም ከድጃ በወጣቱ ኮርታበታለች፡፡ #ሙሀመድ ከድጃ ጋር የተቀጠረው እንዲሁ በአጋጣሚ አልነበረም፡፡ የሚያሳድጉት አጎቱ ጥሪት አነስተኛ በመሆኑ እንጂ፡፡
የሙሀመድ አባት አብደላህ ገና ሳይወለዱ ነበር የሞቱት፡፡ እናታቸውን ያጡት ደግሞ በ6 አመታቸው ነበር፡፡ ቢሆንም በአያቱ ዘንድ አደገ፡፡ አያቱ ሲሞቱ አጎቱ ተረከቧቸው፡፡
#መሀመድ አጎቱ ጋር መኖር ሲጀምር ፍየል በመጠበቅ ተግባር ተሰማራ፡፡ ግን ብዙም ሳይቆይ አጎትየው የገቢያቸውን መጠን ለማሳደግ ጥረት ማድረግ ጀመሩ፡፡
#አንድ #ቀን ከድጃ ወንዶችን ወደ ምድረ ሻም በመላክ እንደምታሰማራ ስላወቁ ነጋዴው ወደተባለው ሀገር ለመጓዝ በዝግጅት ላይ ሳሉ ሙሀመድን አስጠርተው ስለሁኔታው ሊነግሯቸው ወሰኑ፡፡
"የወንድሜ ልጅ ሆይ እንደምታውቀው አንዳች የሌለኝ ደሀ ነኝ ፤ ግዜው ደግሞ በድርቅ ተመቷል፡፡ ከድጃ ሰው ቀጥራ እንደምታስነግድ ሰምቻለው በርግጥ የምትከፍለው ገንዘብ አነስተኛ በመሆኑ ደስ አያሰኝም፡፡ #እናም ስለዚህ ጉዳይ እሷኑ ባነጋግርልህ " ሲሉ አቡጧሊብ ጥያቄ ለመሀመድ አቀረቡ፡፡ ሙሀመድም እንዲህ አላቸው "አጎቴ ሆይ እንዳሻህ ማድረግ ትችላለህ ሀሳብህ የኔም ሀሳብ ነው መጭው አለም ከዱንያ አለም በላጭ ነው" አሏቸው፡፡
#አቡጧሊብ ጊዜ ማጥፋት አልፈለጉም ወንድሞቻቸውን አስከትለው ወደ ኸድጃ ቤት አመሩ፡፡ እሷም ከሀር በተሰራ ባማረ ልብስ ተውባ በፈገግታ ተቀበለቻቸው፡፡
አቡጧሊብም "የተከበርሽው ከድጃ ሆይ እኛ የመጣነው ለጉዳይ ነው ሰዎችን ገንዘብ እየከፈልሽ እንደምታስነግጂ ሰምቻለው፡፡ ለሌሎች በምትከፊይው ላይ ጨምረሽ ተመሳሳይ ስራ እንዲሰራልሽ መሀመድን አትቀጥሪምን? " አሉ
ከድጃም "እንኳንስ ለሚወደድ ለቅርብ ዘመድ ለማይታወቀውም ቢሆን ጥያቄዎ በኔ ዘንድ ተቀባይነት አለው" በማለት አስደሳች መልስ ሰጠች፡፡
አቡጧሊብ አስደሳቹን ዜና ይዘው ወደ መሀመድ (ሰዐወ) ተመለሱ፡፡ ብስራቱን ከነገሩት በኋላ "ይህ ፈጣሪ ላንተ የላከው ሲሳይ ነው " አሉ፡፡
ሩህሩሁ አጎት መጪው ጊዜ ያረገዘውን ቢረዱ ይህ ለከድጃ ከሰማይ የወረደ ፀጋ ነው ባሉ ነበር፡፡ ሆኖም ከዚህ መልካም ዜና በስተጀርባ የሚመጣውን የላቀ ዕጣ የሚያውቅ አንድም ሰው አልነበረም፡፡
እድለኛዋ ከድጃ አቡጧሊብ ያቀረቡትን ጥያቄ በደስታ ተቀበለች ፤ ይህም ሙሀመድ (ሰዐወ) እና ከድጃ (ረዐ) ለመጀመሪያ ጊዜ የተዋወቁበት አጋጣሚ ፈጠረ፡፡ ጉዳዩ በመካ ነዋሪዎች ዘንድ ተዳረሰ፡፡ በየአጋጣሚው የታላቁን ሰው መልካም ትሩፋት እውነተኛነት ዘረዘሩላቸው፡፡ ከድጃም ይበልጥ ደስ አላት፡፡ #መይሰራ ከተባለው አገልጋይ ጋር ወደ ሻም እንዲሄዱ ለማድረግ መዘጋጀታቸውን አስታወቀች፡፡ ሙሀመድም የተሰጣቸውን አማና ተቀብለው ለንግድ ከመይሰራ ጋር ወደ ሻም አመሩ፡፡

❥ሀያት ቢንት ከድር❥

ይ-----ቀ-----ጥ---ላ------ል

💌:::::::::::::Telegram:::::::::::::💌

https://t.me/joinchat/AAAAAEOFD8riR2kM4HsIJg
💌:::::::::እውነተኛ ፍቅር::::::::💌

🍃:::::ክፍል 4⃣

ከሻም ጉዞ መልስ ከድጃ (ረዐ) #ለሙሀመድ (ሰዐወ) "ለአንተ እኔ ዘንድ ጥሩ ደስታና ስጦታ ተቀምጦልሀል ከሁሉም ሰራተኞች የበለጠ እጥፍ ተጨማሪ ገንዘብ ይከፈልሀል" አለችው፡፡ #ሙሀመድም (ሰዐወ) ከጉዞ መልስ አጎቱ ጋር ተመለሰ፡፡ #አቡጣሊብም አባት ለልጅ አቀባበል ከሚያደርገው በላይ በደስታ ተቀበሉት፡፡ ከዚያም እንዲህ አሉት
"#ልጄ #ሆይ ከድጃ ከፈለችህ"
ሙሀመድም "ከውሉ በተጨማሪ ትርፍ ገንዘብ ጨምራ እንደምትሰጠኝ ቃል ገባችልኝ " አለ
#አቡጣሊብም "ልጄ ሆይ የወላጆችህ አደራ አለብኝ እንደምታዬኝ አርጅቻለሁ የሞትም ምልክቱ እየታየብኝ ነው ስለዚህ አንተን ድሬ ወግ ማዕረግህን ማየት እፈልጋለሁኝ እናም ከቁረይሾች ጥሩ ሚስት ብፈልግልህና ብድርህስ " አሉ፡፡
#ሙሀመድም "አጎቴ ሆይ አንተ እንደፈለክ ማድረግ ትችላለህ እኔ ያንተን ትዕዛዝ ለመፈፀም ዝግጁ ነኝ " አለ፡፡
ከሻም መልስ በሁለተኛው ቀን ታላቁ ሙሀመድ (ሰዐወ) ገላቸውን ታጥበው አቡጣሊብ በገዙላቸው ልብስ ተውበው ወደ ከድጃ ሄዱ፡፡ ከድጃም እውነተኛ ፣ ታማኝ ፣ ፍትሀዊ ፣ አዛኝ ፣ መልካም ሰሪን ታላቁን ወጣት በውበቱ ላይ አዲስ ልብስን ተጎናፅፎ ስታየው ተደነቀች ከዚያም "#እንዲህ #አምረህ የመጣኸው ከኔ አንድ ነገር ፈልገህ ሳይሆን አይቀርም ምን ልታዘዝ ሀጃህ ምንድነው?" አለችው፡፡
"#ከአንቺ ዘንድ ያለኝን ገንዘብ ፈልጌ ነው " አላት፡፡
"#መሀመድ ሆይ ይህ ውዐትና ገንዘብ ይዘህ በንደዚህ ሁኔታህ ምን ልትሰራበት ነው" አለችው፡፡
"አጎቴ ከቁረይሽ የሆነችን ሚስት እድርልሀለው ስላለኝ ተስማምቼ ነው የመጣሁት " አላት፡፡
"#ሚስት ልታገባ አስበህ ከሆነ እኔ እጅግ ቆንጆ የሆነች ገንዘብ ያላት ለዘርህ ቅርብ የሆነች ሹማምንቶች ለጋብቻ ጠይቀዋት እንቢ ያለች በሰዎች ዘንድ የተከበረች አዕምሮዋ የተረጋጋና የሞላ አንተን እንጂ ከአንተ ምንም የማትፈልግ ሚስት አዘጋጅቼልሀለው፡፡" አለችና #እንዲህ ስትል ቀጠለች "ከአንተ የማልደብቀው ሁለት ነውር አላት አንደኛው ነውሯ አግብታ ታውቃለች ሁለተኛው በዕድሜ ከአንተ ትበልጣለች " አለች፡፡
#መሀመድም "አንቺ ጥሩዋ ሴት ሆይ ማናት እሷ የትስ ነው ያለችው " አላት
"ያንተ ምርኮኛ ናት እዚሁ ቅርብ አጠገብህ ታያታለህ ስሟም ከድጃ ይባላል" አለችው፡፡
#መሀመድም ሁሉም ነገር በተገለጠለት ጊዜ ምንም መልስ ሳይሰጥ ዝም አለ፡፡
ከድጃም "የእሺታ መልስ ስጠኝና ልቤን አሳርፈው" አለችው፡፡
አሁንም ከወጣቱ መልስ ስታጣ "አላህ ካለ እኔ ከታጋሾች ሆኜ ታገኘኛለህ አንተንም በምንም አልወነጅልህም" አለች፡፡
#መሀመድም (ሰዐወ) "ከድጃ ሆይ አንቺ የተከበርሽና ባለብዙ ሀብት እኔ ደግሞ የአንቺ ተቀጣሪና ከምትሰጪኝ ገንዘብ ሌላ ምንም የለኝም እናም ገንዘብ የሌለው ፈልጎም ቢሆን ቢጤውን ያገባል" አላት፡፡
.
.
አላለቀም

❥ሀያት ቢንት ከድር❥

ይ...ቀ...ጥ...ላ....ል

💌:::::::::::Telegram:::::::::💌

https://t.me/joinchat/AAAAAEOFD8riR2kM4HsIJg
💌:::::::እውነተኛ ፍቅር :::::::💌

🌱ክፍል 5⃣

... ከድጃም እንዲህ አለችው "ገንዘቡን ብናደባልቀው ይበዛል እንጂ አያንስም"፡፡ ወጣቱም በድጋሚ ምንም ሳይመልስላት ዝም አለ፡፡
#ከድጃም "በግልፅም ሆነ በድብቅ የሚሰሩትን የሚያውቅና የሚያይ በሆነው ጌታዬ ይሁንብኝ በኔ በኩል ምንም የሚሸፍነው ነገር የለም፡፡ #ሁሉም #ነገር እውነት ነው በል አሁን ወደ ቤተሰቦችህ ሂድና አጎትህን ለጋብቻ እንዲጠይቁኝ ንገራቸው፡፡ ምናልባት አባቴ ብዙ ገንዘብ ለኒካህ ከጠየቃቸው የጠየቀውን በሙሉ እኔ እሰጥሀለው፡፡ #እኔ ያንተ ነኝ እኔው መረጥኩህ ከአንተ ሌላ ማንንም አልፈልግም፡፡ ልቀርብህ ሳስብ አትራቀኝ " አለችው ልመና በተቀላቀለበት አነጋገር፡፡
#መሀመድ (ሰዐወ) ተነስቶ ከቤቷ ወጣ፡፡ ከድጃ መሀመድ (ሰዐወ) ከመምጣቱ በፊት ለወዳጅ ጓደኛዋ ለነፊሳ አጫውታት ነበር፡፡ ነፊሳም እሱን አሳምና ከምትወደው ሰው ጋር እንደምታጋባት ቃል ገብታላት ነበር፡፡ #ወጣቱ መሀመድና ነፊሳ ሲገናኙ ነፊሳ ስለታላቋ ሴት ስለ ከድጃ መልካም ባህሪና እንዲሁም እሱን ማግባት እንደምትፈልግ ከገንዘቧ እንደምታስበልጠው አንድ በአንድ ነገረችው፡፡ ጥያቄዋን እንዲቀበልም አሳመነችው፡፡
#ታላቁ #ሰው አጎቱ ቤት ተመለሰ፡፡ አቡጣሊብን ከወንድሞቻቸውና እህቶቻቸው ጋር ቤት ቁጭ ብሎ አገኛቸው፡፡ አጎትዬው በፈገግታ ተቀበሉት ከዚያም "ከድጃ ከከባድ ስጦታ ጋር እንደላከችህ እገምታለው" አሉት፡፡ መሀመድም "አጎቴ ሆይ ግምትህ ትክክል ነው፡፡ #ከአንተ ጉዳይ አለኝ " አለ፡፡
#አቡጣሊብም "ከአንተ ጉዳይ ጀርባ ጌታህ አለ፡፡ ለመሆኑ ምንድናት ጉዳይዋ" አሉት፡፡
#መሀመድም "ሂዱና ከድጃን ለትዳር እንደምፈልጋት ቤተሰቧን ጠይቁና አምጡልኝ " አለ፡፡
የመሀመድ አጎቶች ተያዩ ከአቡጣሊብ በስተቀር ማንም ምንም መናገር አልፈለገም፡፡ #አቡጣሊብም "ልጄ ሆይ ከድጃ እጅግ የተከበረችና በሰዎች ዘንድ የተወደደች ብዙ ሀብት ያላት ከአሁን በፊት ሁለት ሰዎች አግብታና በሞት የተለዩዋት ንብረታቸውን ወርሳ የምትኖር አሁን በቅርቡ ታላላቅ ሹማምንቶች ለጋብቻ ጠይቀዋት እንቢ ያለች ናት፡፡ አንተ የወንድሜ ልጅ ደግሞ ምንም ንግድ የለህም የርሷ ተቀጣሪ ነህ፡፡ ስለዚህ ራሷን አሳልፋ አትሰጥህም" አሉት፡፡
#ሙሀመድም (ሰዐወ) "አጎቴ ሆይ አሁን ያልከውን በሙሉ አውቀዋለሁ እረዳሀለው የጋብቻ ጥያቄው ግን ከራሷ ነው የመጣው፡፡ " አላቸው
.
.
.
አላለቀም

❥ሀያት ቢንት ከድር ❥

ይ...ቀ....ጥ....ላ,.....ል

💌:::::::::ቴሌግራማችን:::::::::::::💌


https://t.me/joinchat/AAAAAEOFD8riR2kM4HsIJg