ቴዎ ፍሎስ theophilus
219 subscribers
144 photos
7 files
7 links
" ከወደደን ከትልቅ ፍቅሩ የተነሣ በበደላችን ሙታን እንኳ በሆንን ጊዜ ከክርስቶስ ጋር ሕይወት ሰጠን::
(ወደ ኤፌሶን ሰዎች 2:5)
በዚህ ቻናል የተለያዩ ትምህርቶችና፡ ስብከቶች እንዲሁም ፡ስነ መለኮታዊ ይዘት ያላቸዉ አስተምሮቶች ይቀርበታል። በተጨማሪም ቅዱሳን በinbox ለሚጠይቁት ጥያቄ መልስን የሚያገኙበት መንፈሳዊ ቻናል ነዉ።


መንፈሳዊ ጥያቄን ለመጠየቅ inbox @tsedeM
Download Telegram
እንደ አይሁድ ባህል ከዋነኛዉ ቀጥሎ መናኛ ማቅረብ የተለመደ ነዉ። ጌታ ኢየሱስ ሆይ ካንተ  መናኛ መጠበቅ ግን አንተን አለማወቅ ነዉ።

#ከፀደቀ #መንፈሰ
ስለወደደን ወደድነዉ እንጂ መዉደዳችንን አይቶ አይደለም የወደደን አስቀድሞ ነዉ እርሱ የወደደን
#ከፀደቀ #መንፈሰ
ርዕስ #በእግዚአብሔር #ፊት #ጻዲቅ ክፍል 1

የእግዚአብሔር ፅድቅ ክርስቶስ አጸደቀን

#ከፀደቀ #መንፈሰ
ቀን 24_06_2016
ርዕስ #በእግዚአብሔር #ፊት #ጻዲቅ ክፍል 2

የእኛ ፅድቅ በእግዚአብሔር ፊት
#ለመፅደቅ #ፅድቅን #ያዋጣ #የለም
#ከፀደቀ #መንፈሰ
ቀን 28_06_2016
በስራዬ ነዉ መፅደቅ የምፈልገዉ የሚሉ ሰዎች እግዚአብሔር የሚፈልገዉን የፅድቅ ልክ ቢያዉቁ ያለ ማንገራገር የእግዚአብሔር ፅድቅ የሆነዉን ክርስቶስን ይቀበሉ ነበር።
#ከፀደቀ #መንፈሰ
አራት መነኩሴዎች ከሚኖሩበት ሀገር ወደ ሌላ ሀገር ለመሄድ ጉዞን ይጀምራሉ፣ አርፍደዉ ስለተነሱ የፈለጉበት ቦታ በጊዜ ስላልደረሱ፣ እዛዉ በደረሱበት ቦታ አረፍ ብለዉ ለመሄድ ይወስናሉ፡ ሰዓቱም ስለመሸ ምሽቱንም ባሉበት ቦታ ድንኳን ይዘዉ ስለነበር ድንኳናቸዉ ዘረጉ። ከመተኛታቸዉ በፊት ለመፀለይ ይስማማሉ ከመፀለያችን በፊት አንድ ህግ እናዉጣ አለ አንደኛው መነኩሴ ይህም ህግ ሁላችንም የምንፀልየዉ በዉስጣችን ነዉ ምን አይነት ነገር ቢፈጠር ማዉራት አይፈቀድም አለ፣ የቀሩት ሁሉም በወጣዉ ህግ ተስማምተዉ በዉስጣቸዉ ድምፅ ሳያሰሙ መፀለይ ይጀምራሉ። በጣም ስለጨለመ በድንኳናቸዉ ዉስጥ ሻማ ለኩሰዉ ነበር የሚፀልዮት። ትንሽ እንደቆዮም ከዉጪ በመጣ ንፍስ እየበራ የነበረዉ ሻማ ያጠፍዋዉ።
አንደኛዉ መነኩሴ ከመካከላቸዉ ወይኔ ሻማዉ እኮ ጠፍ አለ፣ ሁለኛዉ መነኩሴ ቀበል አድርጎ በፀጥታ ነዉ መፀለይ ያለብን አለ፣ሶስተኛዉ ደግሞ እባካችሁ ዝም እንበል ያወጣነዉን ህግ እየጣሳችሁ እኮ ነዉ አለ፣ አራተኛዉ መነኩሴ በመጀመሪያ ፈገግ ብሎ እኔ ብቻ ነኝ ያላወራሁት አለ።
ይህንን ታሪክ ያነሳሁት አንድ መልእክት ለማስተላለፍ ነዉ።
በዚህን ጊዜ የአገልጋዮችን ስህተት ወደ social media ይዞ መጥቶ መተቸት የተለመደ ነዉ፣ በአስተምህሮ ወይም በልምምድ ስህተት ዉስጥ ያለን ሰዉ እንድንቃመዉ መፅሐፍ ቅዱስ በተደጋጋሚ ያስተምረናል 👉ፊል 3:2 ማቴ 16፡12 ገላ 5:5_11_12 1ዮሐ 2:22...... መፅሐፍ ቅዱስ ስህተትን እንድንቃወም ብቻ ሳይሆን የሚያስተምረን ስህተትን ስንቃወም አስቀድመን ማወቅ ስላለብን ነገር እንደ መመሪያ ያስተምረናል። ነገሩ ስህተት መሆኑን ብቻ ማወቅ ሳይሆን ያንን ስህተት የምናቀናበትን መንገድ አስቀድመን ማወቅ መቻል አለብን። ምክንያቱም በአሁን ሰዓት ስህተት የሆነን ነገር ለመቃወም በተሳሳተ መንገድ እየተቃወሙ ያሉ እየበዙ ስለመጡ። በቤተክርስቲያን ዉስጥ በአስተምህሮም ሆነ በልምምድ በስህተት መንገድ ያሉ አገልጋዮች ከመፅሐፍ ቅዱስ መምሪያ ዉጪ ስለሆኑ ነዉ። ከመመሪያው ዉጪ ሆነዉ የተሳሳቱትን የምንመልሳቸዉ በመመሪያዉ ነዉ። ስለዚህ የሳቱትን ለመመለስ የመፅሐፍ ቅዱስ መመሪያን ልንከተል ይገባል። ለእኛ ሲባል የሚሻር የመፅሐፍ ቅዱስ መመሪያም ሆነ ህግ የለም። ለምሳሌ መፅሐፍ ቅዱስ " ማንም ሰው የሚናገር ቢሆን፥ እንደ እግዚአብሔር ቃል ይናገር" ይላል(1ኛ ጴጥ4:11) ይህ ለሁሉም ሰዉ የሚሰራ መመሪያ ነዉ። የተሳሳተን ሰዉ በመሳደብ ሳይሆን እንደ እግዚአብሔር ቃል በመናገር ነዉ ልናቀናዉ የምንችለዉ። እኛ ስንሳደብ የእኛ ስድብ ልክ ስለማይሆን።" ለእያንዳንዱ እንዴት እንድትመልሱ እንደሚገባችሁ ታውቁ ዘንድ ንግግራችሁ ሁልጊዜ፥ በጨው እንደ ተቀመመ፥ በጸጋ ይሁን።" ይላል መፅሐፍ ቅዱስ።እግዚአብሔር የአንደበታችንን ቃል ብቻ ሳይሆን የልባችንን motive (ምክንያት) የሚያይ አምላክ ነዉ የተሳሳተን ሰዉ ስንቃወም እርሱን ለመመለስና ገንዘብ ለማድረግ እንዲሁም በእዛ ስህተት መንገድ የሚሄዱትን ምዕመናንን ለማቅናት እንጂ የተሳሳቱትን ፈፅሞ ለመስበርና ለማጥፍት መሆን የለበትም " እግዚአብሔር እንዲህ ይላል። የወደቁ አይነሡምን? የሳተስ አይመለስምን? "( ኤር 8:4) ይላል የሳቱት ቢመለሱ እኛ ለእነርሱ የሚመለስ ልብ እንዳለን እናረጋግጥ። ተሳስታችኋል የተባሉ ከስህተታቸዉ የተመለሱ እዉነተኛዉን አስተምህሮ የሚያስተምራቸዉ አጥተዉ ግራ በመጋባት ዉስጥ ያሉ በርካታ ሰዎች አሉ።😔 ስህተትን መናገር ብቻ ሳይሆን ከስህተቱ ለተመለሰ ሰዉ በፍቅር የሚያቅፍ እጅ ሊኖረን ይገባል።ለዚህ ደግሞ እዉነትን በፍቅር ልንይዘዉ ይገባል " ነገር ግን እውነትን በፍቅር እየያዝን"(ኤፌ4:15) ስህተቱን ለመናገር እንደረበታነዉ ሁሉ እዉነተኛዉን አስተምህሮ ለማስተማር መትጋት አለብን። " እውነትንም ታውቃላችሁ እውነትም አርነት ያወጣችኋል አላቸው። "(ዮሐ8:32) በስህተት የተያዘን ሰዉ ነፃ የምናወጣዉ በእዉነት ነዉ። 1+1 ሶስት አይደለም ፥4ትም አይደለም፥10ም አይደለም እያልክ ያልሆነዉን ከምትነግረኝ የሆነዉን 2 ብትነግረኝ ያልሆነዉን እኔ በቀላሉ እለያለሁ። አማኞች ስህተት የሆነዉ ነገር እንዲለዩ እዉነተኛዉን የእግዚአብሔርን ቃል እናስተምራቸዉ።
ይህ ከላይ የገለፅኩላችሁ ስህተትን ስንቃወም መፅሐፍ ቅዱስ ከሚሰጠን መመሪያዎች በጥቂቱ ናቸዉ።
መጀመሪያ ወዳነሳሁላችሁ ታሪክ ልመላሳችሁ፣ አራቱም መነኩሴዎች ያወጡትን ህግ ሽረዋል። አራቱም የሻሩት ልክ በሚመስል ምክንያት ነዉ፣ አንደኛዉ የሻማ መጥፍቱን እንዲያዉቁ ተናገረ ፥ሁለተኛው ደግሞ የወጣዉን ህግ ለተናገረዉ ሰዉ ለማስታወስ ተናገረ፥ሶስተኛዉ ደግሞ ሁለቱም ፀጥ እንዲሉ እንዳይናገሩ ተናገራቸዉ፥አራተኛዉ በስተመጨረሻ እኔ ብቻ አልተናገርኩም ብሎ አለመናገሩን ተናገረና ህጉን አፈረሰ።

ተወዳጆች የእግዚአብሔር ቃል የሁላችንም መመሪያ ነዉ። አንድ አገልጋይ ከተሳሳተ ልንመልሰዉ የሚገባ እንደ እግዚአብሔር ቃል እንጂ አሳማኝ በሚመስል ምክንያት ግን ስህተት በሆነ መንገድ እንዲሁም የእግዚአብሔርን ህግ በመሻር መሆን የለበትም።
ጌታ ኢየሱስ ታልፎ በሚሰጥበት ምሽት
ይሁዳ ጭፍሮችንና ከካህናት አለቆች ከፈሪሳውያንም ከሎሌዎችን ጋር በችቦና በፋና በጋሻ ጦር ሆኖ ወደ ኢየሱስ መጣ
ኢየሱስም የሚመጣበትን ሁሉ አውቆ ወጣና ማንን ትፈልጋላችሁ አላቸው። የናዝሬቱን ኢየሱስን ብለው መለሱለት። ኢየሱስ። እኔ ነኝ አላቸው። አሳልፎ የሰጠውም ይሁዳ ደግሞ ከእነርሱ ጋር ቆሞ ነበር።እንግዲህ። እኔ ነኝ ባላቸው ጊዜ ወደ ኋላ አፈግፍገው በምድር ወደቁ።ደግሞም። ማንን ትፈልጋላችሁ? ብሎ ጠየቃቸው። እነርሱም። የናዝሬቱን ኢየሱስን አሉት።
ኢየሱስ መልሶ። እኔ ነኝ አልኋችሁ፤ እንግዲህ እኔን ትፈልጉ እንደ ሆናችሁ እነዚህ ይሂዱ ተዉአቸው አለ፤ይህም። ከእነዚህ ከሰጠኸኝ አንዱን ስንኳ አላጠፋሁም ያለው ቃል ይፈጸም ዘንድ ነው። ስምዖን ጴጥሮስም ሰይፍ ስለ ነበረው መዘዘው፥ የሊቀ ካህናቱንም ባርያ መትቶ ቀኝ ጆሮውን ቈረጠ፤ የባርያውም ስም ማልኮስ ነበረ።ኢየሱስም ጴጥሮስን። ሰይፍህን ወደ ሰገባው ክተተው፤ አብ የሰጠኝን ጽዋ አልጠጣትምን? አለው።
(ዮሐ 18_1_11) ጴጥሮስ የማልኮስን ጆሮ ለመቁረጥ በቂ ምክንያት ነዉ ያለዉ። ግን ልክ አልለበረም። ኢየሱስ ጎበዝ ብሎ አላበረታታዉም ወዲያዉኑ ሰይፍህን ወደ ሰገባዉ ክተት ነዉ ያለዉ። ተወዳጆች ከእኛ ልክ ካልሆነ አሳማኝ ከሚመስል ምክንያት ይልቅ የእግዚአብሔር ቃል መመሪያ ሁሌም ልክ ነዉ።
ክፍል 2 ይቀጥላል ..

#ከፀደቀ #መንፈሰ
እግዚአብሔር እኛን የወደደበትን ፍቅር በፍፁም አብራርተን ልንጨርሰዉ አንችልም። ምክንያቱም በዚህ ፍቅር ማንንም ወደን ስለማናዉቅ። በዚህ ፍቅር ልክ ማንም እርስ በእርስ ሲዋደድ ስላላየን። ከምንረዳዉ በላይ ጥልቅ ነዉ ከምናስበውና ከምንገምተው በላይ ትልቅ ነዉ።

#ከፀደቀ #መንፈሰ
አንድ ሰዉ ስለ እግዚአብሔር ፀጋና፣ፅድቅ ተምሮ ታዲያ ሀጢአትን ብሰራ ምን ችግር አለዉ? ብሎ ካሰበ ትምህርቱ በፍፁም አልገባዉም። በክርስቶስ መፅደቃችን በገባን ልክ ራሳችንን ለፅድቅ ተገዢዎች አድርገን ለማቅረብ እንተጋለን።

#ከፀደቀ #መንፈሰ
#ጴጥሮስ #ሲያምን #ተራመደ #ሲፈራ #ደግሞ #መስጠም #ጀመረ
ማመንም አለማመንም በህይወት ላይ የሚታይ ለዉጥን ያመጣል።

#ከፀደቀ #መንፈሰ
#እንደ #ፀና #ቀረ በመጋቢና ዘማሪ #ተከስተ #ጌትነት ግለ ታሪክ የተፃፈ መፅሐፍ። በጣም የወደድኩት መፅሐፍ ነዉ። ዛሬ ልጀምረዉና ቀስ ብዬ እጨርሰዋለሁ ብዬ ማንበብ ጀምሬ ራሴን የመጨረሻዉ ገፅ ላይ አገኘሁት።
ተኬ በዚህ መፅሐፉ ከድካሙም ከብርታቱም እንድንማር በታማኝነት ዘግቦልናል። እንዲህ አይነት ግለ ታሪክ የያዘ መፅሐፍ በሀገራችን ብዙም አልተለመደም። በተለይም በእኛ በወንጌላውያን አማኞች ዘንድ። ለብዙዎች ዓርአያ የሚሆን መፅሐፍ ነዉ ብዬ አስባለሁ።ተኬ ይህንን መፅሐፍ እንዲፅፍ መኖሪያዉን አሜሪካ ማድረጉ የጠቀመዉ ይመስለኛል። በዚህ መፅሐፍ የተኬን ቅንነት፥ታማኝነት፥ ትህትና፥የእግዚአብሔርን ዉለታ የማይረሳ አመስጋኝ እንደሆነ አስተዉያለሁ።#ተኬ የእግዚአብሔር ሞገስና እረዳትነት እንደ አርሞንዔም ጠል የረሰረሰ ሰዉ እንደሆነ ያሳብቅበታል።  እግዚአብሔርን ስለ አንተ እናመሰግነዋለን።
#እንደ #ፀና #ቀረን እንድታነቡት ግብዣዬ ነዉ።

#ከፀደቀ #መንፈሰ
፦ሳምራዊቷን ሴት ስለ ዉሃ አዉርቷት እኔ የሕይወት ዉሃ ነኝ አላት።
፦ከ5ሺ የሚልቁትን ህዝብ በ2 አሳና በ5 እንጀራ በተአምራቱ ከመገባቸዉ በኃላ የህይወት እንጀራ እኔ ነኝ አላቸዉ
፦የማርታና የማርያም ወንድም የሆነዉን አልአዛርን ከሞት ከማስነሳቱ በፊት ትንሣኤና ሕይወት እኔ ነኝ አለ።

፦ፈፅሞ ሊገባን የማይችለዉን ታላቁን የመለኮትን ጥበብ በሚገባን ቋንቋ የተናገረን እስኪገባን ድረስ ያስረዳን ኢየሱስ ይባረክ።


#ከፀደቀ #መንፈሰ
#ከሰለሞን #የሚበልጥ
ሁለት ሴቶች በንጉስ ሰለሞን ፊት ቀርበዉ መከራከር ይጀምራሉ ሁለቱም በአንድ ቤት ዉስጥ ነዉ የሚኖሩት። ሁለቱም በቅርቡ ነዉ የወለዱት። አንደኛዋ እናት ግን በልጇ ላይ ተኝታበት ገድላዉ ነበር። ደኅነኛውም ወስዳ ለራሷ አደረገችዉ የሞተዉን ደግሞ ከወሰደችበት የእናት እቅፍ ዉስጥ አኖረችዉ።እናትየዉም ስትነቃ የእርሷን አይደለም ያቀፈችዉ የኔ በህይወት ያለዉ እንጂ የሞተዉ አይደለም ይሄንንማ አልቀበልም ብላ ለመከራከር በንጉስ ሰለሞን ፊት ይዛት ቀረበች። ንጉስ ሰለሞንም ይህንን ታሪክ እንደሰማ ደኅነኛውን ሕፃን ለሁለት ከፍላችሁ ለአንዲቱ አንዱን ክፍል፥ ለሁለተኛይቱም ሁለተኛውን ክፍል ስጡ አለ።" በዚህም ጥበቡ በህይወት ያለዉ ህፃን የማን እንደሆነ አወቀ ለእናቱም ልጇን ሰጣት።
#ተወዳጆች #ኢየሱስ ከሰለሞን #ይበልጣል እርሱ ቢሆን የሞተዉ ህፃን የት አለ? ነበር የሚለዉ ምክንያቱም ህይወት መስጠት የሚችል ስለሆነ
#ኢየሱስ #ከሰለሞን #ይበልጣል

#ከፀደቀ #መንፈሰ
ዛሬ በእድሜዉ ትንሽ ገፍ ያሉ ምናልባት ከ60ዎቹ ያለፉ አንድ አባት በአጋጣሚ አጊንቻቸዉ በጌታ እንደሆንኩኝ እንኳን ሳይጠይቁኝ፣ ስለ ጌታ ኢየሱስ መናገር ጀመሩ እኔም፣ የመስማት ፍላጎት እንዳለኝ፣ ገለፅኩላቸዉ ትኩረቴንና ጆሮዬን ሰጠዋቸዉ።በጌታ እንደሆንኩኝና እንደማገለግልም ነገርኳቸዉ። እሳቸዉም ስላገልግሎቴ ትንሽ ላጫዉት ምናልባት ለአንተ ሊጠቅምህ ይችላል አሉኝ። ለ40 አመታት ያህል የእግዚአብሔርን መንግስት በድካሜም በብትርታቴም አገልግያለሁ፣ነገር ግን እንዳገለገልኩት ዓመታትና፣ በዉስጤ እንዳለው አቅም ልክ ፍሬያማ ልሆን አልቻልኩኝም አሉኝ። ምክንያቱ ምን መሰለህ አሉኝ የአገልግሎት አብዛኛዉን እድሜዬን መለወጥ ከማልችለዉ ነገር ጋር ስታገል ነዉ ያሳለፍኩት ፣ያንን ነገር አሁን ላይ ሳስበዉ ይቆጨኛል፣መለወጥ የማልችለዉን ነገር ትቼ መስራት ወደምችላቸዉ ባተኩር በብዙ ፍሬያማ እሆን ነበር አሉኝ፣አሁን ላይ በህይወት ያሉትን ደግሞም ያለፉትን በምድሪቱ ላይ ታላላቅ በጎ ተፅዕኖ የፈጠሩትን የእግዚአብሔር ሰዎች ጠቀሱልኝና ፣ከእዚህ ከአብዛኛዎቹ ጋር አገልግሎት፣ በተመሳሳይ ጊዜ ነዉ የጀመርነዉ አሁን እነርሱ በአብዛኛው አማኝ ልብ ዉስጥ አሉ ምክንያቱም ለብዙዎች የመባረክና፥ የመታነፅ፥ ብሎም ለብዙ አገልጋዮች የመነሳት ምክንያት ስለሆኑ፣ ከኢትዮጵያ አልፈዉ በአለም ዙሪያ ዛሬም ቢሆን የእግዚአብሔርን ሀሳብ ያገለግላሉ እኔ ግን በዚያን ጊዜ ልለዉጠዉ ከማልችለዉ ነገር ጋር እታገል ነበር፣ በዙሪያዬ የነበሩ ሰዎች በአገልግሎቴ ብዙም ደስተኛ አልነበሩም፣ እነርሱን ለማስረዳት በአንድ ቤተክርስቲያን ቁጭ ብዬ 27 አመት ፈጀብኝ ከ27 በኃላ ነዉ ነገሩ እንደማይለወጥ የገባኝ፣ አስበከዋል የኔ ልጅ ከ27 አመት በኃላ ልክ እንዳልነበርክ ሲገባህ፣ ለካ ብዙ ስራ መስራት እችል ነበር አሉኝ። የጠቀስኩልህ በህይወት ያሉም የሌሉም አብረዉኝ አገልግሎት የጀመሩ አገልጋዮች በምድሪቱ ላይ ታላላቅ የሆነን ተፅዕኖን የፈጠሩት ሁሉም ሰዉ ስለተቀበላቸዉ አልነበረም ወደሚቀበሏቸዉ እየሄዱ እንጂ፣ በፅድቅና በእዉነት እያገለገሉ ብዙ ትችትና፥ ነቀፌታ፣ስድብ፣ድብደባም ጭምር ይደርስባቸዉ ነበር፣ እነርሱ ግን ጥሪያቸዉ ላይ ብቻ ነበር ትኩረት ያደርጉ የነበረዉ። ለዛ ነዉ ተፅእኖን መፍጠር የቻሉት። እኔ ግን ያልተቀበሉኝ እንዲቀበሉኝ ስታገልና፣ ሳስረዳ እድሜዬን አባከንኩ ወደሚሰሙኝ ብሄድ ብዙ እንደማተርፍ አሁን ገና ነዉ የገባኝ አሉኝ።የሳቸዉን ታሪክ በሀዘን ስሜት ሆኜ ብሰማዉም ደግሞ ካሳለፉት ህይወት ብዙ ነገር ተምሪያለሁ። ምናልባት ይሄ መልእክት አንድ ሰዉ ሊጠቅም ይችላል ብዬ ስላሰቡኩኝ ነዉ የፃፉኩት።
የእግዚአብሔር አገልጋይ ብትሆንም በፅድቅና በታማኝነት ብታገለግልም ሁሉ ይቀበሉኛል ብለህ አታስብ። ሁሉ ይቀበለኝ ካልክ የማይቀበሉህ ሰዉ ሲገጥሙህ ልብህ ይጎዳል እነርሱ ደግሞ እንዲቀበሉህ ስታስረዳህ ለሚሰሙህ መልእክትህን ሳታሰማ ከጊዜህ ጋር ትተላለፍለህ። የምናመልከዉና የምንከተለዉስ ጌታ ሲያገለግል መቼ የሰሙት ሁሉ ተቀበሉት?

መለወጥ በማትችለዉ ጉዳይ ላይ እድሜህን እትጨርስ መስራት በምትችለዉ ጉዳይ ላይ አተኩር።አንተን የሚጠብቁ ብዙ ስራዎች ስላሉ።

በእየሱስ ስም ዘመናችሁ አይበላ አሜን።
#ከፀደቀ #መንፈሰ
ሰይጣን እዉነተኛ የሆነዉን ነገር በተሳሳተ መንገድ መጠቀም ብቻ አይደለም አላማዉ እዉነተኛ የሆነዉን ነገር ሀሰተኛ ነዉ እስክልን ድረስ በብርቱ ይሰራል። ሀሰተኛ አገልጋዮችን የሚያበዛዉ እነርሱ ሀሰተኛ ናቸዉ እስክንል ብቻ አይደለም እዉነተኛ የእግዚአብሔር አገልጋዮችን እንደ ሀሰተኛ አገልጋዮች እስክንቆጥራቸዉ ድረስ ነዉ ሰይጣን በረቀቀ መንገድ የሚሰራው። ማለትም እዉነተኞችን እንዳንሰማቸዉ፥ እንዳናከብራቸዉ፥ በአጠቃላይ ሁሉንም የእግዚአብሔር አገልጋዮቹን በሀሰተኛ መነፅር እንድናያቸዉ የሰይጣን ትልቁ የቤት ስራዉ ነዉ። ደግሜ እላለሁ እንዳለው ሐዋርያው ጳዉሎስ እኔም ደግሜ እላለሁ ሰይጣን እዉነተኛዉን ነገር በተሳሳተ መንገድ ተጠቅሞ እዉነተኛዉ ከሆነዉ ነገር ጋር ሊያለያየን ነዉ የሚፈልገዉ። እጣቢዉን ከነ ልጁ እንዳትደፍዉ ተጠንቀቅ። አንዳንድ የአፍሪካ ሀገራት ያሉ አገልጋዮች እስኪመለኩ ድረስ የሚፈሩ አሉ። እነርሱ ሲመጡ ምዕመኑ ይንበረከካሉ አምልኮም ሲደረግለትም ያየሁት አለ ይህ ፈፅሞ ስህተት ነዉ። የዚህ ልኩ ግን እዉነተኛ የእግዚአብሔር አገልጋዮችን መናቅና አለማክበር አይደለም። መፅሐፍ ቅዱስ እዉነተኛ የእግዚአብሔር አገልጋዮችን ልክ በሆነ መንገድ እንድናከብርራቸዉ ያዘናል " እንግዲህ በሙሉ ደስታ በጌታ ተቀበሉት፥ እርሱን የሚመስሉትንም አክብሩአቸው፤"
( ፊል2:29)" በመልካም የሚያስተዳድሩ ሽማግሌዎች፥ ይልቁንም በመስበክና በማስተማር የሚደክሙት፥ እጥፍ ክብር ይገባቸዋል።"(1ኛ ጢሞ 5:17) ሀሰተኛ ነብያት አሉ የሚለዉ ድምዳሜህ እዉነተኞችን ባለመቀመል እንዳይንፀባረቅ። ምክንያቱም አንዳንድ ሰዉ ሀሰተኞችን ከመቃወም ብዛት ፈፅሞ እዉነተኞችን እስካለመቀበል የደረሱ ስላሉ።
የሰይጣንን ሀሳብ እንዳንስተዉ እግዚአብሔር በጥበብ መንፈስ ይሙላን አሜን።

#ከፀደቀ #መንፈሰ
በአንዳንድ ቤተክርስቲያን በአገልግሎትም ሆነ በሌላ አጋጣሚ ከተገኘዉ የዛን ቤተክርቲያን አገልጋዮችን በፍፁም ሳልጠይቅ የማላልፈዉ ጥያቄ አለ እርሱም የወንጌል ስርጭት ህብረትና Bible study team እዚ church ምን ይመስላል የሚል የተለመደ ጥያቄ አለኝ፣ከጠየኳቸዉም በኃላ በምላሻቸዉም ተመርኩዤ ሀሳቤን አንፀባርቃለሁ። ህብረቱ  ከሌለ ለመጀመር እንቅስቃሴዉን እንዲያደርጉ፣ ካለ ደግሞ ያላቸዉን experience እንዲያካፍሉኝ እጠይቃቸዋለሁ። እኔ በ bible study እና በወንጌል ስርጭት ህብረት በብዙ ስለተጠቀምኩ ፥ስለታነፅኩ፥ስለተሰራዉበት ማዉራት አይሰለቸኝም።
ምግብ ቤት ገብተን ጥሩ ምግብ ካገኘን ለጠየቁንም ላልጠየቁንም ስለዛ ምግብ ቤት ማዉራታችን አይቀርም። ጥሩ ነገር ለተጠቀምንበት ምላሽ እኛ ለጓደኞቻችን ወደ እዛ ቤት እንዲሄዱ የምንሰጠዉ ምስክርነት ነዉ። በእነዚህ ሁለቱ ህብረት በብዙ ተጠቅሜያለሁና እናንተም  ተጠቀሙ የሚለዉ ለተጠቀምኩበት የምሰጠዉ የዘወትር ምስክርነት ነዉ። በቤተክርስቲያናችሁ ካሉ የወንጌል ስርጭትና Bible study team join አድርጉ። እናንተም ነገ በብዙ ተጠቅማችሁ ምስክር እንደምትሆኑ አልጠራጠርም።
ብዙ ወዳጆቼን በወንጌል ስርጭት ህብረት ምክንያት አግንቻለሁ፣ ተግባብቺያለሁ፣ስለዚህም እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ።
#ከፀደቀ #መንፈሰ
ጥያቄ አለኝ🙋‍♂
በማቴ 25 :32_46 ባለዉ ክፍል ዉስጥ #ፍየሎችና #በጎቹ የተባሉት እነማን ናቸዉ #አማኞች ወይስ ያላመኑ? አማኞች ከሆኑ ከእምነት ይልቅ ስራ ነዉ ዋጋ ያለዉ ማለት ነዉ? ምክንያቱም #በበጎቹ የተመሰሉት ወደ መንግስቱ የመግባታቸዉ ምክንያት ለሰዎች የሰሩት በጎነት ተቆጥሮ ስለሆነ። #የማያምኑ ከሆኑ ደግሞ በስራ ብቻ መዳን ይቻላል ማለት ነዉ? ያለ እምነት 🤔
#ይህ ጥያቄ የበርካታ ሰዉ ነዉ የጥያቄዉን መልስ በእርጋታ ሆናችሁ አድምጡት

#ከፀደቀ #መንፈሰ