ስንክሳር ወግጻዌ ዘተዋሕዶ
853 subscribers
3.46K photos
103 videos
194 files
1.2K links
የየዕለቱ ስንክሳር እና ግጻዌ የሚቀርብበት ቻናል ነው፡፡

ለማንኛውም አስተያየት እና እርማት
@zetaodokos ላይ ይላኩልን።

👇👇የYoutube Channel ይቀላቀሉ👇👇
https://youtube.com/channel/UCupqpIYe_mMpSM7jMT3Njhw
Download Telegram
#ኦርቶዶክሳዊ_የጾታ_ትምህርት
#ክፍል_1
#ፍቅር_ምንድነው_?
ፍቅር እውር ነው ?
አንድ ፈላስፋ ሲናገር ምን አለ በመጀመሪያ ፈጣሪ ሰውን ከመፍጠሩ በፊት ስሜቶችን ፈጠረ ፍቅር ፣ እብደት ፣ ቅናትና ውሸትን ከዛ ከፈጠራቸው ቡሃላ ተሰወረባቸው ። ስሜቶችም ኩኩሉ መጫወት ጀመሩ ። እብደት ቆጣሪ ነበር ። መጀመሪያ ውሸት ከዛ ቅናት ተያዘ ፍቅር ግን ከፅጌሬዳ አበባ ጀርባ ነበርና የተደበቀው ቢፈልገው ቢፈልገው አጣው ። ከዛ ቅናት ተናደደና ከአበባው ጀርባ እንደተደበቀ ነገረው ። እብደትም ቀስ ብሎ ሊያይ ፅጌሬዳውን ሳብ አርጎ ቢለቀው እሾሁ ሄዶ የፍቅርን አይን ወጋው ።ፍቅርም በከፍተኛ ድምፅ ጮኸ ፈጣሪም ተገለጠ በተፈጠረው ነገርም አዘነ ። የፍቅር ሁለቱም አይኖቹም እንደ ጠፉ አየ ። ፈጣሪም እብደትን አይኑን አጥፍተኸዋልና ከአሁን ቡሃላ ፍቅርን እጁን ይዘህ ወደ ሚሄድበት ቦታ ትመራዋለህ ብሎ አዘዘው። ከዛን ጊዜ ጀምሮ ፍቅርን ወደ ሚሄድበት ቦታ እጁን ይዞት የሚመራው እብደት ሆነ። እናማ ይሄ ታውሯል እንዴ ከዚች ጋር ፡ ይቺ አብዳለች እንዴ ከሱ ጋ አትበሉ ። ፍቅር ታውሯል የሚመራውም በእብደት ነውና ይላል ። እኔ ግን ፍቅር እውር ሳይሆን እንደውም ማየት ያለብንን ነገር የሚያሳየን አይናማ ነው እላለው። የፍቅር መገኛውና ምንጩ እግዚአብሔር ሲሆን የህግ ሁሉ ፍፃሜም ነው ።ለዚህ ነው ጳውሎስ የትእዛዝ ፍፃሜ ግን "በንፁህ ልብ ፣ በመልካም ጠባይ ፣ ጥርጥር በሌለበት ሃይማኖት መዋደድ ነው " ። ባለሙያዎች ፍቅር 3 ደረጃዎች አሉት ይላሉ #1ኛ.Relationship ይባላል። relat ማለት መገናኘት ሲሆን ship ደሞ ካርጎ በሚለው እንተርጉመው ። ማንኛውም ሰው የራሱ የሆነ አስተሳሰብ ፀባይና ባህሪ አለው ።ይሄንን ጭነቱን ይዞ ከአንድ ሰው ጋር ሲገናኝ ሲተዋወቅ ሪሌት አደረገ ወይም relationship ጀመረ ይባላል ። #2ኛ.ደረጃው ደሞ Friendship ይባላል። ይሄን ደሞ flow በሚለው እንተርጉመው ። የአንዱ አስተሳሰብ ወደ አንዷ የአንዷ ፀባይ ወደ አንዱ ሲፈስ freindship ይመሰረታል ። #3ኛ.ደረጃው ደሞ Intermacy ይባላል ። ይህም in to see me በሚለው ይተረጎማል ። ሪሌት አርገን ሀሳብ ፍሎው ካደረግን ቡሃላ ወደ ኢንቱ ሲ ሚ ወይም ውስጥን ወደ ማሳየት ያድጋል። አላማችንን ግባችንን የልባችንን ነገር ምናሳየው እዚህ ደረጃ ላይ ስንደርስ ነው ።በዚህ ውስጥ ያለፈ ፍቅር ጠንካራ ይሆናል ግቡም ልብ እንጂ የወሲብ ስሜት አይደለም። ፍፃሜውም በቃልኪዳን የታሰረ ጋብቻ ይሆናል ይላሉ ። #ሊቃውንቶች ደሞ በትዳር ጓደኞች መካከል ሊኖር የሚገባ ፍቅርን በደረጃ መለየት ይከብዳል ። ባልና ሚስት በ1 አካል ላይ ያሉ 2 አይኖች ናቸውና ይላሉ ። ሰው ለ2ቱ አይኖቹ የተለያየ ግምትና የፍቅር ሚዛን እንደማይኖረው ሁሉ በትዳር ጓደኞችም መካከል የሚኖር ፍቅርም ገደብና መጠን የሌለው ፍጹም #ፍቅር ነው ። የክርስቲያናዊ ጋብቻ ፍቅር መሰረቱ #ፍትወት አይደለም ። #ትዳር መሰረቱን ፍቅር ሲያደርግ ትዕግስት ይኖረዋል ፣ አንዱ ለአንዱ እንዲያዝን ያደርጋል ፣ አያቀናናም ፣ አያበሳጭም ፣ መተማመንን ያሰፍናል ፣ ይጸናል። በ1ኛ ቆሮ 13 ላይ ጳውሎስ የፍቅርን ባህርያት ነግሮናል ። "ፍቅር ይታገሳል ቸርነትንም ያደርጋል ፡ ፍቅር አይቀናም ፍቅር አይመካም አይታበይም ፡ የማይገባውን አያደርግም ፡ የራሱንም አይፈልግም ፡አይበሳጭም በደልንም አይቆጥርም ፡ ከእውነት ጋር ደስ ይለዋል እንጂ ስለ አመፃ ደስ አይለውም ፡ ሁሉን ያምናል ፡ ሁሉን ተስፋ ያደርጋል ፡ በሁሉ ይፀናል ፡ ፍቅር ለዘወትር አይወድቅም ፡ ትንቢት ቢሆን ይሻራል ፡ ልሳንም ቢሆን ይቀራል ፡ እምነት ተስፋ ፍቅር እነዚህ ሶስቱ ፀንተው ይኖራሉ ከነዚህም የሚበልጠው #ፍቅር ነው " ይላል። ም/ቱም ብናምን እግዚአብሔርን ነው ተስፋም ብናደርግ በእግዚአብሔር ነው #ፍቅር ግን እራሱ እግዚአብሔር ነውና ።

ፍኖተ መንግስተ ሰማያት
ይህ ቻናል ብሂለ አበው፣እራሳችንን እንድንፈትሽ የሚያደርጉ ጽሑፎች እንዲሁም ልዩ ልዩ ሐይማኖታዊ ትምህርቶችና መልዕክቶች የሚተላለፉበት መንፈሳዊ ቻናል ነው፡፡
ለሚኖራችሁ ማንኛውም ሀሳብ ጥያቄና አስተያየት

👉 ኢዮአታም

ላይ ልታደርሱን ትችላላችሁ፡፡
https://t.me/zekidanemeheret
#ኦርቶዶክሳዊ_የጾታ_ትምህርት
#ክፍል_2
#እውነተኛ_ፍቅር
"ወደ እውነተኛ ፍቅር ስንደርስ ወደ እግዚአብሔር መድረሳችንና የጉዞአችንም መጨረሻ ነው ። በእውነተኛ ፍቅር ተንሳፈን ከዓለም ባሻገር አብ ወልድና መንፈስቅዱስ ወዳሉበት ደሴት እንደርሳለን " (ቅዱስ ይስሐቅ/ሶርያዊ/ የእውነተኛ ፍቅር ምንጭ #እግዚአብሔር ነው ። እግዚአብሔር ደግሞ ለሁለት የፍቅር ተጓዳኞች ቃላት ሊገልፀው የማይችለው የመዋደድን ጸጋ ይሰጣቸዋል ። #ከልብ የሆነ ፍቅር በወርቅ ፣ በብር ፣ በዕንቁ ፣ በአልማዝና በፔትሮሊየም የማይለውጡት ፣ዝገት የማይበላው ፣ ቀናትና ዘመናት ሊሽሩት አቅም የማያገኙለት የእውነተኛ ስሜት ነጸብራቅ ነው ። #ፍቅር ጥልቅ ነገር ነው ። ለባልና ለሚስትም ትልቁ ሐብት ውበትና እርካታቸው #ፍቅራቸው ነው ።ባል ለሚስቱ ሚስትም ለባሏ የምትመግበው ፍቅር ትዳሩን በመልካም ውበት እንዲያሸበርቅ የሚያደርገው የሕይወት ፈርጥ ነው ።ራሳቸውን ለይተው /በገዳም ህይወት/ ለመኖር ከተሰጣቸው በስተቀር ሰው ያለ ፍቅር ብቻውን መኖር አይችልም። ለዚህ ነው እግዚአብሔርም አለ "ረዳት እንፍጠርለት"ያለው ። #ፍቅር በሀገር ርቀት ተገድቦ የሚወሰን አይደለም ። ፍቅርን ሀገር አይወስነውም ። ድንበርም አይከለክለውም ። ክልል ጥሶ የመጓዝ አቅሙም አስተማማኝ ነው ። ፍቅርን ሐብትና ድህነት ፣ በዜግነት መለያየትም አያግደውም ። ቅዱስ ጳውሎስ "አይሁዳዊ ወይም የግሪክ ሰው የለም ባሪያ ወይም ጨዋ የለም " እንዳለው ሁሉም ሰው ለፍቅር እኩል ነው ። /ገላ 3÷28/ ። #ፍቅር ከባድ ኃይል ያለው ሕይወት ነው ። "ሰው እናትና አባቱን ይተዋል " እንደተባለው እናትና አባት ያህል ነገር እስከማስተው ድረስ ብርቱ አቅም አለው ። #ፍቅር ለማንም አይሸነፍም ። በማንም ልብ ውስጥ ገብቶ የሰውን ማንነት የሚያንበረክክ ጀግና ነው ። #እውነተኛ ፍቅር ማስመሰልን አያውቅም ። ከሽንገላም የጸዳ ነው ። ፍቅር በአንደበት ብቻ የሚገለፅ ሳይሆን በሥራና በእውነት የተደገፈም ነው ።"በሥራና በእውነት እንጂ በቃልና በአንደበት ብቻ አንዋደድ /1ኛ ዮሐ3÷18/ ። #እውነተኛ_ፍቅር በጥቅም የማይለካ ፣ በመከራ ቀን የማይበገር ፣ የማይሞት ፣ ሁሌም የሚያብብና የማይደርቅ ፣ ጎርፍ የማይንደው ጠንካራና ጽኑ ነው ። "ፍቅር እንደ ሞት የበረታች ናትና... ብዙ ውሃ ፍቅርን ያጠፋት ዘንድ አይችልም ፡ ፈሳሾችም አያሰጥሟትም "ተብሎ /መኃ 8÷6/ የተመዘገበው ለዚህ ነው ። በአጠቃላይ ከእውነተኛ ፍቅር የሚታጨደው #ደስታ ነው ። ለዚህም ይመስላል ምሁራን "ሕይወት አበባ ሲሆን ፍቅር ደግሞ ከዚህ የሚቀሰም ማር ነው " ያሉት ። ፍቅር የሚጓጓለት ድንቅ የሕይወት አንዱ ክፍል ነው ። እውነተኛ ፍቅር የሕይወት ግሩም ቅመም ናትና ።በቀጣይ ክፍላችን ደሞ #12ቱን የፍቅር አይነቶች እናያለን ። ይቆየን

ፍኖተ መንግስተ ሰማያት
ይህ ቻናል ብሂለ አበው፣እራሳችንን እንድንፈትሽ የሚያደርጉ ጽሑፎች እንዲሁም ልዩ ልዩ ሐይማኖታዊ ትምህርቶችና መልዕክቶች የሚተላለፉበት መንፈሳዊ ቻናል ነው፡፡
ለሚኖራችሁ ማንኛውም ሀሳብ ጥያቄና አስተያየት

👉 ኢዮአታም

ላይ ልታደርሱን ትችላላችሁ፡፡
https://t.me/zekidanemeheret
#ክርስቲያናዊ_ሥነ_ምግባር
ተከታታይ ትምህርት
#ክፍል_2
@zekidanemeheret
#10ቱ_ትዕዛዛት (ኦሪ ዘፀ 20)
#1.እኔ እግዚአብሔር አምላክህ ነኝ ከግብፅ ምድር ያወጣሁህ ነኝ ከኔ በቀር ሌሎቹ አማልክት አይሁኑልህ ።
#2.የእግዚአብሔር የአምላክህን ስም በከንቱ አታንሳ ። #3.የሰንበትን ቀን ትቀድሰው ዘንድ አስብ ።
#4.እናትና አባትህን አክብር ። #5.አትግደል
#6.አታመንዝር
#7.አትስረቅ
#8.በባልንጀራህ ላይ በሐሰት አትመስክር
#9.የባልንጀራህን ቤት አትመኝ #10.ባልንጀራህን እንደራስህ ውደድ።
🖊የክርስትና ህግ የፍቅር ህግ ነው ። ቅዱስ ጳውሎስ ሌላውን የሚወድ ሕግን ፈፅሞታል ካለ ቡሃላ ከ10ቱ ትዕዛዛት የተወሰኑትን በመጥቀስ #ፍቅር የሕግ ሁሉ ፍፃሜ መሆኑን በግልፅ ይናገራል። /ሮሜ 13÷8/ 🖊ጌታችን እንዳስተማረን ፍቅር በሁለት ይከፈላል ። #1ኛ_ፍቅረ_እግዚአብሔር #2ኛ_ፍቅረ_ቢፅ
🖊በሌላ በኩል ደግሞ ከአዎንታዊና አሉታዊ ከመነገራቸው አንፃር በሁለት ይከፈላሉ ።
#1ኛ_ሕግ_በአሉታ_የተነገሩ /አታድርግ/
#2ኛ_ትዕዛዝ_በአዎንታ_የተነገሩ /አድርግ/ ይባላሉ
🖊ከዚህም ሌላ ከአፈፃፀማቸው አንፃር ሲታዩ በሦስት ይከፈላሉ ። #1ኛ_በሐልዩ /በማሰብ/ የሚፈፀሙ ህግ1,3,4 እና 9 #2ኛ_በነቢብ /በመናገር/ የሚፈፀሙ ህግ 2,8
#3ኛ_በገቢር /በማድረግ/ ህግ 5,6,7,10 ናቸው ።
🖊#10ቱ ትዕዛዛት ለሙሴ በተሰጡ ጊዜ በሁለት የድንጋይ ፅላቶች ላይ ተፅፈው ነበር ። እንዲሁም ሁሉ በተለይም እስራኤል ዘነፍስ የምንባለው ለእኛ ለክርስቲያኖች ከልባችን ፅላት ላይ በመንፈስ ልንፅፈው ይገባል። በቤተክርስቲያናችን በፅላቶቻችን ላይ የጌታችን የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ስም ይገኛል ። ጌታችን ደግሞ ማንኛውንም ነገር በስሜ ብትለምኑ እኔ አደርገዋለው ካለ ቡሃላ ብትወዱኝስ ትዕዛዜን ጠብቁ ብሎ አስተምሯል ። እንዲህ ከሆነ የሚያስፈልገንን ነገር ለመለመን የጌታችን ስሙ ስለተፃፈበት በዙሪያው ተሰብስበን መለመን ያስፈልጋል ። ህጉ ከልባችን ስለማይጠፋ ሕጉን መጠበቅና መፈፀም ይገባናል ።
🖊ለዚህም በቀጣይ እያንዳንዳቸውን በዝርዝር እንማማራለን ።

ይቀጥላል....

@zekidanemeheret
ለሌሎችም ማጋራትን አይርሱ
👉ለመቀላቀል 👇👇👇👇
@zekidanemeheret @zekidanemeheret @zekidanemeheret
#ክርስቲያናዊ_ሥነምግባር
#ክፍል-11
#9 የባልንጀራህን _ሚስት{ቤት} _ንብረት_አትመኝ አትግደል ፣ አታመንዝር፣ አትስረቅ ፣በሐሰት አትመስክር በማለት
ክፉ አድራጎትን ወይም የጥፋት ሥራዎችን የሐሰት ንግግሮችን ይከለክላል።
🖊 #አትመኝ በማለቱ ደግሞ ክፉ ምኞትንና መጥፎ ሐሳብን ይከለክላል። በውጭ በተግባር የሚደረጉት ከውስጥ በልቡናችን ከሚፈፀሙት ጋር ማለት ከምኞትና ከሐሳብ ጋር እንደሚታየው እንደ ግንዱ የተያያዙ ናቸው ። ሥሩ ደኀና ከሆነ ግንዱም ደኀና ይሆናል ። አንድ ነገር በድርጊት ከመፈፀሙ በፊት ነገሩ የሚጠነሰሰውና የሚጀመረው በምኞትና በሐሳብ ውስጥ ውስጡን ነው ። ክፉ ሰው ከልቡ ክፉ ነገርን ያወጣል ፤ ደግ ሰው ግን ከልቡ ደጋግ ነገሮችን ያወጣል።
🖊 #መመኘት ማለት የሌላውን ሰው ሚስት / ባልና ሀብት ለራስ እንዲሆን መፈለግና ማሰብ ስለሆነ አንድ ነገርን የተመኘ ሰው ጊዜና ቦታ ባይገድበውና ሁኔታዎች ቢመቻቹለት በልቡ የፈለገውን በሐሳብ ያቀደውን ፣ በስሜቱ የፈቀደውን ከማድረግ አይመለስም።
🖊 ስለዚህ የኀጢአት ምንጩ የወንጀል አባቱ በልቡና የሚገኘው ክፉ #ምኞት ነው ። ስለዚህ የሰውን ንብረት ከመመኘት መታቀብ አለብን ።
🖊ይህንንም ለማጥፋት እና ኀሊናን ለማፅዳት መትጋት አለብን ። የሕግ ሁሉ ፍፃሜና ማጠቃለያ #ፍቅር ነው ። ሁሉም ትዕዛዞች በፍቅር ይጠቃለላሉ። 🖊ባልንጀራውንም አምላኩንም የሚወድ ህግን ይጠብቃል።
ዘፍ፫ ፤ ማር፯÷፳፩-፳፫ ፤ ሮሜ፩÷፳፱ ኢያ፯÷፮-፳፮ ፤ ፪ኛሳሙ፲፩÷፲፬-፲፯/፲፪÷፲፭ ፤ መክ ፪÷፲/፩÷፯-፲ ፤ ዘፍ ፳፭÷፳፱-፴ ፤ ዘኁ ፲፩÷፬-፭ /፲፩÷፬ ፤ መዝ ፵፰/፵፱/፲፪÷፲፯ ፤ ሉቃ ፲፪÷፲፭ ፤ ፩ጢሞ ፮÷፱ ፤ ኤፌ ፭÷፭ ፤ ፩ኛቆሮ፲፪÷፩ /፲፬÷፩ ፤ ገላ፭÷፲፯
@zekidanemeheret

ይቀጥላል....

🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
ተጨማሪ👇👇👇ለማግኘት
@zekidanemeheret @zekidanemeheret @zekidanemeheret
#ፍኖተ_ቅዱሳን
#ክፍል_3
#10ሩ_ማዕረጋተ_ቅድስና
ከባለፈው የቀጠለ ንፅሀ ስጋን ገንዘብ ያደረጉ ሰዎች ቀጥለው የሚሸጋገሩት ወደ ንፅሀ ነፍስ ነው ። ትሩፋተ ስጋን አብዝቶ የሰራ ሰው የሚሸጋገረው ትሩፋተ ነፍስን ወደ መስራት ነውና ። በዚህም መሰረት አንድ ሰው ከንፅሀ ስጋ በሃላ አብዝቶ ትሩፋተ ነፍስ ከሰራ የሚከተሉትን መዓርጋት ገንዘብ ማድረግ ይችላል
#4ኛ #አንብዕ ፦ እንባ ማለት ነው ። የሀዘን እንባ ሰው በደረሰበት ሀዘን ልቡ ተወግቶ ፊቱን አስከፍቶ የሚያለቅሰው ሲሆን የደስታው እንባ ደግሞ ልቡናው በሐሴት ተሞልቶ ሰውነቱ ስሜቱን መቆጣጠር ባቃተው ጊዜ የሚያለቅሰው ነው ። "አንብዕ " ግን ከዚህ ፈፅሞ የተለየ ነው ። ይኸውም ቅዱሳን ሰውነታቸው በሐዘን ሳይከፋ በስጋዊ ሐሴትም ሳይሞላ ሳይሰቀቁ ከዓይናቸው የሚያፈልቁት እንባ ነው ።
#5ኛ #ኩነኔ ፦ ቅዱሳን ከራሳቸው ሰውነት ጋር የሚያደርጉት ( የፈቃደ ስጋና የፈቃደ ነፍስ መጋጨት ) ዋናው ነው ። በዚህ ተጋድሎ ፈቃደ ስጋቸውን ሙሉ ለሙሉ ለፈቃደ ነፍሳቸው ለማስገዛት የበቁ ሰዎች "ለመዓርገ ኩነኔ " በቁ ይባላል ። ኩነኔ ማለት በአጭር ቃል ስጋን ለነፍስ ማስገዛት ማለት ነው ። ስጋ ለነፍስ ተገዛ ማለት ደሞ እንስሳዊ ባህሪያቸው ፍፁም ደክሞ መልአካዊ ባህሪያቸው ሰልጥኖ ይታያሉ ። ለስጋዊ ደማዊ ሰው የሚከብደውን ሁሉ መስራት ይችላሉ ። ለምሳሌ በቅጠላ ቅጠል ብቻ ለብዙ ጊዜ መኖርን ፣ ከእንቅልፍ መጥፋት የተነሳ በትጋሃ ሌሊት ማደርን ፣ በየቀኑ እጅግ ብዙ ስግደት መስገድን ፣ ከስግደትና ከፀሎት ውጪ በሚሆኑበት ሰዓትም ከቅዱሳት መፃህፍት አለመለየት
#6ኛ #ፍቅርፍቅር ታላቅ ፀጋ ነው ። እግዚአብሔር ፍቅር ነው የሚባለው የባህሪ ገንዘቡ ስለሆነ ነው ። ሰዎች በተጋድሎ እየበረቱ እግዚአብሔር የፈጠረውን ፍጥረት ሁሉ ሳይንቁ አስተካክሎ መውደድ ነው ። ለዚህ ደረጃ የበቃ ሰው ሌላውን ሰው ኃጥዕ ጻድቅ ፣ አማኒ ከሃዲ ፣ ነጭ ጥቁር ፣ ደቂቅ ልሂቅ ፣ አዋቂ አላዋቂ ሳይል አስተካክሎ መውደድ ነው ።
#7ኛ #ሑሰት ፦ ይህ ደግሞ ነቢየ እግዚአብሔር ኤልሳዕ በኢየሩሳሌም ሆኖ የሶርያው ንጉስ ወልደ አዴር እልፍኙን ዘግቶ ከባለስልጣናቱ ጋር የመከረውን ማንም ሰው ሳይነግረውና ሳይሰማ በሚያውቅበት ፀጋ ካለበት ቦታ ሆኖ ጠፈር ገፈር ሳይከለክለው እንደ ፀሀይ ብርሃን ካሰቡት ደርሶ የፈለጉትን ነገር ማወቅ ማለት ነው ። ይህም በኢየሩሳሌም ሆኖ በቢታንያ የአልዓዛርን ሞት አይቶ የነገራቸውን ጌታን የሚመስሉበት ፀጋ ነው ።
... ይቀጥላል ...

👉ለመቀላቀል 👇👇👇 @zekidanemeheret @zekidanemeheret @zekidanemeheret
✞✞✞ እንኩዋን #ለቅዱስ_ጐርጐርዮስ_መነኮስ_ለቅድስት_ክርስቶስ_ሠምራ_እና_ለቅዱስ_አድሊጦስ_ሐዋርያ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞✞✞

✞✞✞ #ቅዱስ_ጐርጐርዮስ_መነኮስ ✞✞✞

=>በዚህ ስም ተጠርተው: ለምዕመናን አብርተው ያለፉ አባቶቻችን ብዙ ናቸው:: ለምሳሌም:-
*ጐርጐርዮስ ዘኑሲስ
*ጐርጐርዮስ ነባቤ መለኮት
*ጐርጐርዮስ ዘሮሜ
*ጐርጐርዮስ መንክራዊ
*ጐርጐርዮስ ዘአርማንያ
*ጐርጐርዮስ ረዓዬ ኅቡዓትን መጥቀስ እንችላለን::

+ከእነዚህ ዐበይት ጐርጐርዮሶች አንዱ ገዳማዊው ቅዱስ ዛሬ የሚከበረው ነው:: ቅዱስ ጐርጐርዮስ የተወለደው በ4ኛው መቶ ክ/ዘመን በላይኛው ግብጽ አካባቢ ነው:: ወላጆቹ እጅግ ባለ ጠጐች በመሆናቸው የሚፈልገውን ሁሉ አሟልተው አሳድገውታል::

+በተለይ ደግሞ ሥጋዊ (የዮናናውያንን ጥበብ) እንዲማር አድርገው ወደ #ቤተ_ክርስቲያን ሰደውታል:: በዚያም ትምሕርተ ቤተ ክርስቲያንን ከሥርዓቱ ጋር አጥንቶ እጅግ አንባቢ ስለ ነበረ #አናጉንስጢስ (አንባቢ) ሆኖ ተሾመ::

+አንባቢ በሆነባቸው ዘመናትም ወጣ ገባ ሳይል ያገለግል ነበርና ጣዕመ #መንፈስ_ቅዱስ አደረበት:: ስለዚህም አንደበቱ ጥዑም (ለዛ ያለው) ነበር:: ትንሽ ቆይቶም አበው 'ይገባሃል' ብለው ዲቁናን ሾሙት:: አሁንም ታጥቆ ያለ ዕረፍት ማገልገሉን ቀጠለ::

+ዘመኑ ነጫጭ ርግቦች (የተባረኩ መነኮሳት) የበዙበት ነበርና ቅዱስ ጐርጐርዮስ አዘውትሮ ወደ ገዳም እየሔደ ይጐበኛቸው: በእጆቻቸውም ይባረክ ነበር:: በተለይ #ሊቀ_ምኔት ታላቁ ቅዱስ ዻኩሚስ (#አባ_ባኹም) በቅርቡ ነበርና ሁሌ እየሔደ ይጨዋወተው ነበር::

+ትንሽ ቆይቶ ግን ቅዱሱ የምናኔ ፍላጐቱ እየጨመረ ሔደ:: አንድ ቀን ከገዳም ውሎ ሲመለስ ወላጆቹ ጥያቄ ጠየቁት::
"ልናጋባህ እንፈልጋለንና ምን ትላለህ?" አሉት:: እርሱም ጭራሹኑ እንደማይፈልግ መለሰላቸው:: ሊያሳዝኑት አልፈለጉምና ድጋሚ አልጠየቁትም::

+ትንሽ ቆይተውም ተከታትለው ዐረፉ:: ቅዱስ ጐርጐርዮስ ወላጆቹን ቀብሮ: ሃብት ንብረቱን ሸጦ ጉዞ ጀመረ:: ወደ #አባ_ዻኩሚስ ደርሶም ያን ሁሉ ገንዘብ በታላቁ ቅዱስ ፊት አፈሰሰው:: "ምን ላድርገው ልጄ?" ቢለው "አባቴ! ፈጣሪህ ያዘዘውን" አለው::

+አባ ዻኩሚስም መነኮሳት በመብዛታቸው ቤት አልነበረምና ብዙ ቤቶችን አነጸበት:: የቅዱሱ ገንዘብ ገዳም ከታነጸበት በሁዋላ ምናኔን አንድ ብሎ ጀመረ::

+ቅዱሱ ባጭር ታጥቆ: በጾምና ጸሎት: ውሃ በመቅዳት: በመጥረግ: ምግብ በማዘጋጀት: እግዚአብሔርንም አበውንም አስደሰተ:: ቅዱሱ ምንም ቢናገሩት አይመልስም:: ማንንም ቀና ብሎ አያይም::

+"እሺ" ከማለት በቀር ትርፍ ቃል አልነበረውም:: በጸሎት እንባው: በስግደት ደግሞ ላቡ ይንቆረቆር ነበር:: ፍቅሩ: ትዕግስቱ: ትሕትናውና ታዛዥነቱ እጅግ ብዙ ዓለማውያንን ማረከ:: ስለ እርሱ የሰሙ ኃጥአን ሔደው ምንም ሳይናገራቸው በማየት ብቻ ይማሩ ነበር:: ፊቱ ብሩህ: ደግና ቅን በመሆኑ እርሱን ማየቱ በቂ ነበር::

+ለ13 ዓመታት በገዳመ ዻኩሚስ ከተጋደለ በሁዋላ ወደ ገዳመ #ቅዱስ_መቃርስ ከ2ኛው አባ መቃርስ ጋር ተጉዋዘ:: በዚያም በዓት ወስኖ ከሰው ጋር ሳይገናኝ 7 ዓመታትን አሳለፈ:: በጸጋ ላይ ጸጋ: በበረከት ላይ በረከት ሆኖለት በ22ኛ ዓመቱ አባቶችን ሰበሰባቸው::

+መንገድ ሊሔድ መሆኑን ነግሯቸው "በጸሎት አስቡኝ" አላቸው:: በማግስቱ በዚህ ቀን ሲመጡ ግን በፍቅር ዐርፎ አገኙት:: መነኮሳትም በክብር ገንዘው: ከበረከቱ ተሳትፈው: በታላቅ ዝማሬ ቀብረውታል::

+"+ #ቅድስት_ክርስቶስ_ሠምራ +"+
=>ኢትዮዽያዊቷ #ቅድስት_እናት_ክርስቶስ_ሠምራ ቅንነቷ: ደግነቷና ቅድስናዋ እጅግ የበዛ ነው:: አንድ ቀን ግን ገና በትዳር ውስጥ እያለች: ከአገልጋዮቿ አንዷን ትጠራትና ታዛታለች:: ያቺ አገልጋይ ግን የታዘዘችውን ጀሮ ዳባ ልበስ ብላ ሳትታዘዛት ትቀራለች::

+ደጋግማ ብትነግራትም ልትሰማት አልቻለችም:: ያን ጊዜ ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ልትገስጻት ብላ ጠጠር ብትወረውርባት ያች አገልጋይ ወድቃ ሞተችባት:: ቅድስቲቱ እጅግ ደንግጣ አለቀሰች:: የምታደርገውንም አጣች::

+ወዲያው ግን ፈጠን ብላ: ወገቧን ታጥቃ ትጸልይ ጀመረች:: "ጌታየ ሆይ! ከሞት አስነሳልኝና ዓለምን ትቼ በቀሪ ዘመኔ አንተን አገልለግልሃለሁ" ብላ ፈጣሪን በብዙ እንባ ተማጸነችው:: ያን ጊዜም አገልጋዩዋ ከሞት ተነሳችላት::

+ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ጊዜን አላጠፋችም:: ልጆቿን በቤት ትታ: ሃብትን ብረቷን ንቃ: አንድ ልጇን አዝላ: ቤቷን እንደ ተከፈተ ትታው ወደ ገዳም ወጣች:: በዚህ ዕለትም (መስከረም 24 ቀን) ወደ #ደብረ_ሊባኖስ ገዳም ገባች::

+"+ #ቅዱስ_አድሊጦስ_ሐዋርያ +"+

=>ቅዱሱ ሐዋርያ ተወልዶ ያደገው በግሪክ #አቴና (ATHENS) ውስጥ ሲሆን በነገድ እሥራኤላዊ ነው:: በአደገባት አቴና ከተማ ሥርዓተ ኦሪትን ከወገኖቹ: የግሪክን ፍልስፍና ደግሞ ከአርዮስፋጐስ ተምሯል:: #መድኃኔ_ዓለም ዘመነ ስብከቱ ሲጀምር ግን አድሊጦስ ወደ #ኢየሩሳሌም ሔዶ አደመጠው: ተማረከበትም::

+ወዲያውም "ጌታ ሆይ! ልከተልህ?" ሲል ጠየቀው:: ልብን የሚመረምር ጌታም ፈቅዶለት ከ72ቱ አርድእት ደመረው:: ከዚያም ከጌታችን ዘንድ ተምሮ: መንፈስ ቅዱስንም ተቀብሎ: ለወንጌል አገልግሎት ተሠማርቶ በርካታ አሕዛብን አሳምኗል:: በመጨረሻም ተወልዶ ባደገባት አቴና በዚህች ቀን ገድለውታል::
=>አምላከ ቅዱሳን በትእግስት: በፍቅርና በትሕትና ይሸልመን:: ከበረከታቸውም ያድለን::

=>መስከረም 24 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ ጐርጐርዮስ ገዳማዊ
2.ቅድስ ክርስቶስ ሠምራ (ደብረ ሊባኖስ የገባችበት)
3.ቅዱስ አድሊጦስ ሐዋርያ (ከ72ቱ አርድእት)
4.አቡነ ሰላማ

=>ወርኀዊ በዓላት
1.ቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት (መምሕረ ትሩፋት)
2.ቅዱስ ቶማስ ዘመርዐስ
3.አቡነ ዘዮሐንስ ጻድቅ ዘክብራን
4.ቅዱስ አጋቢጦስ (ጻድቅ ኤዺስቆዾስ)
5.ቅዱስ አብላርዮስ ታላቁ
6."24ቱ" ካኅናተ ሰማይ (ሱራፌል)
7.ቅዱስ አባ ሙሴ ጸሊም (ኢትዮዽያዊ)

=>+"+ #ፍቅር ያስታግሳል:: ፍቅር ያስተዛዝናል:: ፍቅር አያቀናናም::ፍቅር አያስመካም:: ፍቅር አያስታብይም:: ብቻዬን ይድላኝ አያሰኝም:: አያበሳጭም:: ክፉ ነገርን አያሳስብም:: ከእውነት ጋር ደስ ይለዋል እንጂ ስለ ዓመፃ ደስ አይለውም:: ሁሉን ይታገሣል:: ሁሉን ያምናል:: ሁሉን ተስፋ ያደርጋል:: በሁሉ ይጸናል:: +"+ (1ቆሮ. 13:4)

<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>
✞✞✞ እንኩዋን #ለቅዱስ_ጐርጐርዮስ_መነኮስ_ለቅድስት_ክርስቶስ_ሠምራ_እና_ለቅዱስ_አድሊጦስ_ሐዋርያ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞✞✞

✞✞✞ #ቅዱስ_ጐርጐርዮስ_መነኮስ ✞✞✞

=>በዚህ ስም ተጠርተው: ለምዕመናን አብርተው ያለፉ አባቶቻችን ብዙ ናቸው:: ለምሳሌም:-
*ጐርጐርዮስ ዘኑሲስ
*ጐርጐርዮስ ነባቤ መለኮት
*ጐርጐርዮስ ዘሮሜ
*ጐርጐርዮስ መንክራዊ
*ጐርጐርዮስ ዘአርማንያ
*ጐርጐርዮስ ረዓዬ ኅቡዓትን መጥቀስ እንችላለን::

+ከእነዚህ ዐበይት ጐርጐርዮሶች አንዱ ገዳማዊው ቅዱስ ዛሬ የሚከበረው ነው:: ቅዱስ ጐርጐርዮስ የተወለደው በ4ኛው መቶ ክ/ዘመን በላይኛው ግብጽ አካባቢ ነው:: ወላጆቹ እጅግ ባለ ጠጐች በመሆናቸው የሚፈልገውን ሁሉ አሟልተው አሳድገውታል::

+በተለይ ደግሞ ሥጋዊ (የዮናናውያንን ጥበብ) እንዲማር አድርገው ወደ #ቤተ_ክርስቲያን ሰደውታል:: በዚያም ትምሕርተ ቤተ ክርስቲያንን ከሥርዓቱ ጋር አጥንቶ እጅግ አንባቢ ስለ ነበረ #አናጉንስጢስ (አንባቢ) ሆኖ ተሾመ::

+አንባቢ በሆነባቸው ዘመናትም ወጣ ገባ ሳይል ያገለግል ነበርና ጣዕመ #መንፈስ_ቅዱስ አደረበት:: ስለዚህም አንደበቱ ጥዑም (ለዛ ያለው) ነበር:: ትንሽ ቆይቶም አበው 'ይገባሃል' ብለው ዲቁናን ሾሙት:: አሁንም ታጥቆ ያለ ዕረፍት ማገልገሉን ቀጠለ::

+ዘመኑ ነጫጭ ርግቦች (የተባረኩ መነኮሳት) የበዙበት ነበርና ቅዱስ ጐርጐርዮስ አዘውትሮ ወደ ገዳም እየሔደ ይጐበኛቸው: በእጆቻቸውም ይባረክ ነበር:: በተለይ #ሊቀ_ምኔት ታላቁ ቅዱስ ዻኩሚስ (#አባ_ባኹም) በቅርቡ ነበርና ሁሌ እየሔደ ይጨዋወተው ነበር::

+ትንሽ ቆይቶ ግን ቅዱሱ የምናኔ ፍላጐቱ እየጨመረ ሔደ:: አንድ ቀን ከገዳም ውሎ ሲመለስ ወላጆቹ ጥያቄ ጠየቁት::
"ልናጋባህ እንፈልጋለንና ምን ትላለህ?" አሉት:: እርሱም ጭራሹኑ እንደማይፈልግ መለሰላቸው:: ሊያሳዝኑት አልፈለጉምና ድጋሚ አልጠየቁትም::

+ትንሽ ቆይተውም ተከታትለው ዐረፉ:: ቅዱስ ጐርጐርዮስ ወላጆቹን ቀብሮ: ሃብት ንብረቱን ሸጦ ጉዞ ጀመረ:: ወደ #አባ_ዻኩሚስ ደርሶም ያን ሁሉ ገንዘብ በታላቁ ቅዱስ ፊት አፈሰሰው:: "ምን ላድርገው ልጄ?" ቢለው "አባቴ! ፈጣሪህ ያዘዘውን" አለው::

+አባ ዻኩሚስም መነኮሳት በመብዛታቸው ቤት አልነበረምና ብዙ ቤቶችን አነጸበት:: የቅዱሱ ገንዘብ ገዳም ከታነጸበት በሁዋላ ምናኔን አንድ ብሎ ጀመረ::

+ቅዱሱ ባጭር ታጥቆ: በጾምና ጸሎት: ውሃ በመቅዳት: በመጥረግ: ምግብ በማዘጋጀት: እግዚአብሔርንም አበውንም አስደሰተ:: ቅዱሱ ምንም ቢናገሩት አይመልስም:: ማንንም ቀና ብሎ አያይም::

+"እሺ" ከማለት በቀር ትርፍ ቃል አልነበረውም:: በጸሎት እንባው: በስግደት ደግሞ ላቡ ይንቆረቆር ነበር:: ፍቅሩ: ትዕግስቱ: ትሕትናውና ታዛዥነቱ እጅግ ብዙ ዓለማውያንን ማረከ:: ስለ እርሱ የሰሙ ኃጥአን ሔደው ምንም ሳይናገራቸው በማየት ብቻ ይማሩ ነበር:: ፊቱ ብሩህ: ደግና ቅን በመሆኑ እርሱን ማየቱ በቂ ነበር::

+ለ13 ዓመታት በገዳመ ዻኩሚስ ከተጋደለ በሁዋላ ወደ ገዳመ #ቅዱስ_መቃርስ ከ2ኛው አባ መቃርስ ጋር ተጉዋዘ:: በዚያም በዓት ወስኖ ከሰው ጋር ሳይገናኝ 7 ዓመታትን አሳለፈ:: በጸጋ ላይ ጸጋ: በበረከት ላይ በረከት ሆኖለት በ22ኛ ዓመቱ አባቶችን ሰበሰባቸው::

+መንገድ ሊሔድ መሆኑን ነግሯቸው "በጸሎት አስቡኝ" አላቸው:: በማግስቱ በዚህ ቀን ሲመጡ ግን በፍቅር ዐርፎ አገኙት:: መነኮሳትም በክብር ገንዘው: ከበረከቱ ተሳትፈው: በታላቅ ዝማሬ ቀብረውታል::

+"+ #ቅድስት_ክርስቶስ_ሠምራ +"+
=>ኢትዮዽያዊቷ #ቅድስት_እናት_ክርስቶስ_ሠምራ ቅንነቷ: ደግነቷና ቅድስናዋ እጅግ የበዛ ነው:: አንድ ቀን ግን ገና በትዳር ውስጥ እያለች: ከአገልጋዮቿ አንዷን ትጠራትና ታዛታለች:: ያቺ አገልጋይ ግን የታዘዘችውን ጀሮ ዳባ ልበስ ብላ ሳትታዘዛት ትቀራለች::

+ደጋግማ ብትነግራትም ልትሰማት አልቻለችም:: ያን ጊዜ ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ልትገስጻት ብላ ጠጠር ብትወረውርባት ያች አገልጋይ ወድቃ ሞተችባት:: ቅድስቲቱ እጅግ ደንግጣ አለቀሰች:: የምታደርገውንም አጣች::

+ወዲያው ግን ፈጠን ብላ: ወገቧን ታጥቃ ትጸልይ ጀመረች:: "ጌታዬ ሆይ! ከሞት አስነሳልኝና ዓለምን ትቼ በቀሪ ዘመኔ አንተን አገልለግልሃለሁ" ብላ ፈጣሪን በብዙ እንባ ተማጸነችው:: ያን ጊዜም አገልጋዩዋ ከሞት ተነሳችላት::

+ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ጊዜን አላጠፋችም:: ልጆቿን በቤት ትታ: ሃብትን ብረቷን ንቃ: አንድ ልጇን አዝላ: ቤቷን እንደ ተከፈተ ትታው ወደ ገዳም ወጣች:: በዚህ ዕለትም (መስከረም 24 ቀን) ወደ #ደብረ_ሊባኖስ ገዳም ገባች::

+"+ #ቅዱስ_አድሊጦስ_ሐዋርያ +"+

=>ቅዱሱ ሐዋርያ ተወልዶ ያደገው በግሪክ #አቴና (ATHENS) ውስጥ ሲሆን በነገድ እሥራኤላዊ ነው:: በአደገባት አቴና ከተማ ሥርዓተ ኦሪትን ከወገኖቹ: የግሪክን ፍልስፍና ደግሞ ከአርዮስፋጐስ ተምሯል:: #መድኃኔ_ዓለም ዘመነ ስብከቱ ሲጀምር ግን አድሊጦስ ወደ #ኢየሩሳሌም ሔዶ አደመጠው: ተማረከበትም::

+ወዲያውም "ጌታ ሆይ! ልከተልህ?" ሲል ጠየቀው:: ልብን የሚመረምር ጌታም ፈቅዶለት ከ72ቱ አርድእት ደመረው:: ከዚያም ከጌታችን ዘንድ ተምሮ: መንፈስ ቅዱስንም ተቀብሎ: ለወንጌል አገልግሎት ተሠማርቶ በርካታ አሕዛብን አሳምኗል:: በመጨረሻም ተወልዶ ባደገባት አቴና በዚህች ቀን ገድለውታል::
=>አምላከ ቅዱሳን በትእግስት: በፍቅርና በትሕትና ይሸልመን:: ከበረከታቸውም ያድለን::

=>መስከረም 24 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ ጐርጐርዮስ ገዳማዊ
2.ቅድስ ክርስቶስ ሠምራ (ደብረ ሊባኖስ የገባችበት)
3.ቅዱስ አድሊጦስ ሐዋርያ (ከ72ቱ አርድእት)
4.አቡነ ሰላማ

=>ወርኀዊ በዓላት
1.ቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት (መምሕረ ትሩፋት)
2.ቅዱስ ቶማስ ዘመርዐስ
3.አቡነ ዘዮሐንስ ጻድቅ ዘክብራን
4.ቅዱስ አጋቢጦስ (ጻድቅ ኤዺስቆዾስ)
5.ቅዱስ አብላርዮስ ታላቁ
6."24ቱ" ካኅናተ ሰማይ (ሱራፌል)
7.ቅዱስ አባ ሙሴ ጸሊም (ኢትዮዽያዊ)

=>+"+ #ፍቅር ያስታግሳል:: ፍቅር ያስተዛዝናል:: ፍቅር አያቀናናም::ፍቅር አያስመካም:: ፍቅር አያስታብይም:: ብቻዬን ይድላኝ አያሰኝም:: አያበሳጭም:: ክፉ ነገርን አያሳስብም:: ከእውነት ጋር ደስ ይለዋል እንጂ ስለ ዓመፃ ደስ አይለውም:: ሁሉን ይታገሣል:: ሁሉን ያምናል:: ሁሉን ተስፋ ያደርጋል:: በሁሉ ይጸናል:: +"+ (1ቆሮ. 13:4)

<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>

(#ዲያቆን_ዮርዳኖስ_አበበ)
✞✞✞ እንኳን #ለቅዱስ_ጐርጐርዮስ_መነኮስ_ለቅድስት_ክርስቶስ_ሠምራ_እና_ለቅዱስ_አድሊጦስ_ሐዋርያ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞✞✞

†   🕊   ቅዱስ_ጐርጐርዮስ_መነኮስ    🕊   †

=>በዚህ ስም ተጠርተው: ለምዕመናን አብርተው ያለፉ አባቶቻችን ብዙ ናቸው:: ለምሳሌም:-
*ጐርጐርዮስ ዘኑሲስ
*ጐርጐርዮስ ነባቤ መለኮት
*ጐርጐርዮስ ዘሮሜ
*ጐርጐርዮስ መንክራዊ
*ጐርጐርዮስ ዘአርማንያ
*ጐርጐርዮስ ረዓዬ ኅቡዓትን መጥቀስ እንችላለን::

+ከእነዚህ ዐበይት ጐርጐርዮሶች አንዱ ገዳማዊው ቅዱስ ዛሬ የሚከበረው ነው:: ቅዱስ ጐርጐርዮስ የተወለደው በ4ኛው መቶ ክ/ዘመን በላይኛው ግብጽ አካባቢ ነው:: ወላጆቹ እጅግ ባለ ጠጐች በመሆናቸው የሚፈልገውን ሁሉ አሟልተው አሳድገውታል::

+በተለይ ደግሞ ሥጋዊ (የዮናናውያንን ጥበብ) እንዲማር አድርገው ወደ #ቤተ_ክርስቲያን ሰደውታል:: በዚያም ትምህርተ ቤተ ክርስቲያንን ከሥርዓቱ ጋር አጥንቶ እጅግ አንባቢ ስለ ነበረ #አናጉንስጢስ (አንባቢ) ሆኖ ተሾመ::

+አንባቢ በሆነባቸው ዘመናትም ወጣ ገባ ሳይል ያገለግል ነበርና ጣዕመ #መንፈስ_ቅዱስ አደረበት:: ስለዚህም አንደበቱ ጥዑም (ለዛ ያለው) ነበር:: ትንሽ ቆይቶም አበው 'ይገባሃል' ብለው ዲቁናን ሾሙት:: አሁንም ታጥቆ ያለ ዕረፍት ማገልገሉን ቀጠለ::

+ዘመኑ ነጫጭ ርግቦች (የተባረኩ መነኮሳት) የበዙበት ነበርና ቅዱስ ጐርጐርዮስ አዘውትሮ ወደ ገዳም እየሔደ ይጐበኛቸው: በእጆቻቸውም ይባረክ ነበር:: በተለይ #ሊቀ_ምኔት ታላቁ ቅዱስ ዻኩሚስ (#አባ_ባኹም) በቅርቡ ነበርና ሁሌ እየሔደ ይጨዋወተው ነበር::

+ትንሽ ቆይቶ ግን ቅዱሱ የምናኔ ፍላጐቱ እየጨመረ ሔደ:: አንድ ቀን ከገዳም ውሎ ሲመለስ ወላጆቹ ጥያቄ ጠየቁት::
"ልናጋባህ እንፈልጋለንና ምን ትላለህ?" አሉት:: እርሱም ጭራሹኑ እንደማይፈልግ መለሰላቸው:: ሊያሳዝኑት አልፈለጉምና ድጋሚ አልጠየቁትም::

+ትንሽ ቆይተውም ተከታትለው ዐረፉ:: ቅዱስ ጐርጐርዮስ ወላጆቹን ቀብሮ: ሃብት ንብረቱን ሸጦ ጉዞ ጀመረ:: ወደ #አባ_ዻኩሚስ ደርሶም ያን ሁሉ ገንዘብ በታላቁ ቅዱስ ፊት አፈሰሰው:: "ምን ላድርገው ልጄ?" ቢለው "አባቴ! ፈጣሪህ ያዘዘውን" አለው::

+አባ ዻኩሚስም መነኮሳት በመብዛታቸው ቤት አልነበረምና ብዙ ቤቶችን አነጸበት:: የቅዱሱ ገንዘብ ገዳም ከታነጸበት በሁዋላ ምናኔን አንድ ብሎ ጀመረ::

+ቅዱሱ ባጭር ታጥቆ: በጾምና ጸሎት: ውሃ በመቅዳት: በመጥረግ: ምግብ በማዘጋጀት: እግዚአብሔርንም አበውንም አስደሰተ:: ቅዱሱ ምንም ቢናገሩት አይመልስም:: ማንንም ቀና ብሎ አያይም::

+"እሺ" ከማለት በቀር ትርፍ ቃል አልነበረውም:: በጸሎት እንባው: በስግደት ደግሞ ላቡ ይንቆረቆር ነበር:: ፍቅሩ: ትዕግስቱ: ትሕትናውና ታዛዥነቱ እጅግ ብዙ ዓለማውያንን ማረከ:: ስለ እርሱ የሰሙ ኃጥአን ሔደው ምንም ሳይናገራቸው በማየት ብቻ ይማሩ ነበር:: ፊቱ ብሩህ: ደግና ቅን በመሆኑ እርሱን ማየቱ በቂ ነበር::

+ለ13 ዓመታት በገዳመ ዻኩሚስ ከተጋደለ በሁዋላ ወደ ገዳመ #ቅዱስ_መቃርስ ከ2ኛው አባ መቃርስ ጋር ተጉዋዘ:: በዚያም በዓት ወስኖ ከሰው ጋር ሳይገናኝ 7 ዓመታትን አሳለፈ:: በጸጋ ላይ ጸጋ: በበረከት ላይ በረከት ሆኖለት በ22ኛ ዓመቱ አባቶችን ሰበሰባቸው::

+መንገድ ሊሔድ መሆኑን ነግሯቸው "በጸሎት አስቡኝ" አላቸው:: በማግስቱ በዚህ ቀን ሲመጡ ግን በፍቅር ዐርፎ አገኙት:: መነኮሳትም በክብር ገንዘው: ከበረከቱ ተሳትፈው: በታላቅ ዝማሬ ቀብረውታል::

†   🕊   ቅድስት_ክርስቶስ_ሠምራ    🕊   †

=>ኢትዮዽያዊቷ #ቅድስት_እናት_ክርስቶስ_ሠምራ ቅንነቷ: ደግነቷና ቅድስናዋ እጅግ የበዛ ነው:: አንድ ቀን ግን ገና በትዳር ውስጥ እያለች: ከአገልጋዮቿ አንዷን ትጠራትና ታዛታለች:: ያቺ አገልጋይ ግን የታዘዘችውን ጆሮ ዳባ ልበስ ብላ ሳትታዘዛት ትቀራለች::

+ደጋግማ ብትነግራትም ልትሰማት አልቻለችም:: ያን ጊዜ ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ልትገስጻት ብላ ጠጠር ብትወረውርባት ያች አገልጋይ ወድቃ ሞተችባት:: ቅድስቲቱ እጅግ ደንግጣ አለቀሰች:: የምታደርገውንም አጣች::

+ወዲያው ግን ፈጠን ብላ: ወገቧን ታጥቃ ትጸልይ ጀመረች:: "ጌታዬ ሆይ! ከሞት አስነሳልኝና ዓለምን ትቼ በቀሪ ዘመኔ አንተን አገለግልሃለሁ" ብላ ፈጣሪን በብዙ እንባ ተማጸነችው:: ያን ጊዜም አገልጋዩዋ ከሞት ተነሳችላት::

+ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ጊዜን አላጠፋችም:: ልጆቿን በቤት ትታ: ሃብትን ንብረቷን ንቃ: አንድ ልጇን አዝላ: ቤቷን እንደ ተከፈተ ትታው ወደ ገዳም ወጣች:: በዚህ ዕለትም (መስከረም 24 ቀን) ወደ #ደብረ_ሊባኖስ ገዳም ገባች::

†   🕊   ቅዱስ_አድሊጦስ_ሐዋርያ    🕊   †

=>ቅዱሱ ሐዋርያ ተወልዶ ያደገው በግሪክ #አቴና (ATHENS) ውስጥ ሲሆን በነገድ እሥራኤላዊ ነው:: በአደገባት አቴና ከተማ ሥርዓተ ኦሪትን ከወገኖቹ: የግሪክን ፍልስፍና ደግሞ ከአርዮስፋጐስ ተምሯል:: #መድኃኔ_ዓለም ዘመነ ስብከቱ ሲጀምር ግን አድሊጦስ ወደ #ኢየሩሳሌም ሔዶ አደመጠው: ተማረከበትም::

+ወዲያውም "ጌታ ሆይ! ልከተልህ?" ሲል ጠየቀው:: ልብን የሚመረምር ጌታም ፈቅዶለት ከ72ቱ አርድእት ደመረው:: ከዚያም ከጌታችን ዘንድ ተምሮ: መንፈስ ቅዱስንም ተቀብሎ: ለወንጌል አገልግሎት ተሠማርቶ በርካታ አሕዛብን አሳምኗል:: በመጨረሻም ተወልዶ ባደገባት አቴና በዚህች ቀን ገድለውታል::

=>አምላከ ቅዱሳን በትእግስት: በፍቅርና በትሕትና ይሸልመን:: ከበረከታቸውም ያድለን::

=>መስከረም 24 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=

1.ቅዱስ ጐርጐርዮስ ገዳማዊ
2.ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ (ደብረ ሊባኖስ የገባችበት)
3.ቅዱስ አድሊጦስ ሐዋርያ (ከ72ቱ አርድእት)
4.አቡነ ሰላማ

=>ወርኀዊ የቅዱሳን በዓላት

1.ቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት (መምሕረ ትሩፋት)
2.ቅዱስ ቶማስ ዘመርዐስ
3.አቡነ ዘዮሐንስ ጻድቅ ዘክብራን
4.ቅዱስ አጋቢጦስ (ጻድቅ ኤዺስቆዾስ)
5.ቅዱስ አብላርዮስ ታላቁ
6."24ቱ" ካኅናተ ሰማይ (ሱራፌል)
7.ቅዱስ አባ ሙሴ ጸሊም (ኢትዮዽያዊ)

=>+"+ #ፍቅር ያስታግሳል:: ፍቅር ያስተዛዝናል:: ፍቅር አያቀናናም::ፍቅር አያስመካም:: ፍቅር አያስታብይም:: ብቻዬን ይድላኝ አያሰኝም:: አያበሳጭም:: ክፉ ነገርን አያሳስብም:: ከእውነት ጋር ደስ ይለዋል እንጂ ስለ ዓመፃ ደስ አይለውም:: ሁሉን ይታገሣል:: ሁሉን ያምናል:: ሁሉን ተስፋ ያደርጋል:: በሁሉ ይጸናል:: +"+ (1ቆሮ. 13፥4)

† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †

[ ዲያቆን ዮርዳኖስ አበበ  ]


💚💛@sinkisar_gisawe_z_tewahedo
💚💛
    🇯 🇴 🇮 🇳 &🇸 🇭 🇦 🇷 🇪   
        ✥┈┈•◦●◈◎❖◎◈●◦•┈┈✥
  ✧━━━━━━━━━━━━━━━━━✧
      ❍ㅤ           ⎙ㅤ         ⌲ 
ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ         ˢᵃᵛᵉ          ˢʰᵃʳᵉ