ስንክሳር ወግጻዌ ዘተዋሕዶ
853 subscribers
3.46K photos
103 videos
194 files
1.2K links
የየዕለቱ ስንክሳር እና ግጻዌ የሚቀርብበት ቻናል ነው፡፡

ለማንኛውም አስተያየት እና እርማት
@zetaodokos ላይ ይላኩልን።

👇👇የYoutube Channel ይቀላቀሉ👇👇
https://youtube.com/channel/UCupqpIYe_mMpSM7jMT3Njhw
Download Telegram
#ክርስቲያናዊ_ሥነ_ምግባር
ተከታታይ ትምህርት
#ክፍል_2
@zekidanemeheret
#10ቱ_ትዕዛዛት (ኦሪ ዘፀ 20)
#1.እኔ እግዚአብሔር አምላክህ ነኝ ከግብፅ ምድር ያወጣሁህ ነኝ ከኔ በቀር ሌሎቹ አማልክት አይሁኑልህ ።
#2.የእግዚአብሔር የአምላክህን ስም በከንቱ አታንሳ ። #3.የሰንበትን ቀን ትቀድሰው ዘንድ አስብ ።
#4.እናትና አባትህን አክብር ። #5.አትግደል
#6.አታመንዝር
#7.አትስረቅ
#8.በባልንጀራህ ላይ በሐሰት አትመስክር
#9.የባልንጀራህን ቤት አትመኝ #10.ባልንጀራህን እንደራስህ ውደድ።
🖊የክርስትና ህግ የፍቅር ህግ ነው ። ቅዱስ ጳውሎስ ሌላውን የሚወድ ሕግን ፈፅሞታል ካለ ቡሃላ ከ10ቱ ትዕዛዛት የተወሰኑትን በመጥቀስ #ፍቅር የሕግ ሁሉ ፍፃሜ መሆኑን በግልፅ ይናገራል። /ሮሜ 13÷8/ 🖊ጌታችን እንዳስተማረን ፍቅር በሁለት ይከፈላል ። #1ኛ_ፍቅረ_እግዚአብሔር #2ኛ_ፍቅረ_ቢፅ
🖊በሌላ በኩል ደግሞ ከአዎንታዊና አሉታዊ ከመነገራቸው አንፃር በሁለት ይከፈላሉ ።
#1ኛ_ሕግ_በአሉታ_የተነገሩ /አታድርግ/
#2ኛ_ትዕዛዝ_በአዎንታ_የተነገሩ /አድርግ/ ይባላሉ
🖊ከዚህም ሌላ ከአፈፃፀማቸው አንፃር ሲታዩ በሦስት ይከፈላሉ ። #1ኛ_በሐልዩ /በማሰብ/ የሚፈፀሙ ህግ1,3,4 እና 9 #2ኛ_በነቢብ /በመናገር/ የሚፈፀሙ ህግ 2,8
#3ኛ_በገቢር /በማድረግ/ ህግ 5,6,7,10 ናቸው ።
🖊#10ቱ ትዕዛዛት ለሙሴ በተሰጡ ጊዜ በሁለት የድንጋይ ፅላቶች ላይ ተፅፈው ነበር ። እንዲሁም ሁሉ በተለይም እስራኤል ዘነፍስ የምንባለው ለእኛ ለክርስቲያኖች ከልባችን ፅላት ላይ በመንፈስ ልንፅፈው ይገባል። በቤተክርስቲያናችን በፅላቶቻችን ላይ የጌታችን የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ስም ይገኛል ። ጌታችን ደግሞ ማንኛውንም ነገር በስሜ ብትለምኑ እኔ አደርገዋለው ካለ ቡሃላ ብትወዱኝስ ትዕዛዜን ጠብቁ ብሎ አስተምሯል ። እንዲህ ከሆነ የሚያስፈልገንን ነገር ለመለመን የጌታችን ስሙ ስለተፃፈበት በዙሪያው ተሰብስበን መለመን ያስፈልጋል ። ህጉ ከልባችን ስለማይጠፋ ሕጉን መጠበቅና መፈፀም ይገባናል ።
🖊ለዚህም በቀጣይ እያንዳንዳቸውን በዝርዝር እንማማራለን ።

ይቀጥላል....

@zekidanemeheret
ለሌሎችም ማጋራትን አይርሱ
👉ለመቀላቀል 👇👇👇👇
@zekidanemeheret @zekidanemeheret @zekidanemeheret