STUDENTS NEWS CHANNEL (የተማሪዎች ዜና መስኮት)
40.8K subscribers
11K photos
271 videos
452 files
1.93K links
የተማሪ እና ተማሪ ነክ መረጃዎች ይቀርቡበታል፡
Download Telegram
ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተለያዩ ሙያዎች ፍላጎት ያላቸውን ተወዳዳሪዎችን አሰልጥኖ መቅጠር እንደሚፈልግ ባወጣው ማስታወቂያ መሠረት ዛሬው እለት በሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ግቢ ምዝገባ መጀመሩም እንገልጻለን ።

Mizan-Tepi University

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያወጣቸውን ስራዎች ONLINE እንድንመዘግባችሁ የምትፈልጉ ዶክመንታችሁን ማለትም የ8,10,12 ፣ መታወቂያ ፊትና ጀርባ አንድ ፓስፖርት ሳይዝ ፎቶ ለልደት ሰርተፍኬት ካላችሁ እና ተጨማሪ በሚጠይቁት ዘርፍ ያላችሁን ዶክመንት አያይዛችሁ @JobsET19
ላይ መላክ ትችላላችሁ የምትልኩት ስካን የተደረገ ፎቶ አንስታቹ ከሆነ ደግሞ ጥርት ያለ መሆን አለበት
ማሳሰቢያ ምዝገባው መጠነኛ ክፍያ አለው

@JobsET19
@JobsET19
@JobsET19
#የጤና_ተማሪዎች_ቅሬታ

እኛ የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የህክምና ተመራቂ ተማሪዎች በዘንድሮ ዓመት ሰኔ 30/2015 አ/ም የኢንተርንሽፕ ፕራክቲስ (internship) ጨርሰን ነገር ግን የEXIT EXAM ለመፈተን ት/ሚኒስተር ባወጣዉ መስፈርት መሰረት በወቅቱ መሰፈርቱን ለማሟላት የሳምንታት ልዩነት በመኖሩ ለፈተናዉ መቀመጥ እንዳልተቻለ የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ አሳዉቆን ነበር::

ይሄም ሊሆን የቻለው የህክምና ተማሪዎቸ አንደ ሌላዉ ትምህርት ዘርፍ በየዩኒቨርሲዉ የሚጣናቀቅበት ሰአት ገደብ እኩል ስላልሆነ ነው፡፡ በመሆኑም አሁን የ7 ዐመት ትምህርታችንን ካጠናቀቅን ወር ያለፈን ቢሆንም EXIT EXAM ለመፈተን ለ6ወር ያለምንም የምረቃ ሥነ-ሥርዓት በየቤታችን ሄደን እንድንጠብቅ ዩኒቨርሲቲዉ አሳዉቆናል።

ስለሆነም ት/ሚኒስተር ባወጣዉ የፈተና ሰአት ልንቀመጥ አልቻልንም።

ካሁን በሁላ ቀጣዩ የEXIT EXAM ከ6ወር በኋላ መሆኑን ት/ሚኒስተር ያወጣዉ መመሪያ ስለሆነ ፤ እኛ 7አመት ሙሉ በትምህርት ቆየተን ብደጋሚ ለሚቀጥሉት 6 ወራት ያለምንም ምክንየት እና ሥራ እንድንቀመጥ እየተገደድን ነው:: ስለሆነም ይሄን ጉዳይ ት/ሚኒስተር አይቶ፡ በዚ ሁለት ወራት በመጨረስ ላይ ያሉ የጤና ተማሪዎች በማማከል አዲስ የፈተና ሥርዓት እንዲያወጣልን እንጠይቃለን።

የወልቂጤ ዩንቨርሲቲ ተመራቂ የህክምና ተማሪዎች

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያወጣቸውን ስራዎች ONLINE እንድንመዘግባችሁ የምትፈልጉ ዶክመንታችሁን ማለትም የ8,10,12 ፣ መታወቂያ ፊትና ጀርባ አንድ ፓስፖርት ሳይዝ ፎቶ ለልደት ሰርተፍኬት ካላችሁ እና ተጨማሪ በሚጠይቁት ዘርፍ ያላችሁን ዶክመንት አያይዛችሁ @JobsET19
ላይ መላክ ትችላላችሁ የምትልኩት ስካን የተደረገ ፎቶ አንስታቹ ከሆነ ደግሞ ጥርት ያለ መሆን አለበት
ማሳሰቢያ ምዝገባው መጠነኛ ክፍያ አለው

@JobsET19
@JobsET19
@JobsET19
" ወጪያቸው በመንግሥት የሚሸፈንላቸውን ተማሪዎች የመግቢያ ፈተና ሰጥተን እንቀበላለን " - አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ2016 ዓ.ም ትምህርት ሚኒስቴር ከሚያስቀምጠው የመቁረጫ ነጥብ በላይ ያመጡ ተማሪዎችን አወዳድሮ እንደሚቀበል መገለጹ ይታወቃል፡፡

በሀገሪቱ የመጀመሪያው ራስ ገዝ ከፍተኛ ትምህርት ተቋም የሆነው ዩኒቨርሲቲው፣ በሚቀጥለው የትምህርት ዘመን ተማሪዎችን የሚቀበልበት መስፈርት ላይ ማብራሪያ አቅርቧል፡፡

በዚህም ዩኒቨርሲቲው ወጪያቸው በመንግሥት የሚሸፈንላቸውን ተማሪዎች የመግቢያ ፈተና ሰጥቶ ይቀበላል፡፡

በአሁኑ ሰዓት በማታው ክፍለ ጊዜ (Extension) በግል እየተማሩ እንደሚገኙ ተማሪዎች፤ በመደበኛው ክፍለ ጊዜም (Regular) ተመሳሳይ ተማሪዎችን ተቀበሎ በመጠነኛ ክፍያ የሚያስተምር መሆኑን ገልጿል።

ዩኒቨርሲቲው በተለያዩ ማህበራዊ ገፆች ላይ " አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሀብታሞች መማሪያ ብቻ ይሆናል" ተብሎ የሚናፈሰው ወሬ ሐሰተኛና የህግ አግባብነት የሌለው ነው ብሏል።

ራስ ገዝ አስተዳደር መሆን ያስፈለገው የገንዘብ አቅም ያላቸው ተማሪዎችን ብቻ ተቀብሎ ለማስተማር እንዳልሆነ ባወጣው ማብራሪያ የገለፀው ዩኒቨርሲቲው፤ "አንድ ተማሪ ወደ ተቋሙ ለመማር ሲመጣ እንደማንኛውም ተማሪ ከክፍያው በፊት የተቋሙን የትምህርት መመዘኛ መስፈርቶች ማግኘት ይጠበቅበታል" ብሏል፡፡

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT
የሬሜዲያል ፈተና በቅርቡ ስለሚሰጥ ተፈታኞች ዝግጅት እንዲያደርጉ ተጠየቀ

ከነሐሴ 23 እስከ ነሐሴ 26 ቀን 2015 ዓ.ም ሊሰጥ የነበረው የሬሜዲያል ፈተና የተራዘመው የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች ስላልተጠናቀቁ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

በሚኒስቴሩ የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ሥራ አስፈጻሚ ኤባ ሚጀና (ዶ/ር) ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለጹት÷ መጠናቀቅ ያለባቸው የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን በአግባቡ ለማጠናቀቅ ሲባል የፈተናውን ጊዜ ላልተወሰነ ጊዜ ማራዘም አስፈልጓል፡፡

የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እንደተጠናቀቁም በቅርቡ ተፈታኞች ለፈተና ስለሚጠሩ ዝግጅት እያደረጉ እንዲጠብቁ አሳስበዋል፡፡

ባለፈው ጊዜ ፈተና ያልወሰዱ እና የማካካሻ ትምህርት ሲከታተሉ የነበሩ 46 ሺህ የሚጠጉ የመንግሥትና የግል ተማሪዎች በቅርቡ ፈተናቸውን እንደሚወስዱ አረጋግጠዋል፡፡

በቅርቡ ፈተናቸውን የሚወስዱ እና የዩኒቨርሲቲ መግቢያ የሚያመጡ የሬሜዲያል ተፈታኞችም ቀደም ብለው የሬሜዲያል ፈተና ወስደው የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ካመጡ ተማሪዎች ጋር ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡበት ጊዜ ተመሳሳይ ስለሆነ ስጋት እንዳይገባቸው አስገንዝበዋል፡፡

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያወጣቸውን ስራዎች ONLINE እንድንመዘግባችሁ የምትፈልጉ ዶክመንታችሁን ማለትም የ8,10,12 ፣ መታወቂያ ፊትና ጀርባ አንድ ፓስፖርት ሳይዝ ፎቶ ለልደት ሰርተፍኬት ካላችሁ እና ተጨማሪ በሚጠይቁት ዘርፍ ያላችሁን ዶክመንት አያይዛችሁ @JobsET19
ላይ መላክ ትችላላችሁ የምትልኩት ስካን የተደረገ ፎቶ አንስታቹ ከሆነ ደግሞ ጥርት ያለ መሆን አለበት
ማሳሰቢያ ምዝገባው መጠነኛ ክፍያ አለው

@JobsET19
@JobsET19
@JobsET19
አክሱም ዩኒቨርሲቲ በሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁና ጊዚያዊ ዲግሪ ሰርተፊኬት የተዘጋጀላቸው ተማሪዎችን ዝርዝር አውጥቷል።

ዩኒቨርሲቲው በሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ተመድበው በመደበኛ መርሐግብር በመጀመሪያ ዲግሪ ፕሮግራም ትምህርታቸውን ተከታትለው ላጠናቀቁ 326 ተማሪዎች Temporary Degree ሰርተፊኬት መዘጋጀቱን ገልጿል።

ተማሪዎቹ በዋቸሞ፣ እንጅባራ፣ ጅማ፣ አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ እንዲሁም ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲዎች ትምህርታቸውን የተከታተሉ ናቸው።

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT
የ8ኛ ክፍል ውጤት ይፋ ተደረገ

የኦሮሚያ ክልል የ2015 የ8ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ይፋ መሆኑን ከክልሉ የትምህርት ቢሮ የተገኘው መረጃ ያሳያል።

የ2015 ዓ/ም የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና የወሰዱ ተማሪዎች ከዚህ በታች የተቀመጠውን ሊንክ በመጠቀም  ስማቸውን እና የID. ቁጥራቸውን በማስገባት ዉጤታችሁን ማየት እንደሚችሉ ቢሮው አሳውቋል።

Website:- https://oromia.ministry.et/#/result

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT
የትምህርት ቤቶች አስተዳዳሪዎች ከአሁን በኋላ የሚመረጡት በካድሬነት ሳይሆን፣ ባላቸው ብቃትና ችሎታቸው ላይ መሠረት ተደርጎ ይሆናል።

በዚህ መሠረት በአገር አቀፍ ደረጃ በብቃታቸውና በችሎታቸው የተመዘኑ 1,600 የትምህርት አስተዳዳሪዎች ሥልጠና ተሰጥቷቸዋል። ይህ ዓይነቱ አሠራር ቀጣይነት ይኖረዋል።

የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ከማሳደግ ሥራ በተጨማሪ የመምህራንና ርዕሳነ መምህራን ብቃትና ችሎታ ማጎልበት ትኩረት ተሰጥቶበታል፡፡

ትኩረት ካገኙ መሠረታዊ ጉዳዮች ትምህርት ቤቶችን በግብዓትና በጥራት ከማሻሻል ባሻገር ክህሎት፣ ብቃትና ችሎታ ባላቸው ርዕሳነ መምህራን እንዲተዳደሩ ማድረግ ትልቁን ድርሻ ይይዛል።

የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ከማሻሻል በተጨማሪ በዕውቀት ተማሪዎቻቸውን ተወዳዳሪ ማድረግ የሚችሉ መምህራንን ማብቃት ከተያዙ ግቦች መካከል አንዱ ነው።

ባለፉት 30 ዓመታት የመንግሥት ትምህርት ቤቶች ጥራት ወርዷል ፤ በኑሮ ለተሻሉ ደግሞ የግል ትምህርት ቤቶች የሚማሩበት ሥርዓት ተዘርግቷል።

ይህ ዓይነት አካሄድ በዜጎች መካከል በኑሮ ደረጃ ከተፈጠሩ ልዩነቶች አልፎ በትምህርት ዘርፍ ላይ መታየቱ ትልቅ ክስረት ነው። ይህ አካሄድ በአገር አቀፍ ደረጃ አደገኛ ሁኔታዎች የሚፈጥር ነው ፤ በየትኛውም የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ዜጎች በገንዘብ ዕጦት ሳቢያ የትምህርት ጥራት ሊጓደልባቸው አይገባም።

ትምህርት የአገር የሉዓላዊነት እሴት መለኪያ ነው ፤ በዚህ ጉዳይ ለዓመታት የተቀለደበት ዘርፍ ነው አሁን እርስ በርስ መነጋገር የማይቻልበት ሁኔታ ላይ መደረሱ የችግሩ ማሳያ ነው። በኢትዮጵያ የትምህርት ዘርፉ ከአሥር ዓመታት በኋላ ትምህርት ቤቶች እንደ አሁኑ የፀብ (የረብሻ) መፍለቂያ ሳይሆኑ የመወዳደሪያና የብቃት ማጎልበቻ ይሆናሉ፡፡

#MoE

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት
@NATIONALEXAMSRESULT
በአማራ ክልል የ2016 ትምህርት ዘመን የተማሪዎች ምዝገባ ከነገ ነሐሴ 23/2015 ዓ.ም ጀምሮ ይካሔዳል፡፡

የተማሪዎች ምዝገባ እስከ ጳጉሜን 03/2015 ዓ.ም ደረስ ይከናወናል፡፡

በክልሉ የሚገኙ ትምህርት ቤቶች መስከረም 02/2016 ዓ.ም ይከፈታሉ የተባለ ሲሆን መስከረም 14/2016 ዓ.ም የመማር ማስተማር ሥራ ይጀምራል ተብሏል፡፡

በአማራ ክልል 6 ነጥብ 3 ሚሊዮን ተማሪዎች ምዝገባ ያደርጋሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ የክልሉ ትምህርት ቢሮ ገልጿል፡፡

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት
@NATIONALEXAMSRESULT
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሚቀጥለው የትምህርት ዘመን ተማሪዎችን የሚቀበልበት መስፈርት እንደሚከተለው ይሆናል፡-

1. እንደማንኛውም ራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ ወጪያቸውን በመንግስት የሚሸፈንላቸውን ተማሪዎችን ፈትኖ ይቀበላል፣

2. በአሁኑ ሰዓት በማታው ክፍለ ጊዜ (Extension) በግል እየተማሩ እንደሚገኙ ተማሪዎች በመደበኛው ክፍለ ጊዜም (Regular) ተመሳሳይ ተማሪዎችን ተቀበሎ በመጠነኛ ክፍያ የሚያስተምር ይሆናል፣

3. ዩኒቨርሲቲው በፊት ከነበረው ከትምህርት ሚኒስቴር ከሚላክለት የተማሪዎች ቅበላ ውጭ በልዩነት ፈትኖ ተማሪዎችን ቢቀበልም ከዚህ በፊት በመንግስት ከሚመደብለት የተማሪዎች ቁጥር ያነሰ አይሆንም፤

4. አዋጁ በግልጽ እንዳስቀመጠው ሁሉንም የኢትዮጵያ ተማሪዎችን ታሳቢ ያደረገ የትምህርት ተቋም እንደሆነ ዩኒቨርሲቲው ይገልፃል

ይሁንና በአሁኑ ሰዓት በተለያዩ ድህረ-ገፆች ላይ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሐብታሞች መማሪያ ብቻ ይሆናል ተብሎ የሚናፈሰው ወሬ ሀሰተኛና የህግ አግባብነት የሌለው መሆኑን ዩኒቨርሲቲው ያሳውቃል፡፡

በመሆኑም የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሁሉም ኢትዮጵያዊ መዳረሻ ፣ የእውቀት መገብያ መናኸሪያ እንዲሆን እንጂ ራስ ገዝ አስተዳደር ያስፈለገው የገንዘብ አቅም ያላቸው ተማሪዎችን ብቻ ተቀብሎ የሚያስተምር ተቋም እንዳይሆን ታስቦ እንደሆነ ለመግለጽ እንወዳለን፡፡
ይህ ማለት አንድ ተማሪ ወደ ተቋሙ ለመማር አስቦ ሲመጣ እንደማንኛውም ተማሪ ከክፍያው በፊት የተቋሙን የትምህርት መመዘኛ መስፈርቶች (Admission paper) ሲያገኝ ብቻ ይሆናል::

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT
" የኢንተርኔት አገልግሎት ባለባቸው አካባቢዎች ፈተናው በኦንላይን ይሰጣል (ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ) " - የትምህርት ሚኒስትር ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ

ትምህርት ሚኒስቴር በሚቀጥለው የትምህርት ዘመን #በዩኒቨርሲቲዎች የሚሰጠው የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የኢንተርኔት አገልግሎት ባለባቸው አካባቢዎች በ #ኦንላይን እንደሚሰጥ አሳውቋል።

ይህን ያሳወቁት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ናቸው።

ሚኒስትሩ ፤ በ2016 የትምህርት ዘመን አዲሱ ሥርዓተ ትምህርት በሁሉም የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ተግባራዊ እንደሚሆን አሳውቀዋል።

ለዚህም ተግባራዊነት ዝግጅቶች መጠናቀቃቸውን ጠቁመዋል።

ፕ/ር ብርሃኑ ፤ በሚቀጥለው የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ እንደሚሰጥ ጠቁመው የኢንተርኔት አገልግሎት ባለባቸው አካባቢዎች ፈተናው በኦንላይን እንደሚሰጥም ገልጸዋል።

በሌላ በኩል ፤ ከአዲሱ የትምህርት ስርዓት ጋር በተያያዘ በመጽሐፍት ሕትመትና ስርጭት ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እየተሰራ ነው በዋል።

በመጀመሪያና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ላይ የመጽሐፍት እጥረት ማጋጠሙን የጠቆሙት ሚኒስትሩ ፤ ችግሩ በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ላይ እንዳያጋጥም ቀደም ብሎ ጨረታ በማውጣት መጽሐፍትን በወቅቱ ለማድረስ እየተሠራ ነው ብለዋል።

መጽሐፍት እስከ መስከረም ወር መጨረሻ ድረስ እንደሚቀርቡ የትምህርት ሚኒስትሩ ጠቁመዋል፡፡

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT
ዲላ ዩኒቨርሲቲ በቡና ላይ ትኩረቱን ያደረገ ትምህርት በበይነ-መረብ መስጠት ሊጀምር ነው፡፡

ዩኒቨርሲቲው ከGIZ ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በቡና ላይ ትኩረት ያደረገ ትምህርት በበይነ-መረብ ለመስጠት የሚያስችል አውደ ጥናት አካሒዷል፡፡

የበይነ-መረብ ትምህርቱ ተግባራዊ ሲሆን በሀገር አቀፍ ደረጃ 1,000 ባለሙያዎችን በመጀመሪያው ዓመት ተቀብሎ ማሰልጠን እንደሚጀምር ተገልጿል።

ዲላ ዩኒቨርሲቲ የቡና ዘርፍ ላይ ትኩረት በማድረግ የሁለተኛ ዲግሪ ትምህርት በመስጠት በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ዩኒቨርሲቲ እንደሆነ ከተቋሙ የተገኘ መረጃ ያሳያል፡፡

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT
በነገዉ እለት ነጻ የትራንስፖርት አገልግሎት በአዲስአበባ ይሰጣል ተባለ

ነገ ጷግሜን 1/2015 ዓ.ም የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ የአገልግሎት ቀንን ምክንያት በማድረግ ከጠዋቱ 12፡00 ጀምሮ ነጻ የትራንስፖርት አገልግሎት እንደሚሰጥ ብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥን ሰምቷል።

አገልግሎቱን የሚሰጡት የከተማ አውቶብስና የከተማ ቀላል ባቡር መሆናቸዉን ቢሮዉ ገልጿል።

#ዳጉ_ጆርናል

@NATIONALEXAMSRESULT
2015 ዓ.ም ስናስታውሰው

በኢትዮጵያውያን የዘመን አቆጣጠር በማገባደድ ላይ የምንገኘው የ2015 ዓ.ም በበጎ፣ በሐዘንም ሆነ በደስታ እጅግ በርካታ ዜናዎች የተስተናገዱበት ዓመት ነበር። ከነዚህ ዜናዎች ጎላ ጎላ ብለው የወጡትን እናስታውሳችሁ፦

• መስከረም 17/2015 ዓ.ም
አርቲስት ማዲንጎ አፈወርቅ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ፡፡ ስርዓተ ቀብሩም መስከረም 19/2015 ዓ.ም በመንበረ ጸባኦት ቅድሥት ሥላሴ ካቴድራል ተፈጸመ፡፡

• መስከረም 24/2015 ዓ.ም
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሳይንስ ሙዚየምን መርቀው ከፈቱ።

• ጥቅምት 1/2015 ዓ.ም
አንጋፋው የስፖርት ሰው ፍቅሩ ኪዳኔ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ፡፡ ስርአተ ቀብራቸውም ጥቅምት 11/2015 ዓ.ም ፓሪስ ውስጥ ተፈጸመ፡፡

• ጥቅምት 23/ 2015 ዓ.ም
ለሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ሰላማዊ እልባት የሰጠ ታሪካዊ ስምምነት በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ ተፈረመ፡፡

• ጥቅምት 27/2015 ዓ.ም
የክብር ዶክተር አርቲስት አሊ ቢራ ከዚህ አለም በሞት ተለየ፡፡ ስርአተ ቀብሩም ጥቅምት 29/2015 ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ተፈፀመ፡፡

• ሕዳር 26/ 2015 ዓ.ም
በአዲስ አበባ ከተማ ቦሌ አራብሳ አካባቢ ሁለት ሕጻናትን በአሰቃቂ ሁኔታ የገደለችው የቤት ሰራተኛ የሞት ቅጣት ተፈረደባት፡፡

• ሕዳር 27/2015 ዓ.ም
ቄስ በሊና ሠርካ ከዚህ አለም በሞት ተለዩ፡፡ ስርአተ ቀብራቸውም ታኅሣሥ 3/2015 ዓ.ም በአዲስ አበባ በጴጥሮስ ወጳውሎስ የፕሮቴስታንት እና ካቶሊክ መካነ መቃብር ተፈፀመ፡፡

• ታኅሣሥ 2/2015 ዓ.ም
አርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ (ባባ) ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ፡፡ ስርአተ ቀብሩም ታኅሣሥ 3/2015 ዓ.ም በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ስላሴ ካቴድራል ተፈፀመ፡፡

• ታኅሣሥ 19/2015 ዓ.ም
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከአዲስ አበባ መቀሌ ዳግም መደበኛ በረራ ጀመረ፡፡

• ታኅሣሥ 24/2015 ዓ.ም
የክብር አርቲስት ማሪቱ ለገሰ ከ22 ዓመት የአሜሪካ ቆይታ በኃላ ወደ ኢትዮጵያ ተመለሰች፡፡

• ጥር 19/2015 ዓ.ም
በ2014 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከወሰዱ ከ890 ሺህ በላይ ተማሪዎች ውስጥ ከ50 በመቶ በላይ ያመጡ ተማሪዎች ቁጥር 29 ሺህ 909 ብቻ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ።

• የካቲት 28/2015 ዓ.ም
አንጋፋው የሥነ ጽሑፍ መምህርና ሐያሲ ተባባሪ ፕሮፌሰር ዘሪሁን አስፋው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ፡፡ ስርአተ ቀብራቸውም የካቲት 29/2015 ዓ.ም በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተፈጸመ፡፡

• የካቲት 28/2015 ዓ.ም
ከኢትዮጵያ የተዘረፉ 538 ያህል ቅርሶች በእንግሊዝ መገኘታቸው ተገለጸ፡፡ ቅርሶቹ በፈረንጆቹ 1868 እንግሊዝ ኢትዮጵያን በወረረችበት ወቅት በወታደሮች የተዘረፉ መሆናቸውም ተነገረ፡፡

• መጋቢት 12/2015 ዓ.ም
የአካባቢ ጉዳይ ተመራማሪው ዶክተር ተወልደ ብርሃን ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ፡፡ ስርአተ ቀብራቸውም መጋቢት 13/2015 ዓ.ም በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተፈጸመ፡፡

• መጋቢት 12/2015 ዓ.ም
በሞግዚቷ ተሰርቃ የተወሰደችው የ2 ዓመቷ ሕጻን ሶሊያና ዳንኤል በሱሉልታ ክፍለ ከተማ መገኘቷን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ፡፡

• መጋቢት 12/2015 ዓ.ም
ብፁዕ አቡነ አረጋዊ (ዶ/ር) ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ፡፡ ስርአተ ቀብራቸውም መጋቢት 17/2015 ዓ.ም በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተፈጸመ፡፡

• መጋቢት 13/2015 ዓ.ም
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓትን) ከሽብርተኛ ድርጅት ዝርዝር ሰረዘ፡፡

• መጋቢት 14/2015 ዓ.ም
አቶ ጌታቸው ረዳ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር ሆነው ተሾሙ፡፡

• መጋቢት 14/ 2015 ዓ.ም
የታላቁ የኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ ግንባታ 90 በመቶ መድረሱ ተገለጸ፡፡

• መጋቢት 21/ 2015 ዓ.ም
“የምፅአት ቀን በመቅረቡ ሞት እና መፈናቀል ይኖራል” በሚል ስጋት በመቶዎች የሚቆጠሩ ኡጋንዳውያን በስደት ወደ ኢትዮጵያ መግባታቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

• መጋቢት 18 /2015 ዓ.ም
“የፒያኖዋ እመቤት” እማሆይ ፅጌማርያም ገብሩ አረፉ። ስርአተ ቀብራቸውም መጋቢት 22/2015 ዓ.ም በእየሩሳሌም (እስራኤል) ተፈጸመ፡፡

• ሚያዝያ 7/2015 ዓ.ም
“የክልል ልዩ ኃይል” የሚባል አደረጃጀት ማብቃቱን የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ገለጹ።

• ሚያዝያ 15/2015 ዓ.ም
ታዋቂው የአፋን ኦሮሞ ድምፃዊ ዘሪሁን ወዳጆ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ። ስርአተ ቀብሩም ሚያዝያ 18/2015 ዓ.ም በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተፈጸመ፡፡

• ሚያዝያ 19/2015 ዓ.ም
የአማራ ክልል ብልጽግና ጽህፈት ቤት ኃላፊ የነበሩት ግርማ የሺጥላ ተገደሉ፡፡ ስርአተ ቀብራቸውም ሚያዝያ 22/2015 ዓ.ም በትውልድ ቦታቸው ሰሜን ሸዋ ዞን መሃል ሜዳ ከተማ ተካሄደ፡፡

• ሚያዝያ 27/2015 ዓ.ም
ታዋቂው የክላርኔት የሙዚቃ መሣሪያ ተጫዋች ዳዊት ፍሬው ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ፡፡ ስርአተ ቀብሩም ግንቦት 6/2015 ዓ.ም በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተፈጸመ፡፡

• ግንቦት 4/2015 ዓ.ም
አንጋፋዋ ድምጻዊት ሂሩት በቀለ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየች። ስርአተ ቀብሯም ግንቦት 7/2015 ዓ.ም በጴጥሮስ ወጳውሎስ መካነ መቃብር ተፈጸመ፡፡

• ሰኔ 19/2015 ዓ.ም
የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳ የስራ መልቀቂያ አስገቡ፡፡

• ሐምሌ 10/2015 ዓ.ም
ኢትዮጵያ በአንድ ጀንበር 500 ሚሊየን ችግኝ የመትከል መርሐ ግብሯን አሳካች፡፡

• ሐምሌ 13/2015 ዓ.ም
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለቢኒያም በለጠ (መቄዶኒያ) እና ለአርቲስት ደበበ እሸቱ የክብር ዶክትሬት ሰጠ፡፡

• ሐምሌ 13/2015 ዓ.ም
እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ለአርቲስት እጅጋየሁ ሽባባው (ጂጂ) የክብር ዶክትሬት ሰጠ፡፡

• ነሐሴ 3/2015 ዓ.ም
አርቲስት አብነት ዳግም ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።

• ነሐሴ 8/2015 ዓ.ም
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በአማራ ክልል የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አጸደቀ፡፡

• ነሐሴ 18/2015 ዓ.ም
ኢትዮጵያ የብሪክስ አባል ሀገራትን ተቀላቅላለች።

• ነሐሴ 19/2015 ዓ.ም
አቶ አረጋ ከበደ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሆነው ተሾሙ፡፡

• ነሐሴ 19/2015 ዓ.ም
የፊልምና የቴሌቭዥን ድራማዎች ዳይሬክተር አሸብር ካብታሙ ከዚህ ዓም በሞት ተለየ፡፡ ስርአተ ቀብሩም ነሐሴ 22/2015 ዓ.ም በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ቤተ ክርስቲያን ተፈፀመ፡፡

#EBC

@NATIONALEXAMSRESULT
@InEthiopia_Opportunities ቴልግራም ቻናልን ይቀላቀሉና በየእለቱ እነዚህን መረጃዎች ያግኙና የእድሉ ተጠቃሚ ይሁኑ!!!
Join
@InEthiopia_Opportunities
@InEthiopia_Opportunities
@InEthiopia_Opportunities