Natinael Mekonnen
7.92K subscribers
15.6K photos
1.06K videos
20 files
2.48K links
ይህ ቻናል ቴሌግራሜ hacked በተደረገበት ሳት ለግዝያዊነት የከፈትኩት ቻናል ነው ለችግር ጊዜ ይጠቅማል ተቀላቀሉ
በቀጥታ መረጃዎችን ለመስጠት ከፈለጉ @NatnaelMekonnen7 በማለት መረጃዎችን ይላኩልን
Facebook.com/natnaelmekonnen.et
Instagram.com/natnaelmekonnen21
Telegram https://t.me/NatinaelMekonnen21
Download Telegram
ለፉሲካ በአል ወደ ሀገር እየገቡ ላሉ 2ኛ ትውልድ ኢትዮጵያውያን በቦሌ አለም አቀፍ ኤርፖርት አቀባበል እየተደረገላቸው ነው::

በአቀባበል ስነ ስርዓት ላይ የቱሪዝም ሚንስትሯ አምባሳደር ናሲሴ ጫሊን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።

“Back to your origins” የሚል ስያሜ የተሰጠው እና ጠ/ሚር ዐቢይ አህመድ በውጭ ለሚኖሩ የ2ኛ ትውልድ ኢትዮጵያውያን ያቀረቡት ጥሪ በሶስት ዙሮች የሚካሄድ ነው::

በዚህም እከታህሳስ 20 እስከ ጥር 30 በመጀመሪያው ዙር ከብዝኃ ባህል መሰረትዎ ጋር ይገናኙ በሚል በተሰየመው መርሃ ግብር ወደ ሀገራቸው ገብተው እንደነበር ይታወሳል።

አሁን ደግሞ ታሪካዊ መሰረትዎን ይወቁ (connect to your historical roots) በሚል በተሰየመው መርሀግብር በሁለተኛ ዙር ወደ ሀገር እየገቡ ይገኛሉ::

በሁለተኛው ምዕራፍ ኢትዮጵያውያን የእረፍት ጊዜያቸውን (Spring Break) ተጠቅመው የሀገራቸውን ታሪክ እንዲያውቁ፣ የአያቶቻቸውንና ቅድመ አያቶቻቸውን አይበገሬነትና መስዋዕትነት
እንዲሁም ከራሳቸው አልፎ ለጥቁር ህዝቦች ነፃነት ያበረከቱትን አስተዋፅዖ አንዲረዱ በማድረግ የሀገር ፍቅር ስሜታቸው እንዲዳብር ብሎም በዚህ አኩሪ
ታሪክ ተነሳስተው በዘመናቸው ፍሬያማ አስተዋፅዖ እንዲያበረክቱ ለማስቻል ያለመ ነው::

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የበረራ ትኬት፣ሆቴሎች፣ አስጎብኚ ድርጅቶች የዋጋ ቅናሽ በማድረግ 2ኛ ትውልድ ኢትዮጵያውያኑን ተቀብለው በማስተናገድ ላይ ናቸው::
TPLF ወልቃይትን ይቅርና በትግራይ ክልል መከላከያ ይዞት የነበረን 1 ኢንች መሬት በጦርነት መያዝ አይችልም። ጦርነት ከፍቶ አንድ ኢንች መሬት ልያዝ ካለ የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ሙሉ በሙሉ ለመጣሱ ማረጋገጫ ይሰጣል። የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት TPLF ጦርነት እንዲከፍት አይደለም ትጥቅ እንዲኖረው አይፈቅድለትም። የስምምነት አስኳሉና ቀዳሚው ጉዳይ ተኩስ ማቆም ትጥቅ መፍታት ነውና።

TPLF ይህን የሰላም ስምምነት ላለመፈፀም ያለውን ትጥቅ ይዞ ለመቀጠል ቀድሞ በእኔ ስር ለነበሩት ለወልቃይት ወይም ለራያ መሬት ነው ጦርነት የምከፍተው ችግሬ ከአማራ ክልል ጋር ነው በሚል እንደለመዱት ሌላውን እንደሞኝና እንደአላዋቂ በመቁጠር ከፋፍሎ የፖለቲካ ወታደራዊ ድል ለማስመዝገብ ጦርነት እከፍታለሁ ብሎ ከገፋበት ግጭቱ በቀጥታ ከፌደራል መንግስቱ ጋር ይሆናል። TPLF ም ራሱን ለማጥፋት በፈቃዱ እንደወሰነ ይቆጠራል።

መንግስት የአማራን የኦሮሚያን የሲዳማን የአፋርን የሶማሌን የቤንሻንጉልን እንዲሁም የሌሎቹን ክልሎች ልዩሃይል ትጥቅ ያስፈታውና የልዩሃይል አባላትን ወደፖሊስ መከላከያ እንዲቀላቀሉ ወይም ምርጫቸውን እንዲከተሉ ያደረገው እነሱ በታጠቀው TPLF ወይም ሌላ አካል እንዲጠቁ አይደለም። ከመከላከያ ጋር ተገዳዳሪ የሆነ ሃይል በአንድ ሐገር ውስጥ እንዳይኖር ነው። እነሱን ትጥቅ አስፈትቶ ለዛውም በሰላም ስምምነቱ ዋና ጉዳይ የሆነውን ተኩስ የማቆምና ትጥቅ የመፍታት ስምምነትና አጀንዳን ደርቦ የትግራይ ክልል እስከ ትጥቁ ይቀጥል ሲፈልግ በተመቸው ጊዜ ጦርነት ይክፈት ሊባል አይችልም። የኢትዮጵያ መከላከያ መቀሌ ሊገባ ጫፍ ደርሶ እንዲቆም የተደረገው በጉልበት አሸንፎ ሁሉንም ነገር ከመቆጣጠር በጉልበት ለተሸነፈው TPLF በ1/5 ጥርነፋ አንድ አይነት መረጃ እየተጋተ ለደገፈው ቁጥሩ ለማይናቅ የትግራይ ሕዝብ ለኢትዮጵያ ቀጣይ ሁኔታ ጉዳዩን በሰላም መጨረስ የተሻለ ዕድል ይዞ ይመጣል የአሸናፊ ተሸናፊ ትርክት ቀርቶ የኢትዮጵዬ አሸናፊነት ይታወጃል ሁሉንም አሸናፊ የሚያደርግ የፖለቲካ ባህል ይገነባል በሚል ነበር።

ከሰሞኑም በራያ በኩል የጦርነት ትንኮሳ ሲደረግ የፌዴራል መንግስቱ መከላከያ ምላሽ ያልሰጠው መላሽ የሚሰጥ ከሆነ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ የሚሆን በመሆኑ አሁንም የጥሞና እና የሰላም ዕድል በተለይ ለትግራይ ሕዝብ የሰላም ፍላጎት ቦታ በመስጠት ነው። TPLF በሁሉም በኩል ላለው የፖለቲካ ኤሊት ከፍተኛ ንቀት ስላለውና ራሱን እንደብልጥ አዋቂ አድርጎ የሚያስብ ከመሆኑ አንፃር በመከፋፈል በተናጠል ቀስ ቀስ እያልኩ የፖለቲካ ወታደራዊ ድል አስመዘግባለሁ ብሎ የሚያደርገው ሙከራ የመጨረሻው ሊሆን ይችላል።
የሲዳማ ፌዴራሊስት ፓርቲን በተመለከተ ከቦርዱ የተሰጠ መግለጫ

የሲዳማ ፌዴራሊስት ፓርቲ ሊቀመንበር ከሀገር መውጣታቸውንና ፓርቲውንም የሚመራ ሰው መወከላቸውን ከውጭ ሀገር ሆነው ለቦርዱ ሲያሳውቁ ከፓርቲው አመራሮች መኃል ይህ በሊቀመንበሩ የተሰጠው የውክልና ሥልጣን ደንቡን የተፃረረ ነው የሚል ቅሬታ ለቦርዱ አቀረቡ፡፡ ቦርዱም ሊቀመንበሩ የሰጡት የውክልና ሥልጣን ከፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ አንፃር የተፈፀመ መሆን አለመሆኑን መረመረ፡፡ የፓርቲው መተዳደያ ደንብ አንቀጽ 22/1/ የፓርቲው ሊቀመንበር በማይኖሩበት ወቅት ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበሩ ሊቀመንበሩን ተክተው እንደሚሰሩ ደንግጓል፡፡ በዚሁ የፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ መሠረት ከሀገር በወጡት የፓርቲው ሊቀመንበር የተሰጠው ውክልና ደንቡን የተፃረረ በመሆኑ ቦርዱ ሳይቀበለው ቀርቷል፡፡ በመተዳደሪያ ደንቡ አንቀጽ 22/1/ መሠረትም እንዲፈፅም ወስኗል፡፡ ይሁንና በፓርቲው አመራሮች መኃል አለመግባባቱ እየጨመረ በመሄዱ በአዋጅ ቁጥር 1162/2011 አንቀጽ 74 (6) መሠረት ጉዳያቸው በባለሙያዎች ጉባኤ እንዲታይ ቦርዱ ወስኖ የባለሙያዎች ጉባኤ እያቋቋመ ይገኛል፡፡

ፓርቲው በ2015 በጀት ዓመት ከመንግሥት የሚሰጠውን ድጋፍ ከቦርዱ ብር 1,184,259.85 (አንድ ሚሊዮን አንድ መቶ ሰማንያ አራት ሺህ ሁለት መቶ ሃምሣ ዘጠኝ ብር ከሰማንያ አምስት ሣንቲም) ወስዷል፡፡ በአዋጅ ቁጥር 1162/2011 አንቀጽ 82/2/ መሠረት ፓርቲዎች ስለወሰዱት የመንግሥት ድጋፍ የኦዲት ሪፖርት የማቅረብ ግዴታ አለባቸው፡፡ ይሁንና የኦዲት ሪፖርቱን ፓርቲው ሳያቀርብ በመቅረቱ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ እንዲያቀርብ ሳያቀርብ ቢቀር ፓርቲው የመሰረዝ ዕጣ ፈንታ እንደሚገጥመው በማሳሰብ ቦርዱ ለፓርቲው አሳውቋል፡፡ ይሁንና ፓርቲው ይህንንም ሪፖርት እስከ ዛሬው ቀን ድረስ አላቀረበም፡፡

በአመራሮቹ መኃል ያለውን ልዩነት በፓርቲው ደንብና በአዋጅ 1162/2011 መሠረት ለመፍታት ጥረት እየተደረገ ባለበት ሁኔታ፤ እንዲሁም ከግብር ከፋዮች ተሰብስቦ ለፓርቲው የተሰጠውን የድጋፍ ገንዘብ እንዲያወራርድ በሕጉ መሠረት ፓርቲው ተጠይቆ እያለ፤ በተለያዩ ማኅበራዊና መደበኛ ሚዲያዎች ላይ በመቅረብ የተሳሳተ መረጃ በመስጠት የቦርዱን ጥረት እያንኳሰሱ ሥሙንም የማጥፋት ሥራ ጥቂት የፓርቲው አመራሮች እየሠሩ ይገኛሉ፡፡ በመሆኑም ቦርዱ ይህን መግለጫ ለመስጠት ተገዷል፡፡

እንደሚታወቀው ቅሬታ አለኝ የሚል ማንኛውም የፖለቲካ ፓርቲ፣ የፖለቲካ ፓርቲ አመራርም ሆነ የፖለቲካ ፓርቲ አባል በፓርቲው መተዳደሪያ ደንብና በምርጫ አዋጁ የተቀመጡ የቅሬታ አቀራረብ ሂደቶችን ተከትሎ ቅሬታውን ማቅረብ እንዲሁም ቦርዱም በሚሰጠው ውሣኔ ቅር የተሰኘ አካልም ጉዳዩን ለፍርድ ቤት ማቅረብ እንደሚችል በአዋጁ በግልፅ ተደንግጓል፡፡ በዚሁ መሠረትም ጉዳያቸውን ለከፍተኛ ፍርድ ቤት አቅርበው እየታየ ይገኛል፡፡

ጉዳዩ በፍርድ ቤት እየታየ እያለ ቦርዱም ለጉዳዩ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ ባለበት ሁኔታ የቦርዱን ስም በማይገባ እና በተሳሳተ መንገድ የተለያዩ ሚዲያዎችን በመጠቀም የሚካሄድን የስም ማጥፋት ተግባር ቦርዱ እንደማይቀበለው አጥብቆ እየገለፀ ይህ የስም ማጥፋት እና የተሳሳተ መረጃ የማሰራጨት ሂደት በፓርቲው ጥቂት አመራሮች የሚቀጥል ሆኖ ቢገኝ ቦርዱ ሕጋዊ እርምጃ ለመውሰድ የሚገደድ መሆኑን አጥብቆ ያሳስባል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

ሚያዝያ 24 ቀን 2ዐ16 ዓ.ም.
“ በየጊዜው ወጣቶች የምገብርበት የጦርነት ምዕራፍ መዘጋት አለበት “ - አቶ ጌታቸው ረዳ

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ በክልሉ ኮሚኒኬሽን ቢሮ በኩል ዛሬ መልዕክት አሰራጭተው ነበር።

በዚህም ፤ “ የህዝባችን ሁለንተናዊ መብትና ጥቅም ከማረጋገጥና አስተማማኝ ከማድረግ የሚቀድም ሌላ አጀንዳ የለንም “ ብለዋል።

“ የህዝባችን ጥቅምና መብት የሚያረጋግጥ መንገድ ሁሉ እንጓዘዋለን “ ያሉት አቶ ጌታቸው “ ጉዞው እንዲሳካ የህዝቡ ተሳትፎ ወሳኝ ነው “ ሲሉ አክለዋል።

ፕሬዜዳንቱ ፤ “ ከሚገባው በላይ ያበረከተ ህዝብ በቅንነትና ታማኝነት ማገለገል ይገባል “ ሲሉም ገልጸዋል።

“ ህዝቡ ከጦርነትና ጦርነት ወለድ ችግሮች በማላቀቅ ወደ አስተማማኝ ሰላም እንዲሸጋገር መስራት ይገባል “ ሲሉም አስገንዝበዋል።

አቶ ጌታቸው ረዳ ፤ “ በየጊዜው ትኩስ ሃይል የሆኑትን ወጣቶች የምንገብርበት የጦርነት ምዕራፍ ተዘግቶ ፤ የልማትና የእድገት ፍላጎታችን እንዲሳካ መስራት አለብን “ ብለዋል።
በአዲስ አበባ ቅርጫ ተከልክሏል የሚባለው ሃሰት ነው አልተከለከለም!

በአዲስ አበባ ከተማ በዘንድሮዉ ዓመት የሚከበረዉን የትንሳኤ በአል አስመልክቶ ህብረተሰቡ በየቤቱ በእርድ መልክ የሚጠቀመዉን እና በየአካባቢዉ የቁም እንስሳትን ቅርጫ በማረድ የሚከፋፈለዉን ተከልክሏል በሚል በማህበራዊ ሚዲያዉ ሀሰተኛ መረጃ እየተሰራጨ ይገኛል።

በመሆኑም ከዚህ ጋር በተያያዘ ምንም አይነት ክልከላ ያልተደረገ ሲሆን በየአካባቢዉ በህገ ወጥ መንገድ እርድ በመፈፀም ለሆቴሎች እና ለስጋ ቤቶች በማከፋፈል ተግባር ላይ የሚገኙ አካላት የቁም እንስሳቱ ጤንነት ባልተረጋገጠበት ሁኔታ የከተማዉን ነዋሪ ጤንነት ላይ ጉዳት የሚያደርስ በመሆኑ ጥብቅ ቁጥጥር ይደረጋል።

የከተማችን ነዋሪ በአላትን ሽፋን በማድረግ ጤንነቱ ያልተረጋገጠ እንስሳት አርዶ ማከፋፈል በጤና ላይ የሚያደርሰዉን ጉዳት ግምት ዉስጥ በማስገባት በህገወጥ እርድ የሚሰማሩ አካላት በሚደረገዉ ቁጥጥር ተባባሪ እንዲሆን መልክታችንን እናስተላልፋለን።
እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የትንሣኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! አደረሰን! በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የአብሮነት እና የመተሳሰብ እንዲሆን መልካም ምኞቴን እገልጻለሁ። ሃገራችንን ሰላም ያድርግልን!

መልካም የትንሣኤ በዓል!!
እስራኤል አልጀዚራን ዘጋች፤ ጣቢያው ድንገተኛ ብርበራ ተደርጎበታል!

እስራኤል የአልጀዚራ ቴሌቪዥን ጣቢያን ዘጋች። ጣቢያውን የዘጋችው ''የሐማስ አፈ ቀላጤ ሆኗል'' በሚል ክስ ነው።ጠቅላይ ሚኒስትር ናታንያሁ “የእስራኤል ካቢኔ ጣቢያው እንዲዘጋ ወስኗል” ብለዋል።

ይህን ተከትሎ ፖሊስ በጣቢያው ቢሮ ኢየሩሳሌም፣ አምባሳደር ሆቴል ድንገተኛ ወረራ በመፈጸም ብርበራ አድርጓል።እስራኤል “አልጀዚራ ለብሔራዊ ደኅንነቴ ሥጋት ነው” ማለቷን ጣቢያው፣ “ቀሽም ነገር ግን አደገኛ ዉሸት” ሲል አጣጥሎታል።ጣቢያው በሕግ መብቱን እንደሚያስከብር ዝቷል።

የእስራኤል የኮሚኒኬሽን ሚኒስትር ሽሎሞ ካርሂ በድንገተኛ ወረራው አንዳንድ ቁሳቁሶች ተወስደዋል ብለዋል።በዚሁ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤት የኤክስ ገጽ በተለጠፈ ተንቀሳቃሽ ምሥል ፖሊሶች ወደ ሆቴሉ ገብተው ሲበረብሩ ያሳያል።የቢቢሲ ጋዜጠኞች ወደ ሥፍራው አቅንተው የነበረ ቢሆንም ወደ ውስጥ እንዳይገቡ፣ ክስተቱንም እንዳይቀርጹ ተከልክለዋል።

ሮይተርስ እንደዘገበው የእስራኤል ሳተላይት አገልግሎት አልጀዚራ ይታይበት በነበረ ምሥል አሁን የጽሑፍ መልእክት ብቻ እየታየ ይገኛል፤ መልእክቱም “መንግሥት በወሰነው መሠረት በእስራኤል የአልጀዚራ ሥርጭት እንዲቆም ተደርጓል” የሚል ነው።አልጀዚራ በሳተላይት ይታገድ እንጂ አሁንም በእስራኤል በፌስቡክ እየታየ ነው።
ዛሬ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራ ቁጥር ET154 ከሀዋሳ ወደ አዲስ አበባ በመጓዝ ላይ እያለ በአውሮፕላን ውስጥ ጭስ ታይቷል።

ነገር ግን አውሮፕላኑ በአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፍያ በተመደበለት የመንገደኞች ማስተናገጃ በር ያለ ምንም እክል መቆሙን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አሳውቋል።

መንገዶኞቹም ከአውሮፕላን ላይ ደህንነታቸው እንደተጠበቀ መወርዳቸውን ገልጿል።

" በአሁኑ ሰአት የክስተቱ መንስኤ በመጣራት ላይ ይገኛል " ያለው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለተፈጠረው ክስተት ደንበኞቹን ይቅርታ ይጠይቋል።
የኢጋድ አባል ሀገራት የውሃ ሚኒስትሮች በጅጅጋ እየመከሩ ነው

የኢትዮጵያ የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶ/ር ሀብታሙ ኢተፋን ጨምሮ የኬኒያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ኡጋንዳና ጅቡቲ የውሃ ሚኒስትሮች ጂግጂጋ መግባታቸው ተገለጸ።

ሚኒስትሮቹ ጂግጂጋ የገቡት በቀጠናው ሀገራት መካከል የሚኖሩ ዜጎችን ታሳቢ ያደረገ ድንበር ተሻጋሪ የከርሰምድር ውሃ አጠቃቀም ላይ ለመምከር መሆኑ ተጠቁሟል። የቀጠናው ሀገራት የውሃ ሚኒስትሮች በተጨማሪ የዩኒሴፍ የአለም ባንክና ሌሎች አጋር ድርጅቶች በውይይቱ ላይ እየተሳተፉ እንደሚገኙ ተጠቁሟል።

ሚኒስትሮቹ ጅግጂጋ ሲደርሱ የሶማሌ ብሔራዊ ክልል ፕሬዝዳንት ሙስጠፌ መሀመድ በጅጅጋ ኤርፖርት በመገኘት አቀባበል እንዳደረጉላቸው ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

   
በስልጤ ዞን ኬራቴ ከተማ ለመዋኘት ወደ ወንዝ የወረደች የ8 አመት ታዳጊ ሰጥማ ህይወቷ ማለፉ ተነገረ

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ስልጤ ዞን ሁልበረግ ወረዳ ለመዋኘት ወደ ወንዝ የወረደች የ8 ዓመት ታዳጊ በዉሃ ሰጥማ ህይወቷ ማለፉ የወረዳዉ ፖሊስ ገልጿል።

የ8 ዓመቷ ታዳጊ ሚያዝያ 29 ቀን 2016 ዓ.ም 6:00 ሰዓት ግድም የሁልባረግ ወረዳ ዋና ከተማ ኬራቴን አቋርጦ በሚያልፈዉ የፉርፉሮ ወንዝ ላይ ለመዋኘት ከወረዱ ህፃናት መሀከል መስጠሟ ተነግሯል።

ሟች ህፃን ከወላጅ እናቷ ጋር ሆና ከምትኖርበት ሀዋሳ ከተማ በእንግድነት ወደ ሁልባረግ የመጣች ሲሆን አስከሬኗ በተሽከርካሪ ተጭኖ ወደ ሀዋሳ ተመልሷል። እንዲህ አይነቱ አሳዛኝ አደጋ ዳግመኛ እንዳያጋጥም ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ለህፃናት ተገቢዉ ጥበቃና ጥንቃቄ እንዲያደርግ ፖሊስ መልእክት አስተላልፏል።
" ከቅርብ ጊዜ ወዲህ #ጅቦቹ ሰው መተናኮስ ፤ በቀን መታየትና #ሰብሰብ ብሎ መሄድ ጀምረዋል " - ነዋሪዎች

" በኛ ቀበሌ ብቻ 3 ህጸናት በጅቦች ተበልተዋል። 2ቱ ሲሞቱ አንዷ ተርፋለች " - አቶ ማርቆስ ቡታ

ከሰሞኑን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ውስጥ የተራቡ ጅቦች እያደረሱ ስላለው ጥቃት የሚመለከቱ መረጃዎችን ማጋራታችን ይታወሳል።

በተለይ በስልጤ ዞን እና በሀላባ ዙሪያ በተፈጸሙ የጅብ ጥቃቶች ምክኒያት የሰው ህይወት መጥፋትና የአካል ጉዳት መድረሱን መግለጻችን አይዘነጋም።

በወቅቱ " የጅብ መንጋ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ  ተከስቷል " የሚለውን ዜና የሰሙ የሲዳማ ክልል፣ የሀዋሳ ከተማ ዙሪያ ነዋሪዎች " ችግሩ እኛም ጋር አለ እንዲያዉም ከህጻናት ባለፈ አዋቂዎችንም አሳስቦናል " በማለት መልዕክቶቻቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አድረሰዋል።

ጉዳዩን በተመለከተ የቲክቫህ ኢትዮጵያ የሀዋሳ አባል በሀዋሳ ዙሪያ ቡሽሎ ፣ ፊንጭ ውሀና ገመጦ... ወዘተ ቀበሌዎች ያሉ ማህበረሰቦችና የጸጥታ አካላትን አነጋግሯል።

የአካባቢው ነዋሪዎች በጊዜ ወደ ቤታቸው መግባት መጀመራቸውን በመጥቀስ ህጻናት ልጆቸውም ፍርሀት እንዳደረባቸዉ ገልጸዋል።

በተለያየ ጊዜ በ5 ሰዎች ላይ የጅብ ጥቃት ደርሶ እንደነበር እና 2 ህጻናት እንደሞቱ 1 ህጻን እንዲሁም 4 አዋቂዎች ደግሞ እንደተጎዱ አስረድተዋል። የሚመለከተው አካል አንዳች መፍትሄ እንዲሰጣቸውም ጠይቀዋል።

በአካባቢው ለረዥም ጊዜያት ጅቦች እንደነበሩ የሚገልጹት ነዋሪዎቹ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን ሰው መተናኮስ ፤ በቀን መታየትና #ሰብሰብ ብሎ መሄድ መጀመራቸው እንዳስገረማቸው ገልጸዋል።

ጉዳዩን በተመለከተ ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡት የቡሽሎ ቀበሌ ሰላምና ጸጥታ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ማርቆስ ቡታ ፤ " በእኛ ቀበሌ ብቻ 3 ህጻናት በጅቦች ተበልተዋል " ሲሉ ተናግረዋል።

2ቱ መሞታቸውን ፤ አንዷ ህጻን በወቅቱ በተደረገ ርብርብ ተርፋ በተደረገላት ህክምና መዳኗን ገልጸዋል።

በአጎራባች ቀበሌያት ውስጥ በ2 አዋቂ ሰዎች ላይ አሰቃቂ አደጋ ቢደርስም ለመትረፍ እንደቻሉ የጠቀሱት አቶ ማርቆስ ችግሩ አሳሳቢ በመሆን የጸጥታ አካላት እየተነጋገረበት ነው ብለዋል።

ማህበረሰቡ በጊዜ በመግባት የሚሰጠዉን የጥንቃቄ መልእክት በአግባቡ እንዲተገብርም ጠይቀዋል።
የፌዴራል ቤቶች ኮፖሬሽን የጽዱ ኢትዮጵያን ንቅናቄን በመቀላቀል የ 5 ሚሊየን ብር ድጋፍ አደረገ

ኮርፖሬሽኑ በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ይፋ ለሆነው የ“ጽዱ ጎዳና - ኑሮ በጤና” ንቅናቄ የ5 ሚሊየን ብር የገንዘብ ድጋፍ አድርጓል፡፡

የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ውብና ዘመናዊ ከተማ ለመፍጠር የሚደረገውን አገራዊ ጥረት የሚያግዙ በርካታ ሥራዎችን እያከናወነም ነው ፡፡

በሚገነባቸው ዘመናዊ ሕንጻዎችና የመኖሪያ መንደሮች ውበትን ፣ጥራትንና እና ዘመናዊነት ታሳቢ ያደረጉ ግንባታዎች እንዲሆኑ በማድረግ ላይ የሚገኝ ሲሆን በቀጣይ ለጽዱ ኢትዮጵያ ንቅንናቄ መሰል ድጋፎቹን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ኮርፖሬሽኑ አስታውቋል፡፡

የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በአምስት ዓመታት ውስጥ ብቻ ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት ታሳቢ በማድረግ ከግማሽ ቢሊየን ብር በላይ ድጋፍ አድጓል፡፡
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ጠሚ አቢይ አህመድ ዛሬ ወለጋ ነቀምት ሲደርሱ የተደረገላቸው አቀባበል
የሲዳማ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የ2016 ዓ.ም አጠቃላይ ክልላዊ የፖሊስ አመራርና አባላት የፍትህ ማሻሻያ (ትራንስፎርሜሽን) ግምገማ ተካሄደ።

በአጠቃላይ የግምገማው አፈፃፀም በተቀመጠለት የጊዜ ሰሌዳ የተከናወነ ሲሆን 12700 የሚሆን አመራር እና አባላት በግምገማው ሂደት አልፈዋል።

በዚህም በግምገማው 291 የሚሆኑ አመራሮች በከባድ ማስጠንቀቂያ ያለፉ ሲሆን 41 አመራር እና አባላት ላይ በብልሹ አሰራር በተጨማሪም ህዝብን የሚያማርር ተግባር በመፈፀማቸው በህግ እንዲጠየቁ እና ከስራ በማገድ እርምጃ ተወስዶባቸዋል።

የክልሉ ሰላምና  ፀጥታ ቢሮ ሀላፊ  አቶ አለማየሁ ጢሞቲዎስ  እንደገለፁት የፖሊስን ተቋም ለማዘመን በሚደረገው ርብርብ አባሉ በተሰማራበት የስራ ዘርፍ ቁርጠኛ ሆኖ ለማሳካት ርብርብ ሲያደርግ ጥቂት አመራርና አባላት እየተከናወነ ያለውን ስራ የሚያደናቅፉ የስነ-ምግባር ችግር የሚስተዋልባቸው  በመኖራቸው በየጊዜው በመከታተል  የእርምት እርምጃ በመውሰድ ማስተካከሉ ለተቋማዊ ለውጡ ወሳኝ ነው ብለዋል።

ሀላፊው አክለውም ፖሊስ ውድ የሆነውን ህይወቱን ሳይሳሳ ለሀገርና ህዝብ የሚሰጥ ይህ ሀይል በጥቂት አባላትና አመራር የሙያ ስነ-ምግባር ችግር ሊወቀስ ስለማይገባ በየጊዜው አባላቱ ያለበትን ቁመና በመገምገምና በመከታተል የዘመነና ብቃት ያለው አባልን ለመፍጠር በትኩረት ይሰራል ብለዋል።

የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ሽመልስ ቶማስ በበኩላቸው የቱሪስት መስህብ የሆነው ክልሉ ላስመዘገበው አስተማማኝ ሰላም ህብረተሰቡና የፀጥታ ተቋሙ እያከናወነ ያለው ቅንጅታዊ ስራ ነው ያሉት ኮሚሽነሩ ይህንን አጠናክሮ ለማስቀጠል አመራርና አባላቱ የተሰጣቸውን ሀላፊነት በብቃት መወጣት ይኖርባቸዋል ብለዋል።

ከምን ግዜውም በተሻለ ህብረተሰቡ ለፖሊስ አለኝታነቱን በተግባር እያሳየ ባለበት በዚህ ጊዜ አንዳንድ አመራርና አባላት ከሙያዊ ስነ-ምግባር ባፈነገጠ የተቋሙን ስም የሚያጠለሹ መኖራቸው በግምገማው የተለየ በመሆኑ እነዚህን አመራርና አባላት አስተማሪ እርምጃ በመውሰድ ለተቋማዊ  ስኬት ይሰራል ብለዋል።
የቱሪዝም ሚንስትር አምባሳደር ናሲሴ ጫሊ ለህዝብ ተወካዮች ምክርቤት የንግድና ቱሪዝም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ባቀረቡት የ9ወራት አፈፃፀም ሪፓርት ላይ ያነሷቸው ነጥቦች

•የቱሪዝም መረጃ አያያዝን ለማዘመን የሚያስችል tourism satellite account(TSA) ስርአትን ወደ ስራ ለማስገባት ዝግጅት እየተደረገ ነው::

•የኮንሶ አለም አቀፍ ቅርስን ጨምሮ የ8 ቅርሶች ጥገና ስራ እየተከናወነ ነው::

•ኢትዮጵያ በዩኔስኮ የጌዲኦ መልካምድር እና የባሌ ተራሮችን በሚዳሰስ ቅርስነት በሀረሪ ክልል የሚከበረውን ሸዋል ኢድ ደግሞ በማይዳሰስ ወካይ ቅርስነት ከ 40 አመት በህላ ለመጀመሪያ ጊዜ በአንድ አመት ውስጥ ብቻ ሶስት ቅርሶቿን ማስመዝገብ የቻለችበት አመት መሆኑን::

•የሚንስቴር መስሪያ ቤቱን የስራ አካባቢ ምቹ በማድረግ እና የሰው ሀብት ልማት ላይ ውጤታማ ስራዎች ተከናውነዋል::

•የድሬ ሼክ ሁሴን መካነ ቅርስ ዙሪያ የሚስተዋሉ መሰረታዊ የቱሪስት አገልግሎቶች ጉድለቶችን ለመሙላት ፕሮጀክት ተቀርፆ ለትግበራ ዝግጁ ተደርጓል።

•በነጭ ሳር ብሄራዊ ፓርክ የኬብል ካር እና ቱሪስት አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል ፕሮጀክት ጥናት፣ የዲዛይን ስራ ማጠናቀቅ ተችላል፡፡

•የጂማ አባጂፋር ቤተመንግስት እድሳት ተጠናቆ በሚቀጥለው አመት መጀመሪያ ለአገልግሎት ክፍት ይደረጋል::

•ከፈረንሳይ መንግስት ጋር በመተባበር በላሊበላ ከተማ በዋናነት ቱሪስቶች በከተማዉና አካባቢዉ የሚገኙ ቅርሶችን ከመጎብኘት ባሻገር ያለዉን ዕምቅ የባህል ሀብት በአንድ ስፍራ መጎብኘት የሚችሉበት ደረጃዉን የጠበቀ የባህል/ቱሪዝም ማዕከል ግንባታ በመጠናቀቅ ላይ ነዉ፡፡

•በአፋር ክልል በኤርታኢሌ የእሳተ ጎመራ ድንቅ የተፈጥሮ ትዕይንት መመልከቻ ቦታ ላይ ለጎብኝዎች መወጣጫ የሚሆን ደረጃዎች ግንባታ ለማስጀመር የቅድመ ዝግጅት ስራዎች በመከናዎን ላይ ናቸዉ፡፡

•በተለያዩ የቱሪዝም ኢንቨስትመንት ዘርፎች 75 የሀገር ውስጥ እና 16 የውጭ ባለሃብቶች ሴክተሩን ተቀላቅለዋል፡፡

•ከዘርፉ በ9ወራት የሚገኘውን የውጪ ምንዛሪ ገቢ3.5 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቅዶ 3.2 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ማግኘት ተችሏል፡፡

•በዘርፉ ባለፉት 9ወራት 81,673 የስራ እድሎች ተፈጥረዋል፡፡ ከዚህ መካከል 30,968 ቋሚ የስራ እድሎች ሲሆኑ 50,705 ደግሞ ግዚያዊ ናቸው::