ፒያሳ መሃሙድ ጋ ጠብቂኝ
183K subscribers
279 photos
1 video
16 files
200 links
እዚህ Channel ላይ ያስተምራሉ ያዝናናሉ ብለን የምናስባቸውን
🎯ተከታታይ ልቦለድ
🎯ግጥም
🎯ወግ
🎯ፍልስፍና
🎯ምክር
🎯መነባንብ

#ማንኛውም አይነት ፅሁፎች📕 ከፈለጉ ይቀላቀሉን
የተለያዩ PDF መፅሐፍት ከፈለጉ @Eyosibooks
አስተያየት ካሎት👇👇
☎️• 0922788490

📩@Eyos18
Download Telegram
😎ጠላፊዎቹ

#ክፍል_አርባ_አንድ

#በኬንፎሌት

#ትርጉም_ወንዳየሁ_ንጉሴ


hቦትውድ ወደ ሼዲያክ

ኤዲ ዲኪን የበረራ ባልደረቦቹ ወደ ጀልባው ሲገቡ ሲያይ ሊፈጽመው
ያሰበው ክህደት በዓይነ ህሊናው ድቅን አለበት፡ መቼም ሊያደርግ ያሰበውን
ቢያውቁ ዓይንህን ላፈር እንደሚሉት ምንም ጥርጥር የለውም፡፡ ነዳጁ ባዶ መሆኑን እያወቀ አይሮፕላኑ ባህር ውስጥ ገብቶ ሁሉም እንዲያልቅ ሊያደርግ እንደነበር ያወቁበት መሰለው፡፡

የነዳጅ መጠኑን መቆጣጠር የበረራ መሀንዲሱ ስራ ነው፡፡ ስለዚህ ሰው በዚህ ምክንያት ቢያልቅ ተጠያቂ እሱ ነው፡፡

ሰሞኑን ያሳይ የነበረውን እንግዳ ባህሪ ቢያውቁ ምን ይላሉ? እነሱ በማያውቁት ነገር አዕምሮው ተወጥሮ ቆይቷል፡፡ ትናንት ማታ ራት ላይ ቶም ሉተርን ሲያስፈራራው ነው ያመሸው፡፡ የወንዶች መፀዳጃ ቤት ውስጥ
መስኮት ሲሰበር እሱ
እዚያው ነበር፡፡ ስለዚህ ኤዲን ቢጠረጥሩ
አይፈረድባቸውም፡፡ እንዲህ አይነት ነገር ቢታወቅ ወሬው በአንድ ጊዜ ነው
አይሮፕላኑ ውስጥ የሚዛመተው፡፡

የስራ ባልደረቦቹ በእሱ ላይ ከእንግዲህ እምነት ሊጥሉ እንደማይችሉ ማወቁ በራሱ የኮሶ መድኃኒት እንደመዋጥ ነው የሆነበት፡፡ ከሁሉም
የአይሮፕላኑ ሰራተኞች አቋመ ጽኑ መሆኑ ያኮራው ነበር፡ የሌሎችን ስህተት በቀላሉ ማለፍ ስለማይችል አንዳንዴ ሰዎች በግል ችግራቸው ምክንያት ግዴታቸውን መወጣት ሲያቅታቸው የሚሳደብበት ጊዜ አለ፡፡በይቅርታ ሊታለፍ አይችልም ይላቸዋል ስህተት ሲፈጽሙ ከተገኙ፡፡ አሁን ግን እሱ ራሱ የሚታመን ሰው አልሆነም፡፡

አሁን ለእንደዚህ አይነት ጉዳይ የሚጨነቅበት ጊዜ አይደለም፡፡ ሚስቱን
ለማዳን የማይፈነቅለው ድንጋይ የማይምሰው ጉድጓድ የለም፡፡ ስለዚህ
ሚስጥሩን በሆዱ ይዞ ለብቻው ሊፈጽም ቆርጦ ተነስቷል፡ ስለሌሎች ስሜት
አሁን መጨነቅ የለበትም፡፡ ሆነም ቀረ ህይወታቸውን አንዴ አደጋ ላይ ጥሏል፡፡ ውጤቱም እንዳሰበው ሊሆን ነው፡ አቋመ ጽኑው መሀንዲሱ ዲኪን
ወደማይታመነው ዲኪን መቀየሩ ነው፡፡

በርካታ ተሳፋሪዎች ትንሽ እንቅልፍ ብናገኝ ብለው አይሮፕላኑ ውስጥ
ቀርተዋል፡ የኤፍ.ቢ.አዩ ኦሊስ  ፊልድና  እስረኛው ፍራንክ ጎርዲኖም ከአይሮፕላኑ አልወረዱም፡፡ ቶም ሉተር ባለጸጉራም ጃኬቱን ለብሶና ቆቡን አናቱ ላይ ደፍቶ ጀልባው ላይ። ወጣ፡፡ ኤዲም ከኋላው መጣና ጠጋ ብሎ
‹‹የአየር መንገዱ ህንጻ ጋ ሂድና ስልኩ ያለበት ቦታ እወስድሃለሁ›› አለው፡

ቦትውድ ከእንጨት የተሰሩ ቤቶች የተገጠገጡባት ትንሽ ከተማ ስትሆን
የአይሮፕላኑ ተሳፋሪዎች በየሱቁ ብዙም የሚገዛ ነገር አላገኙም፡፡ መንደሪቱ
የስልክ አገልግሎት አላት፡፡ ኒውፋውንድ ላንድ አሁንም በእንግሊዝ ቅኝ ግዛት ስር ስለሆነች መኪኖች የሚሄዱት ግራቸውን ይዘው ነው፡፡

ተሳፋሪዎቹ ወደ ፓን አሜሪካ አየር መንገድ ህንጻ ሄዱ፡፡ ኤዲ ከቦትውድ ሰላሳ ስምንት ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኝ አየር ማረፊያ ላይ ካረፈ አይሮፕላን በሬዲዮ የተላከ የአየር ጠባይ መረጃ አነበበ፡፡ ከዚያም ለሚቀጥለው ጉዞ የሚያስፈልገውን የነዳጅ መጠን ስሌት ሰራ፡
ሲሰራ አፉን ደም ደም አለው፡፡ ከዚህ በኋላ የበረራ መሀንዲስ አይሆንም።

ካፒቴኑ የኤዲን የነዳጅ ፍላጎት መጠን ስሌት አምኖ መቀበል ይኖርበታል፡፡ የሰራው ስራ እንዲታመንለት ስሌቱን ሁለት ጊዜ ቼክ አደረገና
‹‹ሌላ ሰው ቢያጣራው እወድ ነበር›› ብሎ ለካፒቴኑ ሰጠው።

‹‹ችግር የለውም›› አለ ካፒቴኑ ለነገሩ ትኩረት ባለመስጠት፡ ‹‹እስቲ
ተናፍሼ ልምጣ›› አለና ወጥቶ ሄደ፡ ኤዲም ካፒቴኑን ተከትሎ ወጣና ቶም ሉተርን ፓን አሜሪካን ህንጻ አጠገብ ሁለት እጁን ኪሱ ከቶ አገኘው፡፡ ‹‹ወደ ስልኩ እንሂድና ከጓደኞችህ
ጋር እንድትነጋገር አድርጌ ቶሎ ወደ ስራዬ እመለሳለሁ›› አለው፡ ሉተር
በመጀመሪያ ጎተት እያለ ነበር የሚሄደው፡፡ በኋላ ግን የትናንት ማታውን
ግብግብ አስታወሰና ቶሎ ቶሎ መራመድ ጀመረ፡፡ ኤዲን እንደገና ማናደዱ
ትርፉ ራስን መጉዳት መሆኑን ተረድቷል፡፡
በመንገዳቸው ላይ መርቪንና ናንሲን አገኙና የአንገት ሰላምታ
ሰጥተዋቸው አለፉ፡፡ ሁለቱም አንድ ላይ በመሆናቸው የተደሰቱ ይመስላሉ፡ሰዎች እሱና ካሮል አን አንድ ላይ ሲሆኑ እንደሚያስቀኑ ይነግሩት ነበር፡ እሷን ሲያስታውስ ብስጭቱ እንደገና ተቀሰቀሰበት፡፡

ስልክ ቤት ገቡና ሉተር የስልክ ቁጥሩን በብጣሽ ወረቀት ጽፎ ለስልከኛው ሰጠው:፡ ኤዲ የሚናገረውን እንዲሰማ አልፈለገም፡፡ ኦፕሬተሩ እስኪያገናኛቸው ድረስ የስልክ መደወያው ክፍል ውስጥ ገብተው ጠበቁ ማለዳ በመሆኑ ብዙ ስልክ ደዋይ የለም፡፡

ኤዲ ካሮል አንን  አይሮፕላኑን የሚያሳርፍበት ቦታ ድረስ ይዘዋት እንዲመጡ ሉተር  እንደሚነግራቸው ገምቷል።
ካሮል አንን በእጁ ካስገባ
በኋላ ደግሞ ሌላ ያሰበውን ነገር ለመስራት ነጻነት ያገኛል ነገር ግን ምን
ሊያደርግ ነው ያሰበው? ወዲያው ለፖሊስ ማሳወቅ? ሉተር ከጠረጠረ ድረስ ደግሞ ዝም ብሎ መጠበቅ የግድ ነው፡፡ ታዲያ በዚህ ጊዜ ውስጥ የሬዲዮ መገናኛውን ከመስበር አይመለስም፡፡ የፖሊስ እርዳታ እስኪደርስ
ጎርዲኖና ሉተር ከአይሮፕላኑ ወጥተው በመኪና ያመልጡና አንዱ ጋ
ይሸጎጣሉ፡፡ ካናዳ ይግቡ አሜሪካ ማንም የሚያውቅ አይኖርም፡፡ ኤዲ
እንዳያመልጡ አስቀድሞ ለፖሊስ ቢነግር ደግሞ ከፖሊሶች ጋር ሲታኮሱ
የካሮል አን ህይወት አደጋ ላይ ይወድቃል፡፡ ኤዲ እንዲህ እንዲሆን
አይፈልግም::

ስልኩ ሲጮህ ሉተር አነሳና ‹‹እኔ ነኝ የዕቅድ ለውጥ መኖሩን ልነግራችሁ የደወልኩት፡፡ ሴትየዋን በጀልባ አይሮፕላኑ ድረስ ካላመጣችሁ የምትፈልጉትን አልፈጽምም ብሏል ሰውየው፡፡ እኔ በበኩሌ ያለውን አምኜ
ተቀብያለሁ፡ ስለዚህ ይዛችኋት እንድትመጡ›› አለና መልሳቸውን ጠበቀ፡፡
ከዚያም ‹‹ሊያናግሩህ ይፈልጋሉ›› አለው ኤዲን፡፡

ሉተር በመጀመሪያ ትዕዛዝ ሲሰጠው ልክ የወሮበሎቹ መሪ መስሎ ነበር የሚታየው፡፡ ካነጋገሩ ግን ካሮል አንን ወደ መገናኛቸው ቦታ እንዲያመጣለት
ለማዘዝ ስልጣን የሌለው ሆኖ ታየው፡፡

‹‹ሊያናግረኝ የሚፈልገው አለቃችሁ ነው?››

‹‹እኔ ነኝ አለቃ›› አለ ሉተር እየከበደው ‹‹ነገር ግን ግብረ አበሮች አሉኝ››

የሉተር ግብረ አበሮች  ካሮል አንን ቦታው ድረስ ማምጣት እንደማይፈልጉ ይታወቃል፡፡ ከእነሱ ጋር መነጋገሩ የሚፈይድለት ነገር አለ? የለም፡፡ ካሮል አንን ስልኩጋ ያመጡና አስለቅሰው የመንፈስ ጽናቱን ይፈታተኑታል፡፡ ‹‹ስትፈልጉ ገደል ግቡ  በላቸው›› አለ  ጮክ ብሎ
እንዲሰሙት፡፡

ሉተር የኤዲ አነጋገር አስደንግጦት እነዚህን ሰዎች እንዲህ ልትናገራቸው አትችልም›› አለ እሱም ጮክ ብሎ፡፡

ሉተር የወሮበሎቹ መሪ ከሆነ ምን አስፈራው? አሁን የሉተርን ስልጣን መገምገም አይረባውም፡፡ ዕቅዱን ማሳካት ነው ያለበት፡፡ ሉተርም ‹‹ወይ አናግራቸዋለሁ ወይም አላናግራቸውም በል›› አለው ኤዲን፡፡

ላናግራቸው እንደማልፈልግ ንገራቸው ለእነዚህ ድንጋይ ራሶች አለው።

አይ አምላኬ አለና ሉተር የስልኩን እጀታ አንስቶ ‹‹አላናግራችሁም
ብሏል፡፡ ሰውየው አስቸጋሪ ነው:›› ንግግሩን ቆም አደረገና ‹‹ጥሩ ሃሳብ ነው እነግረዋለሁ››ብሎ የስልኩን እጀታ እንደያዘ
‹‹ሚስትህ ቀርባለች
ታናግራታለህ?›› አለው ኤዲን፡፡

ኤዲ ስልኩን ሊቀበል እጁን ዘረጋና መልሶ ተወው፡፡ ከእሷ ጋር ከተነጋገረ ምህረት ጠያቂ ሊሆን ነው ነገር ግን ድምጿን ቢሰማ አይጠላም እንደማያነጋግራት በራስ ንቅናቄ ለሉተር አመለከተው፡፡

ሉተር ኤዲ ላይ አፈጠጠና ‹‹አላናግርሽም ብሏል ባልሽ፡፡ ዞር በይ አንቺ
ሸርሙጣ!›› አላት ካሮል አንን፡፡
😎ጠላፊዎቹ

#ክፍል_አርባ_ሁለት

#በኬንፎሌት

#ትርጉም_ወንዳየሁ_ንጉሴ


ማርጋሬት ከእንቅልፏ  ስትነቃ ሃሳብ ውስጥ ገባች፡: ዛሬ ለአባቴ ቁርጡን እነግረዋለሁ  አለች በሆዷ አሜሪካ ሲደርሱ ከእነሱ ጋር
እንደማትኖር ከቤት ወጥታ ቤት ተከራይታ እና ስራ ይዛ ልትኖር እንደሆነ
ትነግራቸዋለች፡፡ መቼም አባቷ ይህን ሲሰሙ ኮረንቲ ይጨብጣሉ፡፡

ማርጋሬት ነገሩን ባሰበችው ቁጥር ፍርሃትና ሃፍረት ይሰማታል አባቷን ለመቃወም ስትነሳ የሚሰማት ይኸው ነው፡፡ አሁን አስራ ዘጠኝ ዓመቴ ነው፡፡ አሁን ልጅ አይደለሁም፡፡ ትናንት ከድንቅ ሰው ጋር ወሲብ
ፈጽሜያለሁ፡፡ ታዲያ ለምንድነው የምፈራው? ስትል ታስባለች፡

ለምን አባቷ ሁልጊዜ እንደ አውሬ በግርግም ውስጥ እንደሚዘጉባት አይገባትም፡ ኤልሳቤትንም እንዲሁ ነበር የሚያደርጓት፡፡ ፔርሱን ግን ለቀቅ አድርገውታል፡፡ ሴት ልጆቻቸውን እንደ ጌጣጌጥ ነው የሚቆጥሯቸው: አንድ
የሆነ ስራ እንስራ ብለው የተነሱ እንደሆን ቁጣቸው ለጉድ ነው፡፡ ለምሳሌ
ዋና እንዋኝ ወይም ብስክሌት እንንዳ ብለው ቢነሱ በቃ አለቀላቸው፡
ልብስ የፈለጉትን ያህል ቢያወጡ ምንም የማይሉትን ያህል መጽሐፍ
እንግዛ ቢሉ ጸጉራቸው ይቆማል፡

ማርጋሬት ይህን ባሰበች ቁጥር ሽንፈቷ አይደለም የሚያሳምማት፡፡አባቷ የእሷን ሀሳብ ውድቅ ለማድረግ የሚያወርዱባት የስድብ ውርጅብኝና
የፌዝ ጋጋታ እንጂ፡

ብዙ ጊዜ አባቷን ለማታለል ሞክራለች፡ የተሳካላት ግን ጥቂት ጊዜ ብቻ ነው፡፡

ሁልጊዜም ከአባቷ ትዕዛዝ ውጭ የምትፈጽመው በሌሎች እርዳታ
ነው:: ስለወሲብ ያስተማረቻት ዘመዷ ሞኒካ ናት፡፡ ፔርሲ ተኩስ አስተምሯታል፡፡ ሹፌራቸው መኪና መንዳት አስለምዷታል አሁን ደግሞ
ሄሪና ናንሲ ሌኔሃን ነጻነቷን እንድትቀዳጅ ይረዷት ይሆናል።

አሁን ለየት ያለ ስሜት እየተሰማት ነው፡፡ መኝታዋ ላይ ተጋድማ መላ አካላቷን ደባበሰችው፡፡ ከዚህ ቀደም ጸጉሯ የተንጨፈረረ ቅርጿ ደግሞ የማያምር አድርጋ ትገምት ነበር፡፡ አሁን ግን ገላዋን እየወደደችው
መጥታለች፡ ሄሪ ‹‹ቅርጽሽ ያምራል›› ብሏታል
አይሮፕላኑ ውስጥ የሰዎች ሹክሹክታና የዕቃ ኳኳታ ይሰማታል ተጓዦች ከመኝታቸው እየተነሱ ነው መጋረጃውን ገለጥ አድርጋ ስታይ ዱባው አስተናጋጅ ኒኪ የእናትና የአባቷን መኝታዎች ወደ መቀመጫነት እየቀየረ ነው፡፡ ሄሪ ሙሉ ልብሱን ለብሶ ቁጭ ብሎ በተመስጦ በመስኮት ወደ ውጭ ይመለከታል፡፡
እሱን ስታይ አፈረችና ሳያያት ወዲያው መጋረጃውን ዘጋችው::ከጥቂት ሰዓት በፊት በወሲብ ሲያብዱ ቢቆዩም አሁን ግን ሁኔታው
አሳፈራት።

ሌሎቹ ሰዎች የት ሄደው ይሆን?› ስትል አሰበች፡፡ ፔርሲና አባቷ ውጭ ወጥተው ይሆናል፡ አባቷ ለወትሮው በጧት ነው የሚነሱት፡ እናቷ
ግን በጧት መነሳት አይሆንላቸውም፡፡ ምናልባትም መታጠቢያ ቤት ይሆናሉ፡ ሚስተር መምበሪም በቦታው የለም፡፡

ማርጋሬት በመስኮት ስትመለከት ነግቷል፡፡ የሰማይ በራሪው አይሮፕላን
አንድ ትንሽ የወደብ ከተማ ዳርቻ ላይ ታስሮ ቆሟል፡ እንደገና መኝታዋ ላይ
ጋደም አለች፡፡ የለሊቱ ሁኔታ በዓይነ ህሊናዋ ድቅን አለ፡፡ የትናንቱ ቀን ድንግልናዋ የተወሰደበት ቀን አድርጋ ነው የቆጠረችው፡፡ ከኢያን  ጋር ስትፈጽም የነበረው ወሲብ ችግር ያልተለየውና ጥድፍ ጥድፍ ያለ ነበር፡
ከእሱ ጋር ወሲብ ከፈጸመች በኋላ ሁልጊዜ በእፍረት ትሸማቀቃለች፡ትናንት ከሄሪ ጋር ያደረገችው ግን አስደስቷታል፡፡ እያንዳንዱ የስውነት ክፍሏ እየተቆጠረና እየተዳበሰ የተፈጸመ ወሲብ ነበር፡፡ ምንም እፍረት ያልነበረበት፡፡ እንደ ሴት ራሷን የቆጠረችበት ወቅት ነበር፡፡ እንዲህ አይነት ወሲብ ከሄሪ ጋር በተደጋጋሚ መፈጸም አለብኝ አለች ለራሷ፡ የትናንት ማታው ትዝታ የወሲብ ፍላጎቷን ቀሰቀሰባትና ሰውነቷን አወራጨች።

ሄሪ የክት ልብሱን ለብሶ መስኮቱ ጋ ተቀምጦ በተመስጦ ሲያይ ሰርቃ
አየችው:፡ የሆነ ነገር እያሰላሰለ መሆኑን መልከ መልካም ፊቱ ነገራት::
ልትስመው ዳዳት፡፡ መጋረጃውን ገለጥ አደረገችና ‹‹እንደምን አደርክ ሄሪ አለችው፡፡

ድንገት የሰማው ድምጽ ሲሰርቅ እንደተያዘ ሰው አስደነገጠውና ደንብሮ
ዞር አለ፡፡ ሲያያት አየችውና ፈገግታ ተለዋወጡ፡፡ እንደ ጅል ለረጅም ጊዜ ሲሳሳቁ ቆዩ፡፡ በኋላም ማርጋሬት አይኗን ሰበረችና ተነሳች።

አስተናጋጁ የእናቷን መቀመጫ ከሚያዘጋጅበት ቀና ብሎ ‹‹ደህና አደርሽ እመቤት ማርጋሬት ቡና ላምጣልሽ?›› አላት፡

‹‹ኒኪ ይቅርብኝ አመሰግናለሁ›› አለችው ሁኔታ እንደ ጭራቅ ለራሷ
አስፈራት፡፡ ጸጉሯ ተንጨፍርሯል፡፡ ልብስም በቅጡ አልለበሰችም፡፡ ሄሪ ግን ጢሙን ተላጭቶና ዘንጦ አዲስ ሳንቲም መስሏል

ብትስመው በወደደች፡፡

ነጠላ ጫማዋን እግሯ ላይ ሰካች፤ ሌሊት ለወሲብ ስትቻኮል ሄሪ አልጋ
ስር እንዴት እንደተወችውና አባቷ ሳያይዋት እንዴት አድርጋ አንስታ አልጋው ውስጥ እንደከተተችው እየታወሳት፡፡

የሌሊት ልብሷን ስትለብስ እርቃኗን ስለነበረች ሄሪ ጡቶቿ ላይ ዓይኑን
ተከለ፡፡ ቢያያትም ምንም አልመሰላትም፡፡ ሄሪ ጡቷን ሲያይ ደስ አላት፡ የሌሊት ልብሷን መቀነት ጠበቅ አደረገችና ጸጉሯን አሻሸች፡፡
ኒክ ስራውን ጨረሰ፡፡ ሄሪን መሳም ስለፈለገች ኒኪ ከዚያ ቦታ ቶሎ እንዲ ሄድላት ፈለገች፡፡ ኒኪ ግን የልቧን ፍላጎት ስላላወቀ መቀመጫውን ላዘጋጅልሽ?›› አላት

እሺ›› አለች ውስጧ በንዴት እየጨሰ፡፡ ሄሪን ድጋሚ የምትስምበት ጊዜ እንደሰማይ ራቃት፡፡ የመታጠቢያ ዕቃዎቿን የያዘችበትን ቦርሳዋን
አነሳችና ሄሪ በሀዘኔታ እያያት ተነስታ ሄደች፡፡

ሌላው አስተናጋጅ ዴቪ መብል ክፍሉ ውስጥ ምግብ እየደረደረ ነው፡፡
እግረ መንገዷን አንድ የእንጆሪ ፍሬ ሰርቃ አፏ ላይ አደረገች፡ ስትሄድ
ብዙዎቹ መኝታዎች
ወደ መቀመጫነት ተለውጠዋል አንዳንዶቹ
ተሳፋሪዎች ቡና እየጠጡ ነው፡ ሚስተር መምበሪ ከሳይንቲስቱና ከባሮን
ጋቦን ጋር ወሬ ይዟል፡፡

መታጠቢያ ክፍሉ ውስጥ ስትገባ እናቷ መስታወት ፊት ቁጭ ብለው ይዋባሉ፡፡ እሳቸውን ስታይ እፍረት ተሰማት፡ ‹እናቴ ካለችበት አንድ ሁለት ርምጃ ርቀት ላይ እንዴት እንዲህ ያለ ነገር አደርጋለሁ? አለች በሆዷ፡
ጉንጮቿ በእፍረት በርበሬ መስለዋል፡፡ ‹‹እንዴት አደርሽ እማማ›› አለች

‹‹ምን ሆነሽ ነው ፊትሽ እንደዚህ የቀላው? እንቅልፍ አልተኛሽም እንዴ?›› ሲሉ ጠየቋት፡፡

‹‹ኧረ በደምብ ተኝቻለሁ›› አለች ማርጋሬት፡፡ ‹‹አንዲት ፍሬ እንጆሪ ከጠረጴዛ ላይ አንስቼ ስለበላሁ ነው›› አለችና መጸዳጃ ቤት ጥልቅ አለች ከዚያም መታጠቢያው ላይ ውሃ ሞላችና ፊቷን ታጠበች፡:

ትናንት የለበሰችውን ልብስ ዛሬም በመልበሷ ደስ አላላትም፡፡ የታጠበ
ልብስ ብትለውጥ በወደደች: አንገቷ ስርና ጡቶቿ ውስጥ ሽቶ
አርከፈከፈች፡፡ ሽቶ ለይቶ የሚያውቅ ያየችው ወንድ ሄሪን ብቻ ነው፡፡

ረጅም ጊዜ ፈጅታ ጸጉሯን አበጠረች፡፡ ያላት ውበቷ ጸጉሯ ስለሆነ ለጸጉሯ የማትሆነው የለም፡፡ መልኬን ለማሳመር ስል ማድረግ ያለብኝ ሁሉ
አደርጋለሁ አለች ለራሷ፡ እስካሁን ስለመልኳ ተጨንቃ አታውቅም፡፡ ዛሬ ግን አስተሳሰቧ ተለውጧል፡፡ ገላዬን ልቅም አድርጎ የሚያሳይና ረጅም ታኮ
ጫማ ያስፈልገኛል፡፡ ከገላዬና ከጸጉሬ ከለር ጋር የሚሄድ ልብስ መምረጥ
አለብኝ፡፡› አሁን የለበሰችው ልብስ እንደ ሽክላ ቀይ ነው፡፡ እንዲያው ዝም ብሎ የወረደና ቅርጸ ቢስ መሆኑን በመስታወት አይታ ትከሻውጋ ቀጥ ያለና
ወገቡ ጋ በመቀነት ሸብ የሚደረግ ቢሆን ጥሩ ነበር ስትል ተመኘች።ሜክአፕ ባትቀባባም ያላት መልክ በቂ ነው፡ ጥርሶቿም አያሳጡም፡፡

‹‹ከሚስተር ቫንዴርፖስት ጋር ለመጫወት ልትሄጂ ነው አይደለም?››
አሉ እናት፡፡
😎ጠላፊዎቹ

#ክፍል_አርባ_ሦስት

#በኬንፎሌት

#ትርጉም_ወንዳየሁ_ንጉሴ


ዳያና ላቭሴይ እውነተኛ ፍቅር በአጭር ጊዜ እንደማይለቅ በሃዘን
አስታወሰች፡፡ መርቪን በፍቅሯ የተነደፈ ጊዜ የጠየቀችውን ነገር ሁሉ
በፍጥነት ለማድረግ ደስተኛ ነበር፡፡ አንድ ነገር ከፈለገች በመኪና በመሄድ ያመጣላት ነበር፡፡ ሲኒማ አምሮኛል ካለች ከስራውም ቀርቶም ቢሆን ይዟት ይገባ ነበር፡፡ ከባሰም ለጉብኝት ፓሪስ ይወስዳት ነበር፡ የፈለገችው ሻርፕ እስኪገኝ ድረስ በማንቼስተር ሱቆች እግሩ እስኪቀጥን እየዞረ ሲያስስ ቢውል አይደክመውም፡፡ ቴአትር ቤት ገብተው በመሃል ደበረኝ ካለችው ሳይጨርሱ ቢወጡ ቅር አይለውም፡፡ ታዲያ ይሄ ታዛዥነት ከተጋቡ በኋላ ቀስ በቀስእንደ ጉም በኖ ጠፋ፡፡ ከዚያ በኋላ የጠየቀችውን ባይነሳትም ያደርግ የነበረው
ግን በዳተኝነት ነበር፡፡ ግድ የለም ልታገስ ብሎ እንጂ እንደ በፊቱ በፍቅር
ማድረጉን እየተወ መጣ፡፡ በመጨረሻ እንደውም ትዕግስት እያጣ ሲመጣ
ሚስቱን ጭራሹን ‹‹ዞር በይ›› ማለት አመጣ፡፡
ታዲያ ማርክም እንዲህ ሊያደርገኝ ይችላል የሚል ፍርሃት አጫረባት፡

ማርክ እንግሊዝ አገር በቆየበት ጊዜ ባሪያዋ ሆኖ ነው የስነበተው
በጠፉ በሁለተኛው ቀን ተጣልተው መኝታ ለይተውነበር፡ ሆኖም እኩለ
ሌሊት ላይ እውጭ ያለው ንፋስ የቀላቀለ ዝናብ አይሮፕላኑን እንዳልተገራ
ፈረስ ሲያሰግረው ዳያና በጣም ፈራችና ዓይኗን በጨው አጥባና ክብሯን ሽጣ ወደ ማርክ መኝታ ሄደች፡፡ እንደዚያም ሆኖ ውጤቱ አላማረም፡፡ በኋላ ወደ እኔ ይመጣል ብላ ብትጠብቅም እሱም ኩራት ልቡን ነፍቶት ሳይመጣ
በመቅረቱ በንዴት ኤሌክትሪክ ልትጨብጥ ምንም አልቀራትም:

ዛሬ ጧት ምንም አልተነጋገሩም ማለት ይቻላል፡፡ ጧት ከእንቅልፏ
የነቃችው አይሮፕላኑ ቦትውድ ሲያርፍ ሲሆን ከአልጋዋ ስትነሳ ማርክ
ወጥቶ መሄዱን አወቀች፡፡ ጧት ቁርስ ላይ መሳ ለመሳ ተቀምጠው በሃሳብ
ተውጠው ምግባቸውን ሲቆነጣጥሩ ነበር፡፡
ዳያናን መርቪን ከናንሲ ጋር የሙሽሮች ክፍልን ተጋርተው ማደራቸው
ለምን እንደዚህ እንዳናደዳት አልገባትም፡ ማርክ በዚህ ረገድ ቢያግዛት
በወደደች። በተቃራኒ አሁንም መርቪንን ትወጂዋለሽ እንዴ?ሲል
ጠይቋታል፡፡ ትዳሯንና ቤት ንብረቷን ትታ ከእሱ ጋር መኮብለሏን እያወቀ
ማርክ እንዲህ ማለቱ አናዷታል፡፡

ዙሪያዋን ስትመለከት በቀኝዋ የተቀመጡት ልዕልት ላቪኒያና ሉሉ ቤል
የቆጡን የባጡን ያወራሉ፡፡ ሁለቱም አይሮፕላኑ ሲወዛወዝ ስላደረ እንቅልፍ
ባይናቸው ሳይዞር ስለነጋባቸው ተዳክመዋል፡፡ በግራ በኩል የኤፍ.ቢ.አዩ ሰው ኦሊስ ፊልድና እስረኛው ፍራንኪ ጎርዲኖ በጸጥታ ምግባቸውን ይበላሉ።

የጎርዲኖ እግር በእግረ ሙቅ ከመቀመጫው ጋር ተጠፍሯል፡ሁሉም
በድካም የዛሉና ነጭናጫ ሆነዋል፡፡ እንዲህ ያለ አለቅጥ የረዘመ ሌሊት
ገጥሟቸው አያውቅም፡፡
አስተናጋጁ ዴቪ ቁርስ የተበላባቸውን ሰሃኖችና ቁሳቁሶች እየሰበሰበ
ነው፡፡ ልዕልት ላቪኒያ ‹‹እንቁላሉ አልበሰለም ሞርቶዴላው ደግሞ በጣም
ሙክክ ብሏል›› በማለት ስሞታ ያሰማሉ፡ ዴቪ ቡና ቢያመጣም ዳያና
አልጠጣችም::

ማርክን ሰረቅ አድርጋ አይታ ፈገግ ስትል እሱም በፈገግታ ተቀበላት
‹‹ከነጋ አንዴ እንኳን አላናገርከኝም›› አለችው፡፡
‹‹ምክንያቱም ከኔ ይልቅ ለመርቪን ልብሽ መጥፋቱን ስላወቅሁ ነው›
ወዲያው ጸጸት ገባት፡፡ መቅናቱ ትክክል ነው፡ ‹‹ይቅር በለኝ ማርክዬ›
አለች ‹‹ልቤ ያለው ካንተጋ ብቻ ነው እውነቴን ነው››
እጁን ሰዶ እጇን ያዝ አደረገና ‹‹እውነትሽን ነው?››
‹‹እውነቴን ነው፡፡ ትናንት ምን እንደነካኝ አላውቅም››

‹‹እሺ›› አለ ማርክ፡፡
ሁለቱም አፍቃሪዎቿ አፍጥጠውባታል፡፡ አንድ ውሳኔ ላይ መድረስ
እንዳለባት አውቃለች፡ ከመርቪን ጋር ብቻዋን ብትነጋገር ማርክን
አስከፋዋለሁ ብላ ገምታለች፡፡ አሁን መርቪንን ትቼ ከማርክ ጋር ነው
ያለሁት ስለዚህ ማርክን ነው መደገፍ ያለብኝ ስትል አሰበች፡፡

ልቧ  ከበሮ  እየደለቀ ‹‹ማርክ ፊት የማታናግረኝ ከሆነ ልሰማው አልፈልግም›› አለችው፡:

መርቪን ደንገጥ አለና ‹‹እሺ›› አለ በብስጭት፡፡ ወዲያው ራሱን አረጋጋና ‹‹ከዚህ በፊት ያልሺኝን ተገንዝቤያለሁ፤ምን ያህል ቀዝቃዛ እንደነበርኩ አንቺም ምን ያህል ብቸኝነት ይሰማሽ እንደነበር…›› ንግግሩንቆም አደረገ፤ ዳያና ምንም መልስ አልሰጠችም፡፡ ይቅርታ ማለት ወይም መጸጸትን መግለጽ የመርቪን ባህሪ አይደለም፡፡ ምን ሊል ነው?› አለች ዳያና በሆዷ።

‹‹እስካሁን ላደረግሁት ሁሉ ይቅር በይኝ›› አለ መርቪን፡ ዳያና የመርቪን አባባል ቢገርማትም እውነቱን መናገሩን አውቃለች፡ ‹ይህ ሁሉ ለውጥ ከየት መጣ?›

መርቪን ቀጠለና ‹‹የተዋወቅን ሰሞን አንቺን ለማስደሰት ጥረት አደርግ
ነበር፡፡ እንዲከፋሽ አልፈልግም ነበር፡፡ አሁን ኑሮሽን ጨለማ ማድረጌ
ተሰምቶኛል፡ ደስታ ማግኘት መብትሽ ነው፡፡ የሰው ሁሉ ዓይን ማረፊያ እንደሆንሽ አውቃለሁ፡››

ዳያና ይህን ስትሰማ እምባዋ በዓይኗ ሞላ፡፡ የወንዶችን ዓይን መሳቧ
እውነት ነው፡፡

‹‹አንቺን ማሳዘኔ ሀጢያት ነው›› አለ መርቪን፡፡ ‹‹ከዚህ በኋላ አንቺን ለማስደሰት እጥራለሁ፡››

ከዚህ በኋላ ጥሩ እሆናለሁ› ማለቱ ፍርሃት ለቀቀባት፡ ወደ ቤቷ እንድትመለስ ይፈልጋል ማለት ነው፡፡ እሷ ግን እንዲጠይቃት እንኳን
አትፈልግም፡፡ ‹‹ወደ አንተ ተመልሼ አልመጣም›› አለች ዳያና፡

‹‹ከማርክ ጋር ደስተኛ ህይወት የምትኖሪ ይመስልሻል?››

ዳያና ራሷን በአዎንታ ነቀነቀች፡፡

‹‹ያስብልኛል ብለሽ ታምኛለሽ?››

‹‹አዎ ያስብልኛል››

ማርክ ጣልቃ ገባና ‹‹እኔን እንደ እቃ ቆጥራችሁ ስለኔ ትናገራላችሁ? አለ፡፡

ዳያና የማርክን እጅ ለቀም አድርጋ ያዘችና ‹‹እንዋደዳለን›› አለችው:
‹‹አይ!›› አለ መርቪን፡፡ ለተወሰኑ ደቂቃዎች ፊቱ ላይ የለበጣ ፈገግታ
ተነበበ ‹‹ትዋደዳላችሁ›› አለ፡፡
መርቪን የተለሳለሰ መሰለ፡፡ ይሄ የእሱ ባህሪ አይደለም፡፡
ወይዘሮ ሌኔሃን ሄደህ ከሚስትህ ጋር ተነጋገር አለችህ እንዴ?›› አለች ዳያና ተጠራጥራ።
አላለችም፡፡ ሆኖም ልናገር እንደምችል ታውቃለች››
‹‹ታዲያ ፈጠን ብለህ ተናገረውና ይውጣልህ›› አለ ማርክ፡፡
መርቪን ማርክን ገላመጠውና ‹ጎረምሳው አንተን እዚህ ነገር ውስጥ
የሚያገባህ ነገር የለም፤ ዳያና እኮ አሁንም ባለቤቴ ናት›› አለ፡፡

ማርክ ፍቅረኛውን ለማገዝ ‹‹ተው እባክህ!  ከዚህ በኋላ ከእጅህ ወጥታለች፤ ደግሞ ጎረምሳው አትበለኝ ሽ
ሽሜ›› አለው መርቪንን፡፡

‹‹መርቪን እዚህ አምባጓሮ ማንሳት አትችልም የምትለው ካለህ
አውጣና ተናገረው፤ አለበለዚያ አንድ ዓይነት ኃይል ያለህ አታስመስል››
አለችው ዳያና፡፡
‹‹ደህና፧ ነገሩ እንዲህ ነው›› ትንፋሹን ዋጥ አደረገና ‹‹መንገዱን ጨርቅ ያድርግላችሁ፤ ወደ ቤትሽ እንድትመለሺ ስጠይቅሽ ‹ምን ሲደረግ ብለሻል፧ ይሄ ሰው እኔ ማድረግ የማልችለውን አድርጎ ከሆነና ከእሱ ጋር
መኖር ደስታ የሚሰጥሽ ከሆነ መልካም እድል ይግጠማችሁ፡፡ መልካሙን
እመኝላችኋለሁ ይሄው ነው›› አለ፡፡ ከዚያም ጸጥታ ነገሰ፡

ማርክ ሊናገር ሲል ዳያና አቋረጠችውና ‹‹አንተ የተረገምክ እምነተ ቢስ
የሆንክ ሰው!›› አለች ‹‹እንዴት ያለኸው ደፋር ነህ!›› አለችና ምራቋን ጢቅ
አደረገች፡፡

መርቪን አባባሏ ግራ አጋባውና ‹‹ምነው?›› አላት፡፡
😎ጠላፊዎቹ

#ክፍል_አርባ_አራት

#በኬንፎሌት

#ትርጉም_ወንዳየሁ_ንጉሴ


አይሮፕላኑ ወደ ማረፊያው ሼዲያክ ቤይ ለማረፍ እየወረደ እያለ ሄሪ የሌዲ ኦክሰንፎርድን ጌጣ ጌጦች መስረቅ ወይም አለመስረቅ ሃሳቡን እልባት ለመስጠት ተቸግሯል፡ ጌጡን ለመስረቅ የነበረው ጉጉት በማርጋሬት
ምክንያት ቀንሷል፡ ቦስተን ይዟት ሄዶ ቤት ተከራይቶ እየኖሩና ራሷን እንድትችል እየረዳት በ ይበልጥ ከእሷ ጋር ሊላመድ ይፈልጋል፡ ደስታዋ ያስደስተዋል፡ ቀለል ያለ ኑሮ ለመኖር ያላትን ጉጉት ይጋራል፡

እናቷን ከዘረፈ ግን ይህ ሁሉ ያከትመለታል፡፡
በአንጻሩ ኒውዮርክ ከመድረሳቸው በፊት የመጨረሻ ማረፊያቸው ከተማ ሼዲያክ ስለሆነ በዚህ ጉዳይ ላይ ቶሎ መወሰን አለበት፡ ሻንጣ   ክፍሉም የመግባት የመጨረሻ ዕድሉ ይሄ ብቻ ነው፡

ማርጋሬትንም ዕንቁውንም በእጁ ማድረግ የሚችልበትን መንገድ እያሰበ ነው፡ በመጀመሪያ ዕንቁው ቢጠፋ እሱ የሰረቀ መሆኑን ታውቅ ይሆን? ሌዲኦክፎርድ  ዕንቁው መጥፋቱን የሚያውቁት ኒውዮርክ ከደረሱ በኋላ
ልዶርፍ አስቶሪያ ሆቴል ውስጥ ሻንጣቸውን ሲከፍቱ ነው: ዕንቁው 'የጠፋው አይሮፕላኑ ውስጥ፣ በፊት ወይም በኋላ መሆን አለመሆኑን ማንም
አያውቅም፡፡ ማርጋሬት ሄሪ ሌባ መሆኑን ስለምታውቅ እሱ ነው የሰረቀው
ብላ ትጠረጥር ይሆናል። እኔ አልሰረቅሁም ቢላት ታምነዋለች? ታምነው
ይሆናል።

ከዚህ በኋላስ? እሱ ባንክ ውስጥ አንድ መቶ ሺ ዶላር ወሽቆ በድህነት ይኖራሉ! በዚህ አይነት ብዙ ዓመት ሊገፉ አይችሉም፡፡ ወደ እንግሊዝ አገር ትመለስና ሴት ወታደሮችን ትቀላቀላለች፡ ሄሪ ደግሞ ካናዳ ሄዶ የአየር
ኃይል ፓይለት ይሆናል፡፡ ጦርነቱ ሲያበቃ ገንዘቡን ከባንክ ያወጣና መኖሪያ
ቤት ይገዛል፧ እሷም አሜሪካ ትመጣና አብረው መኖር ይጀምራሉ፤ አብረው
ሲኖሩም ይህን ሁሉ ገንዘብ ከየት እንዳመጣ ትጠይቀዋለች።
የሆነውን ሁሉ ወዲያው ወይም ቆይቶ ይነግራት ይሆናል፡ በኋላ ቢነግራት ነው ግን የሚሻለው፡፡

አይሮፕላኑ ሼዲያክ ላይ ሲያርፍ ሁሉም ሲወጡ እሱ የሚቆይበትን ምክንያት መንገር አለበት፡፡ አመመኝ ቢላት አብሬህ እሆናለሁ የምትለው በመሆኑ ሁሉም ነገር ተበላሸ ማለት ነው፡፡ ስለዚህ ከሰዎቹ ጋር ወጥታ
መሄዷን ማረጋገጥ አለበት፡
ሄሪ ማርጋሬትን አሻግሮ ያያታል፡፡ የመቀመጫ ቀበቶዋን እያጠበቀች
ነው፡ በዓይነ ህሊናው ደግሞ ራቁቷን ሆና አጎጠጎጤዋ ፈጦ ወጥቶ እና እግሮቿ ከፈት ብለው ብልቷ ዙሪያ ያከፈከፈው ጸጉር ይታየዋል፡፡ ይችን
የመሰለች ቆንጆ ለዕንቁ መለወጡ ጅል የሆነ አያስመስለውም? ታዲያ

እነዚህን ዕንቁዎች መተው ማለት ዘወትር የሚመኘውን የባለጸጋ ኑሮ ሊያደርግ ያሰበውን ነገር ነገራት እንበል፡፡ የናትሽን ዕንቁ ብሰርቅ ምን ይመስልሻል? ቢላት ጥሩ ሃሳብ ነው፤ ይቺ አሮጊት እነዚህ ዕንቁዎች
አይገቧትም ብላ እንደማትመልስለት  ያውቃል፡ በፖለቲካ  አመለካከቷ ተራማጅ  በመሆኗ በፍትሃዊ ክፍፍል ታምናለች፡፡ ይሄ ደግሞ በጽንለ ሃሳብ ደረጃ ነው፡፡ ሄሪ እናትና አባቷ ያላቸውን አንድ ዕንቁ ቢወስድባቸው በጣም በጣም ትበሳጫለች በዚህም ምክንያት ለእሱ ያላት ፍቅር ሁሉ ይተናል።

ይህን በአዕምሮው ሲያሰላስል ከእሷ ጋር ዓይን ላይን ግጥም አሉና
ፈገግ አለች፡ እሱም በእፍረት ፈገግ አለና ፊቱን ወደ መስኮቱ አዞረ፡፥

አይሮፕላኑ ባህር ዳርቻው ላይ ለማረፍ ዝቅ እያለ ነው። ዙሪያዋን የተበታተኑ መንደሮች የተገጠገጡ ሲሆን ከመንደሮቹ ጀርባ የእርሻ ቦታ ይታያል፡ ወደ ማረፊያቸው እየተጠጉ ሲመጡ በመንደሮቹ መሃል እንደ እባብ እየተሹለከለከ እስከ ወደቡ የተዘረጋው የባቡር ሃዲድ ከሩቅ ተለይቶ
ይታያል በባህሩ ዳርቻ ላይ በርካታ መርከቦችና አንድ የአየር በራሪ ጀልባ መልህቃቸውን ጥለዋል።ከወደቡ በስተምስራቅ እዚህም እዛም የበጋ መዝኔኛ
ቤቶች ፈንጠቅጠቅ ያሉበት አሸዋማ የባህር ዳርቻ ይታያል፡ ሄሪ እንደዚህ
ያለ የበጋ መዝናኛ ቤት እንዲኖረው ይፈልጋል፡፡ ይህንንማ በእጄ ካላስገባሁ
ሞቻለሁ! ሀብታም እሆናለሁ› ሲል በሆዱ ተመኘ፡፡

አይሮፕላኑ ባህሩ ዳርቻ ላይ በሰላም አረፈ፡ ሄሪ አሁን ተረጋግቷል፡ በአይሮፕላን መብረርንም ተላምዷል፡
‹‹ስንት ሰዓት ነው?›› ሲል ሄሪ ፔርሲን ጠየቀው፡
‹‹ብአገሩ ሰዓት አቆጣጠር ከቀኑ አምስት ሰዓት ነው፡፡ አንድ ሰዓት ዘግይተን ነው የደረስነው››

‹‹ሼዲያክ ላይ ስንት ሰአት እንቆያለን?››

‹‹አንድ ሰዓት››

ሄሪ ማርጋሬት ቀድማ እንድትሄድና ከጥቂት ጊዜ በኋላ እንደሚከተላት
ይነግራታል እሷም ካንተ ጋር እቆያለሁ ብላ እንደማታስቸግር ገምቷል፡፡
አንድ አስተናጋጅ የአይሮፕላኑን በር ሲከፍት ተሳፋሪዎች ልብሶቻቸውን
ደረቡ: የኦክስንፎርድ ቤተሰብ ከአይሮፕላን ለመውጣት ተነሳ፡፡ እስካሁን
አፉን ለጉሞ የቀረው ክላይቭ መምበሪም ከመቀመጫው ተነሳ፡
ማርጋሬትን ‹‹አንቺ ሂጂና እኔ እከተልሻለሁ›› አላትና ወደ መጸዳጃ ቤት ሄደ።

ሰው እስኪወጣ የሆነ ነገር ልስራ ብሎ ጸጉሩን አበጣጠረ እጁንም ታጠበ፡፡ አንድ የአይሮፕላኑ ሰራተኛ በደረጃው ወርዶ አልፎ ሲሄድ አየ፡፡
ሰዓቱን አየና ተጨማሪ ሁለት ደቂቃ ለመጠበቅ ወስነ፡፡ሁሉም ወጥተው እንደሆነ ለማየት ዙሪያ ገባውን አማተረ፡፡ ቦትውድ ላይ ሁሉም አሸልበው  ነበር
አሁን ግን ብዙዎቹ እግሮቻቸውን ለማፍታታተና ንጹህ አየር ለመቀበል እየወጡ ነው፡፡ ኦሊስ ፊልድና እስረኛው እስካሁን ሲያደርጉ እንደነበረው አይሮፕላኑ ላይ ይቆያሉ፡፡
መምበሪ ፍራንኪን እንዲጠብቅ የተመደበ ከሆነ ከአይሮፕላኑ ወጥቶ መሄዱ እንግዳ ነገር ነው፡፡ ሄሪን አሁንም ግርምት ውስጥ የከተተው ሙሉ ልብስ የለበሰው ሰው ነው።
ቲም ሉተር።

የጽዳት ሰራተኞች ወዲያውኑ እየተግተለተሉ መምጣታቸው አይቀርም
ብሎ ጆሮውን ቀስሮ አዳመጠ፡፡ በበሩ በኩል የሚመጣ ድምጽ የለም፡፡ በሩን ትንሽ ከፈት አደረገና አየ፡ ምንም ነገር አለመኖሩን አረጋገጠና ኮቴ ሳያሰማ ወጣ።

ከወጣበት በር ትይዩ ኩሽና ያለ ሲሆን ሰው የለበትም፡፡ ወደ ሌላው የአይሮፕላኑ ክፍልም ዘው ሲል የሰው ዘር አይታይም ወደ ሳሎኑ ሲገባ መጥረጊያ የያዘች ሴት ጀርባዋን ሰጥታው ቆማለች፡፡ ደረጃውን ወጣ፡፡
Lያለምንም መጠራጠር ኮቴ ሳያሰማ ደረጃውን ቀስ ብሎ ወጣ፡፡ ደረጃው መጠምዘዣ ላይ ሲደርስ ቆም አለና ዓይኑን ወረወረ፡ ማንም የለም ወደፊት ሊሄድ ሲል አንድ ሰው ደረጃው ስር ሲሄድ አየና ከመቅጽበት
ኮሪደሩ ላይ ልጥፍ ብሎ ዓይኑን አጮልቆ ሲያይ ባለፈው ጊዜ ሻንጣ
ሲበረብር ያየው ሚኪ ፊን ነው፡፡ ሰውየው የበረራ መሃንዲሱ ቦታ ሲደርስ
ዞር ብሎ አየ፡፡ ሄሪ በዚህ ጊዜ እንዳይታይ ግድግዳው ላይ ልጥፍ አለና አዳመጠ፡ ይሄ ሰው የት ነው የሚሄደው? ሲል መልስ
የሌለው ጥያቄ ጠየቀ የሰውየው ኮቴ እየራቀ ሲሄድ ጸጥታ ሰፈነ፡፡

በደረጃው ወጣ፡፡ ደረጃውን ወጥቶ እንደጨረሰ አሻግሮ ሲመለከት ሰው የለም፡ በቀጥታ ያመራው ወደ ሻንጣዎቹ መቀመጫ ክፍል ነው፡፡ እዚያም ገብቶ በሩን ቀስ ብሎ ዘጋና ትንፋሹን በረጅሙ ለቀቀው፡፡
ሻንጣዎቹን ሲቃኝ አንድ ትልቅ ሳጥን ላይ ዓይኑ ተተከለ፡፡የሌዲ ኦክሰንፎርድ ሳይሆን አይቀርም፡፡ ጠጋ ብሎ ሲያይ ኦክሰንፎርድ የሚል ስም ተለጥፎበታል፡፡
😎ጠላፊዎቹ

#ክፍል_አርባ_አምስት

#በኬንፎሌት

#ትርጉም_ወንዳየሁ_ንጉሴ


ናንሲ ባህሩ ዳር ቁጭ ብላለች፡፡ መርቪን ላቭሴይ አጠገቧ ተቀምጧል፡፡
የባህሩ ውሃ በማዕበል እየተገፋ ይመጣል፣ ይመለሳል፡፡ ናንሲ ዓይኗን
ጨፍናለች፡ ሌሊት በደምብ አልተኛችም:: መርቪንና እሷ
እሷ ማታ መጋጨታቸው ትዝ አላትና ፈገግ አለች ከእሱ ጋር የምር ግንኙነት
አለመመስረቷ ደስ ብሏታል፡ ለወሲብ መቻኮሉ ጥሩ
አይደለም፡፡የመጣችበትን ዓላማ ከግብ ማድረስ አለባት፡፡

ሼዲያክ የዓሳ ማጥመጃ ፤መንደርና የባህር ዳር መዝናኛ ከተማ ናት፡፡
በባህሩ ዳርቻ ላይ የዓሳ
ማጥመጃ ጀልባዎች፣ መርከቦች፣ ሌሎች ሁለት
አይሮፕላኖችና እነሱ የመጡበት አይሮፕላን ይታያል፡፡ ብዙዎቹ የአይሮፕላኑ ተሳፋሪዎች በባህሩ ዳርቻ ላይ ወዲያ ወዲህ ይላሉ፡፡

ሁለት የፖሊስ መኪኖች እየበረሩ መጥተው ጎማቸውን ሲጢጥ
አድርገው ሲቆሙ የአካባቢው ፀጥታ ታወከ፡፡ ከመኪኖቹም ውስጥ ሰባት
ስምንት ያህል ፖሊሶች እየዘለሉ ወጡ፡፡  በቀጥታ ወደ ተሳፋሪዎቹ
ማስተናገጃ ሲያመሩ የሆነ ሰው ሊይዙ የመጡ ይመስላል›› አለች ናንሲ፡
እሱም በመስማማት ራሱን ነቀነቀና ‹‹ማንን ይሆን?›› አለ፡፡
‹‹ምናልባትም ፍራንኪ ጎርዲኖን››
‹ሊሆን አይችልም እሱ እንደሆነ እንደታሰረ ነው፡፡››
አይሮፕላን ውስጥ ሲገቡ ሁለቱ ወደ ባህሩ ዳርቻ ሲያመሩ ሁለቱ ደግሞ
ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ፖሊሶቹ ከመናኸሪያው ወጡና ሶስቱ መንደሩ ውስጥ መንጎራደድ ጀመሩ፡፡

ፖሊሶቹ የሆነ ሰው እንደሚፈልጉ ያስታውቅባቸዋል፡ አንዱ
የአይሮፕላኑ ሰራተኛ ከአይሮፕላኑ ሲወጣ አየችና ናንሲ ‹ፖሊሶቹ ማንን ነው የሚፈልጉት?›› ስትል ጠየቀች:

ሰውየው ምስጢር ለማውጣት እየተጠራጠረ ሄሪ ቫንዴርፖስት
የተባለውን ሰው ነው የሚፈልጉት፤ ስሙ የሀሰት ነው›› አለ፡፡

ናንሲ ግንባሯን ከሰከሰችና ይሄ ልጅ ከኦክሰንፎርድ ቤተሰብ ጋር ተቀምጦ የነበረው ነው፡ ልጁ የማርጋሬትን ልብ ሳይሰርቅ አልቀረም›› ስትል
ገመተች ናንሲ፡

መርቪን ‹‹ከአይሮፕላኑ ወጥቶ ሄዷል እንዴ? እኔ ከአይሮፕላኑ ሲወጣ
አላየሁትም›› አለ፡፡

‹‹እኔም አላስተዋልኩም›› አለች ናንሲ፡

‹‹ልጁ አጭበርባሪ ይመስላል››

‹‹እውነት?›› አለች ናንሲ፡ እሷ ልጁ ከጥሩ ቤተሰብ የተገኘ ነበር የመሰላት፡ ‹‹ጥሩ ባህሪ አይቼበታለሁ: ማርጋሬት ከልጁ ጋር ፍቅር ሳይዛት አልቀረችም፡፡ ፖሊስ እንደሚፈልገው ስታውቅ ታዝናለች›› አለች

‹‹ወላጆቿ ፖሊስ እጅ መውደቁ ደስ ሳያሰኛቸው አይቀርም›› አለ
መርቪን፡፡ናንሲ ስለወላጆቿ ግድ የላትም፡ በአይሮፕላኑ መብል ክፍል ውስጥ
ሎርድ ኦክሰንፎርድ ያሳዩት የነበረው ጋጠወጥ ባህሪ መርቪንና ናንሲ
ያስታውሳሉ፡ ለእንደዚህ አይነት ሰው ውርደት ሲያንሰው ነው ናንሲ ከእንደዚህ አይነት ወመኔ ጋር ማርጋሬት ፍቅር ስለያዛት አዘነችላት፡

መርቪንም ቀጠለና ‹‹እኔ ስለሌላ ሰው ማውራት አልፈልግም›› አለ፡
ናንሲ ጆሮዋን ቀሰረች፡
መርቪን ቀጠለና ‹‹የተገናኘነው ከጥቂት ሰዓታት በፊት ስለሆነ በደምብ ላውቅሽ እፈልጋለሁ፡›› ናንሲም እርግጠኛ መሆን አትችልም አንተ ደደብ አለች በሆዷ
ሆኖም ይህን ማለቱ አስደስቷታል፡ ምንም መልስ አልሰጠችውም፡፡

‹‹ብፊት አንቺን ኒውዮርክ አድርሼ ወደ ማንቼስተር መመለስ ነበር የማስበው፡፡ አሁን ግን አላደርገውም›› አላት፡

ናንሲ ፈገግ አለች ይህን እንዲል ነበር ስትጠብቅ የነበረው:፡ እጇን ሰደደችና እጁን ያዝ አደረገች፡፡ ‹‹ይህን ስላልክ ደስ ብሎኛል›› አለችው፡

‹‹ደስ ብሎሻል? ችግሩ ከዚህ በኋላ አትላንቲክን ማቋረጡ የሚቻል አይሆንም፡፡ የጦር መርከቦች ብቻ ናቸው ይህን ማድረግ የሚችሉት፡››ናንሲ በመስማማት ራሷን ነቀነቀች፡
አሁን ከተለያየን ምናልባትም የምንገናኘው ከብዙ ጊዜ በኋላ ነው፡፡።
እኔ ግን ላጣሽ አልፈልግም›› አለ መርቪን፡፡

‹‹እኔም እንደዚያው›› አለች ናንሲ፡፡

‹‹ከእኔ ጋር ኢንግላንድ ትሄጃለሽ?›› ሲል ጠየቃት፡፡
ናንሲ ፈገግታዋ ከፊቷ ላይ ጠፋ፡፡ ‹‹ምን አልክ?››
‹‹ከእኔ ጋር ወደ ኢንግላንድ እንመለስ፡፡ ሆቴል ውስጥ ትቆያለሽ ወይም ቤት ትገዣለሽ ወይም አፓርትማ ትከራያለሽ››

ናንሲ ያቀረበላት ሃሳብ በጣም አስቆጣት፡፡ ጥርሷን በንዴት አፋጨች፡፡
‹‹አብደሃል እንዴ?›› አለችው፡፡ መርቪንን ፊት ለፊት ማየት ጠልታ
ፊቷን አዞረች፡፡ በእጅጉ አዘነችበት፡፡
መርቪን አባባሏ አስደነገጠው ግራ አጋባው፡፡ ‹‹ምነው?›› ሲል ጠየቃት፡፡

‹‹እኔ አሜሪካ ውስጥ የራሴ ኑሮ፣ ቤት፣ ሁለት ልጆችና በሚሊዮንዐየሚቆጠር ዶላር ገቢ የሚያስገኝ ፋብሪካ አለኝ፡፡ አንተ እንዴት ይህን ሁሉ እርግፍ አድርጌ ትቼ በማንቼስተር ሆቴል እንድቀመጥ ትጠይቀኛለህ?››

‹‹ይህን ካልፈለግሽ ከእኔ ጋር ተጠቃለይ››

‹‹እኔ እኮ ባገሬ የተከበርኩ ሴት ነኝ እንደ ቅምጥ ልኖር አልችልም፡››

‹‹ይኸውልሽ ልንጋባ እንችላለን፤ ይህን አረጋግጥልሻለሁ፧ እኔ አሁን
በዚህ ደቂቃ ውስጥ እንድትወስኚ አይደለም የጠየቅሁሽ››

‹‹ይህ አይደለም ዋናው ነጥብ መርቪን›› አለች ‹‹እኔን የገረመኝ ሁሉን
ጣጥለሽ ተከትለሽኝ ኢንግላንድ ነይ ያልከኝ ነው፡፡››
‹‹ታዲያ እንዴት ነው አንድ ላይ ልንኖር የምንችለው?››
‹‹ታዲያ ጥያቄውን መጠየቅ ሲገባህ ወደ መልሱ ሄድክ››
‹‹አንድ መልስ ስላለ ብቻ ነው ይህን ያልኩት››
‹‹ሶስት መልሶች ናቸው ያሉት፤ አንተ እንዳልከው አንተን ተከትዬ ወደ
ኢንግላንድ መመለስ ወይም አንተ ወደ አሜሪካ መጥተህ ከእኔ ጋር መኖር
ወይም ሌላ ቦታ ለምሳሌ ቤርሙዳ እንኖራለን›› አለች፡፡
በአባባሏ አልተደሰተም፡፡ ‹‹አገሬ ጦርነት ላይ ነች፤ እኔም የድርሻዬን ማበርከት አለብኝ፤ ጦርነት ውስጥ ገብቼ ለመዋጋት እድሜዬ ቢያልፍም ለአየር ኃይሉ የአይሮፕላን ሞተሮች ሰርቼ አቀርባለሁ፡፡ በእዚህ መስክ ከእኔ የተሻለ እውቀት ያለው የለም፡፡ አገሬ በጣም ትፈልገኛለች››

አሁን ያላት ነገሩን አባባሰው፡ ‹‹ለምንድነው የእኔ አገር እኔን
እንደማትፈልገኝ አድርገህ የምታስበው?›› አለች እኔ የወታደር ጫማ አመርታለሁ፡፡ አሜሪካ ጦርነቱ ውስጥ ከገባች ብዙ የወታደሮች ጫማ
ያስፈልጋታል››
‹‹እኔ ማንቼስተር ውስጥ ፋብሪካ አለኝ››
‹‹እኔ ደግሞ ቦስተን ውስጥ ካንተ የበለጠ ፋብሪካ አለኝ››
‹‹ታዲያ ሴት እንደ ወንድ እኮ አይደለችም››
‹ሴት ከወንድ እንዴት ታንሳለች አንተ ጅል!›› ብላ ጮኸችበት፡፡
ጅል› ማለቷ ወዲያው ጸጸታት፡፡ ፊቱ ቅጭም ሲል ታያት፡፡ በጣም
እንዳበሳጨችው ገባት፡፡ ከወንበሩ ተነሳ፡፡ እንደከፋው እንዳይሄድ አንድ ነገር
ማለት ብትፈልግም ትክክለኛው ቃል አልመጣላት አለ፡፡ እሱም አፍታም ሳይቆይ ጥሏት ሄደ፡፡

ምን ማለቴ ነው? አለች ምርር ብሏት፡ አባባሉ  ቢያበሳጭም ስላስከፋችው ደግሞ ተናደደች፡፡ በዚህ ሁኔታ እንዲርቃት አልፈለገችም ወዳዋለች፡ ወንዶችን ፊት ለፊት በመጋፈጥ ለውጥ ማምጣት እንደማይቻል
እያደር ገብቷታል፡፡ ወንዶች ከወንዶች በኩል
የሚመጣውን ጠብ ለምደውታል፡ ከሴቶች የሚመጣውን ግን መቀበል ይከብዳቸዋል፡፡ በንግድ
ስራዋ ላይ ከሰራተኞች የሚመጣ ችግር ሲገጥማት ድምጿን አለስልሳና
አለዝባ ትመልሳቸዋለች እንጂ አታካሮ አትገጥምም፡፡ አሁን ግን ያ ባህሪዋ ሸሽቷት በአስር ዓመት ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ልቧን የወሰደውን ሰው
አበሳጭታ አባረረችው፡
😎ጠላፊዎቹ

#ክፍል_አርባ_ስድስት

#በኬንፎሌት

#ትርጉም_ወንዳየሁ_ንጉሴ


መጋዘኑ ውስጥ አምጥቶ ሲወረውራት ክርኗና ጉልበቷ በመጎዳቱ ቁስሉ ጠዘጠዛት፡፡ ‹‹አንተ አሳማ!›› ብላ ፒተርን በሌለበት ተሳደበች፡፡
ጫማዋን አጠለቀችና ቦርሳዋን አንስታ ዙሪያውን ቃኘች። ሌላ በር አገኘችና ለመክፈት ብትሞክርም በጥብቅ የተዘጋ በመሆኑ መክፈት አልቻለችም::

ቤቱ ከባህር ዳርቻው የራቀ ቢሆንም የአይሮፕላኑ ተሳፋሪዎች ወይም
ሌላ ሰው በዚያ በኩል ሊያልፍ ይችላል፡፡ ናንሲም ጉሮሮዋ እስኪሰነጠቅ
‹‹የሰው ያለህ!›› ስትል ጮኸች፡

ጉሮሮዋ ደርቆ ድምጿ እንዳይዘጋ በየአንድ ደቂቃ ልዩነት አንድ ጊዜ
መጣራቷን ቀጠለች፡
ሁለቱም በሮች በወፍራም እንጨት የተሰሩና ግጥም ያሉ በመሆናቸው
ዲጂኖ ወይም ሌላ ብታገኝ ሰብራ ወይም ፈልቅቃ ትከፍተው ነበር፡፡
ምናልባትም አንድ የሆነ የእጅ መሳሪያ አገኝ ብላ አካባቢውን ቃኘች፡፡ የቤቱ
ባለቤት ዕቃውን በስርዓት የሚይዝ ኖሮ የእጅ መሳሪያዎቹን መጋዘኑ ውስጥ አልተዋቸውም፡፡ መጋዘኑ ውስጥ አንድም የሚታይ የአትክልት መኮትኮቻም ሆነ አካፋና ዶማ የለም፡፡

እንደገና ‹‹የሰው ያለህ!›› መልስ የለም፡፡

ቁጭ ብላ መተከዝ ሆነ ያላት አማራጭ፡ ኮቷን ይዛ በመምጣቷ ብርዱ
ብዙም አላስቸገራትም፡፡ መጣራቱን ባታቆምም ጊዜ እያለፈ ሲሄድ ተስፋዋ
እየተሟጠጠ ሄደ፡ ይሄን ጊዜ ተሳፋሪዎቹ አይሮፕላኑ ላይ እንደገና እየገቡ
ይሆናል፡፡ ጥቂት ቆይቶ እሷን ጥሎ ይበራል፡፡
በአሁኑ ሰዓት እያስጨነቃት ያለው ኩባንያውን ማጣቱ አይደለም፡፡አይበለውና ለሳምንት ያህል ሰው ወደ መጋዘኑ ዝር ባይል ምን ይውጣታል፡ እዚሁ ልትሞት አይደል፡፡ ይህም ጭንቀት ላይ ስለጣላት ያለማቋረጥ
ጩኸቷን አስነካችው፡፡

ጥረቷ ሁሉ አለመሳካቱን ስታውቅ ዝም ብላ ቁጭ አለች፡፡ ፒተር ክፉ
ሰው ቢሆንም ነፍሰ ገዳይ ስላልሆነ እዚህ እንድሞት አይተወኝም ብላ ገመተች፡፡ ሼዲያክ ፖሊስ መምሪያ ስልክ ደውሎ ከመጋዘኑ እንዲያወጧት ይነግራቸው ይሆናል፡፡ ነገር ግን ከቦርድ ስብሰባው በፊት
አይነግራቸውም፡፡ ያለችበት ቦታ የማያሰጋ ቢሆንም ስጋት መፍጠሩ አልቀረም፡ ፒተር ካሰበችው በላይ ጨካኝ ቢሆንስ! ቢረሳትስ? ቢያመውስ?
ወይም የሆነ አደጋ ቢገጥመውስ? ታዲያ ከዚህ ማጥ ውስጥ የሚያወጣት
መቼም ማነው?

የአይሮፕላኑ ሞተሮች ሲያስገመግሙ ስትሰማ የነበራት ተስፋ ሁሉ ጨለመ  የገዛ ወንድሟ ለክፉ እንደዳረጋት መርቪንም ሊደርስላት እንደማይችል አወቀች፡፡ መርቪን ይህን ጊዜ አይሮፕላኑ ውስጥ ቁጭ ብሎ የአይሮፕላኑን መነሳት እየጠበቀ ይሆናል፡፡ አይሮፕላኑ ውስጥ ሲያጣት ‹ምን ሆና ይሆን?› ማለቱ ባይቀርም በመጨረሻ የተለያዩት ‹‹አንተ ጅል!›› ብላ ሰድባው ስለሆነ ከእሷ ጋር አብቅቷል ብሎ ያስብ ይሆናል፡፡እንግሊዝ አገር ተከትለሽኝ  ነይ ማለቱ ብልግናውን ያሳያል፡ ሆኖም
ማንም ወንድ ይህን ስለሚል መናደድ አልነበረባትም፡፡ የተለያዩት በጥል ስለሆነ ካሁን በኋላ እንደማታገኘው ተገነዘበች፡፡ ‹‹ኩባንያዬንም ተነጠቅሁ፣
መርቪንንም ተነጠቅሁ፣ በረሃብም እሞታለሁ›› ስትል አላዘነች፡፡

ጉንጯ ላይ የፈሰሰውን እንባ በእጅጌዋ ጠረገች፡፡ ከእዚህ ችግር ለመውጣት ወገቧን ጠበቅ ማድረግ እንዳለባት ተገነዘበች፡፡ ከዚህ መውጪያ መንገድ መኖር አለበት፡፡ በዙሪያዋ በሩን ለመስበር የሚጠቅም አንዳች መሳሪያ ካለ ቃኘች፡ ግድግዳውን በጥፍሮቻቸው ፍቀው ከእስር ያመለጡ እስረኞች እንዳሉ  አስታወሰች፡፡ እሷ ደግሞ የዓመታት ጊዜ
የላትም፡፡ ከጥፍር የጠነከረ መሳሪያ ያስፈልጋታል፡፡ ቦርሳዋን ፈታተሸች፡፡
ከዝሆን ጥርስ የተሰራ ማበጠሪያ፣ ሊፒስቲክ፣ መሃረብ፣ የባንክ ቼክ ቡክ፣
ገንዘብ፣ ከወርቅ የተሰራ ብዕር አላት፡፡ ሁሉም በር ለመክፈት አይጠቅሙም
የለበሰችውን ልብስ ተመለከተች፡፡ ቀበቶ ታጥቃለች: የቀበቶ ማያያዣው
ምናልባት በሩን ለመቦርቦር ሊጠቅም ይችል ይሆናል፡ ቡርቦራው ረጅም ጊዜ
ሊወስድ ይችላል ነገር ግን ከዚህ ሌላ አማራጭ የለም፡፡

ወደ በሩ አመራች፡፡ በሩ ከወፍራም እንጨት የተሰራ ነው፡፡ በሩን በሙሉ መቦርቦር አይኖርባትም፡፡ የተወሰነ ጥልቀት ከቦረቦረች ሊሰበር ይችላል፡፡ እንደገና ለእርዳታ ተጣራች፡፡ የሚሰማ የለም፡፡ቀበቶዋን ስትፈታ ቀሚሷ ወለቀ፡  ከዚያም ቀሚሷን አጠፈችና
አስቀመጠችው፡ የሚያያት ሰው ባይኖርም የሚያምር ፓንት አድርጋለች፡፡

በአራት ማዕዘን ቅርጽ ቦረቦረች፡ የቀበቶው ማያያዣ ጠንካራ ባለመሆኑ
ተጣመመ: ቢሆንም ቡርቦራዋን ቀጠለች፡፡ በመሃል በመሃል የድረሱልኝ
ጥሪዋን ታሰማለች፡፡ በትዕግስት ስትፈቀፍቅ የእንጨት ፍግፋጊ መሬቱ ላይ መርገፍ ጀመረ፡፡ እንጨቱ ለስለስ ያለ ነው፡፡ አየሩ እርጥበት ስላለው
ቡርቦራዋን በተስፋ ቀጠለች፡፡ ስትቦረቡር የቀበቶው ማያያዣ እየወለቀ
ያስቸግራታል፡፡ እያነሳች ትቀጥላለች፡፡  አምስት  ስድስት ጊዜ እየወደቀ
እያነሳች ብትቦረቡርም ስራው ፈቀቅ አልል ሲላት ለቅሶዋን ለቀቀችው፡
በሲቃ በሩንም በጡጫ ደበደበች፡፡

ከውጨው ድምጽ ተሰማ፡፡ ‹‹ሰው አለ እዚህ›› አለ ድምጹ፡፡

ድምጹን ስትሰማ በሩን መደብደቧን አቆመች፡፡ በትክክል ድምጽ
ሰምታለች፡፡ ‹‹የሰው ያለህ! ከዚህ አውጡኝ›› አለች፡፡
‹‹ናንሲ አንቺ ነሽ?››
ናንሲ ልቧ በደስታ ዘለለ፡፡ የሰማችው ድምጽ የእንግሊዛውያን ቅላጼ
ያለው ነው፡፡ ድምጹንም አወቀችውና ‹‹መርቪን! ተመስገን አምላኬ!›› አለች፡፡
‹‹አንቺን ያልፈለግሁበት ቦታ የለም፡፡ እዚህ ምን ትሰሪያለሽ?››
‹‹ከዚህ ማጥ አውጣኝ መርቪኔ››

መርቪን በሩን ነቀነቀው፡፡ ‹‹ተዘግቷል!›› አላት
‹‹በጎን በኩል ና››
‹‹መጣሁ››
‹‹መርቪን?!››
‹‹በሩ ተቀርቅሯል፡፡ ትንሽ ጠብቂኝ›› አለ መርቪን፡፡
‹‹በፓንትና በስቶኪንግ ብቻ መሆኗ ትዝ አላትና ገላዋን በኮቷ ሸፈነች፡
ጥቂት ደቂቃ ቆይቶ በሩ ወለል ብሎ ተከፈተ፡፡ ሮጣ መርቪን ደረት ላይ
ተለጠፈች፡፡ ‹‹እዚህ ሞቼ እቀር ነበር›› አለችና ለቅሶዋን ለቀቀችው::
መርቪንም ደረቱ ላይ እንደተለጠፈች ጸጉሯን እያሻሽ ‹‹አይዞሽ
አይዞሽ!›› አላት፡፡
‹‹ፒተር ነው እዚህ የዘጋብኝ›› አለች ዓይኗ እምባ አቆርዝዞ::
‹‹ይሄ ወንድምሽ የሆነ በድብቅ የሚሰራው ነገር ሳይኖር አይቀርም፡፡
ወንድምሽ ርጉም ሰው ነው፡፡››
በአሁኗ ደቂቃ ናንሲ  ስለወንድሟ ሳይሆን ስለመርቪን ነው
የምታስበው፡፡ በእምባ በተንቆረዘዙ ዓይኖቿ መላ አካላቱን ቃኘችና ጊዜ
ሳታጠፋ ፊቱን አገላብጣ ሳመችው፡፡ ለጠቀችና ከንፈሮቹን በስሜት
ጨመጨመቻቸው፡ በዚህ ጊዜ የወሲብ ፍላጎቷ በእጅጉ ተነሳሳ፡፡ እሱም
አላሳፈራትም፡፡ እጆቹን ሰደደና ደረቱ ውስጥ ከቶ እቅፍ አደረጋት፡ እሷም
የእሱን ገላ ስለተራበች ከእቅፉ ውስጥ መውጣት አልፈለገችም፡: እጆቹን ወደ
ቂጧ ሲሰድ ፓንቷን ነካና ደንገጥ ብሎ አቆመ:

‹‹ቀሚስሽ የት ሄደ?›› ሲል ጠየቃት፡፡

‹‹በሩን ለመፈግፈግ ብዬ ቀበቶዬን ፈትቼው ስለነበር ቀሚሴም ያለቀበቶ
ወገቤ ላይ መቆም ስላልቻለ አሽቀንጥሬ ጣልኩት›› አለች እየሳቀች፡፡
‹‹እንዴት ጥሩ አጋጣሚ ነው›› አለና እጁን ሰዶ ቂጧንና ጭኗን መደባበስ ያዘ፡፡ በዚህ ጊዜ ብልቱ ቆሞ ሆዷን ሲነካካት ታወቃት፡ እሷም ሱሪው ውስጥ እጇን ከታ ብልቱን ታሻሸው ጀመር፡
😎ጠላፊዎቹ

#ክፍል_አርባ_ሰባት

#በኬንፎሌት

#ትርጉም_ወንዳየሁ_ንጉሴ


ከሼዲያክ ወደ ቤይ ኦፍ ፈንዲ

አይሮፕላኑ ከካናዳ ወደ ኒውዮርክ ሲያቀና ማርጋሬት በጭንቀት ተወጥራለች ሄሪን ምን ዋጠው?› እያለች ታስባለች፡፡

ፖሊሶች ሄሪ በሃሰት ፓስፖርት እንደሚጓዝ አውቀዋል፡፡ ተሳፋሪዎቹም
ይህን ነው የተገነዘቡት፡ ፖሊሶቹ እንዴት እንደደረሱበት አልገባት ብሏታል ከያዙት ምን እንደሚያደርጉት ነው ያልታወቀው:: ምናልባትም ወደ እንግሊዝ አገር ይመልሱትና ጌጣጌጦቹን በመስረቁ እስር ቤት ይወረውሩት ይሆናል፤ ወይም ወደ ጦር ሰራዊት ውስጥ ይጨምሩታል። ታዲያ እንዴት ልታገኘው ነው?

እስካሁን እንዳልያዙት ግን አውቃለች፡፡ ለመጨረሻ ጊዜ ያየችው ሼዲያክ ላይ አይሮፕላኑ ሲያርፍ ወደ መታጠቢያ ቤት ሲገባ ነው፡ ታዲያ ያኔ ይሆን ያቀደው? ችግር እንደደረሰበት አውቋል ማለት ነው፡፡
ፖሊሶቹ አይሮፕላኑን በሙሉ ቢያስሱም አላገኙትም፡፡ አይሮፕላኑ ሲያርፍ ሾልኮ ጠፍቷል ማለት ነው:: ታዲያ የት ሄደ? ምናልባትም
ከአይሮፕላኑ ወርዶ ጫካ ጫካውን እያሳበረና ሊፍት እየጠየቀ ሄዶ ይሆናል፡
ታዲያ ከዚህ በኋላ በዓይነ ስጋ ታየው ይሆን?

በዚህ ተስፋ መቁረጥ እንደሌለባት ተገንዝባለች፡፡ ሄሪን በማጣቷ ብትጎዳም ናንሲ አለችላት፡፡

አባቷ  ዓላማዋን ከማሳካት አያግዷትም፡ ለራሳቸው  ሁሉ ነገር የጠመመባቸውና ስደተኛ ስለሆኑ የማስገደድ ኃይላቸው ተዳክሟል፡ ሆኖም እንደ ቆሰለ አውሬ እንደገና አገርሽቶባቸው ዓላማዋን የሚያሰናክል ነገር ያደርጉ ይሆናል፡፡
አይሮፕላኑ ሽቅብ መጎኑን ጨርሶ የመቀመጫ ቀበቶዋን ፈትታ ናንሲን ለማነጋገር ሄደች።

አስተናጋጁ ለምሳ ጠረጴዛ እያዘጋጀ ነው፡፡ አባቷ ቦታቸው ላይ ቁጭ
ብለዋል ኦሊስ ፊልድ ከፍራንክ ጎርደን ጋር በካቴና ተጠፍሮ ቁጭ ብሏል፡
ማርጋሬት ወደ ሙሽሮቹ ክፍል ሄዳ ደጋግማ አንኳክታ ምላሽ ስታጣ በሩን
ከፈተች፤ ማንም የለም፡፡

በድንጋጤ ክው አለች፡፡

ምናልባትም ናንሲ መታጠቢያ ክፍል ውስጥ እየተቆነጃጀች ይሆናል፡
መርቪን ላቭሴይ የት ሄደ? ወደ መታጠቢያ ክፍል የሄደ ከሆነ ታየው ነበር ክፍሉ ውስጥ አንድ ቦታ ተደብቀው እንደሆን ቃኘች፡፡ ነገር ግን ምንም መደበቂያ የለም፡፡

የናንሲ ወንድም ፒተርና ጓደኛው የሙሽሮቹ ክፍል አጠገብ ተቀምጠዋል፡ ‹‹ሚስስ ሌኔሃን የት ነች?›› ስትል ጠየቀችው ፒተርን

‹‹ሼዲያክ ላይ ነው የወረደችው››

‹‹ምን አልክ?›› ስትል ጠየቀችው ‹‹አንተ እንዴት አወቅህ?››

‹‹ነግራኛለች››

‹‹ለምን ግን?›› ስትል ጠየቀችው ‹‹ለምንድነው የወረደችው?››

ፒተር የተሰደበ ያህል ተሰማው፡ ‹‹እኔ እንጃ›› ሲል መለሰላት፡ ‹‹ወደ ኒውዮርክ እንደማልሄድ ለፓይለቱ ንገርልኝ ነው ያለችኝ›› አላት ፊቱን አኮሳትሮ፡፡

ማርጋሬት ፒተርን በጥያቄ ማጣደፍ ነውር መሆኑን ብታውቅም አጥብቃ መጠየቁን አላቋረጠችም:፡ ‹‹ናንሲ የት ሄደች?››

ፒተር በዚህ ጊዜ አጠገቡ ያለውን ጋዜጣ አነሳና ‹‹እኔ የማውቀው ነገር የለም›› ሲል መልስ ሰጥቷት ማንበቡን ቀጠለ

ማርጋሬት ሆድ ባሳት፡ ናንሲ እንዴት እንዲህ ታደርጋለች አለች ምን ያህል በእሷ ላይ ተስፋዋን እንደጣለች ታውቃለች፡ ሆኖም
ነገር ሳይገጥማት ከመንገዷ አልተስተጎለችም መልእክት ትታ ይሆናል።

ከአስተያየቱ የነገራት ውሽቱን እንደሆነ ጠረጠረች ማርጋሬት እንደ ፖሊስ ስለመረመረችው ደስ አላለውም፡፡ በደመነፍስ ‹‹እውነቱን አይደለም
የነገርከኝ›› ስትል አፈጠጠችበት፡፡ አባባሏ ትክክል ባይሆንም ምላሹን ግን ትጠብቃለች፡፡

ፒተር ፊቱ በንዴት ቲማቲም መስሏል፡ ‹‹እንደ አባትሽ ጋጠወጥ ነሽ ከፊቴ ጥፊ!›› አላት፡

የፒተር ስድብ አንገቷን አስደፋት። ያባትሽን መጥፎ ባህሪ ይዘሻል ከሚል ስድብ በላይ የምትጠላው ነገር የለም፡፡ ምንም ሳትተነፍስ ውልቅ ብላ ሄደች፤ በዓይኗ እንባ እንደሞላ አልፋ ስትሄድ ውቧን የመርቪንን ሚስት ዳያና ላቭስሌይን አየቻት። አይሮፕላኑ ውስጥ ያለው ተጓዥ በሙሉ ባሏን
ከድታ ከፍቅረኛዋ ጋር ስለኮበለለችው ሚስትና መልሶ በእጁ ለማስገባት አገር አቋርጦ ስለተከተላት ባሏና ቦታ አጥቶ ባሏ ከሞተባት ሴት ጋር በሙሽሮች ክፍል ውስጥ ለመዳበል የመገደዱን ወሬ በደስታ እየተቀባበለ ሲያወጋ ነው የሰነበተው፡፡ ማርጋሬት ባሏና ናንሲ የት እንደገቡ ዳያና ታውቅ እንደሆን መጠየቅ ፈለገች፡፡ በርግጥ ይህን ጥያቄ መጠየቅ የሚያሳፍር ቢሆንም መጥፋታቸው አሳስቧታል፡፡ ዳያና አጠገብ ተቀመጠችና ‹‹ይቅርታ መርቪንና ናንሲ የት እንደገቡ ታውቂ ይሆን?›› ስትል ጠየቀቻት፡ ዳያና ጥያቄው አስገርሟት ‹‹ምን ሆኑ? በሙሽሮች ክፍል ውስጥ የሉም እንዴ?››

‹‹ጭራሽ አይሮፕላኑ ውስጥ የሉም፡፡ እኛ ስንሳፈር እነሱ ቀርተዋል››

‹‹እውነት?›› ዳያና ደነገጠች አጠፋፋቸውም እንቆቅልሽ ሆኖባታል፡
‹‹እንዴት ሊሆን ይችላል? አይሮፕላኑ አመለጣቸው እንዴ?››

‹‹የናንሲ ወንድም ጉዞውን ለማቋረጥ ወስነዋል ቢልም አላመንኩትም›› አለች ማርጋሬት፡፡

ሁለቱም ለኔ የነገሩኝ ነገር የለም›› አለች ዳያና፡፡ ‹‹ብቻ ክፉ ነገር.አይድረስባቸው::››

‹‹ምን ማለትሽ ነው ማርዬ?›› ሲል ጠየቃት ፍቅረኛዋ፡፡

‹‹ክፉ አይንካቸው ነው ያልኩት?››

ማርጋሬትም የዳያናን ሃሳብ መቀበሏን ራሷን በመነቅነቅ ገለጸች፡

‹‹ወንድምየውን ግን አላመንኩትም፡፡ የተናገረው ውሸት ይመስለኛል››

ማርክም ቀበል አደረገና ‹‹እኔም ይመስለኛል፡፡ አሁን አየር ላይ ስለሆንን የሚሆነውን ከመጠበቅ በስተቀር ማድረግ የምንችለው ነገር የለም››
‹‹ከዚህ በኋላ የሚያደርገው ነገር አያገባኝም›› አለች ዳያና መናደዷ በግልጽ እየታወቀባት፡፡ ‹‹የአምስት ዓመት ባሌ ስለሆነ ግን ክፉ እንዲያገኘው አልፈልግም፤ ያስጨነቀኝ ደግሞ ይኸው ነው››

‹‹አሜሪካ ስንደርስ ከእሱ መልእክት እናገኝ ይሆናል›› አለ ማርክ በማስተዛዘን አይነት፡፡

‹‹እስቲ እሱ ይሁነና›› አለች ዳያና፡፡

አስተናጋጁ የማርጋሬትን ክንድ ነካ አደረገና ‹‹ክብርት ማርጋሬት ምሳ ደርሷል፧ ቤተሰቦችሽ ለመብል ተሰይመዋል›› አላት

‹‹አመሰግናለሁ›› አለች ማርጋሬት ‹የምግብ አፒታይቴ ተዘግቷል፡፡››

ማርጋሬት ለመሄድ ስትነሳ ዳያና ‹‹ከናንሲ ጋር ወዳጅ ናችሁ?›› ስትል ጠየቀቻት፡፡
በፋብሪካዋ ውስጥ ስራ ልትቀጥረኝ ቃል ገብታልኝ ነበር›› አለች ማርጋሬት በምሬት፡፡ ከንፈሯን እንደነከሰች ዞራ ሄደች፡፡

እናትና አባቷ እንዲሁም እንዲሁም ፔርሲ የመጀመርያው ዙር ምግብ
ቀርቦላቸዋል፡ ማርጋሬትም እንደተቀመጠች ‹‹ይቅርታ አባባ ስለዘገየሁ››
አለች፡፡ የቀረበላትንም ምግብ ትቆነጣጥራለች፡ አልቅሽ አልቅሽ አላት፡ ሄሪና
ናንሲ ሳይነግሯት እብስ ብለዋል፡ አሁን የሚረዳት የለም፡ እንደ እህቷ
ኤልሳቤት ለመኮብለል አስባ ነበር አሁን ግን ሁሉ ነገር ተበላሽቶባታል፡

ሁለተኛው ዙር ምግብ ቀረበ፡፡ ሾርባ ነው፡፡ ሾርባውን አንድ ጊዜ ፉት
አደረገችና ተወችው: ድካምና ንዴት በአንድ ላይ ተሰማት አሟታል፡ የምግብ ፍላጎቷ ተዘግቷል፡ ምቹው አይሮፕላን እስር ቤት
ሆኖባታል፡ ለሃያ ሰባት ሰዓት ስለበረሩ ጉዞው ሰልችቷቸዋል፡ እናቷ
😎ጠላፊዎቹ

#ክፍል_አርባ_ስምንት

#በኬንፎሌት

#ትርጉም_ወንዳየሁ_ንጉሴ


ድንገት የሞተሩ ድምጽ ተለወጠ፤ሁሉም ተሳፋሪ የሆነውን ሁሉ ባለማወቁ በፍርሃት ረጭ አለ፡፡ አይሮፕላኑ ተንቀጠቀጠና ወደ ታች መውረድ ጀመረ፡

አራቱም ሞተሮች በአንድ ጊዜ ሲጠፉ የኤዲም ዕጣ ፈንታ አብሮ ተዘጋ።

ችግር ከመከሰቱ በፊት ሃሳቡን ቢለውጥ ኖሮ ይሄ ችግር አይመጣም፡፡
ሃሳቡ በውጥን ላይ ብቻ ቢቀር አይሮፕላኑ ሰላማዊ መንገዱን ይጓዝ ነበር
አሁን ግን ምንም ሆነ ምን ችግሩ ዓይኑን አፍጥጦ ጥርሱን አግጦ መጥቷል፡፡ ከዚህ በኋላ እንደተሳፋሪ መብረር ካልሆነ በስተቀር የበረራ መሀንዲስ መሆን አይችልም፡፡ አልቆለታል። በንዴት ስህተት እንዳይሰራ
መጠንቀቅ አለበት፡ ይህን ዕቅድ በርጋት መከወን አለበት፡፡ ከዚያ በኋላ
ህይወቱን ያመሰቃቀሉበት ርጉሞች ላይ ይዘምታል።

አይሮፕላኑ በድንገት ባህር ላይ ማረፍ ሊገደድ ነው: ሚስቱን ያገቱበት ወሮበሎች አይሮፕላኑ ላይ ይወጡና ፍራንክ ጎርዲኖን ያስፈታሉ፡ ከዚያ በኋላ የሚሆነው አይታወቅም:፡ ካሮል አን ደህና ስለመሆኗ ምንም ማረጋገጫ የለም፡፡ ወሮበሎቹ ወደ አይሮፕላኑ ሲመጡ የጠረፍ ጠባቂ
ፖሊሶች አደጋ ይጥሉባቸው ይሆናል፡፡ ኤዲ በዚህ ስራ ውስጥ ለፈጸመው እስር ቤት ይወረወር ይሆናል፡፡ እሱ እጣ ፈንታው ሆኖ እዚህ ውስጥ በመግባቱ ነው
ለእስር  የሚበቃው።ካሮል አንን በደህና እጁ እንዳስገባ ሌላ የሚፈልገው ነገር የለም::

የአይሮፕላኑ ሞተሮች ቀጥ ካሉ ከአፍታ በኋላ የካፒቴን ቤከር ድምጽ በጆሮ ማዳመጫው መጣና ‹‹ምንድነው ነገሩ?›› ሲል ጠየቀ፡፡

ኤዲ በድንጋጤ አፉ ስለደረቀበት ከመናገሩ በፊት ሁለት ጊዜ ምራቁን ዋጥ አደረገ ‹‹ገና አላወቅሁትም›› አለና  መለሰ፤ ነገር ግን መልሱን ያውቃል፡ ሞተሮቹ መስራት ያቆሙት ነዳጅ ስላለቀ ነው፡፡ እሱ ነው ነዳጅ
ወደ ሞተሮቹ እንዳይደርስ ሆን ብሎ ያደረገው። አይሮፕላኑ ስድስት የነዳጅ
ታንከሮች ያሉት ሲሆን ነዳጅ ወደ ሞተሮቹ የሚያደርሰው ክንፉ ላይ ባሉት
ታንከሮች አማካይነት ነው፡፡ ወደ ሞተሮቹ ነዳጅ
የሚያመጡትን ፓምፖች ሆን ብሎ እንዳይሰሩ አድርጓቸዋል፡፡ ሌላ ኢንጂነር
ቢያየው ሆን ብሎ እንዳይሰሩ እንደተደረጉ ያውቅበታል፡

ረዳት ኢንጂነሩ ሚኪ ፊን ተራው ባይደርስም ድንገት ሊመጣ ይችላል ብሎ ተጨንቋል፡ ነገር ግን ሚኪ እንቅልፉን እየለጠጠ ይሆናል ይህን ጊዜ፡
በረራው ረጅም ጊዜ የሚወስድ በሚሆንበት ጊዜ ከስራ ውጭ ያሉ
የአይሮፕላኑ ሰራተኞች ይተኛሉ፡

ሼዲያክ ላይ ሁለት ጊዜ አስፈሪ የፖሊስ ምርመራዎች ነበሩ፡
የመጀመሪያው ፖሊሶች አይሮፕላኑ ላይ የተሳፈረውን የፍራንኪ ጎርዲኖ
ግብረ አበር ስም ማወቃቸውን ገልጸው ነበር፡፡ ኤዲ ሉተርን ማለታቸውን
ገምቷል በዚህም ምክንያት ሉተር  አልቆለታል ብሎ  ካሮል አንን የሚያስለቅቅበትን ሌላ ስልት ማውጠንጠን ጀምሮ ነበር፡፡ በኋላ ደግሞ
ፖሊሶቹ ሄሪ ቫንዴርፖስትን እንደሚፈልጉ ሲገልጹ ኤዲ ጮቤ ረገጠ፡፡ከድንጋጤው መለስ ሲል ከሃብታም ቤተሰብ የተወለደ የሚመስለው ቫንዴርፖስት ለምን በሀሰት ፓስፖርት እንደሚጓዝ ገርሞታል፡የፖሊሶችን ትኩረት ከሉተር ወደ ራሱ እንዲዞር በማድረጉ ቫንዴርፖስትን በሆዱ እግዚአብሔር ይስጥህ  ብሎታል፡።
ፖሊሶችም በምርመራው  ብዙም ሳይገፉበት ርግፍ አድርገው ተዉት፡ ስለዚህ ሉተር ተረዳና በዕቅዱ መሰረት እነ ኤዲ የጀመሩትን ሊያከናውኑ ተነሱ፡፡
የፖሊሶችን

ለካፒቴን ቤከር ግን የተፈጸመው ሁሉ ጥርጣሬን የሚቀሰቅስ ሆኖበታል፡፡ ኤዲ ገና ከድንጋጤው ሳያገግም አንድ ድንገተኛ ሃሳብ ይዞ ብቅ አለ፡፡ አይሮፕላኑ ላይ ጎርዲኖ
ተባባሪ አለው ማለት እሱን ነጻ ለማውጣት የተዘጋጀ ሰው አለ ሲል ደመደመ፡፡ ስለዚህ ጎርዲኖን ከአይሮፕላኑ ላይ ማስወረድ ፈለገ፡፡ ይህ ማለት ደግሞ የኤዲ እቅድ ውሃ በላው ማለት ነው፡፡

ህግ እንዳይከበር በማድረጉ በህግ እንደሚጠይቀው የኤፍ.ቢ.አዩ ኦሊስ ፊልድ ካፒቴን ቤከር ላይ ዝቶ ነበር፡፡ በመጨረሻ ካፒቴኑ ኒውዮርክ ለሚገኘው ለፓን አሜሪካን አየር መንገድ መስሪያ ቤት ስልክ ደውሎ ለችግሩ መፍትሄ እንዲሰጡ ነገራቸው፡፡ አየር መንገዱም ጎርዲኖ በአይሮፕላኑ
መጓዙን እንዲቀጥል ሲፈቅድለት ኤዲም በእፎይታ ተነፈሰ፡፡

ሼዲያክ ላይ አንድ አስደሳች መልዕክት ደረሰው፡፡ የመጣው የኮድ
መልዕክት ከጓደኛው ስቲቭ አፕል ባይ መሆኑ አያጠራጥርም፡ መልዕክቱም አንድ የባህር ኃይል ጀልባ አይሮፕላኑ የሚያርፍበት አካባቢ ጥበቃ እያደረገ መሆኑንና እንዳይታወቅ ከእይታ ውጭ ሆኖ ወደ አይሮፕላኑ የሚጠጋ ማንኛውንም ጀልባ ለመምታት የተዘጋጀ መሆኑን ይገልጻል፡

ይሄ ለኤዲ ትልቅ ነገር ነው፡፡ በኋላ ወሮበሎቹ ከህግ እንደማያመልጡ
ማረጋገጫ ቢሰጠውም ዕቅዱ ግን ያለምንም እንከን ባሰበው መልኩ
እንዲጠናቀቅ እንቅፋት እንዳይፈጠር ምኞቱ ነው፡፡
ካፒቴን ቤከር ወደ ኤዲ መጣ፡፡ ኤዲ እጁ እየተንቀጠቀጠ ለሞተሩ ነዳጅ የሚመግበውን ፓምፕ ከፈተውና ‹‹ታንከሩ ባዶ ስለሆነ ሞተሩ አልነሳ አለ›› አለው::

‹‹ለምን?›› ሲል ካፒቴኑ ተቆጣ፡፡

ኤዲ መልስ አልነበረውም፡፡
የአይሮፕላኑ መሳሪያዎች በመጠባበቂያ ነዳጅና በመጋቢ ቧንቧዎቹ
መካከል የነዳጅ እንቅስቃሴ ወይም ግፊት መኖሩን አያሳዩም፡ ፓይለቶቹ ጋ
ግን የነዳጅ ሁኔታን የሚያሳዩ የነዳጅ መቆጣጠሪያዎች አሉ ካፒቴኑ ሁሉንም በየተራ አየና ‹‹ምንም ነዳጅ የለም›› አለ፡፡ ‹‹በክንፉ ላይ ባለው
ታንከር ውስጥ ምን ያህል ነዳጅ አለን?›› ሲል ጠየቀ፡፡
‹‹ትንሽ ነው የቀረው - የተወሰኑ ኪሎ ሜትሮች ብቻ የሚያስኬድ››
‹‹እንዴት ነው ይህን ያላስተዋልከው?›› ሲል ጠየቀ በቁጣ፡

‹‹እኔ ፓምፕ እያደረገ ነው የመሰለኝ›› አለ ኤዲ በተቆራረጠ ድምጽ
ይህ መልስ ግን ካፒቴኑን አላጠገበውም፡፡

‹‹ሶስቱም ፓምፖች እንዴት ባንድ ጊዜ ስራ ሊያቆሙ እንደቻሉ አልገባኝም›› አለ ካፒቴኑ።

‹‹ቶሎ ባህር ላይ ካላረፍን የቀረው ነዳጅ ተንጠፍጥፎ አይሮፕላኑ ሊወድቅ ይችላል›› አለ ኤዲ፡፡

‹‹ባህር ላይ ልናርፍ ስለሆነ ሁላችሁም ተዘጋጁ›› አለ ቤከር፡፡ ጣቱንም ኤዲ ላይ እያወዛወዘ ‹‹አንተ አታስፈልገኝም አላምንህም›› አለው፡

ኤዲ ሞቱን ተመኘ፡፡ ካፒቴኑ ላይ ክህደት ለመፈጸም በቂ ምክንያት እንዳለው ቢያውቅም የፈጸመውን ድርጊት አልወደደውም፡ ህይወቱን በሙሉ
ሃቀኛ ሆኖ ነው የኖረው:: አጭበርባሪዎችንና አታላዮችን አጥብቆ ይጠላ
ነበር፡፡ አሁን ግን የሚጠላውን ነገር ለማድረግ ተገዷል፡
ካፒቴኑ ናቪጌተሩ ጋ በመሄድ ቻርቱ ላይ ዓይኑን ተከለ፡፡ ናቪጌተሩ ጃክ
አሽፎርድ ኤዲን በግርምታ ገረመመውና ‹‹አሁን ያለነው እዚህ ላይ ነው››
ብሎ ቻርቱ ላይ በመጠቆም ለካፒቴኑ አሳየው፡፡

የኤዲ ዕቅድ ሊሳካ የሚችለው አይሮፕላኑ እሱ ባሰበው ቦታ ከወረደ
ነው፡፡ ወሮበሎቹ እዚህ ቦታ ላይ ነው የሚጠብቁት፡፡ ነገር ግን ድንገት
የሚፈጠር ነገር ካለ ከታሰበው ውጭ ሊደረግ ይችላል፡፡ ካፒቴኑ ሌላ ቦታ
ከመረጠ ግን ኤዲ እሱ ያለው ቦታ የተሻለ ስለሆነ እዚያ ማረፍ እንዳለበት
ካፒቴኑን ማሳሰቡ አይቀርም፡፡ ካፒቴኑ ሊጠረጥር ቢችልም እዚህ ቦታ ከማረፍ የተሻለ ነገር እንደሌለ በሎጂክ መቀበል ይኖርበታል፡ ሌላ ቦታ
እንዲያርፍ የሚያደርግ ከሆነ ግን ትክክል የማይሆነው እሱ ነው፡፡ ስለዚህ የእሱ ጣልቃ ገብነት አያስፈልግም ማለት ነው፡፡ ትንሽ ቆየና ‹‹እዚህ ጋ ነው የምናርፈው›› አለ ካፒቴኑ፡
😎ጠላፊዎቹ

#ክፍል_አርባ_ዘጠኝ

#በኬንፎሌት

#ትርጉም_ወንዳየሁ_ንጉሴ

‹‹እሺ›› አለ ቪንቺኒ ወደ ጀልባዋ ፊቱን አዞረና ‹‹ጆ መጀመሪያ አንተ ና
ቀጥሎ ትንሹ ልጅ በመጨረሻ የኤዲ ሚስት፡፡›› ወደ ውስጥ ሲያዩ ካፒቴኑ ወደ አይሮፕላን መንጃው ክፍል ሲሄድ አየው፡፡ በዚህ ጊዜ ቪንቺኒ ሽጉጡን
መዘዘና ‹‹አንተ ባለህበት ቁም›› ሲል አዘዘው ቤከርን፡፡
ኤዲም ካፒቴን እንደሚልህ አድርግ እባክህ እነዚህ ሰዎች ቀልድ አያውቁም›› አለ ቤከር ባለበት ቆመና እጁን ወደ ላይ አነሳ፡፡

ጆ የተባለው ወሮበላ ‹‹እዚህ ውስጥ ብወድቅ መዋኘት አልችልም›› አለ
ከጀልባው ወደ አይሮፕላኑ መዝለል ፈርቶ፡፡

‹‹መዋኘት አያስፈልግም›› አለ ኤዲ እጁን ዘረጋለት፡፡

ጆም እንደምንም ዘለለና አይሮፕላኑ ውስጥ ገባ፡፡
ከእሱ በፊት ሁለት ሰዎች በደህና መዝለላቸውን አይቶ ትንሹ ልጅ ኮራ ብሎ ዘለለ፤ ነገር ግን ሲዘል ሚዛኑን ሳተና ወደኋላው ሊወድቅ ሲል ኤዲ የልጁን ቀበቶ ይዞ አዳነው ‹‹አመሰግናለሁ›› አለ ልጁ፡፡

አሁን የካሮል አን ተራ ደረሰ ለመዝለል ፈርታ የኤዲን አይን አይን ታያለች በተፈጥሮዋ ፈሪ ሆና ሳይሆን ከእሷ በፊት ትንሹ ልጅ ተንገዳግዶ ባህር ውስጥ ሊገባ ሲል ስላየች ነው የፈራችው፡፡ ኤዲም ፈገግ አለና
‹‹እንደነሱ ዝለይ ማርዬ›› አለ ‹‹አይዞሽ ውሃ ውስጥ አትወድቂም::››

ኤዲ በፍርሃት ልቡ እየደለቀ በጉጉት ጠበቀ ሚስቱ እስክትዘል፡፡ ካሮል
አን መዝለል መቻሏን ተጠራጠረች፡፡ ‹‹ተዘጋጂና ዝለይ!›› አላት እሱም የእሷ
ፍርሃት ተጋብቶበት፡፡

ካሮል አን ጥርሷን ነክሳ እንደ ምንም ዘለለች፤ ነገር ግን ግማሽ አካሏ ባህሩ ውስጥ ሆኖ ገመዱን ለመያዝ ተፍጨረጨረች፤ ‹‹ገመዱን አጥብቀሽ
ያዥ አይዞሽ›› አለ ወደ ባህሩ የምትወድቅ ከሆነ ለመዝለል ተዘጋጅቶ
ኤዲ ተንበረከከና እጇን ለመያዝ እጁን ሰደደ፤ ሆኖም ሚዛኑን ሳተና ወደ
ባህሩ ሲወድቅ እጇን መያዝ አልቻለም፤ የባህሩ ሞገድ ጎትቶ ውሃ ውስጥ
ሲያስቀራት በተስፋ መቁረጥ ጮኸች፡፡

ያለ የሌለ ሀይሏን ተጠቅማ ወደ ኤዲ እየዋኘች ተጠጋች፤ ኤዲ ጥርሷ
ሊንገጫገጭ አየ፧ እንደ ምንም ብሎ እግሯን ያዘ፤ ሆኖም የባህሩ ሞገድ
ሃይለኛ በመሆኑ ከእጁ አፈተለከችና እንደገና ባህሩ ላይ ወደቀች፤ ካሮል አን
እየሰመጠች ነው እሱም እጁን ሰደደና ወገቧን ያዘ፡፡

‹‹አይዞሽ የኔ ማር ይዤሻለሁ›› አለና እንደምንም ተሸክሞ ወደ
አይሮፕላኑ አስገባት፡፡ ካሮል አን ባሏ  እቅፍ ውስጥ ገብታ ማንባቷን ቀጠለች፡፡ እምባ ቢተናነቀውም እንደምንም ዋጥ አደረገው፡፡የምትንቀጠቀጠውን
ሚስቱን ለማረጋጋት አጥብቆ ደረቱ ላይ ለጠፋት
‹‹ደህና ነሽ የኔ ማር? እነዚህ ሰዎች አንገላቱሽ?›› ሲል ጠየቃት

‹‹ደህና ነኝ›› አለች ጥርሷ እየተንገጫገጨ፡፡

የካፒቴኑን ዓይን ለማየት ፈርቶ እየሰረቀ ያየዋል፡፡ ቤከር ወደ ካሮል
አን አማተረና
‹‹ያደረግኸው ሁሉ ለምን እንደሆነ አሁን እየገባኝ መጣ›› አለ፡፡
‹‹ይበቃል የምንሰራው ስራ አለን›› አለ ቪንቺኒም፡፡
ኤዲ ካሮል አንን ለቀቃትና ‹‹እሺ ወደምትፈልጉት ሰው እወስዳችኋለሁ››
‹‹እሺ›› አለ የወሮበሎቹ መሪ፡
‹‹ተከተሉኝ›› አላቸውና ወደ ውስጥ ገቡ፡ ሰራተኞቹ ምንም ነገር ለማድረግ እንዳይሞክሩ ኤዲ አስጠነቀቃቸው:
‹‹ሁላችሁም አደብ ግዙ፡፡ እነዚህ ሰዎች አድርጉ የሚሏችሁን ማድረግ
ብቻ ነው ያለባችሁ አለበለዚያ በጥይት ከመግደል ወደ ኋላ የሚሉ ሰዎች አይደሉም፡ ሰው እንዲጎዳ አልፈልግም፡ ካፒቴኑም ይህንኑ ነው የሚላችሁ አለ ኤዲ፡

‹‹ትክክል ነው›› አለ ካፒቴኑ ‹‹ጎበዝ! እነዚህ ሰዎች መሳሪያ የያዙ ናቸው፤ ብትወራጩ በጥይት ነው የሚሏችሁ ››
ኤዲ ወደ ቪንቺኒ ዞረና ‹‹እንሂድ እንግዲህ፤ ካፒቴን ተሳፋሪዎቹን ማረጋጋት ይኖርብሃል›› አለ፡፡

ቪንቺኒ በኤዲ አባባል መስማማቱን በራሱ ንቅናቄ አሳየ፡
‹‹ካሮል አን ከአይሮፕላኑ ሰራተኞች ጋር ሁኚ፧ እሺ›› አላት፡፡

ኤዲ ሚስቱ ከወሮበሎቹ ጥይት መራቋን ወዶታል፡ በተጨማሪም ባሏ
ለምን እነዚህን ሰዎች ሊተባበር እንደወሰነ ለተሳፋሪዎቹ ታስረዳለታለች፡
ኤዲ ቪንቺኒን ‹‹እባክህ ጠመንጃህን ከተሳፋሪዎች ብታርቅልኝ፧ ይፈራሉ››
‹‹ተነፋ!›› አለ ቪንቺኒ ‹‹እንሂድ›› ሲል አዘዘ ጓደኞቹን፡ ኤዲ ትከሻውን
በንዴት ነቀነቀ፡፡ ሁሉም ቦታ ቦታቸው ላይ እንደተቀመጡ ነው፡፡ ሁለቱ አስተናጋጆች ምንም እንዳልተፈጠረ ሁሉ ለማረጋጋት ጥረት እያደረጉ ነው፡፡
ኤዲ አይሮፕላኑ ውስጥ እየተዘዋወረ ሲያይ መብል ክፍሉ ትርምስምስ
ብሏል፡፡ ወለሉ በሸክላ እና በብርጭቆ ስብርባሪ ተሸፍኗል። ምግብ ተበልቶ
ስላለቀና ተሳፋሪዎች እየጠጡ ስለሆነ የተደፋፋ ነገር አይታይም፡:
ተሳፋሪዎቹ የቪንቺኒን ሽጉጥ ሲያዩ በፍርሃት ድምጻቸውን አጠፉ፡፡ ካፒቴን
ቤከር ወደ ፊት መጣና ‹‹ክቡራንና ክቡራት ለተፈጠረው ችግር ይቅርታ
እጠይቃለሁ፡ ከመቀመጫችሁ እንዳትነሱ፡ አሁን ያለው ችግር ከተወሰነ
ደቂቃ በኋላ መፍትሄ ያገኛል›› አለ፡፡

ኦሊስ ፊልድና ፍራንኪ ጎርዲኖ አብረው ቁጭ ብለዋል አሁን ነፍሰ
ገዳይ እንዲያመልጥ ላደርግ ነው አለ ኤዲ ለራሱ፡ ወደ ጎርዲኖም ጣቱን እየጠቆመ ‹‹ያውልህ ሰውዬህ ውሰደው›› አለ፡፡
ኦሊስ ፊልድ ከተቀመጠበት ተነሳና ‹‹ይሄ የኤፍ ቢ አይ መርማሪ ቶሚ ማክ አርድል ነው›› አለ ‹‹ፍራንኪ ጎርዲኖ ትላንት በመርከብ ኒውዮርክ ደርሶ ወህኒ ገብቷል››
‹‹የአምላክ ያለህ!›› ሲል ኤዲ በግርምት ጮኸ፡፡ ይህን ሁሉ እኩይ ተግባር ሲፈጽም የነበረው ለአስመሳይ ሰው ነው?!

‹‹እኛ ከፍራንኪ ጉዳይ የለንም፡፡ ጀርመናዊው ሳይንቲስት የታለ?›› አለ ቬኒቺኒ

ኤዲ ተገርሞ ቪንቺኒ ላይ አፈጠጠ፡፡ ጎርዲኖን አይፈልጉትም፡፡ ታዲያ
ማንን ነው የሚፈልጉት?ተ

የቶም ሉተር ድምፅ ተሰማ ‹‹እዚህ ነው ያለው፤ በእኔ ቁጥጥር ስር  ነው›› አለ ሉተር ሃርትማን ላይ ሽጉጡን እየደገነ፡፡ተ

ኤዲ የበለጠ እንቆቅልሽ ሆነበት፡፡ የፓትሪያርካ ማፊያ ቡድን ለምንድን ነው ካርል ሃርትማንን ማገት የፈለገው?› ‹‹ሳይንቲስቱን ለምንድን ነው የምትፈልጉት?› ሲል ጠየቀ፡፡

ቀበል አድርጎ ‹‹ተራ ሳይንቲስት እንዳይመስልህ የኒኩሊየር ፊዚስት
ነው›› አለ ሉተር፡

‹‹እናንተ ናዚ ናችሁ?›› ሲል ጠየቀ ኤዲ፡፡

‹‹አይደለንም፧ እኛ ዲሞክራቶች ነን፡፡ እነሱ ሳይንቲስቱን አግተን
እንድንሰጣቸው ስራ አዘውን ነው፡ ረብጣ ገንዘብ ይከፍሉናል›› አለና ቪንቺኒ
ተንከተከተ፡

ሉተርም ‹‹እኔ ዲሞክራት አይደለሁም፡፡ የጀርመን አሜሪካን ትብብር
ማህበር አባል ነኝ፡፡ ይህ ማህበር በናዚ መንግስት የገንዘብ ድጋፍ
የሚንቀሳቀስ ድርጅት ነው፡፡ ሂትለር ራሱ ነው ከአገር አምልጦ የወጣውን
ሳይንቲስት አፍኜ ወደ ጀርመን እንዳመጣው ያዘዘኝ›› አለ፡፡ ሉተር ይህን
ሲናገር በኩራት ነው፡፡ ‹‹እነዚህ ሰዎች ከፍዬ የማሰራቸው እኔ ነኝ፡፡ ስለዚህ ዶክተር ፕሮፌሰር ሃርትማንን ወደ ጀርመን መልሼ እወስደዋለሁ፡
ሳይንቲስቱ እዚያ በጣም ይፈለጋል›› አለ፡

ኤዲ ከሃርትማን ጋር ዓይን ላይን ግጥም አለ፡፡ ሰውዬው ፍርሃት
ጨምድዷቸዋል፡ ኤዲ ወዲያው ፀፀት ገባው፡፡ ሳይንቲስቱ ወደ ጀርመን
ሊመለሱ ነው፡፡ ይሄ ደግሞ የኤዲ ጥፋት ነው፡፡

‹‹ምን ላድርግ ባለቤቴን ስላገቱብኝ ነው የተባበርኳቸው›› አለ፡፡

የሃርትማን አስተያየት ተለወጠ ‹‹ይገባኛል›› አሉ ሳይንቲስቱ ‹‹እንደዚህ
አይነት ክህደቶችን ጀርመን ውስጥ ለምደናቸዋል፡ አንዱን ለማዳን ስትል
ሌላውን አሳልፈህ ትሰጣለህ፡ ምንም ምርጫ አልነበረህም፡፡ በዚህ ራስህን አትውቀስ›› አሉት፡፡
😎በነሱ ቤት

#ክፍል አርባ

#ተከታታይ ልቦለድ

ሰመረ እንቅልፍ ከራቀው ቆየ ፣አብላካት ለእክምና ከአገር ከወጣች ጀምሮ አይምሮው እረፍት አጥቷል ፣ቀልቡ ከሷው ጋር ነበር አብሮ የሄደው ፣ ቤተሰቦቹ እስኪታዘቡት ድረስ ፈዟል ፣ስራ ቦታው ላይም ብዙም መቀመጥ አልቻለም ፣  አብላካት አንድ ነገር ብትሆንስ ፣ እክምናው እንደታሰበው ባይሳካስ ፣ ብሎ ፈርቷል ፣ እራሱንም መውቀሱን አልተወም ፣ 'ምነው አብሬያቸው በሄድኩኝ ኖሮ ፣ 'በሚል ቁጭት ።
የአብላካት እናት ጋር መሄድ እና ከጎኗ መሆን ፈልጎ ነበር። ነገር ግን ፈራ እናት ናትና ፣አብላካት ለሷ ዕፃን ልጇ ነች ፣ ልጇን ላታልልባት አጉል ላደርግባት የመጣው አይነት ወንድ አድርጋ ብታስበኝስ ' በሚል ።
  ዛሬን ግን ማደር የሚችል መስሎ አልታየውም በጣም ከመጨነቁ የተነሳ ወደ አስተናጋጁ ሰሚር ደወለ ........
"ሄሎ "አለው በፍጥነት
"ሰሚር እንዴት ነህ "አለው ሰመረ ልቡ እየመታበት
"ደና ነኝ ሰመረ ፣ ምነው ድምፅህ ልክ አይደለም ጌታነህ ደወለልህ እንዴ ?አቢ እንዴት ናት?"አለው አከታትሎ
"ኧረ እኔጋር አልደወለም ፣አንተን ልጠይቅህ እኮ ነበር ፣ምን አልባት ወይዘሮ መሳይ ጋር ከተደወለ ብዬ እኮ ነው!"አለው ቅር እያለው
"ኧረ እሷ ጋር አልተደወለም ።ቅድም ደውዬላት ነበር ፣ግን አልደወለም በጣም ጨንቆኝ እነጌታነህ ቤት ኤጃለው አለችኝ ፣እዛም አልተደወለም ፣አሁንም ድረስ እዛው ናት ፣"አለና በረጅሙ ተነፈሰ። ሰመረ ጭንቅላቱን መታ መታ አደረገ እና "እኔ ነኝ ጥፋተኛው አብሬያት መሄድ ነበረብኝ "አለ
"አይዞህ ሰመረ ምንም አትሆንም ጠንካራናት "አለው አስተናጋጁ ሰሚር በማፅናናት ።ነገር ግን እሱም ፈርቶ ነበር ፣ ........
"እሺ እባክህ በማንኛውም ሰአት የሰማኽው ነገር ካለ ደውልልኝ "አለው
"እደውላለው እሺ"ብሎት ተሰናብቶት ስልኩን ዘጋው
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
የአብላካት እናት በፍርሃት እንደተዋጠች ስልኳን አነሳችው መስመር ላይ የሚቆራረጥ ድምፅ ይሰማታል የጌታነህ ነበር ተጨነቀች "ም ምን እያልከከኝ ነው አ  አ ይሰማኝም "ተንተባተበች
"አቢ እ....ሷ...."ድምፁ ይቆራረጣል ። የአብላካት እናት የተጣራ ድምፅ ስላልደረሳት ተንቀጠቀጠች ፣የጌታነህ አባት ክፉነገር የሰማች ስለመሰለው ልቡ እየመታ ከመሳይ ሞባይሏን ተቀብሎ "አቤት ጌታነህ እስኪ እየተንቀሳቀስክ አውራ ወይም ዝጋውና  እኔ ልደውል "አለው
"እሺ አ....እ.....ደና ነች.."አለው። የጌታነህ አባት የመጨረሻውን ቃል ሲሰማ ተረጋጋ
"እሺ እሺ እኔ እደውላለው "ብሎ ስልኩን ዘግቶ ወደሚስቱ በመሄድ "ደና ነች "ብሎ አቀፋት ።የአብላካት እናት በእፎይታ ሶፋው ላይ ዘጭ ብላ ተቀመጠች ፣እናም ዕንባዋን ያለማቋረጥ ተብሎ ስነካው ጀመር ፣የጌታነህ እናት እንድትረጋጋ እየነገረች አባበለቻት .....
ቆይቶ የጌታነህ አባት ወደ ልጃቸው ደወሉ  ተነሳላቸው
"ሄሉ ጌትዬ እንዴት ናቹ "አሉት
"ደና ነን አባዬ አሁን ይሰማል"አለ
"አዎ አሁን ይሻላል ፣ሁሉም ነገር በሰላም ተጠናቀቀ"
"አዎ አባዬ ትንሽ ግን ችግር አለ ማለቴ ፣እሷ ላይ አይደለም ማማለቴ ወንድሜ እስካሁን ሊነቃ አልቻለም ዶክተሮቹ ወደሱ ክፍል እንድገባ አልፈቀዱልኝም እኔ ትንሽ ፈርቻለው"አለ በጭንቀት
"ምን መስፍን ማለት ምንድነው ፍፁም ጤነኛ መሆኑን አረጋግጠው የለ እንዴ "አሉት
"ልጄ ምን ሆነ!"አለች የጌታነህ እናት በጩኽት
"ተረጋጊ እስካሁን አልነቃም ከማደንዘዣው ነው እእ ጌትዬ አንተ ተረጋጋ እና ጠብቅ ምንም አይሆንም "አሉት
"እሺ አባ ፣በቃ በዋላ እደውላለው ዶክተሩ እየጠራኝ ነው ...."ብሎ ስልኩን ዘጋው አባት ክው እንዳሉ ሶፋው ላይ ተቀመጡ የጌታነህ እናት ሆዷን በሁለት እጆቿ ጨብጣ ወዲወዲያ ትል ጀመር ፣የአብላካት እናት የልጇን ሰላም መሆን ብታረጋግጥም ፣የመስፍን ነገር ደሞ ያልጠበቀችው ነገር ሆነባት ፣ በመጨረሻው ሰአት ይቅርታዋን በሚያገኝበት ሰአት አንድ ነገር እንዳይሆን ፈራች ፣ለአብላካት እውነታውን ሳታሳውቃት አንድ ነገር እንዳይሆን ፀለየች.......

  ,,,,,,,,,,,,,,ይቀጥላል,,,,,,,,,,,,,,

#ክፍል 41,,,እንዲለቀቀ(5) ሰው ከስር ያለውን ሊንክ #Subscribe🔔ካረገ ይለቀቃል
https://youtube.com/@Weygud18

#Subscribe እያደረጋቹ ቤተሰቦች ተባበሩ #Subscriber
YouTube link👇
https://youtube.com/@Weygud18

መልካም ምሽት ተመኘሁ🙏

🎙ግሩፑን ለማግኘት
              👇👇👇

        @Mtshaf_bicha
        @Mtshaf_bicha
❤️ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
👉አሰተያየት ካላችሁ
📩 @Eyos18     አድርሱን
             📗📒📕📗📒📕
                Join&share
                  @EyosC1
       📚ማንበብ ባህላችን ይሁን📚
┄┉┉✽‌»‌🎶••✿••🎶»‌✽‌┉┉┄
📕ተአምረተ_ኬድሮን

#ተከታታይ ልቦለድ

#ክፍል_አርባ

#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ

አንቺ ወደሬሳ ማቆያው ቀድመሽ ሂጂና ሁኔታውን አመቻቺ… እኔ ቀስ ብዬ በጓሮ በኩል  ሄጂ የግቢውን መብራት አጠፋለሁ…ጄኔሬተሩንም አቶማቲኩን ስላበላሸሁት ሄደው አስተካክለው እስከሚያበሩት 10 ደቂቃ ይኖረናል..በዛ ጊዜ ውስጥ ይዘነው እንሄዳለን››

‹‹እሺ ግን ተጠንቀቅ…. ሰው እንዳያይህ››

‹‹እጠነቀቃለሁ..እንቺ ልክ መብራቱ እደጠፋልሽ ቶሎ አዘጋጂውና ከጋሽ ተካ ጋር ይዛችሁት በጎሮ በኩል መኪና መቆሚያው ድረስ ይዛችሁት ኑ..እኔ የመኪናዬን  ሞተር አስነስቼ ዝግጁ ሆኜ እጠብቃችኋለው…››

ተስማምተው እሱ ወደጎሮ  መብራቱን ሊያቆርጥ እና ግቢውን በጨለማ እንዲዋጥ ሊያደርግ እሷ ደግሞ በሽተኛውን ልትረከብ ወደሬሳ ማቆያ ክፍል ሄደች
መብራቱም ጠፍቶ እነሱም ሬሳውን(በሽተኛውን ) ይዘው  በመምጣት በመኪና ውስጥ አድርገው የውጭ ጥበቃዎችን በጥበብ አልፈው ግቢውን ለቀው ለመውጣት 8 ደቂቃ ብቻ ነበር የፈጀባቸው..

ደ/ር እስክንድር ቀጥታ የነዳው ለዚሁ ጉዳይ ታስቦ ወደተዘጋጀ  ዛሬ ጥዋት ወደተከራዩት አፓርታማ ነበር….ይህን ቤት የተከራዩበት ዋና ምክንያት የሰሚርን ቤት የበሽተኛው ዘመዶች ያውቁታል..እሱ ቤት እንደይወስዱት ደግሞ ከቤተሰቦቹ ጋር ነው የሚኖረው…. በዚህ ምክንያት የግድ   ማንም የማያውቀው እና ሰወር ያለ ቦታ ቤት መከራየት ነበረባቸው….
እንደደረሱ….ያው እንደሬሳ ድርቅርቅ ያለውን በሽተኛ ለሁለት እንደምንም ተጋግዘው ከመኪናው አወረዱትና ከሆስፒታል ባመጡት ተሸከርካሪ ጋሪ እየገፉ ወደቤት  አስገቡትና  …መኝታ ቤት የሚገኝ  አልጋ ላይ  ዘረሩት….

ይሄንን ሁሉ እስኪያደርጉ በመካከላቸው በስሜት ከመግባባት እና በምልክት መልእክት ከመለዋወጥ ውጭ ቃላት አልወጣቸውም ነበር….ሁለቱም በተመሳሳይ ሁኔታ በድን ሆነዋል

‹‹በይ ቶሎ መድሀኒቶቹን አምጪልኝ…››ለመጀመሪያ ጊዜ የተናገረው ዓ.ነገር ነበር

ሮጣ ሄደችና ካስቀመጠችለት በማምጣ ፊቱ ያለው ጠረጵዛ ላይ ዘረገፈችለት…

ሁለት መድሀኒቶችን ቀላቅሎ በመርፌ ክንዱ ላይ ወጋው….እና ከጎን ያለ ወንበር  ሳብ በማድረግ አልጋውን ተጠግቶ በመቀመጥ የሚሆነውን መጠበቅ ጀመረ..ሰሚራ ተገትራ  አይኖቾን የተዘረረው ሬሳ ላይ እንደሰካች ነው…ዶክተርም  ቁና ቁና እየተነፈሰ በየሰከንዶች ልዩነት ሰዓቱን እያየ ይቁነጠነጣል..ሰዓቱ ደግሞ መንቀርፈፉ….

‹‹ምነው ዝም አለ…..?››ሰሚራ ጠየቀች

‹‹እኔ እንጃ …መድሀኒቱ በመላ ሰውነቱ እስኪሰራጭና እስኪሰራ 5 ደቂቃ ይወስድበታል››

‹‹ታዲያ ከሰጠሀው እኮ ቆየ…..?››
‹‹መስሎሽ ነው …ገና ሁለት ደቂቃ ነው››

‹‹ሁፍ!!! ሁለት ደቂቃ ማለት ግን ስንት ነው…..?››

‹‹ሁለት ደቂቃ ማለትማ  ያው ሁለት ደቂቃ ነው..ግን አንዳንዴ  እንደዚህ ይበረክታል››አላት በደመነፍስ

…አይደርስ የለ 5 ደቂቃ ሞላ በሽተኛው ንቅንቅ አልል አለ….

‹‹ምን ይሻላል..…..?የሆነ ምልክት ማሳየት ነበረበት››ደ/ር እስክንድር ነው ግራ በመጋባት ለራሱ ይሁን ለሰሚራ በማያስታውቅ ስሜት ያወራው

‹‹አረ የሆነ ነገር አድርግ..ወይኔ ተዋረድን››

‹‹ቆይ እስቲ ተረጋጊ …ይበልጥ ግራ አታጋቢኝ..››አለና ፊት ለፊቱ ካለ ጠራጴዛ ላይ ከተዘረገፉት መድሀኒቶች ውስጥ አንዱን መርጦ በፊት  ከወጋው በተቃራኒ ባለው ክንዱ ላይ ወጋውና በተመሳሳይ ሁኔታ ውጤቱን መጠበቅ ጀመረ….
አንድ ደቂቃ..ሁለት ደቂቃ…ሶስት ደቂቃ…ምንም የለም..በድን ሬሳ…

‹‹ወይኔ ተበልተናል…ምንድነው የተሸወድኩት…..?››

‹‹እኔ ምን አውቃለሁ…መድሀኒቱ አስተማማኝ ነው …አውቀዋለሁ ብለህኝ ነበር…..?››

‹‹አዎ ብዬሽ ነበር..ግን  አልሆነም››

‹‹ግን አልሆንም ትለኛለህ እንዴ……?ስለሰው ህይወት እኮ ነው እያወራን ያለነው..ገና አለምን በቅጡ መኖር ስላልጀመረ ወጣት››

‹‹መቼስ ይሄ እንዲሆን ፈልገን አይደለም..እንደውም በተቃራኒው የእሱን ህይወት ለማትረፍ ነው እዚህ ሁሉ ውጥንቅጥ ውስጥ የገባነው..ሞክረናል  ግን አልቻልንም››

‹‹መቻል ነበረብን …››ከ20 ደቂቃ በላይ ተገትራ ከቆመችበት ቦታ ተነቃነቀችና ወደእሱ ቀረበች ….እሱም ምን ሊፈጠር ነው በሚል ስጋት ከተቀመጠበት ተነሳና ፊት ለፊቷ ቆመ
እንባዋን እያዘራች….‹‹ልታድነው ይገባ ነበር …መሞት አልነበረበትም…ከባድ  ስህተት ነው የፈፀምነው…››ደረቱን እየመታች  በመንሰቅሰቅ እቅፉ ውስጥ ገባች፡

‹‹አንቺ ምን አደረግሽ..…..?ከምትችይው በላይ ልትረጂው እየሞከርሽ ነበር›››

‹‹አይ ወደ ፖሊስ ጣቢያ ነበር መሄድ የነበረብኝ…የማይሆን  ነገር ነው የሞከርኩት …..››

‹‹የት ነው ያለሁት…..?››ያልታሰበ ከሩቅ የሚመስል ድምጽ ተሰማ…. ሁለቱም በድንጋጤ ፈዘው  ወደአልጋው መመልከት ጀመሩ ....መላኩ በተኛበት እልጋ ላይ አይኖቹን ቁልጭ ቁልጭ እያደረገ ዙሪያ ገባውን ሲቃኝና በጥያቄ አስተያየት ሲያይ ተመለከቱት

‹‹ወይኔ በአላህ ነቃ ..አደረከው ..አደረከው..››ደ/ር ላይ ተጠመጠመችበት….ለቅሶዋን ማቋረጥ አልቻለችም….ከሳቅ ጋር የተቀላቀለ የደስታ እንባ

‹‹የት ነው ያለሁት…..?››በሽተኛው ጥያቄውን ደገመው

‹‹አይዞህ… እኔ ሲስተር ሰሚራ እባላለሁ…እሱ ደግሞ ጎደኛዬ ነው ዶ/ር እስክንድር ይባላል…ያንተን ጤንነት የምንከታተለው እኛ ነን››

‹‹ምን ሆኜ ነው…..?››

‹‹አይዞህ ጥቂት ጉዳት ደርሶብህ ነበር.. አሁን ተርፈሀል….››

‹‹ሰላሜስ…..?ሰላምን ጥሪልኝ..››
‹‹አይዞህ ጠራታለሁ .አሁን ራስህን አታድክም .››

‹‹ጥሩ…ልኝ..››እያለ ወደ እንቅልፍ አለም ገባ 

‹‹መተኛቱ ጥሩ ነው….ይገርማል የሰጠነው መድሀኒት ከሞት ብቻም ሳይሆን ሰሞኑንም ከነበረበት ኮማ ጭምር ነው መንጭቆ ያወጣው….እንዲህ ይሆናል ብዬ አልጠበቅኩም ነበር….ግን አሁን መልሶ ከእንቅልፉ ሲነቃ  ስለፍቅረኛው እና  ስለወንድሙ እንዴት ታስረጂዋለሽ…..?››

‹‹አታስብ ዋናው ወደ ህይወት መመለሱ ነው… ሌላው እዳው ገብስ ነው… የሆነ ዘዴ አላጣም..አንተ ግን ድንቅ ሰው ነህ››

‹‹አረ ድንቅነት በአፍንጫዬ ይውጣ ..ሁለተኛ እንዲህ አይነት ቅብጠት አይዳዳኝም …እንዴ ነፍሴ በአፍንጫዬ ልትወጣ እኮ ነበር››

‹‹ይቅርታ አጨናነቅኩህ አይደል…..?››

‹‹አጨናነቅኩህ ብቻ..ልትውጪኝ እኮ ነበር…ይሄ ልጅማ እንዲህ በቃላሉ ከዚህ ቤት የሚወጣ አይመስለኝም››

‹‹ምን ማለት ነው…..?››

‹‹እኔ እንጃ አይነ ውሀሽ አላማረኝም…ለማንኛውም በየስድስት ሰዓት ልዩነት ይሄንን መድሀኒት ስጭው…ችግር ካለ ደውይልኝ አሁን እኩለ ለሊት ከማለፉ በፊት ወደቤቴ ልሒድ››

‹‹ስላደረክልኝ ነገር በጣም አመሰግናለሁ..ና ልሸኝህ››

‹‹አረ ግድ የለም….ነገ መቼስ ስራ አትመጪም››

‹‹አረ የዓመት ፍቃድ እጠይቃለሁ..እስኪሻለው  ለማን ጥዬው እሔዳለሁ…?››

…ፈገግ ብሎ እየሳቀባት ቤቱን ለቆላት ሄደ 

.በደንብ እስኪሻለው 15 ቀን ፈጀበት..የሆነውን ነገር እና ፍቅረኛውና ወንድሙ ምን እንዳደረጉት የነገረችው እቤቷ በወሰደችው በ3ተኛ ቀን ነበር..የመከዳቱን ነገር ከሰማ በኋላ ለቀጣዬቹ ሶስት ቀናት ህመሙ አገርሽቶበት ለምን ነገርኩት…..? ብላ እስከምትፀፀት ድረስ ነበር እንዲቆጫት ያደረገት..በኋላ ግን ቀስ በቀስ እያገገመ መጣ ..ሲቆይ በእሷ እንክብካቤ እና ማበረታታት ተሻለው….
📕ተአምረተ_ኬድሮን

#ክፍል_አርባ_አንድ

#ተከታታይ ልቦለድ

#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ

በ25ኛው ቀን ጥዋት ቁርስ ከበሉ በኃላ
‹‹ዛሬማታ ልሄድ ነው››
‹‹የት ነው የምትሄደው…..?››ደንገጥ ብላ ጠየቀችው ሰሚራ
‹‹ከከተማ ወጣ ብዬ  ትንሽ ራቅ ብዬ ምን ማድረግ እንዳለብኝ ማሰብ እፈልጋለሁ….››
‹‹ስለምንድነው የምታስበው..…..?ክፉ ነገር አይደለም አይደል…..?››
‹‹እኔ እንጃ …ለጊዜው ምንም የመጣልኝ ነገረ የለም..እንደገደሉኝ ልግደላቸው…ወይስ ይቅር ልበላቸው …..?የማውቀው ነገር የለም…ገንዘቤን ግን ልጅነቴን የሰዋሁበትና ብዙ ፈተና ያየሁበት ስለሆነ ሰባራ ሳንቲም እንደማልተውላቸው እርግጠኛ ነኝ..ምን አልባት እስከዛው በደንብ ቢደሰቱበት  ጥሩ ነው››
‹‹እንዴት አድርገህ ታስመልሳቸዋለህ……..?አሁን እኮ ንብረትህ በእነሱ እጅ ነው..በህይወት መኖርህን ካወቁ ባለ በሌለ  ኃይላቸው ነው አሳደው የሚያስገድሉህ››
‹‹አይዞሽ አታስቢ… እጠነቀቃለሁ….ለዛም ነው ከዚህ ከተማ ራቅ ብዬ በጽሞና ምን ማድረግ እንደምችል ማሰብ አለብኝ የምልሽ››
‹‹ካልክ እሺ ..ቆይ መጣሁ›› ብላ ከነበሩበት ሳሎን ተነስታ ወደመኝታ ቤቷ ከሄደች ከ5 ደቂቃ በኃላ ተመልሳ መጣችና ቼክ እጁ ላይ አስቀመጠችለት፣..ግራ ገብቶት አንዴ የሰጠችውን ቼክ አንዴ ደግሞ እሷን በማፈራረቅና በመገረም ሲያያት  ከቆየ በኃላ
‹‹ምንድነው ይሄ…..?››ጠየቃት
‹‹የራስህ ብር ነው..አንተን እንድገድልላቸው የከፈሉኝ ነው…ሁኔታዎችን እስቲስተካከሉልህ ለመንቀሳቀሻ ይሆንሀል››
‹እንዴ ምን አይነት ሰው ነሽ….?እንዲህ አይነት ሰው እኮ በዚህ ጊዜ አይገኝም››
‹‹አይ እንደምታስበኝ ደግ ሴት ሆኜ አይደለም..ለአንተ ብቻ ነው እንዲህ የሆንኩት..››
በንግግሯ ውስጡ ተነካና‹‹ለእኔ ለምን…..?››ጠየቃት
‹‹እኔ እንጃ….. ›አለችው
..ከተቀመጠበት ተነሳና ስሯ ተንበረከከ..ደነገጠች፡፡ አቀፋት …አንገቷ ሰር ገብቶ ሳማት…. ውርርር አደረጋት፣..አላቆመም… ወደታች አስጎንብሶ ግንባሯን …አይኖቾን… ጉንጮቾን በመጨረሻ ከንፈሯ ላይ ተጣበቀባት…አይኗን ከመጨፈን እና ከንፎሯን ከማነቃነቅ ውጭ ምንም ተቃውሞ አላሰማችም…ደስ የሚሉ እልፍ መሰል ሁለት ደቂቆች አለፉ….
የሚያደርገውን አድርጎ ከተቀመጠበት ተነስቶ ሲቆም እሷ አፍራ  አቀረቀረች…
የሰጠችውን ቼክ መልሶ ጉልበቷ ላይ እያስቀመጠላት..ይሄ ምን አልባት እኔን ለገደልሽበት ቢከፍሉሽም.. አንቺ ግን እኔን ለማዳን ለህክምና ይሄን ቤት ለመከራየት ላወጣሽው ወጪ መሸፈኛ ይሁንሽ…ውለታሽ ግን በዚህ ብር የሚመለስ ወይም የሚጣጣ ፍጽም አይደለም…በሕወቴም ጭምር ከፍዬ አልጨርሰውም››
‹‹ህይወትህን ስፈልግ ያኔ  ትከፍለኛለህ …አሁን ግን ከእኔ ይልቅ አንተ ነህ ችግር ላይ ያለህው …  ደግሞ ከራሴ ገንዘብ ምንም ያወጣሁት ነገር የለም…ከዚህ በተጫማሪ መቶ ሺ ብር ቦነስ ብለው ሰጥተውኝ ነበር…እርግጥ ከላዩ ላይ አንተን ለማሸሽ እና የሬሳ ሳጥኑን ቀይረው ለሰጡኝ አቶ ተካ 50 ሺ ብር ከፍያለሁ..ሌላውን 50 ሺብር   ደግሞ እስከአሁን እየተጠቀምኩበት ነው ፡፡››
‹‹አይዞሽ ለእኔ አትስቢ አልኩሽ እኮ …እነሱም ሆነ ማንም የማያውቀው 5 ሚሊዬን ብር ባንክ አለኝ…..በዛ እጠቀማለሁ፡፡››
‹‹ግን ባረብሽህ ምትሄድበት ይዘህኝ ብትሄድ …..?››
‹‹አረ ደስ ይለኛል..ስራሽን ብዬ እኮ ነው…..?››
‹‹ስራው ይደርሳል››
‹‹በያ ተዘጋጂ….መኪና እንከራይ ››
‹‹ወደየት ነው ግን ምንሄደው…..?››
‹‹እግራችን ወደመራን….››

   ይቀጥላል,,,,,,,,,

#ክፍል 42,,እንዲለቀቀ (10) ሰው ከስር ያለውን ሊንክ #Subscribe🔔ካረገ ይለቀቃል
https://youtube.com/@Weygud18

#Subscribe እያደረጋቹ ቤተሰቦች ተባበሩ #Subscriber
YouTube link👇
https://youtube.com/@Weygud18

መልካም ምሽት ተመኘሁ🙏
🎙ግሩፑን ለማግኘት
              👇👇👇

        @Mtshaf_bicha
        @Mtshaf_bicha
❤️ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
👉አሰተያየት ካላችሁ
📩 @Eyos18     አድርሱን
             📗📒📕📗📒📕
                Join&share
                  @EyosC1
       📚ማንበብ ባህላችን ይሁን📚
┄┉┉✽‌»‌🎶••✿••🎶»‌✽‌┉┉┄
📕ተአምረተ_ኬድሮን

#ክፍል_አርባ_ሁለት

#ተከታታይ ልቦለድ

በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ

የጊቢዋ አጸድ ውስጥ ባለ ወንበር ላይ ቁጭ ብላ የወፎችን ዝማሬ እና የዛፎችን ሽውሽውታ እየታዘበች በሀሳብ እየናወዘች ነው፡፡ያው በህይወቷ አዲስ ክስተት ተከስቷል … አንድ ሰው ላይ ለቀናቶች ሀሳቧ እንደተጣበቀ ነው….ያ ባሪያ ልጅ ልቧን ቅልጥ ሀሰቧን ውስውስ ነው ያደረገባት፡፡ሰሚራ ከምትባለው ፍቀረኛው ጋር ያለውን ታሪክ እና የፍቅር ትስሰር  ሙሉውን ታሪክ ለመጨረስ እራሱ አቅም አነሳት...ስለሱ ከማሰብ የሚያሰንፋት መስሎ እየተሰማት ነው….‹‹ለማንኛውም እስቲ  ታሪኩን ልጨርስ›› ብላ ተቀመጠች …ግን ታሪኩን ለመጨረስ  ንስሯ ያስፈልጋታል..እንደምታየው ደግሞ አሁን ጊቢ ውስጥ  ንስሯ አይታያትም …ብዙም ሳያስጠብቃት ከሄደበት ተመልሶ መጣ 
ቀጥታ ወደዛ ወደተለከፈችበት ታሪክ አመራች …አእምሯዋን ከንስሯ አዕምሮ ጋር በተለመደው መንገድ አቆራኘችው..አዎ አገኘዋቸው…ከከተማ እንውጣ ብለው ላንጋኖ ነው የሄድት …በሀይቁ ዳር በታነፀ ላውንጅ  የተዘጋ መኝታ ክፍል ውስጥ ናቸው፡፡
ህይወት ልክ እንደካርታ ጫወታ ነች…ይበወዝና ተጫዋች ለሆኑት  ኗዋሪዎቾ የሚታደል ዕጣ ፋንታ በሚሉት ምናባዊ ሀዲድ  የምትሸረብ…አጋጣሚ በተባለ የህይወት ሰንሰለታማ  ጉዞ ላይ በትክክለኛው ቦታ በትክክለኛው ጊዜ አንዱ ካንዱ በመገጣጠም መላተም እና በሌላ ገጽ ላይ  በሰከንድ ሽርፍራፊ ሰከንድ መዘግየት ተፈጥሮ ተፈላልጎም ሳይገናኙ  መተላለፍን በውስጧ የያዘች….
በጣርነው መጠን ማናገኝባት…ባመረትነው መጠን ማንሰበስብባት…በተመኘነው መንገድ ማንጓዝበት..እንደሎተሪ ዕጣ ብዙዎቻችን የምንከስርባት…የተወሰነው በማስተዛዘኛ የምንፅናናባት..ጥቂቶች ደግሞ እንደው ጠብታ  ላባቸውን በአልማዝ ተመንዝሮ እጃቸው ላይ የሚቀመጥላቸው …ውጥናቸውን አለም ጠቅላላ ተረባርቦ ከግብ የሚያደርስልቸው ከእርጥብ እድል ጋር የተፈጠሩ…ንግግራቸውን በደቂቃ አለም የሚያደምጥላቸው…እነሱ ለተከዙት አለም ተንሰቅስቆ የሚያለቅስላቸው …እንዲሁ መርቆ የፈጠራቸው አሉ፡፡ … እና ህይወት የካርታ ጫወታ ነች…የጫወታውን ህግ ግን ተፈጥሮዊ ብቻ አይደለም..ሰው ሰራሽም ጭምር ነው … 
ይሄንን ሀሳብ ያሰበችው ሰሚራ ነች ..ፍቅረኛዋ  መላኩ ደረት ላይ ጋደም ብላ እያሰላሰለች የምትገኘው፡፡እንዴት እንዲህ ልሆን ቻልኩ....?እንዴት ከበሽተኛዬ ጋር ፍቅር ውስጥ ገባሁ…...?አጋጣሚው ነው ወደዛ የገፋኝ ወይስ እራሴ ነኝ ፈቅጄ እና አስቤ ወደዚህ ደረቱ ላይ ወደተጋደምኩት ልጅ ልብ ውስጥ የገባሁት…...?
‹‹ምን እያሰብሽ ነው..?››ድንገት በጠየቃት ጥያቄ ለውስጥ ጥያቄዋ መልስ ሳታገኝ  አቋረጠችው፡፡
‹‹መቼ ጥለህኝ እንደምትሄድ እያሰብኩ ነው››አለችው…ለምን እንደዛ እንዳለችው ለራሷም አልተገለጸላትም… ..ምክንያም እያሰበች ያለችው ያንን እንዳልሆነ እሷና እግዚያብሄር ያውቃሉ….ሳታስብ ከንፈሯ ላይ የመጣላት ድንገታዊ መልስ የእውነት ስጋቷ አይደለም ማለት ግን አይቻልም…
‹‹የት ነው ጥዬሽ የምሄደው..?››
‹‹ወደኑሮህ ነዋ››
‹‹ኑሮ ማለት እኮ  የህይወት ደስታሽ የሚመረትበት ቦታ ነው….ማንም ሰው በህይወቱ የሚባክነው ያንን ቦታ ፍለጋ ነው…የደስታው ምንጭ የሚፈልቅበትን ጥግ ለማግኘት …የሰው ልጅ ስኬትም የሚለካው በዚህ ነው…እና እኔ እድለኛ ነኝ .ብዙም ሳለፋ በተዐምራዊ አጋጣሚ አንቺን አግኝቼያለሁ….እንዳገኘውሽ ያወቅኩት ደግሞ በአሁኑ ጊዜ በቃ ስትስቂ ልቤ ትቀልጣለች…ትንፋሽሽን ወደውስጤ ስስበው በሰውነቴ ውስጥ በስብሰው  ያበቃላቸው ሴሎቼ እንኳን መልሰው ህይወት ሲዘሩ ራሱ ይታወቀኛል…..ከጎኔ መኖርሽን ሳይ ዓለም ጠቅላላ ተሰብስባ ከእጄ የገባች ይመስለኝና ልቤ በኩራት አብጣ ልትፈነዳ ትደርሳለች..እና ከአንቺ ተለይቼ መሄድ ማለት ወደባዶነት ሸለቆ ተወርውሮ መከስከስ ማለት እንደሆነ ሚጠፋኝ ይመስልሻል …...?አሁን ባለሁበት ሁኔታ ከንቺ ውጭ ኑሮ ማለት ሲም ካርድ የሌለው ባዶ የሞባይል ቀፎ መሆን ማለት ነው…..››

ከትከት ብላ ሳቀች..ኪ…ኪ..ኪ…እንዴ ‹‹ነገሩን ሁሉ እኮ ስነጽሁፋዊ አደረከው…ከእኔ ከመገናኘትህ በፊት ነጋዴ ነበርኩ ብለሀኝ አልነበር እንዴ..?››

‹‹አዎ በጣም ጎበዝ ነጋዴ ነበርኩ…ምን ተፈጠረ..?››

‹‹አይ ንግግርህ የደራሲ እንጂ የነጋዴ አልመሰለኝ አለኛ…..››

‹‹አታውቂም እንዴ..? ፍቅር እና ችግር ያፈላስፋሉ እኮ….!!!››

‹‹አይ ጥሩ….ለማንኛውም የቀልድህንም ቢሆን በሰማሁት ነገር ደስ ብሎኛል….ምነው በተናገረው መጠን ሊያፈቅረኝ በቻለም ብዬ ተመኝቼያለሁ››

ከደረቱ ላይ ቀና አድርጎ አነሳትና እሱም ከተጋደመበት ቀና ብሎ ተቀመጠ… ወደእሷ ዞሮ አይን ዓይኗን እያየ‹‹አላመንሺኝም እንዴ ..? የምሬን ነው የተናገርኩት….በጣም ነው ያፈቀርኩሽ ..ወደፊት ማግባት የምፈልገው አንቺን ነው….የልጆቼ እናት ላደርግሽም እፈልጋለሁ….. ››
አንገቷን ወደእሱ ዘንበል አድርጋ እጆቾን በመዘርጋት ተጠመጠመችበት ..‹‹በጣም ነው የማፈቅርህ አንተን ስላገኘው እድለኛ ነኝ››
…..
‹‹እሺ አሁን ወጣ ብለን  ቢች ዳር ዘና እንበል…..››አላት በሀሳቡ ተስማማችና ተያይዘው ወጡ…
ላንጋኖ ሀይቅ ላይ ያረፈችው የማታዋ ጀንበር ልዩ ህብረቀለም እየረጨች ስትታይ ለአካባቢው ልዩ ውበት አልብሳዋለች…. ቢች ዳር ኳስ የሚጫወቱ አሉ..ሀይቅ ውስጥ ገብተው የሚዋኙን የሚንቦጫረቁም ጥቂት አይደሉም…… በአካባቢው ደስታ ተመርቶ የሚታደል ወይንም ከንፋሱ ጋር ተቀላቅሎ አየሩን እየሞላው በስፍራው ያለው ሰው ሁሉ እየማገው የሚፈግና የሚደሰት ይመስላል፡፡

‹‹ትዋኚያለሽ …..?››

‹‹አረ ይቅርብኝ …ዝምብለን እዚህ ሳሩ ላይ ቁጭ እንበልና  በማየት እንደሰት..ባይሆን ቆይቶ ከነሸጠኝ አብረን እንገባለን›› አለችውና ቁጭ አለች ..ተከትሎት ከጎኗ ቁጭ አለ…….

ይቀጥላል

#ክፍል 43,,እንዲለቀቀ (15) ሰው ከስር ያለውን ሊንክ #Subscribe🔔ካረገ ይለቀቃል
https://youtube.com/@Weygud18

#Subscribe እያደረጋቹ ቤተሰብ ስለምትሆኑ እናመሰግናለን #Subscriber
YouTube link👇
https://youtube.com/@Weygud18

መልካም ግዜ ተመኘሁ🙏
🎙ግሩፑን ለማግኘት
              👇👇👇

        @Mtshaf_bicha
        @Mtshaf_bicha
❤️ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
👉አሰተያየት ካላችሁ
📩 @Eyos18     አድርሱን
             📗📒📕📗📒📕
                Join&share
                  @EyosC1
       📚ማንበብ ባህላችን ይሁን📚
┄┉┉✽‌»‌🎶••✿••🎶»‌✽‌┉┉┄
📕ታምራተ_ኬድሮን

#ክፍል_አርባ_ሶስት

#ተከታታይ ልቦለድ

#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ

ሁለቱ ፍቅረኛሞች ከአካባቢው ተነስተው የተንቀሳቀሱት ከምሽቱ 2 ሰዓት አካባቢ ነበር…እያመሩ ያሉት ወደመኝታ ቤት ነበር..ልብስ ቀይረው ራት ለመብላት እና ምሽቱን ዘና ብለው ለማሳለፍ ወደ ሬስቶራንት ለመሄድ..ግን  መንገድ ላይ ያላሰቡት ሰው በዛፎችና በጭለማ የተሸፈነውን  ጠባብ  የእግር መንገድ ዘግቶ ሽጉጥ ደቅኖ ጠበቃቸው… መላኩ ቶሎ ብሎ የሰሚራን ክንድ ጨምድዶ ያዘና ጎትቶ ከጀርባው በማድረግ አሱ የግንብ ግድግዳ ሆኖ ከፊቷ ተገተረ…..
‹‹አይ አይ ….ካንተ በፊትማ እሷን ነው መግደል  የምፈልገው››
‹‹አይ እንደጀመርከኝ እኔኑ ጨርሰኝ….››
‹‹አይ መጀመሪያማ እንደህጻን ያታለለቺኝን ይቺን ጊንጥ ፊትህ ደፋትና አንተን አስከትላለሁ..››
‹‹ለመሆኑ እዚህ ድረስ እንዴት ተከትለኸን መጣህ..?››መላኩ  ነው ድንጋጤውን እንደምንም   ተቆጣጥሮ  በጣም የገረመውን እና ያልጠበቀው ነገር እንዴት ሊሆን እንደቻለ ለማወቅ የጠየቀው፡፡

‹‹እግዜር ነው እጄ ላይ የጣላችሁ..እኔማ ሀገር ሰላም ነው ብዬ ልዝናና ነበር እዚህ የመጣሁት
…ግን ሞቶ አልቅሼ በእጄ አፈር
አልብሼ ቀብሬዋለሁ ያልኩት ወንድሜ እዚህ ዘና ብሎ አለሙን ሲቀጭ አገኘሁት…..ለዛውም ገደልኩልህ ብላ 6መቶ ሺ ብሬን ቅርጥፍ አድርጋ ከበላች ቀጣፊ ሴት ጋር…››መለሰለት ሰሎሞን
መላኩ እየተንቀጠቀጠ መናገር ጀመረ‹‹ገራሚ ነህ …አንደኛ በዚህ አፍህ የእግዜያብሄርን ስም ማንሳትህ ትልቅ ድፍረት ነው..እግዚያብሄር እኮ ፍትህ ነው..እግዚያብሄር ፍቅር ነው..እግዜያብሄር የበጎነት የመጨረሻው ጥግ ነው…ታዲያ በምን ስሌት  እግዚያብሄር አንትን ረድቶህ እኛን አንተ እጅ ላይ ይጥለናል ብለህ ታስባለህ …..?ማይሆነውን…..!!!ደግሞ ገንዘቤን የምትለው…ገንዘቡ እኮ የእኔው ነው…ደግሞ እሷ እንደአንተ እና እንደዛች ሴት ከንቱ አትምሰልህ….ገንዘቡን የእኔ መሆኑን በመረዳት ሳትሰስት ሰታኛለች…››
‹‹በቃ ከዚህ በላይ ልፍለፋህን ልስማ  አልፈልግም …..አሁን አይኔ እያየ ሁለታችሁም በአንድ ሳጥን ተዳብላችሁ ትቀበራላችሁ..እዚህ የጀመራችሁት ፍቅር እዛ ያለከልካይ ትኮመኩሙታላችሁ…››ብሎ ወደነሱ የቀሰረውን ሽጉጡን ቀጭ ቀጭ አድርጎ አቀባበለ….ይሄ ቅጭልጭልታ ቀድሞ የተሰማው ለሰሚራ ጆሮ ነበር..ያው ሴት ከወንድ በላይ ንቁ አይደለች….ከሰማችው ድምጽ ጋር እኩል ተሸከርክራ መላኩን  ገፍታር ከፊቱ ተደቀነች.. ሞቱን ቀድማ ልትሞትለት….ተሳካላት…..በዛ ቅፅበት   ዶ..ዶ..የሚል አደንቋሪ ድምጽ ተሰማ  …ወዲያው የብዙ ሰው ጩኸት እና  የሚሮጡ የሰው ኮቴ …ከዛ ሰሚራ ዝልፍልፍ ብላ መላኩ  እጁ ላይ ገንደስ ስትል ይዟት ወደመሬት ሲወርድ ..ሁሉ ነገር የሚሆነው በደመነፍስ ነበር….
…ሰሚራ ድንገተኛ እና ያልታሰበ ከነበረው ከዛ አደጋ ከወራት  ህክምና በኃላ ዳነች…መላኩም ወንድሙንና  እና የበፊት ሚስቱን በግድያ ሙከራ እና በእምነት ማጉደል ከሶ በህግ ቁጥጥር ስር እንዲውሉ በማድረግ  ወህኒ እንዲወረወር አድርጎ ንብረቱን መልሶ ተቆጣጥሯል….አዎ እዚህ ድረስ ያሉ ነገሮች ጥሩና መልካም የሚመስሉ ነገሮች ነበሩ…እንግዲህ ይህ  ድርጊት የተከወነው ከአምስት አመት በፊት ነበር…

በመላኩ ወንድም በሰለሞን  ሽጉጥ ተተኩሶባት ፍቅረኛዋን ቀድማ በተመታችበት ወቅት ከተተኮሱባት ሁለት ሽጉጦች መካከል አንዱ ሽጉጥ በደረቷ ሌላው ደግሞ በጭነቅላቷ ነበር የገባባት…እና በወቅቱ በደረቷ የገባቸውን የጥይት ቀላሀ በቀላሉ ማውጣት ቢቻልም የጭንቅላቷን ማውጣት ግን በጣም አስቸጋሪ ሆኖ ነበር…፡፡
አስቸጋሪነቱ ጭንቅላቷን ቀዶ ጥይቷን  መዞ ማውጣቱ አይደለም….የከበደው ጥይቷ የተቀረቀረችበት ቦታ እንጂ… ጥይቷ ከወጣች የሰሚራ የጤና ሁኔታ በቋሚነት እንደሚበላሽ ….ትውስታዋ ሙሉ በሙሉ ሊጠፋ ከዛም አልፎ የማሰብ አቅሞንም እንደሚጎዳው ከፍተኛ ስጋት ስለጣለባቸው….ለጊዜው  ባለበት እንዲቆይ… በየጊዜው የቅርብ የህክምና ክትትል እንድታደርግና በሂደት የሚሆነውን ለማድረግ ተወሰኖ ነበር..
ለአንድ አመት  በየወሩ እየተማመላለሰች ህክምናዋ በመከታል በጥንቃቄ  ካሳለፈች በኃላ ምንም የሚሰማት እና የሚለወጥ ነገር ስላልነበረ ቀስ በቀስ እየተዘናጋችና ምንም አይፈጠረም በሚል እምነት ክትትሉን አቆመች ….
በዛን የጊዜ ክፍተት ውስጥ…መላኩ በንግዱ አለም ከበፊቱ የበለጠ ተሳክቶለት ከሰሚራ ጋር ያየነበረው የፍቅር ትስስር ይበልጥ እየጎመራ ሄዶ ወደጋብቻ ሊሸጋገር ወራቶች ሲቀሩት….ግን ከሁለት አመት ቆይታ በኃላ ድንገት ወድቃ  ሀኪም  ቤት ዳግመኛ ለመግባት ተገደደች…  ምርመራ ባደረገችበት ጊዜ በጭንቅላቷ መሀከላዊ ስፍራ የተቀረቀረችው ጥይት ብቻ ሳትሆን በፊት ያልነበረ ጎን ላይ  አስደንጋጭ እጢ ተፈጥሮ  ታየ..ሀኪሞቹ ተደናገጡ ..ተስፋ እንደሌላት እና ማድረግ የሚችሉት ብዙም ነገር እንደሌለ ለመላኩ ሲነግሩት አንጠልጥሎ ወደውጭ ሀገር ይዞት ሄደ….ግን የረፈደ ውሳኔ ነበር…ጥይቷ እንዲወጣላት ማድረግ ተቻለ ..እጢውም በጨረር ህክምና እንዲሞሞ ማድረግ ብዙም ከባድ አልነበረም…ይ ሁሉ ቢሆን ግን በህይወት ልትቆይ የምትችለው በዛ ቢባል ለቀጣዩ አንድ ወይም ሁለት አመት እንደሆነ አስምረው ነገረዋቸዋል…ከዛ በኃላ ወይ ትሞታለች ወይ ደግሞ በድን ሆና በህይወት እና በሞት መካከል ተንጠልጥላ ለአመታት ትኖራለች…..ሚሻለው ግን ወዲያው ብትሞት ነው…. የሀኪሞቹ ምክር ነበር፡፡ …የምርመራው ወጤቱ ለሁለቱም  ሰቅጣጭ ነበር…

እንግዲህ እነዚህ ፍቅረኛሞች …ሳቃቸው ከእንባ የተቀላቀለ፤ደስታቸው ከፍራቻ የተጋባ፤ተስፋቸው ጨለማ የገደበው ከሆነ እና በዚህ ሰቀቀን ውስጥ መኖር ከጀመሩ አመት አልፏቸዋል እና ንስሯ ባመጣላት ታሪክ መሰረት በቀደም የዋና ገንዳ ውስጥ ያገኘችው ፤የፈተነችው እና የፎከረችበት ወጣት ታሪክ እንደዚህ ነው…ታማኝ የሚሆነውም ለዚህች ፍቅረኛው ነው…..አግቢኝ እና ውለጂልኝም የሚላት ይችኑ በጀርመናዊዎቹና በአሜሪካኖቹ ሀኪሞች የ አመት ጊዜ ብቻ የተቆረጠላትን ወጣት  ነው….
ኬድሮን አሰበች‹‹እና ምን ላድርግ ….?እንዳለች ልተዋት….? ትውለድለትና ትሙት…. ከዛ እኔ ለእሱ ሚስት ለልጁ ደግሞ እናት ልሁን…..?ነው ወይስ ላድናት……..?›ከህሊናዋ ጋር ከባድ ፈተና ገባች፡፡በእርግጠኝነት   ንስሯ ከረዳት ለእሷ መዳኛ የሚሆን መድሀኒት ሌላ የአለም ጥግ ማሰስ ሳያስፈልጋት …ከዚህችው ከቅድስቲቷ የኢትዬጵያ ምድር  ቆፍር ቆፈር አድርጋ  ስር ማስ ማስ ፤ ቅጠል በጠስ በጠስ በማድረግ  ልታድናት ትችላለች..፡፡ግን  ለምን ታደርገዋለች…..?ለማንኛወም ጊዜ ወስዳ ልታሰብበት ከራሷ ጋር ተስማማች….

ይቀጥላል….

#ክፍል 44,,እንዲለቀቀ (15) ሰው ከስር ያለውን ሊንክ #Subscribe🔔ካረገ ይለቀቃል
https://youtube.com/@Weygud18

#Subscribe እያደረጋቹ ቤተሰብ ስለምትሆኑ እናመሰግናለን #Subscriber
YouTube link👇
https://youtube.com/@Weygud18
📕ታምራተ_ኬድሮን

#ክፍል_አርባ_አራት

#ተከታታይ ልቦለድ

በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ

እየሄደች ነው… ልታናግረው…፡፡ ለምን እሱን ማናገር እንደፈለገች አታውቅም፡፡ ምን አልባት ዳግመኛ አጠገቡ ልትቆምና ያንን ወንዳወንድ ቁመናው እና ቆንጅዬ ባሪያ የሆነ መልኩን በቅርበት ለማየት ፈልጋ ሊሆን ይችላል….ናፍቋትም ሊሆን ይችላል፡፡ 

ንስሯ የት እዳለ በነገራት መሰረት ቀጥታ ቤቱ ነው የሄደችው..የውጩን የጊቢ በር መጥሪያ ስትጫን ዘበኛው ነበር የከፈተላት…‹‹ከመላኩ ጋ ቀጠሮ ነበረኝ ቤት እየጠበኩሽ ነው ብሎ ደውሎልኝ ነበር..?››ብላ ቀላመደች… ዘበኛው ያልተለመደ ነገር ሆኖበት .. ግራ እንደመጋባት አለና በመጠኑ ካቅማማ በኃላ እንድትገባ  ፈቀደላት…
ቀጥታ ቤተኛ እንደሆነ ሰው የተንጣለለውን ግቢ ሰንጥቃ ባለአንድ ፎቅ ከሆነው ዘመናዊ መኖሪያ ቤት  በረንዳው ላይ ደረሰች… የሳሎኑን በር ገፋ ስታደርገው ተከፈተ…የቀኝ እግሯን አስቀድማ ግራዋን አስከትላ ወደውስጥ ከገባች በኃላ  ወደኃላ ዞሯ በራፉን አንኳኳችው…
‹ከገቡ በኃላ ማንኳኳት ከገደሉ በኃላ ማዘን አይነት አይደለም እንዴ…..?››እራሷው በራሷ ነው የጠየቀችው
መላኩ የሳሎኑ መአከላዊ ስፍራ ላይ  ካለችበት ወደውስጥ 4 ወይም 5 ሜትር ያህል ርቆ በመገረም አፍጥጦ እያያት ነበር….
ማንኳኳቷን ስትቀጥል

‹‹አቤት››የሚል ድምጽ አሰማ

‹‹መግባት ይቻላል..?››

‹‹ገብተሻል እኮ ››

‹‹እሺ ካልክ›› ብላ ቀጥታ የሳሎኑን በር መልሳ ዘግታ ወደእሱ አቅጣጫ አመራች ….በተገተረበት ስለማንነቷ በመመራመር ይመስለል ፈዞ እንደቆመ በስሩ አልፋ ልክ እንደቤተኛ ሶፋው ላይ ዘና ብላ ተቀመጠች….መጣና ከፊት ለፊቷ ተቀመጠ

‹‹አውቅሻለሁ ልበል..?››

‹‹እኔን የመሰለች ቆንጆ ልጅ እንዴት ልትረሳ ትችላለህ..?››

‹‹ማለት..?››

‹‹ጎበዝ የዋና ተማሪህ ነበርኩ ብዬ ነዋ››

…ድንገት እንደበራለት ሰው በመደነቅ ‹‹እንዴ አንቺ እብድ ..እቤቴን ደግሞ ማን አሳየሽ..?›› አለት ‹‹ቀላል ሰው  አይደለሁም ብዬህ ነበርኮ..?››

‹‹አረባክሽ.. ፉከራሽን እኮ አየነው..እኔማ አንተን ማሳሳት ካቀተኝ እንጠለጠላለው ብለሽ ስለነበረ..በቃ ይቺ ልጅ አልሆንላት ሲል እራሷን አጥፍትለች ማለት ነው..ምን አይነት ለቃሏ ታማኝ ልጅ ነች ብዬ ሳደንቅሽ ነበር የሰነበትኩት፤ለካ ዝም ብለሽ ጉረኛ ነገር ነሽ..?››

‹‹አንተን ማውጣት አቅቶኝ ሳይሆን አሳዝነኸኝ ነው የተውኩህ ››

ግድግዳውን ሰንጥቆ በመውጣት ውጭ ድረስ ለመሰማት ኃይል ባለው አይነት አንቧራቂ ሳቅ ሳቀ‹‹አሳዘንኩሽ…..?ቀልደኛ ነሽ››

‹‹ቀልድ አይደለም…የዛን ቀን የሄደክው ከፍቅረኛህ ጋር ወደሆቴል አልነበር…..?ስለ ጋብቻ ስታወሩ አልነበር....?እንድታገባህ ስትለምናት አልነበር…..?እሷ መጋባቱ ቀርቶባችሁ እስክትሞት ድረስ የቀራትን ህይወት እንደዚሁ እንድታሳልፉ ስትለምንህ አልነበር…..?ከመሞቷ በፊት ካላገባችህ እና መጽናኝ የሚሆን ልጅም ካልወለደችልህ በሞተች ቀን አብረሀት እንደምትሞት እየነገርካት ስትላቀሱ አልነበር……..?››

ይሄንን ስትነግረው እነዛ የኮከብ ክፋይ የሚመስሉ  ደማቅ አይኖቹን ከወዲህ ወዲያ በመገረም እያሽከረከራቸው ነበር…..

‹‹አንቺ ክፍል ውስጥ ተደብቀሽ ስታዳምጪኝ ነበር እንዴ..?››በንዴት ጡንቻው ውጥርጥር ሲልና … ልነቃት አልነቃት እያለ ከውስጡ ጋር ሙግት እንደገተመ ከሁኔታው ያስታውቃል….

‹‹አይደለም …ክፍል ውስጥ አልነበርኩም…ግን በአካል ባይሆንም ክፍል ውስጥ ገብቼ  እናንተን ምታዘብበት ሌላ ዘዴ ነበረኝ››

‹‹ምን ..?ካሜራ ..?››
‹‹አይደለም…ምንነቱን ቀስ ብዬ ነግርሀለሁ…አሁን ወደመጣሁበት ጉዳይ እንግባ››

‹‹ወደመጣሁበት ጉዳይ .. ..?በይ ሳትዋረጄ በመጣሽበት እግርሽ ሹልክ ብለሽ ቤቴን ለቀሽ ውጪ..››ከመቀመጨው ቀድሞ ተነሳ…

‹‹ሁለተኛ እንኳን እቤቴ እኔ ባለሁበት አካባቢ  በድንገት ባገኝሽ እወነቴን ነው አጠፋሻለሁ…ሲጥ አድርጌ ነው የምገልሽ….››

ዘና ብላ እንደተቀመጠች መልስ መመለሷን ቀጠለች  ‹‹ዝም ብለህ አትፎክር…በቁጣ እያንቧረቁ መናገር እና ፊትን ማጨማደድ የምትለውን አይነት ጭካኔ እንዲኖርህ አያግዝህም››

‹‹ምን ማለት ነው..?››

‹‹እንኳን እኔን ምንህም  ላይ ያልደረስኩትን ልጅ ይቅርና ሰላምን እንኳን እንደዛ በድላህ ፍቅህን ረግጣ የገዛ ወንድምህን በማግባት ስታወድምህ   ለህግ አሳልፎ ከመስጠት ውጭ ምንም ልታደርጋት  አቅም አላገኘህም፡፡››
ተንደርድሮ ወደእሷ ቀረበና  ተንበርክኮ አንገቷን በማነቅ እያረገፈገፋ‹‹ማነሽ …....?አንቺን ማነው የላከብኝ....?ማነው ንገሪኝ..?››

‹‹ማንም …ምን አልባት የምታመልከው አምላክ ሊታረቅህ ፈልጎ ይሆናል…ምን አልባት እስዛሬ የፀለይከው ፀሎት አምላክ መንበር ደርሶ መልስ የማግኛህ ጊዜ ደርሶም ሊሆን ይችላል…››
፣እጁን ከአንገቷ ላይ መንጭቃ በማላቀቅ ገፈተረችውና …ዝርፍጥ ብሎ ወለሉ ላይ በቂጡ ቁጭ አለ …እዛው ባለበት አፍጦ እሷን ከማየት በስተቀር ለመነሳት አልሞከረም

‹‹ሰሚራን ባድንልህ ምን  ታደርግልኛለህ..?››

‹‹ምን  እየቀባጠርሽ ነው…...?ደግሞ በእሷ ልትቀልጂብኝ ነው..?››

‹‹አይደለም ..ካዳንኩልህ ምን ታደርግልኝለህ..?››

‹‹ቅጠል አሽተሸ በመቀባት የምታድኚው ቁስል… ምች መድሀኒት ወይንም ጅንጅብል ጨቅጭቀሽ ከሻይ ጋር አፍልቶ በመጋት  የምታድኚው  ጉንፋን በሽታ  ያመማት መሰለሽ  እንዴ..?››
‹‹አውቃለሁ…ለአመታት በጭንቅላቷ ቆይቶ የነበረው ጥይት እና የጭንቅላት እጢ ተከትሎ…….››
አላስጨረሳትም ‹‹…በፈጠረሽ ማን ነሽ ?ምንድነው ምትፈልጊው....?ይሄን ሁሉ ገበናችኝን ስንት አመት ብትሰልይን ነው ማወቅ የቻልሺው..?››

ጥያቄውን ችላ በማለት  የራሷን ጥያቄ ደግማ ጠየቀችው

‹‹ካዳንኩልህ ምን ታርግልኛለህ..?››

‹‹ እኮ እንዴት ነው የምታዲኚያት…..?የጀርመንና አሜሪካ ጠበብቶች ያቃታቸውን አንቺ እንዴት ብለሽ..?››

‹‹እኔ የተለየ መንፈሳዊ ስጦታ አለኝ …››

‹‹አላምንሽም››

‹‹እንድታምነኝ…አንድ አንተ ብቻ የምታውቀው ታሪክ ልንገርህ…እንደውም ለምን ዛሬ ያየኸውን ህልም አልነግረህም ..…››

ንገሪኝም ተይው ማለት አቅቶት በግራ መጋባት ስሜት እየዋለለ ዝም ብሎ እንዳፈጠጠባት ፈዞ ቀረ…

ጣና ሀይቅ መሀል ላይ ያለች ትንሽ ደሴት ትመስልሀለች….እሷን ከብዙ የሀገሪቷ ሀብታሞች ጋር ተወዳደረህ በጫረታ በማሸነፍ ትገዛና …በጣም ውብ የሆነ በባህላዊ መንገድ እጽብ ድንቅ ተደርጎ የታነፀ ቤት ትሰራበታለህ…በዛች ደሴት ላይ አንተ ከሰራሀት ቤት ውጭ ምንም አይነት ሌላ ቤት የለም፤ደሴቱ ሙሉውን በቡና ተክል፣በሙዝ፣በብርቱካን፣በመንደሪን፣በአፕል እና  በመሰሰሉት የሚበሉ ፍራፍሬዋች የተሞላች ነች…አዕዋፍት እና የዱር እንስሳትም  ከደኑ ጋር ስመም ፈጥረው ተፈጥሮን አድምቀው እና በተፈጥሮም ደምቅው የሚኖርበት ቦታ በመሆኑ ልዩ ድስታ ተሰምቶህ ይሄንን ስጦታ ላዘጋጀህላት ለሰሚራ ትሰጣታለህ…

‹‹ሰሚርዬ ቀሪ ህይወትሽን ምንም እንኳን አጭር ብትሆንም በደስታ የተሞላች እድትሆን ፈልጋለሁ…በዛ ላይ እዚህ ከእኔ እና ከተፈጥሮ ውጭ ምንም አይነት የሰው ልጅ ወደ ሌለበትና ወደማይኖርበት ቦታ ሳመጣሽ ቀሪ ዘመንሽን የብቻዬ ብቻ እንድትሆኚ በመፈለግ እና በመሰሰት ነው…ይቺ ስፍራ የእኔ እና የአንቺ ገነት ነች››ትላታለህ፡
📕ታምራተ_ኬድሮን

#ክፍል_አርባ_አምስት

#ተከታታይ ልቦለድ

በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ


‹‹ግን ምን አይነት ዳቢሎስ ነሽ..?››ሙትት ባለ ድምጽ

‹‹ዳቢሎስ እንኳን አይደለሁም…. ምን አልባት የዳቢሎስ ልጅ ልሆን እችላለሁ…ግን የምትወዳትን ልጅ ላድንልህ እኮ ነው እያልኩህ ያለሁት .. ..?እንደዚህ አይነት በጎ ተግባር  ዳቢሎስ ያሰኛል እንዴ..?››

‹‹አዎ ዳቢሎስ ፍቅር አያውቅም..ፍቅር የማያውቅ ደግሞ ምንም ነገር በነፃ መስጠት አይችልበትም፤ለሰጠሸ ጥሩ የሚመስል ነገር ሁሉ ተመጣጣኝ የሆነ መከራና ስቃይ ያስከፍሉሻል…››

‹‹አልገባኝም..?››

‹‹ለምሳሌ …ያለፋሽበትን ገንዘብ ተመኝተሸ ስጠኝ ብትይው በደስታ ነው የሚሰጥሽ፤የገንዘብን ባለቤት ግደይና ነጥቀሺው ውስጂ ብሎ መንገድን እና ብልሀቱን ያሳይሻል…ከዛ ትገድይና ገንዘብን ታገኚያለሽ ሀብታም እና በፀፀት የሚሰቃይ ሰው ትሆኚያለሽ፡፡አንቺም ፍቅረኛህን ላድንልህ..እና ልንጠቅህ እያልሺኝ ነው…፡፡ያው እኮ ነው በስጋ ከመሞት ታድኛታለሽ ከዛ ፍቅርን በመንጠቅ በመንፈስ ትገያታለሽ…እኔንም እንደዛው፤ታዲያ አንቺ ዳቢሎስ ካልሆንሽ ማን ይሆናል....?››አላት ምርር ባለ የመጠየፍ ንግግር፡

‹‹እሺ እንግዲያው ይቅርብህ…ሁለተኛ አረብሽህም፤ደህና ሁን››ብላ ከመቀመጫዋ ተነሳችና እንደ አመጣጧ ሳሎኑን ሰንጥቃ  በርፍን ከፍታ ወጣች እና መልሳ ዘግታ መንገዶን ቀጠለች…የግቢው አማካይ ስፍራ ስትደርስ   ነበር የበር መከፈት እና ‹‹ማን ነበር ስምሽ..?››የሚል  ከሙታን  መንፈስ የወጣ የሚመስል ድምጽ  ከጀርባዋ የተሰማው

እርምጃዋን ገታችና ቀኝ ኋላ ዞራ ‹‹ሶፊያ››ስትል መለሰችለት
‹‹ከቻልሽ አድርጊው..አድኚልኝ ፤ተስማም..ቼ…ያ….ለሁ››አላትና ከእሷ ምንም አይነት መልስ ሳይጠብቅ ፊቱን መልሶ ወደውስጥ በመግባት  በራፉን በመዝጋት ከእይታዋ ተሰወረ ..

‹‹እውነትም ዳቢሎስ ነገር ነኝ እንዴ..?….ምን እያረግኩ ነው…...?››ስትል አሰበች፡፡ቅድም እዚህ እሱ ጋር ስትመጣ ይሄንን ለማድረግ አልነበረም…ዝም ብላ ፍቅረኛው እደምታድንለት ልትነግረው እና በተስፋ ልታስፈነጥዘው ብቻ ነበር ፍላጎቷ…ያደረገችው ግን ተቃራኒውን ነው..በደስታ እና ሀዘን መካከል ነፍሱ ተንጠልጥላ እዲሰቃይ ፈረደችበት …

‹‹የእውነት ግን ያልኩትን አደርገዋለሁ…..?እሷን አድኜ እሱን ነጥቄያት አገባዋለሁ…..?.ማግባትስ በእውነት እኔ የምፈልገው ነገር ነው....?ወይስ በስቃዩ ለመደሰት…..?››ብላ ተደራራቢ ጥያቄ እራሷን ጠየቀች፡

ለማንኛውም ዛሬ ማታ ከንስሯ ጋር ለመብረር አቅዳለች….ለልጅቷ የሚሆን መድሀኒት የት እደሚገኝ ፍንጩን አግኝታለች ….ቦረና ባሌ መካከል መዳ ወላቡ አካባቢ ነው ለሰሚራ ፈውስ የሚሆነው መድሀኒት ሚገኘው….፡፡ 
የየትኛውም ሀገር አቨዬሽን  የማይቆጣጠረው በረራ ላይ ነች፡፡ግን ደህንነቱ ፍፅም የተረጋገጠ በረራ ….ከየትኛውም አይሮፕላን ጋር እጋጫለሁ ወይም አሞራና ወፎች ተላትመውብን አቅጣጫ ያስቀይሩናል…ነዳጅ አልቆ ወይም ሞተር ጠፍቶ ችግር ላይ እንወድቃለን  ብላ የማትሰጋበት ዥዋዝዌ የመጫወት ያህል ዘና የሚያደርግ በረራ…. ይሄን አይነት በረራ ሳታካሂድ ሶስት ወራት ስላለፋት ናፍቆት ነበር…
እየሄድ ያለው ከአዲስ አበባ ወደ መዳወላቡ ነው ፡፡መዳወላቡ የት እንደምትኝ መገመት ካቃታችሁ..ኬንያ ድንበር አካባቢ ብትሉት አካባውን ለመገመት ይቀላችኋል ፡፡እየበረሩን ያለነው ከንስሯ ጋር ነው…፡፡እሱ ክንፎች  መሀከል ዘና ብሎ ቁጭ ብላለች….
ከመሬት ያሉበትንን ከፍታ ገምታ ለመናገር አትችልም ..…ግን ትንሽ ግልፅ ለማድረግ  ምሳሌ ለመስጠት ያህል በዚህ ሰዓት ( ከምሽቱ ሶስት ሰዓት አካባቢ ነው) ሻሸመኔ ከተማ አካባቢ ደርሰዋል..እላይ ባሉበት ከፍታ ላይ ሆነው ከተማዋ ቁልቁል ስያዮት ከእሷ ቤት ጊቢ ብዙም ሰፍታ አይታያትም….ጭልጭል የሚሉ አንድ ቦታ የተሰበሰቡ መብራቶች ናቸው እንደምልክት የሚታዩት..
የሚፈልገበት ቦታ ላይ ከምሽቱ አራት ሰዓት አካባቢ ነው የደረሱት…ከአውሬ ድምጽ እና ከጥቅጥቅ ጨለማ በተጨማሪ ብዙ ድምጽ ይሰማል..የደረቁ ቅጠሎች በንፋስ ተገፍተው ከዛፍ ሲወድቁ ይሰማል…..ካረፍበት ተራራ ወገብ ላይ እየፈለቀ ቁልቁል ወደ ታች እየተምዘገዘገ የሚወርድው  አረፋ ደፋቂ ፏፏቴ ድምጽ በጣም ይሰማል…የብዙ አውሬዎች መጣራራት እና ማስካካተ ድምጽ ይሰማል…. ….

‹‹የቱ ነው መድሀኒቱ….?››ጠየቀችው ንስሯን 
አንድ ከእሷ ቁመት ብዙም የማትበልጥ ቋጥኝ ላይ ዘና ብሎ ቁጭ በማለት ዝም አለት
የሚያስበውን ማወቅ ስለፈለገች..‹‹አዕመሮህን ክፈትልኝ…..….?››ስትል ጠየቀችው… ቁልፍ አደረገና ችላ አለት ..አንዳንዴ እንዲህ ግግም ብሎ ያስቸግራታል..

‹‹ምን እያሰብክ ነው… ….?ለሊቱን እዚሁ ጫካ ውስጥ ከአውሬ ጋር እናሳልፍ እንዴ…….?››ጠየቀችው
አዕምሮው ውስጥ ሰርስሯ እንዳትገባ እንደከረቸመባት በሹፈት መልክ አንገቱን አሸከረከረባትና ጀርባውን ሰጣት…በቃ ምንም ማድረግ አልችለችም …እስኪለቀው ድረስ መጠበቅ እንዳለባት ስለተረዳች እራሷን አረጋጋች..የሆነ የሚጠብቀው ወይም ለጊዜው ያልጣመው ነገር አለ ማለት ነው ስትል አሰበች..ተወችውና አካባቢውን በመቃኘት ዘና ማለት ጀመረች..
ጥቅጥቅ ያለውን ጫካ ስታይ.. በአካባቢው በቅርብ ርቀት  ከሚገኙ የገጠር መንደሮች ጭል ጭል የሚሉትን  የኩራዝና የፍኖስ መብራቶችን  ..ወደ ላይ አንጋጣ የዘወትር አጫዋቾን ጨረቃን ስትመለከት ሰዓቱ ከምሽቱ አምስት ሰዓት ሆነ …ንስሯ ፀባይ ላይ ምንም የተለወጠ ነገር የለም …አሁንም የነበረበት ቋጥኝ  ላይ በተመስጦ… አረ እንደውም የፀሎት በሚመስል ሁኔታ ያለእንቅስቃሴ አንገቱን ወደጨረቃዋ አንጋጦ ተደምሟል ..
የተቀመጠችበት የወደቀ የግንድ ጉማጅ ቂጧን ስላሳመመት ተነሳችና ቀስ እያለች እሾህ እንዳይቧጭራ እና አውሬ ጉድጋድ ውስጥ ተንሸራታ እንዳትገባ እየተጠነቀቀች ወደ ፏፏቴው ተራመደች… እንደደረሰች ሙሉ ልብሷን ፓንቷንም ሳታስቀር ውልቅልቅ አድርጋ ገባችበት… ፏፏቴው ከላይ ከአለቱ እየተላተመ መቶ ጭንቅላቷ ላይ ሲያርፍ ያለውን ኃይል መቋቋም አቅቶት ልትወድቅ ነበር.. ለጥቂት ነው በአቅራቢያዋ የጋጠማትን የግንድ ቅርንጫፍ ይዛ የተረፈችው‹‹..ደግሞ ውሀው እንዴት አባቱ ይሞቃል…….?››አለችና ድክም እስኪላት ድረስ ሰውነቷን እየተገለባበጠች አስመታችውና ወጥታ ልብሷን ለብሳ ወደ ንስሯ ተመለሰች፡፡
ስሩ እንደደረሰች  ከፊት ለፊቱ ቆማ በትኩረት አየችው…መልኩ ተለየባት… የሆነ አመድ ላይ የተንከባለለ አህያ መስሏል..እንዴ ምን ላይ ተንከባሎ ነው….?..እዚህ ሰውነት ላይ ነው እንዴ ተጭኜ የመጣሁት…….?ነው ወይስ እኔ ውሀ ውስጥ  ሳለው የሆነ ነገር ከሰማይ አመድ ነፋበት..….?አረ አመድ ብቻ አይደለምል  አንገቱንም መሸከም አቅቶታል…››ስለንስሷ ቴና ሀሳ ገብቷት መነብሰልሰል ጀመረች

‹‹ምን ሆንክ….?››
አዕምሮውን ቀስ እያለ ከፈተላት፡፡እሷም እንደምንም እራሷን ለማረጋጋት ሞከረችና ወደአዕምሮው ገባች…አዎ መድሀኒቷን አየቻት …እሷ ካለችበት በ5 ሜትር ያህል ርቀት ላይ ትገኛለች…የተለየች አይነት ልዩ ተክል ነች ….?የአንድ ሰው የማህል ጣትን ነው የምታክለው…የበቀለችው ሌላ ትልቅ የብሳና ዛፍ ላይ ጥገኛ ሆና ነው….የሆነ ሀመራዊ አይነት የተለየ ብርሀን  ትረጫለች…
📕ታምራተ_ኬድሮን

#ክፍል_አርባ_ስድስት

#ተከታታይ ልቦለድ

#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ

‹‹የአባትሽ ዘመዶች ነው ያልከው….?››

‹‹አዎ የአባትሽ ወገኖች … ይሄንን ተክል በምድር ላይ  እንዲበቅል አድርገው ሲበትኑት ለመድሀኒትነት እንዲሆን አስበው አይደለም…››

‹‹እና ለምድነው….?››

‹‹አንቺን ለማግኘት….››ብሎ ጭራሽ ግራ አጋባት

‹‹እንዴት አድርገው ነው እኔን የሚያገኑኝ…….?ደግሞ የት ናቸው….?››

‹‹የት እንዳሉማ ታውቂለሽ….››

‹‹እና እንዴት ነው የሚያገኙኝ ….?››

‹‹ልክ  ያቺን ተክል ስትቀነጥሺ ቀጥታ መልእክቱ እነሱ ጋር ይደርሳል››

‹‹እወነትህን ነው….?››ውስጧ ፈነጠዘች..አባቷ የማግኘት ምኞት ሳታስበው አዘለላት..የእናቷን እውነት የማረጋጋጥ ፍላጎት…

‹‹እና አሪፍ ነዋ..ያለሁበትን ካወቁ ይመጣሉ አይደለ..….?አባቴም ይመጣል አይደል….?››ጠየቀችው

‹‹አይ አባትሽ በጥብቅ እስር ላይ ስላላ መምጣት አይችልም.. ወደዚህ ምድር በመጣ ጊዜ ሳይፈቀድለት  ከሰው ጋር በፍቅር በመቆራኘትና አንቺን ስለወለደ ይሄው ባንቺ እድሜ ሙሉ እንደታሰረ ነው››አንጀቷ ተላወሰ..በምድር ላይ ታስሮ ቢሆን ኖሮ  የፈጀውን ያህል   ይፍጅ  እንጂ   መንግስትንም ገልብጣ ቢሆን አባቷን ታስፈታው ነበር

‹‹እና ታዲያ ዘመዶቹም ቢሆን ይምጡ ምን  ችግር አለው….?››

‹‹ሚመጡት  አንቺን ለመውሰድ ነው››

ደስ አለት..ደነገጠችም ‹‹ወዴየት ነው የሚወስድኝ….?››

‹‹ወደራሳቸው አለም….››

‹‹እኔ መሄድ ካልፈለኩስ….?››
‹‹ፈለግሽም አልፈለግሽም ይወስዱሻል …ምንም አይነት ምደራዊ ኃይል አንቺን ከመውሰድ አያግዳቸውም….››

ለአምስት ደቂቃ በትካዜ  ውስጥ ገባች…ሌላ አለም የማየት ፍላጎት… አባቷን እና ዘመዶቹን የማወቅ ፍላጎት..ደግሞ ይህቺን ምድርስ….?

‹‹ቆይ ሄጄ ሁሉን ነገር ካየሁ በኃላ ተመልሼ ወደምድር መምጣት አልችልም….?››

‹‹አይመስለኝም… ብትመለሺም እንደዚህ ሆነሽ አይደለም…ሙሉ በሙሉ ተቀይረሽ.. ሙሉ በሙሉ እነሱን ሆነሽ..የእነሱን ተልዕኮ ለማስፈፀም ነው ሚሆነው.ያ በእነሱ ፍቃድ ላይ የተመሰረተ ነው.ከፈለጉ እስከወዲያኛው ዳግመኛ ምድርን ላትረግጪ ትችያለሽ፡፡››

‹‹በቃ ይሁን.. ለእኛም እዛ መኖር ይሻለናል..የተለየ ዓለም  እኮ አሪፍ ነው..ይቺን ዓለም እንደሆነ በተቻለ መጠን በርብረናታል…ምን ይቀርብናል….?››

‹‹እና ወሰንሽ››

‹‹አዎ ባክህ እንደውም አሪፍ እድል ነው››
እንግዲያው ተዘጋጂ… ከአምስት ደቂቃ በኃላ ሄደሽ መቀንጠስ ትችያለሽ..ከቀነጠስሽ በኃላ ግን አንድ ሳምንት ብቻ ነው በምድር የመቆየት እድል የሚኖርሽ… ልክ የዛሬ ሳምንት በዚህን ሰዓት ካለሽበት ቦታ መጥተው ይዘውሽ ይፈተለካሉ››

‹‹አንድ ሰምንት..አንድ ሳምንት ፈጠነ..ግን ቢሆንም ቀላል ቀን አይደለም….ብዙ ነገር እንሰራበታለን…እናቴን ሄደን እንሰናበታለን..የልጅነት ጎደኞቼን እሰናበታለሁ… አሪፍ ነው..አንድ ሳምንት ይበቃናል..››አለችና ወደተክሏ ተራመደች..
ደረሰችና ልክ ድፍን  6 ሰዓት ሲሆን  ከብሳናው ዛፍ ቅርንጫፎች መካከል  እጇን ዘረጋችውና ጨበጠችው… ቀነጥሰዋለሁ ስትል በእጇ ሟሞና እንደቅባት ተሙለጭልጮ ወደሰውነቷ ሲገባ ታወቀት… ደነገጠች የቀነጠስችው መስሏት ነበር… እጇ ላይ ግን ምንም ነገር የለም… እጇ  የተለየ ቀለም እያመጣ ነው ..ሀመራዊ እሳት መሰል ቀለም… በመላ ሰውነቷ እየተራወጣ ከተዳረሰ በኃላ አንዘርዝሮና አንቀጥቅጦት በአፏ የቴንስ መጫወቻ የምታክል ድብልብል እሳት ብልቅ ብሎ በመውጣት እንደሮኬት ተተኩሶ ወደሰማይ ተምዘገዘገ ..እያየችው  አየሩን ሰንጥቆ ተሰወረ..ግራ ጋባት …እንደምንም ለመረጋጋት እየሞከረች ወደንሰሯ አዕምሮ ተመለስችና ‹‹ምን እየሆነ ነው….?››ጠየቀችው
‹‹በቃ ጨርሰናል እንሄድ››
‹‹እንዴ መቀንጠስ አልቻልኩም እኮ ..እጄ ላይ ምንም የለም….?››
‹‹እጅሽ ላይ ምን ያደርግልሻል …ተክሉ እኮ በመላ ሰውነትሽ ገብቶ ተዋሀደሽ..አሁን መዳኒቱ ተክሉ ሳይሆን አንቺ ራስሽ ነሽ..በዚህ የሳምንት ጊዚ ውስጥ የፈለግሽውን ማዳንም የፈለከግሽውን መግደልም  ትችያለሽ..››

‹‹ደስ ሲል ››

‹‹ደስ አይልም…››አለና ከመጣ ጀምሮ ተዘፍዝፎበት ከነበረው ቋጥኝ ላይ ክንፉን አርገፍግፎ ተነሳን ማጅራቷን ይዞ ወደሰማይ ተምዘገዘገ  ….ወደጀርባዋ ዞረና ተጣበቀባት…  ወደ አዲስአባ ተመልሰው እቤታችን ሲደርሱ ከምሽቱ 8 ሰዓት አልፎ ነበር… …

‹‹ወይኔ ድክም ብሎኛል..ግን መድሀኒቱን ስላገኘን ከአባቴ ወገኖችም ጋር ልንገናኝ ስለሆነ ደስ ብሎኛል…አንተስ ደስ አላላህም….?››ለመተኛት ወደ አልጋዋ እያመራች ነበር ምትናገረው

‹‹በጣም ከፍቶኛል››አላት ንስሯ

ደነገጠች‹‹ለምን….?››

‹‹ከንቺ ጋር የምኖረው ..በህይወትም የምቆየው ለሳምንት ብቻ ስለሆነ››

በህይወቷ እንደዚህ አይነት ድንጋጤ ደንግጣ አታውቅም.‹‹.እንዴ የእኔ ንስር ሟች ፍጡር ነው እንዴ…….?›ብላ ለመጀመሪያ ጊዜ ያሰበችብት ጊዜ ነው

‹‹ጥዬህ የምሄድ መስሎህ ነው..አብረን እኮ ነው የምንሄደው››

‹‹ይዘሺኝ መሄድ አትቺይም››

‹‹ለምን….?››

‹‹እኔ መጀመሪያም ከዛ ነው የመጣሁት…ለአባትሽ ብዬ እና አሁን ተመልሼ ለመሄድ ፍፅም አይፈቀድልኝም፡፡››

‹‹በቃ ይቀራላ ..እስከዛሬ ካንተ  ጋር እንጂ ከእነሱ ጋር አልኖርኩ.. ምን  ያደርጉልናል እነሱ መቅረት ይችላሉ››

‹‹እሱማ ጊዜው አለፈ..ቅድም ከአፍሽ የወጣችው እሳት አነሱ ጋር መልዕክት ይዛ የምትሄድ ነች…ወደድሽም ጠላሽም አንቺን ይወስዱሻል..እኔ ደግሞ ካለአንቺ ህይወት የለኝም …ተነጥለሺኝ እንደሄድሽ ወዲያው በዛኑ ሰዓት እሞታለሁ..››

‹‹እንዴ  እሞታለሁ ማለት ምን ማለት ነው….?ይሄንን ታዲያ ተክሉን ከመቀንጠሴ በፊት ለምን አልነገርከኝም….?››

‹‹ውሳኔሽ በእኔ ላይ እንዲመሰረት ስላልፈለኩ ››

‹‹ያምሀል እንዴ . ….?.ካንተ ሚበልጥብኝ ነገር አለ…….?

ህይወቴ እኮ ነህ..››አበደች ጮህች ፕሮፌሰሩ ከእንቅልፋቸው ባነው በራፏን እስኪያንኮኩ ድረስ ግቢውን አተረማመችው …፡፡

     ይቀጥላል

#ክፍል 47,,እንዲለቀቀ (15) ሰው ከስር ያለውን ሊንክ #Subscribe🔔ካረገ ይለቀቃል
https://youtube.com/@Weygud18

#Subscribe እያደረጋቹ ቤተሰብ ስለምትሆኑ እናመሰግናለን #Subscriber
YouTube link👇
https://youtube.com/@Weygud18

መልካም ምሽት ተመኘሁ🙏
🎙ግሩፑን ለማግኘት
              👇👇👇

        @Mtshaf_bicha
        @Mtshaf_bicha
❤️ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
👉አሰተያየት ካላችሁ
📩 @Eyos18     አድርሱን
             📗📒📕📗📒📕
                Join&share
                  @EyosC1
       📚ማንበብ ባህላችን ይሁን📚
┄┉┉✽‌»‌🎶••✿••🎶»‌✽‌┉┉┄
📕ተአምራተ_ኬድሮን

#ክፍል_አርባ_ሰባት

#ተከታታይ ልቦለድ

#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ

ለሊቱ ያለእንቅልፍ ነው ያለፈው….የጣር ለሊት…የስቃይ ለሊት…፡፡ደግነቱ ፕሮፌሰሩ ለሊቱን ሙሉ አብረዋት ነው ያሳለፍት…..ይሁን እንጂ እሷ ባዘነች መጠን አብረዋት እያዘኑ ነበር ብሎ በእርግጠኝነት መናገር አይቻልም..ግን በታታሪት ሲያዳምጧት እና ደረቅ አልኳል ሲያጣጧት ነበር..  ወፎች የለሊቱን መንጋት የምስራች ሊያበስሩ ሲንጫጩ ድምጻቸው የተሰማው…
ሁለት ጠርሙስ ብላክ ሌብል  ጠርሙስ ጨርሰዋል..እሷ አንድ ጠርሙስ ከግማሹን ሳትጨርስ አልቀርም፡፡በንዴት፤ በስጋትና በብስጭት ያወራችው ወሬ ቢቀረብ እና ወደ መጻሀፍ ቢገለበጥ አንድ ደለብ ያለ መጽሀፍ ይወጣዋል፡፡

‹‹ፕሮፌሰር ምን አቀበጠኝና ተክሉን ቀነጠስኩ..….?ምን ቅብጥ አደረገኝ….?››

‹‹እንደነገርሺኝ እኮ ሙሉ በሙሉ ሚያመጣውን መዘዝ አልተረዳሽም ነበር››

‹‹እኮ ረጋ ብዬ ጊዜ ወስጄ ማሰብ ነበረብኝ…ንስሬ እንኳን ሊነግረኝ ባይፈልግ…ጎትጉቼ ሙሉውን  መዘዝ መረዳት ነበረብኝ፡፡››

‹‹ግን እርግጠኛ ነሽ ..እንደዚህ ያለ ንስርሽ ለመሄድ እንደምትገደጂ ብታውቂ ኖሮ ተክሏን ከመቀንጠስ ትታቀቢ ነበር….?››

‹‹ይቀልዳሉ እንዴ ፕሮፌሰር..ጭርሽ ለማሰብ እንኳን አልሞክርም…እንዴ ንስሬን ጥዬ እንኳን የማላውቃቸው ..ምን አይነት ፍጡር እንደሆኑ እንኳን እርግጠኛ ወዳልሆንኩባቸው..ይመቹኝ አይመቹኝ  መገመት ወደማልችላቸው  የአባቴ ዘመዶች ይቅርና እግዚያብሄርም ቢጠራኝ  ንስሬን ጥዬ በፍቃደኝነት  ለመሄድ አልፈልግም››

‹‹በቃ ተረጋጊ..ያው በሞትም መለየት እኮ አለ››አሏት ፕሮፈሰሩ …በእሳቸው ቤት እሷን የሚያጽናና ቃል መናገራቸው ነው፡፡

‹‹አይ ፕሮፌሰር …ይቀልዱብኛል አይደል?ይሄም እኮ ያው ሞት  ነው…ሞት ማለት የራስ ከሆኑ ሰዎችና ከሚኖሩበት ዓለም ለዘላለም ተለይቶ በስጋ ወደመሬት ውስጥ መግባት በነፍስ ደግሞ ወደማይታወቅ አለም መጓዝ ማለት አይደል…?አሁን እኔም ከሳምንት በኃላ የሚገጥመኝ  ደግሞ በስጋም በነፍስም ከዚህች ምድርም ሆነ  የእኔ ከሆኑት ሰዎች ሁሉ  ተለይቼ ለዘላለም ወደማይታወቅ አለም በስጋም በነፍስም መጓዝ ነው…ታዲያ ይሄ እንደውም ሙሉ ሞት አይደለም..….?ማንም ሰው ስናፍቀው እንኳን መቃብሬ ጋር ሄዶ በማልቀስ ወይም አበባ በማኖር ሊያጽናና ዕድሉ አይኖረውም …. ነፍሴንም ስጋዬንም ይዤ ነው የምሄደው…››

‹‹እሱስ እውነትሽን ነው››

‹‹አዎ ዋናው ችግር  ግን ይሄ አይደለም..ዋናው ንስሬን ጥዬ መሄድ ያለመፈለጌ ነው..እሱን..››ንግግሯን አቋረጧት፡፡  
‹‹እኔ እኮ በህይወት እስካለሁ ድረስ ልንከባከብልሽ እችላለሁ፡፡››

‹‹አይ አይችሉም… እርሶ የሚችሉት በስርዓት የቀብር ሰርዓቱን ማስፈፀም ብቻ ነው››

‹‹አልገባኝም..››አሏት ደንግጠው፡፡
‹‹እኔ  ጥዬው በሄድኩ ቀን እሱም እደሚሞት ነግሮኛል››

‹‹እንዴት ሆኖ ነው የሚሞተው….?››
‹‹እኔ እንጃ ግን  እኔን ከወሰዱኝ በኃላ ለአንድ ቀንም እንኳን በህይወት መኖር እንደማይችል እርግጠኛ ሆኖ ነግሮኛል››

‹‹አይዞሽ ሳምንት እኮ ብዙ ቀን ነው..የሆነ መውጫ መንገድ ልናገኝ እንችላለን..በተለይ ንስርሽ መላ ሚያጣ አይመስለኝም››

‹‹እኔ እንጃ …. እንደዛ ተስፋ አላደርግም …››

‹‹አይዞሽ…ደግሞ ይሄ ጉዳይን እንደመስዋዕትነት ቁጠሪው..ህይወት ለማትረፍ ነው እዚህ ወጥመድ ውስጥ የገባሽው››

‹‹መስዋዕት አሉኝ….መስዋዕትነትማ እንዲህ በቀልድ አይገለጽም..እኔ ከመስዋዕትነት ይልቅ ክስረት ነው የሚሰማኝ…መስዋዕትነት እኮ ለአንድ ክብር አለማ አቅዶና አስቦ ሕይወትንም ጭምር መስጠት ማለት ነው…ህይወትንም ጭምር ቢሆን አጥቶ ሌላውን ለማኖር ቀድሞም አምኖና ወስኖ መተግበር ማለት ነው…

‹‹ልክ እንደ አርበኞቻችን ማለትሽ ነው….?››

‹‹አዎ እንደውም ዛሬ ለሀገር መስዋዕትነት ስለከፈሉ ሰዎች ምስጋና የምናቀርብበት ቀን አይደል…ሀገር ከምትደፈር የእኔ ህይወት ትቀጠፍ ብለው…ለልጆችና ለልጅ ልጆቻችን ባርነትን ከምናወርስ እኛ ዛሬ ደማችንን እረጭተን አጥንታችንን በትነን ነጻነትና ኩራትን እናወርሳቸው ብለው ታሪክ እንደሰሩት አባቶቻችን   ነው መስዋዕትነት….ልክ እንደ በላይ ዘለቀ፡፡ ከገዛ አብራክ ልጅ ይልቅ ሀገርን ወይም ህዝብን ማስቀደም ማለት ነው…ለሀገር ክብር እና ለወገን መድህን ሆኖ መውደቅ ማለት ነው…ከስኬት በኃላም ላደረጉት ነገር የተለየ ክብር እና ሹመት አለመፈለግ ማለት ነው..ለሚወዱት ነገር ያለንን ነገር ሁሉ ህይወትንም ጭምር በነፃ መስጠት ማለት ነው….
እንደዛአይነት መስዋዕትነት ሚስጥሩ ከባድ ነው….ከድል በኃላ የበላይን ይሄንን ለሀገሩ በነፃ የሰጠውን መስዋዕትነት  ሸፍጠኞቹ እና ባንዳዎቹ አልወደዱለትም ነበር..ምክንያም ስለእሱ ዝናና ታሪክ ሲሰሙ የእነሱን ሆዳምነት እና  ትንሽነታቸውን በየጊዜው ስለሚያሳብቅባቸው ከንጉሱ አላትመው በአደባባይ እንዲሰቀል አደረጉት..ከጠላት በክብር የተረፈች ነፍሱ በገዛ ህዝቦቹ ምቀኝነት እና ክፍት ተነጠቀች…ይሄ ነው መስዋዕትነትን መራር የሚያደርገው…ለዚህ ነው መስዋዕትነት የሚለው ቃል ሚያስጠላኝ፡፡

‹‹ትክክል ነሽ ልጄ…ይሄ የበላይ  ታሪክ የእንግሊዞች ቢሆን፤ይሄ የበላይ  ታሪክ የአሜሪካኖች ቢሆን  ኖሮ አንድ ሺ ፊልም እና አስር ሺ መጽሀፍ ተጽፎበት ነበር…?ስንት መንገድ እና ስንት ዩኒቨርሲቲ በስሙ ተሰይሞለት ነበር…?››
እኚህ  ለሊቱን ከፕሮፌሰሩ ጋር በመጠጥ እያወራረድ በእሷ ለቅሷ ታጅበው  ሲያወሩ ከነበሩት ነጥቦች ጥቂቶቹ  ነበሩ..….

አሁን ሰዕቱ ከማለዳ 12፡45 ይላል…ፕሮፈሰሩ በመጠጥ እና በእሷ ወሬ ተዳክመው ይመስላል እዛው የተቀመጡበት ሶፋ ላይ ደገፍ እንደሉ እንቅልፍ ይዞቸው ጭልጥ ብሏል….ንስሯ ያለው መኝታ ቤት ውሰጥ ነው ከእሷ በላይ ትካዜና ቁዘማ ውስጥ ነው…ልትነካካው አልፈለገችም
እየተንገዳገደች እቤቱን ለቃ ወጣችና ወደ መኪና ማቆሚያ አመራች…‹‹ከጠጡ አይንዱ›› የሚለውን የትራፊኮችን ዋና ምክር አዘል መመሪያ ከቁብም ሳትቆጥር መኪናዋን አስነሳችና ግቢው ለቃ ተፈተለከች..ቀጥታ ወደመላኩ ቤት ነው ያመራችው…
እንደደረሰች ወደጊቢው አጥር አስጠጋችና መንገድ እንዳይዘጋ አስተካክላ መኪናዋን ካቆመች በኃላ ሞተሩን በማጥፋት ከመኪናዋ ወረደችና  የግቢውን በራፍ መጥሪያ በሰከንድ ሽርፋራፊ ውስጥ  ደጋግማ አንጣረረችው ፡፡ከጠበቀችው በፈጠነ  ሁኔታ ተከፈተላተት..ከእንቅልፉ የባነነ እና በአንድ እጁ አይኖቹን እያሻሸ በሌላ እጁ የበራፍን እጄታ ይዞ ‹‹ምን ፈለግሽ….? ›› የሚላት ሰው ስትጠብቅ .. ንቁ እንቅልፍ በዓይኑ እንዳልዞረ የሚያስታውቅ..አይ እንደውም እያለቀሰ የነበረ ከዚህ በፊትም ያየችት ዘበኛ ከፈተላትና…ምንም ነገር ሳይጠይቃት እንድትገባ መንገዱን ዞር ብሎ ለቀቀለት …አልፋ ገባችና መንገዷን ቀጠለች ..በፍጥነት ዘግቷ ከኃላዋ ተከተላት፡፡

‹‹ዛሬ ምን አይነት ቀን ነው…….?ሰው ሁሉ ሲያለቅስ እንቅልፍ አጥቶ የሚያድርበት ቀን ነው እንዴ….?››ከዘበኛው ሁኔታ ተነስታ ውስጧን እየጠየቀች ነው…  እራሷን ለመቆጣጠር በዚህ በተወለካከፈ እርምጃ አንድ ነገር አደናቅፏኝ እንዳትደፋ  እየፈራች ስትራመድ ዘበኛው በታፈነ ድምጽ መናገር ጀመረ

‹‹ጋሼ ደውለውልሽ ነው….?››

‹‹አዎ›› አለችው….ምንም ሳታስብበት

‹‹አይ ቢጨንቃቸው እኮ ነው ..በቃ እኮ 10 ደቂቃም ዕድሜ አይራቸውም …አብቅቶላቸዋል…››

‹‹ማን ነው ያበቃለት ….?››ደንግጣ
📕ተአምራተ_ኬድሮን

#ክፍል_አርባ_ስምንት

#ተከታታይ ልቦለድ

#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ

የሰው ልጅ ውስጡ ሲጨልምበት እና የመጨረሻ ተስፋው መቁረጥ ላይ ሲደርስ ብስጭቱን የሚያራግፍበት ወይም የሚያላክክበት ሶስት አካላት አሉ…መንግስት፤እግዚያሔር እና እናት ፡፡
የመንግስት እንዝለለው…እግዚያብሄርን ግን ሲከፋን ለምን ፈጠርከኝ….? ብለን እንጠይቀዋለን……መፈጠር ትፈጊያለሽ ወይስ ይቅርብሽ ብለህ ምርጫ ሳትሰጠኝ ለምን ፈጠርከኝ…….?እሺ ይሁን ካለፍላጎቴ ከፈጠርከኝሽ በኋላ ለምን እንደፍላጎቴ ልታኖረኝ አልቻልክም.?  ወይም ብትችል እንኳን ለምን አልፈለክም….? ብለን እንጠይቀዋለን…

እሱ በፍቃዱ እኛን መፍጠሩ እና እንደ እኛ ፍቃድ ሳይሆን እንደእራሱ ፍላጎትም የህይወት ጅረታችን  የሚፈስበትን መስመር ማስመሩ ስህተት አይመስልም...የሰው ልጅም ሲበሳጭ ፤ተስፋ ሲቆርጥና ሲማረር ለምን ….?ብለን እሱን መጠየቃችንም ስህተት አይደለም….የእግዚያብሄር ዋናው ጥቅም የህይወት ሸክማችንን ከብዶን ስንንገዳገድ ከመውደቅ ታድጎ እንዲያግዘን  እና የተሰበረ ተስፋችን እንዲጠግንልን የተንኮታኮተ ሞራላችን እንዲያክምልን ነው….ስለዚህ በከፋን ጊዜ ልንነጫነጭበት የግድ ነው…መነጫነጫችንም ክፋት የለውም፡፡
ከእግዜር ቀጥሎ በዚህ ጉዳይ የፈረደባት እናት ነች …አራት አመት ሆነን አርባ አመት ሁላችንም ውስጣችን ጨልሞ ነጋችንን ማለም ድክም ሲለን ወደ እናታችን ጉያ ሮጠን መሸጎጥ የመጀመሪያ ተግባራችን ነው፡፡ 

…እናታችንን በቅርብ አግኝተን የተመኘነውን ማድረግ ባንችል እንኳን ‹‹….እማዬ ለምን ወለድሺኝ….? ››ብለን ባትሰማንም ማማረራችን አይቀርም….በማማረሩ ውስጥ ምስጋና አለው…ለህልውናችን መሰረቷ ሰው ለመሆናችን ዋናዋ ምክንያቷ  እሷ ለመሆኗ እየተናገርን ለዛም እውቅና እየሰጠናት ነው…
አሁን እነኬድሮን ያሉት ደሎመና ነው…ትውልድ ሀገሯ፡፡ያሉት ሳር ቤት ውስጥ ግድግዳውን ተደግፎ በተሰራ እና ግዙፍ አጎዛ በተነጠፈበት ትልቅ መደብ ላይ ፤ ንስሯን ከጉያዋ አድርጋ እናቷ እግሯ ላይ ተኝታ እንባዋን እያንጠባጠበች ነው….አሁን ካሉበት የሳር ቤት ፊት ለፊት ባለአራት ክፍል ቢላ ቤት ቢኖራትም እናቷ ግን አትወደውም…በቃ አስገዳጅ ሆኖባት እንግዳ ካልመጣባት በስተቀር ውሎዋ እዛች ሳር ቤት ውስጥ ነው…ምግቡ እዛው ይሰራል እዛው ብና ይፈላል….እዛው ጋደም ይባላል…

‹‹ገራኮ ማል ታቴ….?››(ሆዴ ምን ሆንሽ….?)ትጠይቃለች እናቷ
ድምጽ ያላጀበውን እንባዋን ከማፍሰስ ውጭ መልስ ልትሰጣት አልቻለችም….እርግጥ ሊሆን ያለውን ነገር ለእሷ ልትነግራት እና ልትሰናበታት  ነው የመጣችው …ግን እንዲህ በቃላሉ ቃላት ከአንደበቷ ልታወጣ አልተቻላትም፡፡

‹‹ሆማ ኢንታኔ ሀርሜ ኮ..ነገኡማ ›( ….ምንም አልሆንኩ እናቴ…ደህና ነኝ)

‹‹ቀሮ ቲያ .ኢንሶቢን ….? ››(የእኔ ብልጥ አትዋሺኝ….?)

‹‹እማ ጨንቆኛል..በጣም ጨንቆኛል..መልሼ ወደሆድሽ ሁሉ መግባት አምሮኛል››

‹‹እኮ ንገሪኝ …እኔ እናትሽ እያለሁ ለማን ይድላው ብለሽ ትጨነቂያለሽ……?ደግሞ ባንቺ ጭንቀት አያምርም..አንቺ እኮ ለተጨነቀው ሁሉ መፍትሄ ስትሰጪ እንጂ ስትጨነቂ  አያምርብሽም››

‹‹እማ አሁን የገጠመኝ ግን ከባድ ችግር  ነው››

‹‹እኮ ምንድነው….?››

‹‹ልሄድ ነው››

ፈገግ አለች እናቷ‹‹እንቺ እኮ ገና ከልጅነትሽ ጡት ሳትጥይ ጀመሮ እንደሄድሽ ነው….ያንቺ መሄድ ምን አዲስ  ነገር ኖሮት ነው
ሊያስጨንቅሽ የቻለው…….?አይዞሽ ልጄ ንስርሽ ከጎንሽ እስካለ የትም ብትሄጂ ምንም ሀሳብ አይገባኝም..በዛ ላይ የእኔ የእናትሽ ፀሎት እና የአባትሽ መንፈስ በየሄድሽበት ሁሉ ይከተልሻል… ይጠብቅሻል፡፡››

‹‹ሀርሜ…ንስሬ አብሮኝ አይሄድም ….››

ባለማመን አፍጥጣ አየችት..ምክንያቱም ንስሯ ለአንድም ቀን ቢሆን ከእሷ የተለየበትን አጋጣሚ እናቷ አታስታውስም..እንደውም እናቷ ሁለት መንታ ልጇች አሉኝ ብላ ነው የምታወራው…ያው እንደሚታወቀው እናቷ በምትኖርበት አካባቢ በጣም የተከበረችና ሰው ሁሉ የሚፈራት  ነች‹‹….አረ ከዳቢሎስ የተወለደች ልጅ አለቻት …አንድ ነገር ብለን ብናስከፋ በልጇ ታስጠፋናለች….አታዩም እንዴ ልጇ እኮ አቅፋ የምትኖረውን ንስር ዳቢሎሱ አባቷ ነው የላከላት›› እያሉ በማንሾካሾክ እንደሚያሟት ታውቃለች……በዛም ምክንያት ሳይወዱ በግዳቸው ይፈሯታል..ስለሚፈሯትም በጣም ያከብሯታል….ግን ይህን ንስሯን የላከላት አባቷ መሆኑን ትጠራጠራለች እንጂ እርግጠኛ አይደለችም እንዴ….….?

‹‹ለምን ልጄ…?ለምንድነው አብሮሽ የማይሄደው….?››

‹‹የምሄድበት ቦታ እሱን ይዤ መሄድ አይፈቀድልኝም….ቢፈቀድልኝ እሱ አዛ መኖር አይችልም…. አየሩ አይስማማውም…››

ከተጋደመችበት ጭኖ ላይ ገፍትራ አስነሳቻትና እንድትቀመጥ አድርጋ ፊት ለፊት አፍጥጣ እያየቻት‹‹እንዴ ቅሪያ…እንዴት እሱን ጥለሽ መሄድ ታስቢያለሽ…….?የህይወት ጉዳይ  ቢሆን እንኳን ማድረግ የለብሽም..እሱን ጥለሽ ሄድሽ ማለት እኔንም አሳዝነሽ ሄድሽ ማለት ነው…በዕድሜሽ ለመጀመሪያ ጊዜ አዝንብሻለሁ››

‹‹ሆድ ለባሰው ማጭድ አታውሰው›ይሏችኋል ይሄ ነው..ከእሷ  ባሰች……በጣም ከባዱን ነገር ጭራሽ የበለጠ ጠጣር አደረገችባት፡፡

‹‹ሀርሜ ወዴት እንደምሄድ እኮ አልገባሽም….?››

‹‹ወደ የትም ይሁን አልኩሽ እኮ ..ንስርሽን ጥለሽ የትም መሄድ አትቺይም›› አለችና..ከእቅፌ ንስሬን መንጭቃ ወስዳ ጉያዋ ውስጥ ወሸቀችው…እሱም እጥፍጥፍ ብሎ ተሸጎጠላት፡፡

አፈረጠችው‹‹አባዬ ጋር ነው የምሄደው››
በእድሜዋ ሙሉ እናቷ በዚህ መጠን ስትደነግጥ አጋጥሞት አያውቅም..ሰው እንዴት እየታየ የሰውነት ቀለሙ እየተቀየረ ይሄዳል..?እንዴት እያያችሁት ደም ስሮቹ እየተወጣጠሩ እና ለእይታ ግልጽ እየሆኑ ይታያል….?ሰው እንዴት በሚያግለበልብ ሙቀት ውስጥ ሆኖ የአንታሪቲካ በረዶ ውስጥ እንደጣሉት ጥርሶቹ እርስ በርሳቸው ይንገጫገጫሉ….መልሰው ቃላት ለመለዋወጥ አያሌ ደቂቃዎች ነው ያሳለፈት…..

‹‹እንዴት አድረገሽ ነው የምትሄጂው….?››

‹‹ወገኖቹ ከስድስት ቀን በኃላ መጥተው ይወስዱኝል››

‹‹እሱስ ይመጣል….?››ጉጉት ባሰቃየው እይታ እያየች ጠየቀቻት
‹‹አይ እሱ እንዲመጣ የሚፈቅዱለት አይመስለኝ››

‹‹እሱስ ትክክል ነሽ…ግን እነሱስ እንደሚመጡ በምን አወቅሽ….?››

የሆነውን ሁሉ አስረዳቻት..ቀስ በቀስ በድንጋጤ ወይቦ የነበረው ፊቷ በደስታ እየደመቀ እና እየፈካ መጣ

‹‹እማ እየሳቅሽ እኮ ነው…….?››በገረሜታ ጠየቀቻት ..እያለቀሰችም እየሳቀችም መሆኗ ገርሞት

‹‹አዎ..በጣም ደስ ብሎኝ ነው››

‹‹እንዴ!! እንዴት ደስ ይልሻል..….?ከሄድኩ እኮ አልመለስም››

‹‹አውቃለሁ…ታውቂያለሽ አይደል ትናፍቂኛለሽ …. በጣም ነው የምወድሽ …ግን ወደአባትሽ ነው የምትሄጂው..ደግሞ በአንቺ ዕድሜ ሙሉ ለብቻዬ ተሸክሜው የኖርኩትን እወነቴን ዛሬ አንቺ አረጋገጥሺልኛል… እንዳልተሳሳትኩ አንቺ ልጄ ምስክር ነሽ…እንቡጥ ልጃገረድ ሆኜ ከሌላ አለም የመጣ ሰው መሰል ፍጡር አፍቅሬ እንደነበረ ….ወደእሱ የመኖሬያ አለምም ለአንድ ቀን ወስዶኝ እንደነበረ…የወለድኳት ልጅ አባትም እሱ እንደሆነ ለዘመድም ለጓደኞቼም ሳወራ ነበር የኖርኩት..ግን አውቃለሁ አንድም ሰው አምኖኝ አያውቅም ነበር…እንደውም ነካ እንደሚያደርግኝ ነው የሚስቡት…ዛሬ እወነቴን እንደነበርና ዕድሜዬን ሙሉ ያፈቀርኩት ፍቅር የእውነት እንደነበር አንቺም ተገንዝበኛል…በህይወቴ ሙሉ ከዚህ በላይ ምንም የሚያስደስተኝ ነገር ሊፈጠር
📕ተአምራተ_ኬድሮን

#ክፍል_አርባ_ዘጠኝ

#ተከታታይ ልቦለድ

በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ

ወደሸገር ተመልሰዋል..ማለት እሷ እና ንስሯ ፡፡ለእናቷ በመጨረሻው ቀን ተመልሳ እንደምታያትና ወደአባቷ ዘመዶችም በምትሄድበት ቀን አጠገቧ እንድትሆን እንደምትፈልግ   ነግራትና ቃል ገብታላት ነው የመጣችው፡፡
እስከዛው ያሉትን ቀጣዬቹን በስስት እየተሸራረፉ በመርገፍና በማለቅ ላይ ያሉትን ቀሪ 5  የሰቀቀን ቀናቶችን ሸገር ልታሳልፍ ወስናለች….ምን አልባትም አይታውቅም… በመሀል ሀሳቧን ልትቀይር ትችላለች፡፡
ግን አሁን ተረጋግታ እቤቷ መቀመጥ አልቻለችም … ሰዓቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ቢያልፍም ልትቆጣጠረው የማትችለው ከውስጧ ሚመነጭ ስውር ስሜት ውጪ ውጪ ይላት ጀመር….ልብሷን ቀያየረችና መኪናዋን ወዳለችበት መራመድ ከጀመረች በኃላ ሀሳቧን ቀየረችና ስልኳን አውጥታ ደወለች..አዎ ነፃ መሆን ነው የምትፈልገው….ላዳ ያለው የምታውቀው ልጅ ጋር ነው የደወለችው፡፡

‹‹ሄሎ››

‹‹ሰላም ነው… .ፈልጌህ ነበር…የት ነህ ያለኸው?››

‹‹ይቅርታ ዛሬ ስራ ላይ አይደለሁም መኪናዬ ተበላሽታ ገራዥ ነች››

‹‹በቃ አንተ ናልኛ ..የእኔ መኪና ስላለች ትይዝልኛለህ …ጥሩ ስሜት ላይ ስላልሆንኩ መንዳት አልፈለኩም››

‹‹ደስ ይለኝ ነበር.. ግን ያው ስራ የለኝም ብዬ ከከተማ ወጣ ብያለሁ…..ከፈለግሽ አንድ ጓደኛዬን ልልክልሽ እችላለሁ››

‹‹ደስ ይለኛል››

‹‹በቃ ንገረውና ቁጥርሽን ሰጠዋለሁ…ይደውልልሻል››

‹‹እሺ አመሰግናለሁ››ስልኳን ዘጋችውና ጊቢዋ ውስጥ እየተዘዋወረች እስኪደወልላት መጠበቅ ጀመረች….፡፡
ብዙም ሳይቆይ ስልኳ ላይ የማታውቀው ቁጥር ተንጫረረ …አነሳችው..አናገረችው ….በ15 ደቂቃ እንደሚደርስ ነገራት…..መጠበቅ ጀመረች…..

‹‹አዎ በዚህ ለሊት ምን አልባት ለመጨረሻ ጊዜ ማበድ እፈልጋለሁ..አዎ ብዙ ነገር ማድረግ አምሮኛል…የማሰብ አቅሜን አዳክሞ ጭንቀቴን የሚቀንስልኝን ማንኛውንም ነገር ለማድረግ እፈልጋለሁ…..መጠጣትና መስከር …መቁላላትና መዋሰብ እፈልጋለሁ…መጣላትና መደባደብም ካገኘሁ አልጠላም…››
እግዜር ይስጠው የመኪና ጥሩንባ ድምጽ ሰማች...ጎበዝ ልጅ ነው… በነገረችው ምልክት መሰረት ሳይሳሳት መምጣቱ አስደሰታት… በራፍን ከፈተችና ወጣች…በምልክት ጠራት … የላዳውን በራፍ ከፈተላትና ገባች፡፡

‹‹ወዴት ልውሰድሽ….?››

‹‹መጠጣት ነው የምፈልገው››አለችው፡፡

‹‹መጠጣት›› አላት ግራ ተጋብቶ፡፡

‹‹መጠጣት ስልህ …ብሽቅጥ እስክል መጠጣት ነው የምፈልገው…የፈለከውን ያህል ከፍልሀለሁ እስከንጋትም ቢሆን አብረኸኝ ትቆይና እቤቴ ታስገባኛለህ››

‹‹ይመችሽ ››አላት….

እንዲሁ ወደደችው…አንድን ሰው አይተን በውስጣችን ስለሰውዬው ደስ የሚል ስሜት ሲሰማን ውቃቢዬ ወዶታል  የምንለው ነገር አለ አይደል..….? እሷም ይሄን የላዳ ሹፌር  እንዳየችው  እንደዛ ነው የተሰማት፡፡

‹‹ምርጫሽ የት አካባቢ ነው?››

‹‹የፈለክበት ውሰደኝ ››

‹‹ቺቺኚያ ይመችሻል››

‹‹ይመችህ››

ነዳው….ንስሯ አምኗት እቤት ሊቀር አልቻለም  …ከፊት ለፊታቸው  በላዳዋ   ፍጥነት መጠን  ሲበር በመኪናዋ መስታወት አሻግራ አየችው….

ደረሱና መኪናዋን ምቹ እና ደህንነቱ የተጠበቀበት ቦታ ፓርክ አድርገው አንዱ ጭፈራ ቤት ገቡ……እሷ ደረቅ አልኮለሏን ስታዝ እሱ ዉሀ አዘዘ..

‹‹ለምን ትንሽ አትሞከርም….? ››

‹‹አይ …የሞያዬ ስነምግባር አይፈቅድልኝም›› ሲል መለሰላት በቀልድ መልክ

..ዝም አለችው… በላይ በላዩ መለጋቱን ቀጠለች….የሙዚቃው ከጣሪያ በላይ ጩኸት…የለሊት ንገስታቶች በገዢ መሳይ  ወንዶች ዙሪያ መሽከርከር፤  በስካር የሚናውዙና የሚደንሱ ወንዶችና ሴቶች የሆቴሉን ወለል መሙላት…የሆነ ትርምስምስ ያለ ነገር ነው የሚታየው….በዛ ላይ መብራቱ በአምስት አይነት ቀለም በመፈራረቅ ቦግ ብልጭ ሲል  እይታን ብዥ ያደርጋል…….ግን በምትፈልገው መጠን ባይሆንም ተመችቷታል ፡፡ቢሆንም ደስታዋን ሙሉ ማድረግ ፈለገች…

‹‹ሌላ ጓደኛ የለህም….?››ድንገት ከመሬት ተነስታ ጠየቀችው፡፡

‹‹ምን አይነት….?››

‹‹ሹፌር››..

‹‹ምን ያደርግልሻል….?››

‹‹ያንተን መኪና የሚነዳልን››

‹‹እኔስ….?››አላት በጥያቄዋ ግራ ተጋብቶ

‹‹አይ አንተማ እንድታጣጣኝ ፈልጌ ነው..ብቻዬን ደበረኝ››

‹‹እ ..ቆይ እስኪ ደዋውዬ ልሞክር››አለና ስልኩን እየጎረጎረ ከሆቴሉ ወጣ..ሲወጣ ከጀርባው ሳታየው ነበር…ቁመናው መስጧታል..በቃ የተለመደው ችግሯ እያገረሸባት ነው..ጭኗ መካከል አሳከካት…ምን አይነት መጥፎ አመል ነው…እዛም አባቷ  አለም ስትሄድ እንዲህ የሚበላት ነገር ወቅት እየጠበቀ ይፈታተናት  ይሆን እንደዛ ከሆነ ምንድነው የምታደርገው….….?

ሀሳቧን ሳትጨርስ መጣና መቀመጫው ላይ ተመልሶ እየተቀመጠ..‹‹ተሳክቶል…ተቀላቅዬሻለሁ››አላት

በደስታ እየፈገገች‹‹ምን ይምጣልህ..?››ሥትል ምርጫውን ጠየቀችው፡፡

‹‹አንቺ የያዝሺውን…››
ሙሉ ጠርሙስ አዘዙ…መጣላቸው…… ይገለብጡት ጀመረ…እየደነሱ እየተቀመጡ …ደግሞ ተመልሰው በመነሳት እየደነሱ ..ውልቅልቃቸው እስኪወጣ ድረስ አስነኩት‹‹  …አቤት ዳንሱ !!ፕሮፌሽናል ነው ፡፡ልቤን ስልብ ነው ያደረገኝ…›አለች በዳንስ ችሎታው ተመስጣ፡፡ይበልጥ ሰውነቱ ላይ ተለጥፋ በተሸሻችው መጠን የጭኗ መብላላ  አደብ እየነሳት ነው…በትርምሱ መካከል በዳንስ ስልት በማሳበብ እጣቷን  ወደጭኗ በመስደድ   ይሉኝታ እስክታጣ ድረስ እያሻሸች  ነው..ደግነቱ ሁሉም በመጠጥ የደመቀ እና በመብራቱ ቦግ ብልጭ ብዥ ያለበት መሆኑ በጃት …
ከለሊቱ አምስት  ሰዓት አካባቢ ሲሆን ግን ተዳከሙ…

‹‹ቤት እንቀይር ….?››አለችው… ቤት መቀየር የፈለገችው ሙዳችውንም ጭምር መቀየር ስለፈለገች  ነው… ተስማማ ..ሂሳብ ዘግተው ወጡ…

‹‹ጭፈራ ቤት ሳይሆን ዝም ብለን የምንጠጣበት ቦታ ነው የምፈልገው…››

ወደላዳዋ ይዟት ሄደ …ቅድም ተጠርቶ የመጣው ጓዳኛውን ገቢና ቁጭ ብሎ ጫቱን ሲቀመቅም  አገኙት..ሁለቱም ተደጋግፈው ከኃላ ገቡ… ላዳዋ ተንቀሳቀሰች… በመስኮቱ አንጋጣ ሰማዮን ሰታይ ንስሯን ቀድሟት ለመብረር ሲያኮበኩብ አየችው…ሰካራሙ ጓደኛው እይታዋን ተከትሎ ወደውጭ በተመሳሳይ ሁኔታ  ካየ በኃላ‹‹ አይገርምም ይሄ አሞራ ቅድምም ስንመጣ ከፊት ለፊታችን ሲበር  ነበር….እርግጠኛ ነኝ የተለየ ከለር ስላለው አስተውዬው ነበር››አለ

‹‹አሞራ አይደለም..ንስር ነው››አረመችው 

‹‹እንዴ.. አዎ ንስር ነው ትክክል ..አንቺ ግን እንዴት አወቅሽ….?››

‹‹የእኔ ነው››በልበ ሙሉነት መለሰችለት፡፡

‹‹የእኔ ነው ስትይ….?››ያዝ ያዝ በሚያደርገው የስካር አንደበት ጠየቃት 

‹‹ወንድሜ ነው››

ሁለቱም ተንከትክተው ሳቁ

‹‹..ቀልደኛ ነሽ..ይበልጥ ስትጠጪ  ደግሞ ይብልጥ ቀልደኛ የመሆን ተስፋ አለሽ ማለት ነው››አላት፡፡

….አስረድቶ ማሰማንም ሆነ ተከራክሮ ማሸንፈ እንደማትችል ስለተረዳች‹‹ይሁንልህ›› አለችው ፡፡
መገናኛ አካባቢ ደርሱ… ብዙም ትርምስ የሌለበት እሷ የማታውቀው ሁለቱ ግን የሚያውቁት ሆቴል ይዘዋት ገቡ..ሹፌሩ ከላዳዋ አልወረደም…‹‹ጫቴን ብቅም ይሻለኝል›› ብሎ ቀረ …እነሱ ተያይዘው ገቡና የተገነጠለ እና ከታዳሚ የራቀ ወንበር ይዘው ተቀመጡ፡፡