ፒያሳ መሃሙድ ጋ ጠብቂኝ
183K subscribers
279 photos
1 video
16 files
201 links
እዚህ Channel ላይ ያስተምራሉ ያዝናናሉ ብለን የምናስባቸውን
🎯ተከታታይ ልቦለድ
🎯ግጥም
🎯ወግ
🎯ፍልስፍና
🎯ምክር
🎯መነባንብ

#ማንኛውም አይነት ፅሁፎች📕 ከፈለጉ ይቀላቀሉን
የተለያዩ PDF መፅሐፍት ከፈለጉ @Eyosibooks
አስተያየት ካሎት👇👇
☎️• 0922788490

📩@Eyos18
Download Telegram
‹‹በቃ አልቅሰሽ ቅበሪኝ….ከዛ በኃላ ሞተ የእያንዳንዱ ሰው ዕጣ ፋንታ መሆኑን አምነሽ ተቀበይና ወደ ህይወትሽ ተመለሺ…የራስሺኝ ሰው ፈልገሽ ኑሮሽን  ኑሪ….የእኔ በድን ታቅፈሽ እዚህ ቤት ባሳለፍሽው ስድስት ቀናት ውስጥ ስራ ላይ ብትሆኚ ኖሮ ሰንት ነፍስ  እንደምታታርፊ አስበሽዋል….… ?ስንት ያንቺን ክትትል የሚፈልጉ ህመምተኞችን እርግፍ አድረግሽ በመተውሽ  በያሉበት ምን ያህል እየተሰቃዩ እንደሆኑ ታውቂያለሽ….…?ያባትሽን መንፈስ ለዘላለም ለማስደሰት እውነታውን ተቀብለሽ  ፈገግ በይ ..በእኔ ስም የአዛውንቶችን ጤንነት ተንከባከቢ…እኔን እያሰብሽ ሞያሽን በጥንቃቄ እና በታማኝነት ስሪ..እያንዳንዱ ሰው ባንቺ እጅ ታከሞ በመዳኑ ተደስቶ ፈገግ ሲል  እኔም ባለሁበት  ፈገግ እንዳልኩ በማሰብ ውስጥሽ ሀሴት ታድርግ….›.

‹‹አዎ አባ እውነትህን ነው..እንዳልከው አደርጋለሁ››

‹‹ስለዚህ ተስማምተናል››

‹‹አዎ አባ ..ተስማምተናል››

‹‹በቃ ደህና ሁኚ ልሄድ ነው

‹‹አባ ከመሄድህ በፊት ››

‹‹እሺ ምንድነው…?››

‹‹ግን ገነት ነው ምትገባው አይደል…?››

‹‹አይ ልጄ..መች ሄድኩና አውቀዋለሁ ..ግን ምንም አይት ፍራቻ እየተሰማኝ አይደለም….እረፍትና እፎይታ ነው ዙሪያዬን የከበበኝ….የሚታየኝ  አንፀባራቂ ብርሀን እንጂ ፅልመት አይደለም….እና ፈጥኜ የመሄድ ፍላጎት ነው ያለኝ…ባከሽ ልጄ እንድዘገይ አታድርጊኝ..››

‹‹እሺ አባ ..አንድ የመጨረሻ ጥያቄ››

‹‹ምን ልጄ…?››

‹‹እማዬን ታገኛታለህ…?››

‹‹አዎ ልጄ ተስፍ አደርጋለሁ..በጣም መቸኮሌ አንድም ለዛ ይመስለኛል››

‹‹እንደምወዳትና በጣምም እንደናፈቀቺኝ ንገርልኝ››

‹‹እሺ ነገርልሻለሁ››
ደግሞ ቀኔ ደርሶ ወደእናንተ  ስመጣ ከእናንተ ጋር አብሬያችሁ መኖር ነው የምፈልገው››

‹‹እሺ ልጄ  እንዳልሽ…ደህና ሁኚልኝ…››

‹‹እሺ አባ ደህና ሁን››

     ይቀጥላል።

#ክፍል 57,,እንዲለቀቀ 👍(20) ሰው ከስር ያለውን ሊንክ #Subscribe🔔ካረገ ይለቀቃል
https://youtube.com/@Weygud18

#Subscribe እያደረጋቹ ቤተሰብ ስለምትሆኑ እናመሰግናለን #Subscriber
YouTube link👇
https://youtube.com/@Weygud18

መልካም ምሽት ተመኘሁ🙏
🎙ግሩፑን ለማግኘት
              👇👇👇

        @Mtshaf_bicha
        @Mtshaf_bicha
❤️ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
👉አሰተያየት ካላችሁ
📩 @Eyos18     አድርሱን
             📗📒📕📗📒📕
                Join&share
                  @EyosC1
       📚ማንበብ ባህላችን ይሁን📚
┄┉┉✽‌»‌🎶••✿••🎶»‌✽‌┉┉┄
❇️ተአምረተ_ኬድሮነ

#ተከታታይ ልቦለድ

#ክፍል_ሃምሳ_ሰባት

በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ


ቫይብሬት ላይ የተደረገ ሞባይል ስልክ ላይ ሲደወል እንዳለ ንዝረት ተንቀጠቀጥችና አዕምሮዋን ከንስሯ ጋር አላቀቀች…
ሰላም ወደኬድሮን ተንደርድራ መጥታ እግሯ ሰር ድፍት አለችና‹‹በጣም አመሰግናለሁ….እግዜር ይስጥሽ››

‹‹ተነሺ ..እኔን አታመስግኚ…እሱ በጣም ስለለመነኝ ነው እንዲህ ያደረኩልሽ…››አለቻት

‹‹ኤርሚ እግዜር ይስጥልኝ….አንተንም በጣም  ነው የማመስግንህ..ምን አይነት ሰላም በውስጤ እንደተሰራጨ አትገምትም››አለች ወደመቀመጫዋ ተመልሳ በመቀመጥ

‹‹በነጋራችን ላይ በጣም ነው የሚያፈቅርሽ …እንደነገረኝ ከሆነ ከልጅነቱ ጀምሮ አንቺን ሲያፈቅርሽ ነው የኖረው….አንድም ቀን አንቺን ማፍቀር አቁሞ አያውቅም..ግን በኑሮ ደራጃ ስለምትለያዩ እሺ አትለኝም የሚል ፍራቻ በውስጡ ስላለ  ካንቺ ሲሸሽ ነው የኖረው››አፈረጠችለት

ባለማመን አንዴ ኬድሮንን አንዴ እሱን በማፈራረቅ ማየት ጀመረች..ኤርምያስም የተቀመጠበት ወንበር ላይ አንገቱን ወደወለሉ እንደደፋ ሚገባበት ጠፍቶታል እጆቹን እያፍተለተለ ነው…

‹‹አላውቅም ነበር…ኤርምያስ እኔን ማፍቀር….…?››

‹‹አዎ….ኤርምያስ አንቺን…››

‹‹እሺ ጥሩ ነው…አሁን ምን እናደርግ …ኤርሚ እርዳኝ ለእድር ሰዎች ንገራቸው…አባቴ ዛሬውኑ እንዲቀበር እፈልጋለሁ….››

‹‹አረ እሺ… ችግር የለውም… አሁኑኑ ነግሬያቸው ልምጣ …ስልካቸውን ስለማላውቅ እናቴ ጋር ሂጄ …››ብሎ ተነሳ 

ኬድሮን የተለየ ሀሳብ አመጣች‹‹ቆይ መጀመሪያ የሬሳ ሳጥን እንግዛና አባትሽኝ  በሳጥኑ ውስጥ በማድረግ  ማዘጋጀት አለመብን..አሁን ዕድርተኛው መጥተው ጓደኞቸው ተሰብስበው እንገንዝ ማለታቸው አይቀርም …እንደዛ ከሆነ ደግሞ ሌላ ሀሚት ላይ ይጥልሻል…በህግም ሊያስጠረጥርሽ ይችላል››

‹‹ታዲያ ምን እናድርግ››አለች ግራ ገብቷትና ያለሳበችውን ነገር ስላነሳው ደንግጣ

‹‹ግድ የለም እኔና ኤርሚ ሳጥኑን ይዘን እንምጣ..ሁሉንም ከጨረስን  ብኃላ ለሌላው ሰው እንናገራለን….››

‹‹አስቸገርኮችሁ አይደል…?›› 

‹አረ አትጨነቂ …እኔን እንደእህትሽ ቁጠሪኝ… ኤሪሚም  ያው ያንቺው ነው..››አለችና ምትናገረው ጠፍቷት በመቁለጭለጨ ላይ ሳለች የደነዘዘውን ኤርሚያስን ይዛው ወጣች…

መኪናው ውስጥ ገብተን የሬሳ ሳጥን ወደሚሸጥበት ቦታ  እያመሩ ሳለ…

‹‹ምን አይነት ተአምር ነው ያደረግሽው……?.››ሲል ጠየቀት

‹‹ያው ላንተ ስል ነው››

‹‹በጣም ነው የማመሰግንሽ….ግን  እንደማፈቅራት ለእሷ ባትነግሪያት ጥሩ ነበር››

‹‹ለምን…?››

‹‹ያው አንደኛ መንገሩ ምንም ውጤት አይኖረውም ሁለተኛ እኔ እና አንቺ……››

‹‹አይ እኔና አንቺ የሚባል ነገር የለም…አኔን እርሳኝ…እኔ ሁለት ቀን ብቻ ነው የቀረኝ..››

‹‹ምን ለመሆን…?››

‹‹ለመብረር…››

‹‹እንዴ የት አሜሪካ ወይስ አውሮፓ……?››

‹‹በለው ከሁለት አንዱ….ስለዚህ እሷኑ ጠበቅ አድርግ.ደግሞ በትክክል ይሳካልሀል….

እንደምታፈቅራት ስነግራት የልቧን ምት በደንብ ታዝቤያለሁ. ዋናው ከዚህ ሀዘን እስክትወጣ ከስሯ አትለይ …….

‹‹እንዴ ወዴት ነው የምለየው….ከእሷ የሚበልጥ ምን ሌላ ጉዳይ ይኖረኛል››

‹‹ምንም ››

‹‹አንቺ ልትበሪ መሆንሽን መስማቴ  ግን ቅር አሰኝቶኛል››

‹‹እኔን እርሳኝ አልኩህ እኮ››

‹‹እኮ እንዴት አድርጌ ልርሳሽ…?››
/////

የሰላምን አባት የቀብር ሁኔታ ካመቻቸችና ከተጠናቀቀ በኃላ ሁለቱንም አንድ ላይ ከለቀስተኞች ጋር ጥላቸው እናም በውስጧ ለመጨረሻ ጊዜ ተሰናብታቸው መልካሙን ሁሉ እየተመኘችላቸው ወደቤቷ ነው የተመለሰችው…ድክምክም ብሏት ነበር…ግቢውን አስከፍታ ስትገባ ግን ድካሟን ሁሉ ከላዮ የሚያበንላት አስደሳች ሁኔታ ነው የጠበቃት…

ግቢው መሀል ላይ ባለች ክፍት ቦታ ጠራጴዛ እና ወንበር ወጥቷል፤…ጠረጵዛው በልዩ ሌዩ ምግቦችና መጠጦች ተሞልቷል …ከዛ አልፎ ዙሪያው በየጥጋጥጉና በየቦታው የዛፍ ቅርንጫፎች ላይም ሳይቀር የተለያዩ የምግብና የፍራፍሬ አይነቶች ተቀምጠዋል…የተለያዩ ጥራጥሬዋች በየቦታው ተበትኗል….በጊቤዋ ውስጥ ያሉ እንስሳት ብቻ ሳይሆኑ እንግዳ የሆኑ ወፎች ሳይቀሩ ግቢውን ወረውት የተበተነላቸውን ጥራጥሬ በደስታ ይለቅማሉ… ጦጣና ዝንጆሮዎቾም ሙዙን እየላጡ ይውጣሉ …የማይፈነጭ እና የማያስካካ ፍጥረት በግቢው አይታይም..  የሆነ እንስሳት አግብቶ ሌሎቹ ሠርግ ተጠርተው አሼሼ ገዳሜ ላይ ያሉ ነው የሚመስለው….ሌላው ይቅር እያንዳንዱ  ተክል   ስሩ ተኮትኩቶና አፈር ታቅፎ ውሃ ጠግቦ እስኪተፋ ድረስ ጠጥቶ ይታያል….በቃ በግቢው አንድም ያልተደሰተ ፍጥረት አልነበረም..ይሄ ሁሉ በፕሮፌሰሩ የተደረገው እነሱ በተደሰቱበት መጠን እኔ እንደምደሰት በደንብ ስለሚያውቁ ነው፡፡

‹‹አትመጪም…  ይሆን ብዬ በስጋት ላይ ነበርኩ …እንኳን በሰላም መጣሽ››አሏት ከእድሜ ጫና የተነሳ ያጎበደድት ፕሮፌሰር…

‹‹አይ እፈልግሻለሁ ብለውኝ የለ..…….?በዛ ላይ  አንድ ቀን ብቻ ነው የቀረኝ …ማታ ወደ እናቴ  እሄዳለሁ.አዎ ነገ ሙሉውን ቀን ከእሷዋ ጋር ነው ማሳለፍ የምትፈልገው………››

‹‹ጥሩ ጥሩ..ነይ እዚህ ጋር ቁጭ በይ›› ብለው ምግብ በሞላበት ጠረጴዛ ዙርያ ከበው ከተቀመጡ ወንበሮች ውስጥ አንድን ሳቡላት… አመስግና ተቀመጠች፡፡

የእጅ ውሀ አመጡላት …‹‹አረ እራሴ እታጠባለሁ›› ብላ በራሷ ተጣበች… ሳሀን ስባ ምንም እንኳን የምግብ ፍላጎት ባይኖራትም እሷቸውን ለማስደሰት ስትል ብቻ መብላት ጀመረች… እሳቸውም ከፊት ለፊቷ ተቀምጠው በስስት እያዮት መመገብ ጀመሩ…

‹‹የሚጠጣ ምን ልቅዳልሽ…….?››

‹‹ውሀ ››

‹‹ወይን ወይም ሌላ ነገር አይሻልሽም…….?››ካለወትሮዋ ዉሀ ማለቷ አስገርሞታል

‹‹አይ ውሀ ነው የምፈልገው….››

‹‹እሺ ካልሽ ››ብለው ውሀ ቀዱላት፡፡

‹‹ጋሼ በዚህ ምድር በኖርኩበት ዓመት የተረዳሁት ነገር ቢኖር  ምድር መተኪያ የሌላቸው ሁለት ነገሮች መታዳሏን ነው ….አዎ  እናትና ውሃ የዚህ ዓለም ሁለት ልዩዎች  ናቸው…››

‹‹እንዴት ልጄ..…….?እንዴት እንደዛ ተረዳሽ…?››

‹‹እናታችን መጀመሪያ ገነታችን ነች..ከተፈጠርንበት ቀን አንስቶ እስክንወለድበት ቀን ድረስ በእናታችን መሀፀን ውስጥ ገነታዊ ኑሮ ነበር የምነኖረው… ያ ስፍራ ሁሉ ነገር በፍፅምና  እንከን አልባ  ስፍራ  ነበር..ሁላችንም ከዛ ያለፍላጎታችን ተገፍትረን ስንወጣ(ስንወለድ) እሪ ብለን ለቅሶችንን የምንለቀው  ምን እንዳጣን በደመነፍስ ስለሚገባን ነው…አዳም እና ሄዋን በሰሩት ሀጥያት ከገነት ወደምድር ተባረሩ የሚባለው ሌላ አይደለም ከእናት መህፀን ወደምድር ተገፍትሮ መውጣት ነው…ከዛ በኋላም ቢሆን  እናት ምን ጊዜም እናት እንደሆነች ነው ምትቀጥለው… እንዳላረጀን እና እንዳላበቃልን የሚሰማን እናታችን በሰላሳ አመታችንም እንደ ህፃን ስትቆጣን ስናይ ነው..ጭንቅላታችንን ስትዳብስልን…ተይ አንቺ ልጅ ብርድ ይመታሻል ስትለን  ነው፡፡
ግን ክፋቱ በፈለግናት  ጊዜ ስለምናገኛት…በጣራናት ጊዜ ሮጣ ስራችን ስለምትገኝ ዋጋዋን ብዙም አናውቀው…. እንደድንገት ስትነጠለን  እና ከእጃችን ተንሸራታ ስናጣት ግን  አንድ ሰው ብቻ እንዳልነበረች ይገለጽልናል…መላ ዓለም እሷን እንደማይተካልን  ትምህርት እናገኛለን…ግን ትምህርት ቀድሞ ያጣኸው ነገር ወደፊት ዞሮ መጥቶ እንድታስተካክለው እድሉን ካላገኘህ ጥቅም የለውም..በደንብ ስትፀፀት እድትኖር ብቻ ነው የሚያግዝህ፡፡

ውሃም በቀላሉ ነው የምናገኘው..እኛ እራሱ በዋናነት የተሰራነው ከውሀ ነው ..ምድርም ሶስት እጆ ውሀ ነው….በቀላሉ ብቻ ሳይሆነ በርካሽም እናገኘዋለን.. ሰውነታችን ከየትኛውም መጠጥ በተሻለ በውሀ ይረካል…በውሃ ጤነኝነት ይሰማዋል…የውስጥ መጠማታችንን ብቻ ሳይሆን በአካልም መዛላችንን በውሀ ነው የምናክመው….ሰውነታንን የምንታጠበው የቆሸሸ ሰውነታችንን ለማጽዳት ብቻ አይደለም ውኃው በሰውነታችን ላይ ሲያርፍ መነፍስን የማረጋጋት እና የአዕምሮ ውጥረትን የማከም ኃይል ስላለው ነው…ግን ‹‹ወይ ስታጠብ ቀለል ይለኛል›› በማለት ያገኘነውን ጥቅም እናቃልለዋለን እንጂ ውሀ መድሀኒት ነው ብለን ዕውቅና መስጠት አንፈልግም ..ወሃ የደም ግፊት መድሀኒት ነው..ውሀ የኩላሊት መድሀኒት ነው…ውሃ የራስ ምታት መድሀኒት ነው…..ወሃ የበሽታዎች ሁሉ ፈውስ ነው…
‹‹የእኔ ውሃ ግን  አንቺ ነበርሽ…››አሏት እዝን እንዳሉ፡፡
‹‹ማለት……….?››አለቻቸው አሳዝነዋት፡፡
‹‹አዎ እኔ ጡረታ እስክወጣ ድረስ በዚህች ሀገር ላይ በጣም ስኬታማ ከሆኑ ጥቂት ሰዎች መካከል አንድ  ነኝ ብዬ አስብና እመፃደቅ ነበር….አምስት ስድስት ዲግሪዎች ስላሉኝ አንቱ የምባል ፕሮፌሰር ስለሆንኩ በቃ እታበይ ነበር….ልክ ጡረታ ስወጣ ግን ግማሽ ህይወት ብቻ ስኖር እንደነበር ተገለጽለኝ..እንደው ወደኃላ ተመልሶ የኖሩትን ህይወት ማስተካከል ቢቻል ካሉኝ ዲግሪዎች መካከል አንድን ብቻ አስቀርቼ ሌሎቹን በልጆች እና የልጅ ልጆች መቀየር ብችል ደስ ይለኝ ነበር..ከዛሬ 40 አመት በፊት አግብቼ ዛሬ የ35 ዓመት ልጅ እና የአምስት አመት የልጅ ልጅ ኖሮኝ ቢሆን ኖሮ በጣም ስኬታማ እና ሙሉ እሆን ነበር..ይሄን ቁጭቴን ባንቺ ነበር እየተፅናናው ለመኖር እውተረተር የነበረው…አሁን ግን….››
‹‹እንዲህ እማ አይዘኑ››
‹‹ተይኝ ልዘን…እነዛ ሁሉ ያገኘዋቸው ግኝቶች …እነዛ ሁሉ የተሸለምኮቸው ሽልማቶች እኔ ካለፍኩ በኃላ ማን ይረከባቸዋል..ማን ነው ሊኮራባቸው የሚችል የእኔ ሰው  ……….?
‹‹አሁን ወደኃላ ተመልሰው አድሉን ቢያገኙ እኮ መልሰው ተመሳሳዩን ነው የሚያደርጉት››
‹‹በፍጽም አላደርገውም..ህይወት ሚዛን መጠበቅ አላባት…እድሜሽን ሙሉ ገንዘብ ለማካበት ሰትባክኚ ቆይተሽ ካረጀሽ እና ጥርስሽ ከረገፈ በኃላ ልዝናና ብትይ አያምርብሽም… ደስታ ሚያመነጨው የሰውነትሽ ዕጢም እንዘይሙን ማምረት ስለሚያቆም አትቺይም….ወንደላጤ ሆነሽ ስትንዘላዘይ ኖረሽ በእኔ ዕድሜ ላግባ ብትይ እንዴት ተደርጎ..እንደው ሚስትዬዋ ተገኝታ ማግባት ቢቻል እንኳን እንዴት መውለድ ይቻላል..…….?ቢወለድ እራሱ የማያሳድጉትን ልጅ  እንዴት ….?ሁሉ ነገር በጊዜው ነው የሚያምረው››
‹‹እና እንዴት መሆን አለበት ይላሉ…….?››ጠየቀቻቸው
‹‹የተወሰነ መማር..የተወሰነ ገንዘብ መስራት… የተወሰን ቁጥር ያለው ቤተሰብ መመስረት…በቃ ከሁሉም የሚያስፈልገውን እና የምትጠቀሚበትን ያህል መውሰድ ነው…አየሽ አኔ አሁን ተማርኩ ከምላቸው ትምህርቶች መካከል ሁለቱን ዲግሪዎች ለአንድ ሰምንት እንኳን አልሰራሁባቸውም…እንዲሁ ለጉራ ካልሆነ በስተቀር  ያን ያህል ፋይዳ አልነበራቸውም …
በልተው እንደጨረሱ እጇን ታጥባ  እሳቸው ቢራቸውን እየጠጡ እሷ ደግሞ ወኃዋን ይዛ ወሬውን ቀጠሉ
‹‹እቤቱን እንግዲህ  ሰጥቼዎታለሁ…..››
‹‹አይ እንደዛማ አይሆንም ….እኔ እኮ ለራሴ የሚበቃ የጡረታ ብር አለኝ..ተከራይቼ ሌላ ቦታ እኖራለሁ..ቤቱ የሚገባወ ለዘመዶችሽ ነው..››
‹‹አይ ይሄ ቤት የሚገባው ለእናቴ ነበር..ግን እናቴ ከተወለደችበት አካባቢ ንቅንቅ ማለት አለትፈልግም….››
‹‹እንደዛ ከሆነ ይሸጥና ብሩን ይጠቀሙበታ››
‹‹አይዞት ለእሷ አያስቡ …በቂ የሆነ ብር ሰጣታለሁ..ይሄ ቤት ግን የሚሸጥ አይደለም…እሺ ጣሪያና ግድግዳው መሸጥ ቀላል ነው…እነዚህ ግቢውን የሞሉትን ዛፎች በስንት ብር ተምኜ ልሽጣቸው…?እነዚህ ዛፎቹን የወረሯቸውን በሺ የሚቆጠሩ ወፎች ስንት ስንት ብር ያወጣሉ...?ዝንጀሮዬን ስንት ልሽጠው..…?ጉሬዛዬንስ….?አዩ አንዳንድ ነገሮች ከሚሰጡት ጥቅም አንፃር ብቻ ሳይሆን ካለቸው ትርጉም  በመነሳት ዋጋ ሊወጣላቸው አይቻልም….አሁን ለአንድ ሀብታም ብሸጠው እኚ አሁን የጠቀስኩሎትን ሁሉ አንድ ሰምንት የሚያቆያቸው ይመስሎታል….?.ዛፎቹን ጨፍጭፎ መሬቱን ነፃ በማድረግ ፎቅ ነው ሚገነባበት…ወፎችስ እድሜ ለክንፋቸው በስደት  በመሸሽ  ነፍሳቸውን ለማቆት ይሞክራሉ..፤ሎሎቹስ….?

‹‹እሱስ ከባድ ነው››
‹‹ስለዚህ ቤቱ አይሸጥምም… ለሌላ ዘመድም ቢሆን ተላልፎ አይሰጥም…ይሄ ቦታ የሚገባው ለእርሷ ብቻ ነው..የእያንዳንዶን ዕጽዋት ሚስጥር የሚያውቁትና የሚረዱት እርሶ  ኖት… ስለዚህ የእርሶ ነው››
ፈገግ አሉ..
‹‹ምነው .. …….?ተሳሳትኩ እንዴ..…….?››አለቻቸው ፈገግታቸው የምፀት ስለነበረ ገርሞት
‹‹ስንት ዓመት ልኖር ብለሽ..…….?በተለይ አንቺ በሌለሽበት..ሁለት አመት ሶስት አመት..ከዛስ ያው የፈራሽው  መድረሱ አይቀርም..እነዚህ ሁሉ የለፋንባቸው ነገሮች አጥፊ እጅ መግባታቸው እና መውደማቸው አይቀሬ ነው…››
‹‹ስለዚህ አንድ ነገር እናድርጋ››
‹‹ምን…….?››
ከመቀመጫዋ ተነሳች..ንስሯ ለማድረግ የፈለገችውን ቀድሞ ገብቶታል ፤ ካለበት ዛፍ ላቆ ልክ ትሪኢት እደሚያሳይ የአየር ኃይል የጦር ጄት መገለባበጥ ጀመረ… እንዲህ የሚያደረግው ሲደሰት ነው…በስንት ቀኑ ፈታ አለ….. 
ወደእሳቸው ቀረበች… ግራ ገብቷቸው በዝምታ ያዩታል…. ከጀረባዋ ቆማ  ፀሎት እንደሚያደሰርስ   የፕሮቴስታንን ፓስተር ሁለት እጇን በጭንቅላታቸው ላይ ጫነችና አይኖቾን ጨፈነች…በፍጽም መመሰጥ ውስጥ ገባች….ቀስ እያለ ሰውነቷ ሲግል ይታወቃታል..አዎ ከልቧ ጀምሮ ኃይል እየተሰበሰብ በደምስሯ በመራወጥ ወደ እጆቾ እየፈሰሰ ነው…ከዛ ወደ ፕሮፌሰሩ ጭንቅላት መተላለፍ  ጀመረ…አይኖን የጨፈነች ቢሆንም እየሆነ ያለው ነገር ሁሉ ይታያታል… ኃይል የሞላው ሀመራዊ ቀለም  ከፕሮፌሰሩ ጭንቅላት አንስቶ ወደ አንገታቸው..ከዛም  ትከሻቸው እያለ ወደመላ ሰውነታቸው ተሰራጨ… መንዘፍዘፍ ጀመሩ….ኦ.. ሽበት የወረረው ነጭ ፀጉራቸው...ከግንባራቸው እየተነሳ ወደ መሬት ይረግፍ ጀመር…በዛው ቅፀበት ሌላ ደማቅ ጥቁር ሉጫ ፀጉር ከእያንዳንዱ የራስ ቅል ቀዳዳቸው በመብቀል ወደ ውጭ በመውጣት ጭንቅላታቸውን ሞላው…

ይቀጥላል
#ክፍል 58,,እንዲለቀቀ 👍(20) ሰው ከስር ያለውን ሊንክ #Subscribe🔔ካረገ ይለቀቃል
https://youtube.com/@Weygud18

#Subscribe እያደረጋቹ ቤተሰብ ስለምትሆኑ እናመሰግናለን #Subscriber
YouTube link👇
https://youtube.com/@Weygud18

መልካም ሰንበት ተመኘሁ🙏
Today's Combo
Live stream finished (4 minutes)
📕ተአምረተ_ኬድሮን

#ተከታታይ ልቦለድ

#ክፍል_ሃምሳ_ስምንት

በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ


ለዓመታት ጎብጦ እና አጎንብሶ የነበረ ትከሻቸው ቋቋቋቋቋ የሚል ድምጽ እያሰማ በመላቀቅ መቃናት ጀመረ…የተጨማደደ እና ተኮመታትሮ የነበረ ቆዳቸው ልክ የሽማግሌ ገፃ-ባህሪ ለመጫወት ጭንብል አጥልቆ እንደነበረ አክተር  ከፊታቸው ተሞሽልቆ በመነሳት መሬት ወደቀ…
ወዲያው መለስተኛ አውሎ ንፋስ ተነሳና እየተሸከረከረ መጥቶ እዚህም እዛም በዙሪያችን የወደቀውን የፕሮፌሰሩን የተወገደ አካል ከአካባቢው ጠራርጎ በአየር ላይ ተሸክሞ ሄደ ..
ከዛ…. ሁሉ ነገር እንዳሰበችው እንደሆነ ካረጋገጠች በኃላ እጆቾን ከጭንቅላታቸው አነሳችና…ወደመቀመጫዋ ተመልሳ ተቀመጠች…

አየቻቸው‹‹…..እንዴት አባቱ የሚያምር ጎረምሳ ሆኖል›ስትል እራሷ በሰራችው ተአምር እራሷ ተደነቀች   …‹‹ውይ እነዛ የአባቴ ዘመዶች መተው ሚወስዱኝ ባይሆን  ኖሮ ይሄን  ፊት ለፊቴ የተቀመጠውን ቆንጅዬ  ጎረምሳ አግብቼ  መኖር ነበር….›ስትል የምፀት ፈግታ ፈገግ አለች፡
ፕሮፌሰሩ ቀስ እያለ ከሰመመኑ ነቃ…
‹‹ወይ ልጄ ምድነው ያደረግሺኝ…….?ራስ ምታቴ እና ጭንቀቴ እኮ ለቆኝ ሄደ››
‹‹አሞህ ነበር እንዴ…….?››
‹‹ምን አልሽኝ…….?››ግራ ተጋብተው
‹‹ ይቅርታ አሞት ነበር እንዴ…….? ለማለት ፈልጌ ነው››
‹‹አንቺን አልረብሽሽም ብዬ ነው እንጂ እንደምትሄጄ ከሰማሁበት ቀን አንስቶ ጤናም የለኝ ነበር..››
‹‹አይ እንኳን ተሸሎት››
‹‹አረ መሻል ብቻ አይደልም …››ንግግራቸውን ሳይጨርሱ አይናቸው እጃቸው ላይ አረፈ..ተጨማዶ ና ተሸብሽቦ የነበረ እጃቸው አሁን በለግላጋ  ጣት እና ለስላሳ ቆዳ ተሸፍኖ ሲያዩት ማመን አልቻሉም… ግራ በመገባት እና  ባለማመን በጃኬታቸው ሸፈኑት..መልሰው ገለጡ…
‹‹ቆይ መጣሁ›› ብለው….ትተዋት ወደቤት በፍጥነት መራመድ ጀመሩ…ከኃላ ተከተለቻቸው…ቀጥታ ወደመኝታ ቤታቸው ሄደው የቁምሳጥናቸው መስታወት ፊት ለፊት  ነው የቆሙት….
‹‹የምን ታአምር ነው.…….?.እኔ የት ሄድኩ……….?ማን ነው ይሄ..…….?እኔ ማነኝ…….…….? ››ፊታቸውን እየዳበሱ ለፈለፉ…
መልስ መስጠት ጀመረች‹‹አሁን የ30 ዓመት ወጣት ሆነዋል..ማለት ሆነሀል፡፡…የሚፀፀቱበት ምንም ነገር የለም..ቀጣይ 45 ዓመት ተሰጥቶታል …. ስዚህ ቅድም እንዳሉት ሚዛናዊ ኑሮ ይኑሩበት..ማለቴ ኑርበት…››
‹‹ምን ጉድ ነው….…….?እኔ ወጣት…አንደገና መወለድ እኮ ነው…….?››
‹‹አዎ ነው..ልክ እንደንስር እንደገና የመታደስ ዕድል..››አለቻቸውና ቤታቸው ለቅቄ ወደራሴ ቤት አመራሁ ..ወደ እናቴ ለመሄድ ልዘጋጅ
////
ንጋት ላይ ነው ጉዞ የጀመሩት፡፡የንጋቱን ቀዝቃዛ አየርን  እየማጉ ሰማዩን ሰንጥቀው ቁልቁል የኢትዬጵያን ደቡባዊዉን መልካ ምድር እየቃኙ እየተጓዙ ነው፡፡እስኪ ትንሽ ከላይ ሆነው ቁልቁል ወደታች ሳያዩ ከፊል ኢትዬጵያ ምን እንደምትመስል አብረናቸው እንመልከት፡

ኢትዬጵያ 12 ታሪካዊ ቅርሶችን በዩኒስኮ በዓለም አቀፍ ቅርስነት አስመዝግባለች፡፡እነዚህም፤ የአክሱም ሀውልቶች፣ የላሊበላ አብያተክርቲያናት፣ የጎንደር ፋሲል ቤተመንግስት፤የሰሜን ብሄራዊ ፓርክ፣ የኮንሶ ሰው ሰራሽ መልካዓ ምድር፣ የጢያ ትክል ድንጋዮች፣የታችኛው አዋሽና የታችኛው ኦሞ ሸለቆ፣ የመስቀል ደመራ፣ የሲዳማ ፊቼ ጨንበላላ፣ የኦሮሞ የገዳ ሥርአት ናቸው። ሌሎችም ለማስመዝገብ   ላይ ያለ አሉ  በዩኔስኮ እንዲመዘገቡ በእቅድ ደረጃ የተያዙ ቅርሶችም እንደ የባሌ ተራራዎች ብሄራዊ ፓርክ፣ የድሬ ሼክ ሁሴን መስጊድ፣ የሶፍ ኦመር ዋሻ፣ የጌዲዩ ሰው ሰራሽና የተፈጥሮ መልከዓምድር፣ የመልካ ካንቱሬ የአርኪዮሎጂ ስፍራዎች ናቸው። በማይጨበጥ ባህላዊ ቅርስነት ደግሞ የአማራና የትግራይ የሻዳይና የአሸንዳ በዓላት የጥምቀት በዓል ይጠቀሳሉ። 
ኢትዬጳያ ግን ለቱሪስት ኢነደስትሪው ግብአት የሚሆኑ ሀብቶቾ እነዚህ ብቻ አይደሉም…ሀገሪቱ እራሱ ሙሉ በሙሉ በዩንሰኮ ቅርስነት ብትመዘገብ አያንስባትም…ግን በዛ መጠን የሚያስብ በዛም መጠን የሚሰሩ ልጆች ወልዳ አለማሳደጎ በጣት የሚቆጠሩትን ብቻ ማስመዝገብ ችላለች፡፡

ይገርማችኋል ይህቺ ሀገር ሙሉ ነች፡፡ሙሉ ስላችሁ ለምሳሌ አየር ፀባዮ  ደጋ ጥቂት ፈቅ ስትሉ ወይና ደጋ ..ብዙም ሳትርቁ ቆላ ታገኛላችሁ፡፡ይሄ ድንቅና መድሎ ያለበት የተፈጥሮ ስጦታ ነው…መልካ ምድሯን ስንመለከት  ለጥ ያለ ሜዳ…ደግሞ ቀጥ ያለ ተራራ..እሱ ሲገርማችሁ ጭው ያለ ገደል…በሌላ ጎኑ እንደጣባ አህያ የተራቆተ መሬት…እንደ ደብረብርሀን የሱፍ በግ ጥቀጥቅ ያለ ጫካ…ኩሬ ሀይቅ ወንዝ….አቤት እነዛ አሜሪካኖቹ ይሄን መልካ ምድር ከዚህ የተመጣጠነ ምግብ ከሆነ አየሯ ጋ ቢያገኙት.. አቤት ይሮፖዎች ያ በቆፈን የሚያኮራምት በረዶ ገላግሎቸው እንዲህ ሚዛኑን የጠበቀ አየር ቢያድላቸው ምን ያህል ተአምራዊ ህይወት ይኖሩ ነበር.. ተፈጥሮ ሚዛኗን የምትጠብቅበት የራሷ ቀመር አለት መሰለኝ ለእነሱ ሀብት ከቆፈን ጋር ስታድል ለእኛ ምርጥ አየር ከችጋር ጋር.. ያስቃል….እነሱ በቱሪስት ሆነው መልካምድሯን አይተው ለመደሰት እና አይሯን ምገው ሀሴት ለማድረግ ምቾት ባለው አይሮፕላን መጥተው ገንዘባቸውን ከስክሰው ከረምረም ብለው ይመለሳሉ..እኛ በስደት መልክ ከችግር ለመላቀቅ በእግር ተጉዘን በባህር ተጉዘን ሀገራቸው እንገባና ጉልበታችንን አንጠፍጥፈን አንገታችንን ደፍተን ስንባዝን ስንባዝን እንኖርና በዛው የውሀ ሽታ ሆነን እንቀራለን የእነሱ አንድ ነፍስ በእኛ ስንት ነፍስ እንደሚመነዘር ስሌቱ አይታወቅም ..ምን አልባት የብራችን ምንዛሬ ወይም ዋጋ ልዩነትን ያህል የነፍሳችንም ዋጋ ልዩነት ይኖረው ይሆናል…

….ይሄን ሁሉ ይምታስበው.ይሄን ሁሉ የምትመኘው በአየር ላይ ሆና ንስሯ ጀርባ ላይ ተጣብቆ ነው እየተጓዙ ያሉት… 

ያው ሰው በተፈጥሮ በመጨረሻው የህይወቱ ማብቂያ ሰዓት ቁጭት ውስጥ መግባቱ እና ፀፀቱን መናዘዙ ተለመደ አይደል..እሷም ያው በግማሽም ሰው በመሆኗ መጠን ከሰውም ኢትዬጵያዊ ስለሆነች ያው ያ ደግሞ ክርስቶስም ለስጋው አደላ የእንደሚባለው ለእሷም ለዘመዶቿ ተቆጭታ ነው እንጂማ የእሷ የአባቷ ዘመዶች በምድራዊ ዕውቀት የማይመዘን ብቃት እንዳላቸው ታውቃለች፡፡

ለማንኛውም አሁን ደሎ ደርሰዋል…ግን ቀጥታ ወደእናቷ ቤት መሄድ አልፈለገችም ..በመጀመሪያ ያደገችበትን ጫካ ልትሰናበት ፈለገች..መቼስ የደሎመና ጫካ ጫካ ብቻ አይደልም …ውስጡ  የቡና ተክል የተሰገሰገበት ነው..ልጅ ሆነው እንጨት ለቀማ ከእኩዬቾ ጋር ስትሰማራ ከቡናው ተክል ድፍኑን ሸምጥጠውን ይመጡት ነበር..የቡና ተክል ጥሬ ሆኖ ድፍን አረንጓዴ ነው …እየበሰለ ሲሄድ ቢጫ እየሆነ ይመጣል በስተመጨረሻ ሙሉ ብስል  ሆኗል የሚባለው ሙሉ ቀይ ሲሆን ነው..ታዲያ በዛን ጊዜ ፍሬውን ቀፈው ይመጣሉ…ቀዩ የቡና ገለፈት በወስጡ የያዘው ፈሳሽ ልዩ ጣዕም አለው….ሌላው የሚገርማት ይሄ አሁን ከላይ ወደታች የማታየው የደሎ ጫካ ወይም ሀራና ደን የመንግስት ነው…በውስጡ ከደኑ ጋ ተሰባጥሮ ሚገኘው የቡና ተክል ደግሞ የግለሰብ ነው….የኢትዬጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲህ ተዋህደው በስምም ሲጠቀሙ በዚህ ደን ብቻ ነው ያየችው፡፡
የሆነው…›› ስትል እራሷን ጠየቀች፡ለመሄጃ 3 ደቂቃ ቀረው….ንስሩ ከነበረበት ጉቶ ጥቅልል ብሎ በመንሸራተት  መሬት ላይ ተዘረረ..እናቷም እሷም በደቂቃ ውስጥ ስሩ ደረሱ..አገላበጡት…ከአይኖቹ ደም እየፈሰሰ ነው…‹‹ወይኔ እማ ቅጠሉ….. ቅጠሉ ነው..መርዝ ነው የተጠቀመው..እማ ምን እናድርግ…?››የማሰቢያ ጊዜ ሳያገኙ ግቢያችን በሰማያዊ ብርሀን ተሞላ…ቀና ስትል በሰማይ ላይ ዲስክ መሳይ መንኮራኩር ብርሀን እየረጨች ሰማየ ሰማያትን በመሰንጠቅ እነሱ  ወዳሉበት አቅጣጫ እየወረደች ነው….መጡ ማለት ነው…መጡ መሰለኝ….ወይኔ ንስሬ….

  ተፈፀመ

#በአዲስ ታሪክ እንመለሳል‼️ ከተመቻችሁ 👍👍

ከስር ያለውን ሊንክ #Subscribe🔔ካረገ ይለቀቃል
https://youtube.com/@Weygud18

#Subscribe እያደረጋቹ ቤተሰብ ስለምትሆኑ እናመሰግናለን #Subscriber
YouTube link👇
https://youtube.com/@Weygud18

መልካም ምሽት ተመኘሁ🙏

🎙ግሩፑን ለማግኘት
              👇👇👇

        @Mtshaf_bicha
        @Mtshaf_bicha
❤️ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
👉አሰተያየት ካላችሁ
📩 @Eyos18     አድርሱን
             📗📒📕📗📒📕
                Join&share
                  @EyosC1
       📚ማንበብ ባህላችን ይሁን📚
┄┉┉✽‌»‌🎶••✿••🎶»‌✽‌┉┉┄
📍አንዳንዴ ምን ሆነሀል ስትባል የማትመልሰው ብዙ መሆን አለ። ለመናገር የማይመች ለመተው የማይቀል ብዙ ስሜት አለ ..ለአንተ የከበደ ለሌላው የቀለለ ነገር አለ ።

💡እንዴ ይሄ እኮ ቀላል ነው ይሄ እኮ አያስጨንቅም በሚባል ቃል የሚሸነፍ ለአንተ/አንቺ ግን የከበደ ስሜት አለ ።
ምን ሆነሀል ስትባል ምንም ብለክ የምታልፈው ውስጥህ ብቻ የምታንሸራሽረው እያዳመጥክ የምትታመምበት ። ከባድ ስሜት አለ ከባድ.......

✔️ምናልባት የምትፈልገው ስፍራ ላይ አልተቀመጥክ ወይንም የምትመኘውን ነገር አላገኘህ ይሆናል፣ ቢሆንም ተስፋ አትቁረጥ ፣ ተስፋ የመኖር ምክንያት ነውና፣

እየኖርን ነው አይደል? በሰው ሳይሆን በፈጣሪ!!
ትላንት የኖርነው ህይወት በነበር ይተካል፣
ሰዎችም ኖረው ነበሩ ይባላሉ፣
ፈጣሪን ግን ነበር ብለን አናወራውም ፤ ያለና የሚኖር ፣ በዛሬያችን ,በነጋችን አልፎም በዘላለም ውስጥ ኗሪ ነው ።
" የትላንት ነበሮቻችን በእሱ መኖር ተረስተዋል"

እናም  ወዳጄ

✔️አትድከም ፣ አትዘን ። ማንያውቃል ሸክምህ ህመምህ ሁሉ ተራግፎ ሌላ ሰው ሆነህ ትነሳ ይሆናል። ያለን ፈጣሪ እንኳን በአንድ ሙሉ ቀንና ሌሊት፣ በቅጽበት ጊዜ ዉስጥም ብዙ ተዓምር ይሠራል።

💡ንፋስ የማይወዘዉዘው ዛፍ የለም። ችግር ፣ ፈተና ፣ ሀሳብ ወስዶ የማይመልሰው ሰዉም የለም። እንዲህም ሆኖ የማይወድቅ ዛፍ አለ። በፈተና የሚፀና የሚበረታ ሰዉም አለ። ዐሳብህ ጉልበትህ ሥሮችህ ታክቶዋቸው በደከሙ ጊዜ ልብህ ብቻ ፈጣሪን ይዞ ይበርታ።


🚨በYouTube አማራጭ ይቀላቀሉን!
❇️SUBSCRIBE NOW
https://youtube.com/@Weygud18
https://youtube.com/@Weygud18

መልካም ግዜ 🙏

🎙ግሩፑን ለማግኘት
              👇👇👇

        @Mtshaf_bicha
        @Mtshaf_bicha
❤️ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
👉አሰተያየት ካላችሁ
📩 @Eyos18     አድርሱን
             📗📒📕📗📒📕
                Join&share
                  @EyosC1
       📚ማንበብ ባህላችን ይሁን📚
┄┉┉✽‌»‌🎶••✿••🎶»‌✽‌┉┉┄
💚ህይወት ከእናንተ ትጠብቃለች!

ዶ/ር ቪክቶር ፍራንክል (Dr. Victor Frankl) ይባላል። በ20ኛው ክፍለ ዘመን የነበረ ኦስትሪያዊ ታዋቂ ኒዎሮሎጂስት (Neurologist) እና ሳይኮሎጂስት (psychologist) ነው። በህይወትና የህይወትን ትርጉም በማግኘት ዙሪያ በሚያነሳቸው ሀሳቦችና አስተምህሮዎች ይታወቃል። በአንድ ወቅትም እንዲህ ብሎ ነበር፦ "ለምን እንደሚኖሩ ለማያውቁና ከህይወት ምንም ለማይጠብቁ ሰዎች ህይወት በእራሷ ከእነርሱ ሌላ ነገር እነደምትጠብ ማሳወቅ በጣም አስፈላጊ ነው።" የህይወት አላማችሁን ፍለጋ ብዙ ዋጋ ብትከፍሉም ላታገኙት ትችላላችሁ፣ ለዘመናት ስታደርጉት የነበራችሁት ነገር የሆነ ጊዜ ስትነቁ ትርጉም አልባ ሊሆንባችሁ ይችላል፣ ከዚህም በላይ ከእራሳችሁና ከህይወታችሁ ምንም የተሻለ እሴትን መጨመር የሚችል ነገር መጠበቅ ታቆሙ ይሆናል። ነገር ግን ይሔንን አስተውሉ። እናንተ በሰውኛ አዕምሮ አስባችሁ፣ አውጥታችሁ አውርዳችሁ ደክሟችሁና ሰልችታችሁ ያላገኛችሁት የህይወት ትርጉም ዝም ብላችሁ ስትኖሩና እያንዳንዱን ሃላፊነታችሁን ስትወጡ በሒደት ወደ እናንተ ይመጣል። እናንተ የምትኖሩት ህይወት አለ፣ ህይወት ደግሞ እንድትኖሯት የምትፈልግበት መንገድ አለ።

አዎ! ህይወት ከእናንተ ትጠብቃለች! እናንተ በህይወታችሁ ውስጥ ትርጉምን እንደምትፈለጉ ሁሉ ህይወታችሁም ከእናንተ አንድ የተለየና የእናንተ መገለጫ የሆነ ልዩ ነገር ትጠብቃለች። የህይወት አላማን ለማግኘት መውጣት መውረድ፣ እራስን ማታገልና ማስጨነቅ አያስፈልግም። አንዳንድ ክስተቶች እራሳቸው ፍሰት አላቸው፣ ሲጨመቁ ከሚያወጡት መልካም ነገር ይልቅ እንዲሁ በራሳቸው ሲፈሱና በኡደታቸው ሲጓዙ የሚያመጡት ውጤት ይበልጥ ትርጉም ይሰጣል። የትኛውም ትልቅ ነገር መነሻው ትንሽ ነው። "ህይወት ትርጉም አልሰጥ አለችኝ" ከማለት ይልቅ "ህይወት ከእኔ ምን ትጠብቃለች?" ብሎ መጠየቅ ብዙ የተደበቁ አቅማችንን እንድናወጣ ያግዘናል። በየትኛውም ዘርፍ ሊሆን ይችላል፣ በምንም ስራ ውስጥ ሊሆን ይችላል በእኛና በእኛ ብቻ መሞላት የሚችል ክፍተት አለ። ተምረን፣ አውቀን፣ ተረድተንና አስተውለን ወይም በተፈጥሮ በተሰጠን የተለየ ክህሎት ይህንን ክፍተት መሙላት አንችላለን። ዓለማችን በችግር የተሞላች ነች፣ ወረድ ስንል አህጉራችን ውስጥ የችግር መዓት አለ፣ ከዛም ወረድ ስንል ሀገራችን ውስጥ ብዙ ያልተፈቱ እንቆቅልሾች አሉ።

አዎ! ጀግናዬ..! ከምታየውና ከምትሰማው ችግርና ክፍተት ውስጥ ለአንተ የትኛው ጎልቶ ይታይሃል? የትኛውን ለመቅረፍ የቀረብክ ይመስልሃል? በየትኛው ላይ ብትሰማራ ነፍስህ የምትረካ ይመስልሃል? ትንሽ ጊዜ አስብ፣ ለተወሰነ ጊዜ አቅድ፣ በቀጣይ ግን ቀጥታ ትግበራውን ጀምር። ብዙ ሰው የማያየውን ነገር ማየት ስትችል ብቻ ከሰዎች የተለየ አዲስ ነገር ማከናወን ትችላለህ። ህይወትን በዓላማ መኖር ውስጥ እይታ፣ ዝግጁነት፣ ቆራጥነትና የተግባር ሰው መሆን በጣም አስፈላጊዎች  ጥበቦች ናቸው። እይታህ የምትሔድበትን አቅጣጫ ያጠራልሃል፣ ዝገጁነት በማንኛው ሰዓት ወደ ተግባር እንድትገባ ያደርግሃል፣ ቆራጥነት ከሃሳብ በላይ ተግባር ላይ እንድታተኩር ያደርግሃል፣ የተግባር ሰው መሆን ደግሞ በውድቀትና በስህተት ውስጥ አያሳለፍና እያስተማረ ለላቀው ውጤት ያበቃሃል። ቀላል፣ የተረጋጋና ትርጉም ያለው ህይወት ለመኖር እንቅስቃሴዎችህን ሁሉ ትግል አታድርገው። የዓለምን ክፍተት ፈልግ፣ ከፍላጎትህ ጋር አቆራኘው፣ እርሱን ለመሙላትም እንቅስቃሴህን ጀምር


🚨በYouTube አማራጭ ይቀላቀሉን!
❇️SUBSCRIBE NOW👇👇👇
https://youtube.com/@Weygud18
https://youtube.com/@Weygud18

መልካም ምሽት ተመኘሁ🙏

🎙ግሩፑን ለማግኘት
              👇👇👇

        @Mtshaf_bicha
        @Mtshaf_bicha
❤️ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
👉አሰተያየት ካላችሁ
📩 @Eyos18     አድርሱን
             📗📒📕📗📒📕
                Join&share
                  @EyosC1
       📚ማንበብ ባህላችን ይሁን📚
┄┉┉✽‌»‌🎶••✿••🎶»‌✽‌┉┉┄
“ደሃ እያለሁ ለምን የድህነቴን ምንጭ አላጣራም?”
*
በ10ሺ ዶላር የተገዛ የወርቅ ጫማ ፣በአልማዝ የተለበጠና 100ሺ ዶላር የተገዛ ሮሌክስ ሰዓት፣ 200ሺ ዶላር ያወጣ ሜርሴዲዝ ቤንዝ ካሉት በርካታ የቅንጦት እቃዎች ጥቂቶቹ ናቸው፡፡

ይህ ሰው የደቡብ ሱዳን ዜጋ ሲሆን በአንድ ወቅት የሀብቱን ምንጭ መንገግስት ለማጣራት ሲሞክር ሀብቱን ሰብስቦ ከሀገሩ አመለጠ፡፡

ታዲያ ይሄን ለምን እንዳደረገ ሲጠየቅ የመለሰው መልስ ሳቅን የሚያጭር ነበር፡፡

የመለሰው መልስ እንዲህ የሚል ነበር…“ደሃ እያለሁ ለምን መንግስት የድህነቴን ምንጭ አላጣራም?”

የአነጋጋሪውን ቢሊየነር ታሪክ በተከታዩ ቪዲዮ ይመልከቱት…

🚨በYouTube አማራጭ ይቀላቀሉን!
❇️SUBSCRIBE NOW👇👇👇
https://youtube.com/@Weygud18
https://youtube.com/@Weygud18

  መልካም ምሽት ተመኘሁ🙏

🎙ግሩፑን ለማግኘት
              👇👇👇

        @Mtshaf_bicha
        @Mtshaf_bicha
❤️ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
👉አሰተያየት ካላችሁ
📩 @Eyos18     አድርሱን
             📗📒📕📗📒📕
                Join&share
                  @EyosC1
       📚ማንበብ ባህላችን ይሁን📚
┄┉┉✽‌»‌🎶••✿••🎶»‌✽‌┉┉┄
Yingalish
Wendi Mak
🎙 JOIN US @Eyosc1

🚨በYouTube አማራጭ ይቀላቀሉን!❇️SUBSCRIBE NOW👇👇👇
https://youtube.com/@Weygud18
ለውብ ቀን

ከዛ በላይ ናችሁ!

ማንም ምንም ይበላችሁ እናንተ ከዛ በላይ ናችሁ፣ ማንም ሰራችሁን ያጣጥል ስራችሁ ግን ከማንም ስራ በላይ ነው፣ ማንም በኑሯችሁ ይፈር ኑሯችሁ ግን ከማንም ኑሮ በላይ ነው፣ ማንም ከፊታችሁ ቆሞ እንደማትችሉ ይንገራችሁ አቅማችሁ ግን ከንግግሩ በላይ ነው። ከውጪ የሚመጣው ጫና ይቅርና በውስጣችሁ እንኳን የሚመላለሰው የገዛ ሃሳባችሁ ከእናንተ በላይ አይደለም። እራሳችሁን በጥራት የምትመለከቱባት የግል መነፅር አላችሁ፣ ለእራሳችሁ የምትሰጡት ቦታ አላችሁ። ውድድራችሁ ከሰዎች ንግግር ወይም ከውስጥ ጩሀታችሁ ጋር ሳይሆን ለእራሳችሁ ከሰጣችሁት ቦታ ጋር እንደሆነ አስተውሉ። ብለሃትንና ጥበብን ትምህርት ቤት ገብታችሁ አትማሩም። እውቀትን ታወሩት ይሆናል ጥበብና ብለሃት ግን በየቀኑ የምትኖሯቸው ናቸው። ጥበበኞች የማይጠቅማቸውን ንግግር አይሰሙም፣ ብልሆች ከጩሀት በላይ በሳል ንግግር ይገዛቸዋል። በየጊዜው ይማራሉ፣ እራሳቸውን በእውቀት መሰረት ላይ ያንፃሉ፣ መንፈሳቸው ጠንካራ ነው፣ ልብና አዕምሯቸው ቅርብ ለቅርብ ናቸው፣ ስለራሳቸው ሚዛናዊ ሀሳብን በማሰብ ይታወቃሉ፣ በእራሳቸው ያምናሉ ከእራሳቸው ጋር ስለሚያወሩት እያንዳንዱ ነገር በሚገባ ይጠነቀቃሉ።

አዎ! እናንተ ከዛ በላይ ናችሁ! ሳትኖሩ ከሚወራባችሁ፣ በጆሯችሁ ከሰማችሁት፣ አዕምሯችሁ ደጋግሞ ከሚነግራችሁ አሉታዊ ማንነት በላይ ናችሁ። ህይወታችሁ በመዳፋችሁ ነች። የትኛውንም ወደ አዕምሯችሁ የሚገባውን አሉታዊ ሀሳብ የማገድ መብት አላችሁ፣ የትኛውንም በአዕምሯችሁ ውስጥ የሚመላለሰውን መጥፎ ሀሳብ ጠራርጎ የማውጣት አቅሙ አላችሁ። የሰዎችን ሀሳብ በማሳደድ አትጠመዱ፣ ስለሚወራባችሁ ነገር ብዙ አትጨነቁ። "ሰዎች ስለእኔ ምን አሉ ሳይሆን እኔ ስለእራሴ ምን እላለሁ?" ብላችሁ ጠይቁ። በማንኛውም ሰዓት በምንም አይነት ሁኔታ ውስጥ እራሳችሁን ልታገኙ ትችላላችሁ፣ በየትኛውም ሰዓት ያልጠበቃችሁት ስፍራ ልትገኙ ትችላላችሁ። ይህም ሁኔታ የህይወታችሁ አንድ አካል እንጂ የህይወታችሁ መጨረሻ እንዳልሆነ አስተውሉ። ሁሉም ነገር በፍጥነት ይቀየራል፣ የትኛውም ከባድ ስሜት እንደ ንፋስ ያልፋል። በተፈጥሮ የደስታችን ጊዜ አጭር የመከራችን ወቅት ግን ረጅም እንደሆነ ልናስብ እንችላለን። ነገር ግን ልዩነቱን ያመጣው አስተሳሰባችን እንጂ በእርግጥም የጊዜው ርዝመት ተለያይቶ አይደለም።

አዎ! ጀግናዬ..! ከየትኞቹም ከባድ ሁኔታዎችህ በላይ ስለመሆንህ አትጠራጠር። የሚሆነው ይሆናል፣ የሚቀረው ይቀራል፣ የምትባለውን ትባላለህ፣ የሚሰጥህ ስም ይሰጥሃል በስተመጨረሻ ግን ህይወት በእራሷ አቅጣጫ ስትቀጥል ትመለከታለህ። አንተ ተስፋ ቆርጠህ ካልቆምክ ምንም የሚቆም የህይወት ፍሰት የለም። ብዙዎች ሰዎችን ሰምተው ባሉበት ቆመው ቀርተዋል፣ ብዙዎች ለራሳቸው በሰጡት መጥፎ ስም ምክንያት ህይወታቸውን ፈተና አድርገውታል። የምትሰማውም ሆነ የምታየው ነገር ሁሉ እውነት እንደሆነ መቀበል አቁም። እውነት የእምነት ቅጂ ነው። ጉዳዩ የሚያወራው ወይም የሚያሳይህ ሰው ሳይሆን የእራስህ አቀባበል ነው። ሀሳብ ሰውን ይገነባል፣ ሀሳብ ሰውን ያፈራርሳል። ማንም የማይገባበት የግል ዓለም እንዳለህ እወቅ። ያንተ ዓለም ያንተ ብቻ ነው። ከማንም ዓለም አያንስም ከማንም ዓለም አይበልጥም። በልብህ ያኖርከውን ያንኑ እምነት በገሃድ አውጥቶ ያሳይሃል። የግል ዓለምህን ጠብቅ። የማንም ሀሳብ ገብቶ እንዳይረብሸው ተጠንቀቅለት። በህይወት አጋጣሚ ከተገኘህበት ሁኔታ የተሻለ ስፍራ እንደምታደርሰው ቃል ግባለት።

🚨በYouTube አማራጭ ይቀላቀሉን!
❇️SUBSCRIBE NOW👇👇👇
https://youtube.com/@Weygud18
https://youtube.com/@Weygud18

#መልካም ቀን

🎙ግሩፑን ለማግኘት
              👇👇👇

        @Mtshaf_bicha
        @Mtshaf_bicha
❤️ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
👉አሰተያየት ካላችሁ
📩 @Eyos18     አድርሱን
             📗📒📕📗📒📕
                Join&share
                  @EyosC1
       📚ማንበብ ባህላችን ይሁን📚
┄┉┉✽‌»‌🎶••✿••🎶»‌✽‌┉┉┄
🆕 What do you want to promote

📌 Advertising services we provide 💸
⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️

➡️ Channel advertisement
➡️ Music advertisement
➡️ Concert announcement
➡️ Company announcement
➡️ YouTube channel advertisement
➡️ Treatments and other sales announcement

     💻 Also, our door is open for those who want to work with us in various Business 🆕🆕 jobs. 🔸

        🔺 Earn double by making your product and service accessible to the masses at an affordable price. You will enjoy working with us. ❤️

Talk to us now 👇⬇️⬇️⬇️

•    @Eyos18
😀.   +251922788490
😀.   +251933324708‌‌
ለውብ ቀናችን

👍ከዚህ ይበልጣል!

አንዳንድ ሃሳቦች ሃሳብ ብቻ ናቸው፤ አንዳንዶችም ቅዠት ሊሆኑ ይችላሉ። ደጋግመህ ታስበዋለህ ነገር ግን ልታደርገው አትሞክርም፤ ደጋግሞ ይታይሃል፣ ይመጣብሃል ነገር ግን በእውን ልታየው አልቻልክም። ጀርባህ ብዙ ታሪክ፣ ኋላህ ብዙ እንቆቅልሽ፣ ብዙ ሸክም ይኖራል። በምንም ተዓምር በእንቆቅልሽ ማንነት፣ ባልተፈታ ታሪክ ታጅበህ ወደፊት መጓዝ፣ ሃሳብህን መኖር፣ እቅድህን መፈፀም፣ ህልምህን መኖር ሊቀልህ አይችልም። ምንም እንኳን መጠኑና አይነቱ ቢለያይም ሁሉም ሰው በህይወት አጋጣሚ በህመም ውስጥ ያልፋል፤ በስቃይ ይፈተናል፤ በግል አጣብቂኝ ውስጥ ይወድቃል፤ ደፋ ቀና ይላል፣ ይታገላል። የተደላደለ ህይወት ለማግኘት ብዙ ርቀት መጓዝ ይኖርበታል፤ ብዙ መሰናክሎችን ማለፍ ይጠበቅበታል፤ መወጣት የማይፈልገውን ሃላፊነት መወጣት ይጠበቅበታል።

አዎ! ጀግናዬ..! ሃላፊነትህ ቢልቅም፣ ተጠያቂነትህ ቢበዛም፣ ችግሮችህ ቢወሳሰቡም ህይወትህ ግን ከዚህ ይበልጣል፤ መቆየትህ ከዚህ ሁሉ ይልቃል። የሚሆኑ የማይመስሉ ታሪኮች ሊከሰቱ ይችላሉ፣ አጣብቂኞቹ ሊደራረቡ ይችላሉ፣ ፍላጎትና አሁናዊው አቅምህ ሊለያዩ ይችላሉ፣ ምኞትህና የጀመርከው መንገድም ሊራራቁ ይችላሉ። ነገር ግን በዚህ መሃልም ቢሆን መዳረሻህ አንድና አንድ ነው፤ በአዎንታዊነት ዘርፍ ከፍ ማለት፤ ጠቃሚ፣ ችግር ፈቺና አንተ የመጣህበት ከባድ መንገድ ላይ ያሉ ሰዎችን ማብቃት፣ መደገፍና አቅጣጫውን መጠቆም። የሆነው ቢሆንም የሚበልጠው ላይ ማተኮር ይኖርብሃል፤ እውነታውን ተቀብሎ መቆም ሳይሆን ወደፊት መጓዝ፣ መሰናክሎችን ተሻግሮ የተሻለውን ህይወት መፍጠር ይጠበቅብሃል።

አዎ! በጊዜ ብዛት የተገለጡ፣ ጊዜ ወዳንተ ያመጣቸው ጉዳዮች ፈቺው ጊዜያቸው ነው፤ የሚያቀላቸው እራሱ አምጪው አምላክ ነው። ፅናትህ እስከ ጥግ ሲሆን እንቆቅልሾችህ ይፈታሉ፤ ትዕግስትህ ሲበዛ የላቀውን ብለሃት ትጎናፀፋለህ። በደረሰብህ ጉዳይ ፈጥነህ ብይን አትስጥ፤ እራስህ ላይ ለመፍረድ፣ ማንነትህን ለመተቸት፣ መንገድህን ለማንቋሸሽ አትቸኩል። ሁሉም ሰው የተመረጠለት መንገድ በእርሱ በመራጩ በእግዚአብሔር ዘንድ ትክክልና እንከን አልባ ነው። ሁኔታህን መቃወም፣ ገጠመኞችህን መተቸት፣ በመጣህበት መንገድ ማፈር ከአምላክህ መቃረን፣ ፈጣሪህን መተቸትና በስራው ማፈር እንደሆነ እወቅ። መሰራት ባለብህ መንገድ ትሰራለህ፤ ብቁ መሆን በሚገባህ አቅጣጫ ብቁ ትሆናለህ። ዋናው ስቃይና ውድቀትህ ሳይሆን ዳግም መነሳትና የፈለክበት ስፍራ መድረስህ ነው።

🚨በYouTube አማራጭ ይቀላቀሉን!
❇️SUBSCRIBE NOW👇👇👇
https://youtube.com/@Weygud18
https://youtube.com/@Weygud18

#መልካም ቀን💚💛

🎙ግሩፑን ለማግኘት
              👇👇👇

        @Mtshaf_bicha
        @Mtshaf_bicha
❤️ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
👉አሰተያየት ካላችሁ
📩 @Eyos18     አድርሱን
             📗📒📕📗📒📕
                Join&share
                  @EyosC1
       📚ማንበብ ባህላችን ይሁን📚
┄┉┉✽‌»‌🎶••✿••🎶»‌✽‌┉┉┄
አይዞህ
Abdu Kiar
👤 Artist: አብዱ ኪያር
📅 Date: 2024
────────
🎙 JOIN US @Eyosc1
🎙 JOIN US @Eyosc1

🚨በYouTube አማራጭ ይቀላቀሉን!
❇️SUBSCRIBE NOW👇👇👇
https://youtube.com/@Weygud18
https://youtube.com/@Weygud18
🌍የዚህ ዓለም እውነታዎች!

ውሾች እና ድመቶች አልጋ ላይ እንዲዘሉ እየፈቀድን ድሆች ግን የግቢያችን ድንጋይ ላይ እንዲቀመጡ አንፈቅድም፡፡

የሰው ዋጋው እየቀነሰ የዶሮ እና የእህል ዋጋ እየጨመረ ሲመጣ በርትተህ ጸልይ፤ ጤናማ አካሄድ አይደለምና፡፡

የውሻ ቡችላ በዋጋ እየተሸጠ ሰውን ግን በነጻ የሚፈልገው ሲታጣ ዘመኑ መክፋቱን እወቀው፡፡

ስለብርቅዬ እንስሳት ብዙዎች እያለቀሱ ይናገራሉ። በምግብ እጥረት ስለሚሞቱት ሕጻናት ግን ቃል አይናገሩም፡፡

ስለ ጠፈር ሳይንስ ብዙ ይወራል (ይሰራል)። የምድር ኑሮ ግን ሲተራመስና ሲጎሳቆል ያስተዋለ የለም፡፡

የወደቁ የታዋቂ ሰዎች ሐውልቶች መልሶ ለመትከል ገንዘብ ይሰበሰባል፤ በየጎዳናው ዳር ስለወደቁት ምስኪን ሕጻናት ግን ምንም አይባልም፡፡

በዚች ምድር ሚሊዮኖች ቤት ሳይኖራቸው በሚልዮን ብሮች እስር ቤቶች ይገነባሉ፡፡

ስለ አየር መበከል ዓለም በሙሉ ይጮሃል። ስለሰው ልጆች ስነ ምግባር መመረዝ ግን ማንም ምንም አይልም፡፡
ሰዎች ሆይ! ... ከዚህ አፍ እና ልብ ከተለያዩበት ትያትረኛ ማንነታችን ፈጥነን እንውጣ ፡፡

☞ ሰዎች ሆይ! ... የሚቀድመውን ብናስቀድም የማይተወን ፈጣሪ ይከተለን ነበር ..።

‌‌‌‌‌‌‌‎‌‌‌‎‌‌‌‌‌‌‎‌‌‌‌‌‌‎‌‌‌‌‌‌‎‌‌‌‌‎‌‌‌‎‌‌‌‌‌‌‎‌‌‌‌‌‌‎‌‌‌‌‌‌‎
🚨በYouTube አማራጭ ይቀላቀሉን!
❇️SUBSCRIBE NOW👇👇👇
https://youtube.com/@Weygud18
https://youtube.com/@Weygud18

#መልካም ምሽት💚💛

🎙ግሩፑን ለማግኘት
              👇👇👇

        @Mtshaf_bicha
        @Mtshaf_bicha
❤️ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
👉አሰተያየት ካላችሁ
📩 @Eyos18     አድርሱን
             📗📒📕📗📒📕
                Join&share
                  @EyosC1
       📚ማንበብ ባህላችን ይሁን📚
┄┉┉✽‌»‌🎶••✿••🎶»‌✽‌┉┉┄
Forwarded from Botton Creater ✅
◇አክሽን ◇የጦርነት ◇የጫካ ◇የወንጀል  እንዲሁም የፍቅር ፊልም ሚመችክ ከሆነ አሁኑኑ JOIN  በለው  ይሄ ቻናል ምርጥ ምርጥ  ፊልሞችን በጥራትና በፍጥነት ያሳያል።  Join 👇
https://t.me/addlist/hsmi4bjCNuRhMTNk
https://t.me/addlist/hsmi4bjCNuRhMTNk