ፒያሳ መሃሙድ ጋ ጠብቂኝ
183K subscribers
280 photos
1 video
16 files
199 links
እዚህ Channel ላይ ያስተምራሉ ያዝናናሉ ብለን የምናስባቸውን
🎯ተከታታይ ልቦለድ
🎯ግጥም
🎯ወግ
🎯ፍልስፍና
🎯ምክር
🎯መነባንብ

#ማንኛውም አይነት ፅሁፎች📕 ከፈለጉ ይቀላቀሉን
የተለያዩ PDF መፅሐፍት ከፈለጉ @Eyosibooks
አስተያየት ካሎት👇👇
☎️• 0922788490

📩@Eyos18
Download Telegram
​​📕ተአምረተ_ኬድሮን

#ተከታታይ ልቦለድ

#ክፍል_ሰላሳ_ዘጠኝ

#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ

በማግስቱ….
ከምሽቱ 1 በሰዓት አካባቢ ነው ሰሚራም ሆነች ዶ/ር እስክንድር የእለቱ የማታ ተረኛ ሆነው ስራቸው ላይ ተስማርተዋል፡፡
ሰሚራ ለመላኩ ዘመዶች ደወለችላቸው…ሰሎሞን ነበር  ስልኩን ያነሳው

‹‹ሄሎ››

‹‹ሄሎ..ሰላም ነሽ?››

‹‹አዎ ሰላም  ነኝ …እንድትመጡ ፈልጌ ነው››

‹‹ማን…..? ››

‹‹እናንተ ናችሁ…. ሁለታችሁም››

‹‹ለምን…..? ምን ተፈጠረ…..?››

‹‹ላደርገው ነው…ማድረግ የምፈልገው ደግሞ እያያችሁ ነው..እናንተ ባላችሁበት››

‹‹አረ ችግር የለውም ..ሁሉን ነገር ካጠናቀቅሽ በኃላ ብትደውይልን ይሻላል››

‹‹እንደዛ አላደርግም…በቃ አሁን በነፍስ ነው ብዬ እንደደወልኩላችሁ አስቡትና  እቤትም ሆነ መንገድ ላይ ለገኛችሁት ሰው እንዲሁም ለሌሎች ዘመዶቻችሁ እየደወላችሁ በነፍስ ነው ተብሎ ተደውሎልናል እያላችሁ ንገሩ ፣እናንተም በ20 ደቂቃ ውስጥ ድረሱ›

‹‹አዎ… በቃ ገባኝ እንመጣለን..ትክክል ነሽ››ስልኩ ተዘጋ 

ሁለቱ ብቻ ሳይሆኑ በሌሎች ከስድስት በማያንሱ ሰዎች ታጅበው ለመምጣት ከ15 ደቂቃ በላይ አልፈጀባቸውም…..ሰላም ያዙኝ ልቀቁኝ በማለት ሆስፒታሉን አተረማመሰችው….ሰሎሞንም እንባውን እየዘራ ወንድሜን እያለ በማጎራት ግቢውን መዞር ጀመረ…
ለስድስት ቀን በኮማ ውስጥ የሰነበተው መላኩ ምን እንደነካው ከዶክተሩና ከሰሚራ ውጭ ማንም በማያውቀው ምክንያት በጣር ነፍስ ጊቢ ነፍስ ውጭ እያቃተተ ነው…ዶ/ር እስክንድር ሲስተር ሰሚራ እና ሌሎች ሁለት ነርሶች ዙሪያውን ከበው  ሊረዱት እየሞከረ ነው..

‹‹ሲስተር ሰሚራ ቶሎ ብለሽ ይሄንን መድሀኒት ውጊው ››ብሎ በወረቀት ላይ የመድሀኒቱን ስም ጽፎ ሰጣት… እሷም ተቀብላ ቶሎ ብላ ወጥታ ሄደችና በሶስት ደቂቃ ውስጥ ይዛ መጣች… መዳሀኒቱን በተንጠለጠው ግሉኮስ ከረጢት ውስጥ በስሪንጅ መጣ ለቀቀችበት ..ቀስ እያለ በቱቦ ውስጥ በመንጠባጠብ ከደም ስሩ ተቀላቀለ…. ከደቂቃዎች በኃላ የበሽተኛው ጣር  እየቀነሰ …መንፈራገጡም እያቆመ መጣ….ከዛ ፀጥ አለ …ሰው ሲሸነፍ ወይም ሲያፈገፍግ ፀጥ ይል የለ….ዶ/ር እስክንድር በማዳመጫ ትንፋሹ አዳመጠው…እጆቹና እያወናጨፈ አንገቱና ቀብሮ በብስጭት ክፍሉን ለቆ ወጣ …ኮሪደር ላይ እነ ሰሎሞን እና አጃቢዎቻቸው ከበቡት.

‹‹ዶክተር..እንዴት ነው በሽተኛው…..?››

‹‹ዶክተር ይሻለዋል ..ፍቅሬ ይድናል…..?››

ለበራካታ ሰከንዶች ተገትሮ ሰላምን አፍጦ ከማየት ውጭ ምንም መናገር አልቻለም፣‹‹….….ይቺን ላየ ሰው እነ ሰላም እና መሀደር ምኑን አክተር ተባሉት ?››ሲል በውስጡ አሰበ…መለስ ብሎም ስለራሱ አሰበ …ወየው ጉድ እኔም ለካ ሌላ ተዋናይ ሆኜያለሁ…አለም ሰፊ መድረክ እኛም ኑሪዎቾ  ተዋናዬች ነን ያለው ማን ነበር …..? ለካ እውነት ነው…›አለና ወደቀልብ በመመለስ ለእነሱ ጥያቄ  መልስ መስጠት ጀመረ 

‹‹አዝናለሁ የተቻለንን አድርገናል…ግን አልተሳካልንም..አርፏል ››ብሎ በተገተሩበት ጥሎቸው እግሮቹን አንቀሳቀሰ  … ግቢውን በጩኸት እና በለቅሶ ሲያደበላልቁት  በውስጡ እየተጠየፋቸው እና እየረገማቸው ጥሎቸው ወደ ቢሮው ሄደ

ሰላም…
..ፍቅሬ ፍቅሬ…
እንጋባለን ብለሀኝ አልነበረ ወይ…
ሙሽራዬ ነሽ አላልከኝም ነበር ወይ..
ለማን ተውከኝ..ለማን ተውከኝ 

ሰሎሞን……
ወንድም ጋሻዬ ….ወንድም ጋሻዬ
የእኔ ብቸኛ..የእኔ ብቸኛ
የአባቴ ምትክ ..የአባቴ ምትክ 
የዓይን ማረፊያዬ….
/////
ከደቂቃዎች በኃላ ሬሳው እየተገፋ ተመላካቹን በእንባ በሚያራጭ እንግሩጉሮአዊ ዜማ እና አንጀት በሚበላ  ሁኔታ በሚያለቅሱት እና ኩርምት ጭብጥ በሚሉት  በወንድሙ  ሰሎሞን እና በፍቅረኛው ሰላም መካከል አልፎ ወደሬሳው ክፍል ተወሰደ…..ሰሚራም እየተንቀጠቀጠች እና እየዘገነናት እራሷን ለማረጋጋት  በትርምሱ መሀል ተሹለክልካ ከሁሉም ነገር በመሸሽ  ቢሮዋ ገብታ ተሸጎጠች
እስከአሁን የሰራችው ስራ እና የፈጠረችው ተግባር ትልቅ ድንጋጤ ውስጥ ከቷት እየተንቀጠቀች  ነው..የሚገርመውና ይበልጥ የሚጨንቀው ግን ከአሁን በኃላ የምትሰራው ስራ ነው…
በበቀልም ሆነ በጥላቻ ተነሳስቶ ሰውን ድፍት አድርጎ መግደል በጣም ቀላል ነው…ሳያስበው በሆነ ብረት ማጅራቱን መጠቅለል እና ዝርግፍ ብሎ ሲወድቅ ጭንቅላቱን በድልዱም ብረት መድገም ነው…አዎ እንደዛ ማድረግ ቀላል ነው… የሚከብደው ከገደሉት በኃላ ያለው ነገር ነው፡፡ሬሳውን ምን ላድርገው…?ግቢው ውስጥ ቆፍሬ ልቅበረው..….?ረሀብ ያንገላታው ውሻ ቆፍሮ አውጥቶ ቢያጋልጠኝስ…?በጆንያ አድርጌ ከከተማ አውጥቼ ራቅ ያለቦታ በመውሰድ ጫካ ውስጥ ልጣለው…?.መንገድ ላይ ፖሊስ ለፍተሻ ቢያስቆመኝስ……..?እንደዛ ሳደርግ ሰው ቢያየኝስ……..?ስቃይ ነው….በዛን ቅጽበት ከሟቹ በላይ ገዳዩ ያሳዝናል…በተለይ  ገዳዩ እንደእሷ አማትር ገዳይ ሲሆን ......ሁኔታው  እንደቅዣት ሆኖባት፤ በውስጧ ስትብሰለሰል  ስልኳ ተንጫረረ….
ከፈጣሪ የተደወለባት ነው የመሰላት….በርግጋ ከተቀመጠችበት በመነሳት ተፈናጥራ ቆመችና የደዋዩን ማንነት ለደቂቆች አትኩራ ተመለከተች…. በፈራ ተባ ስሜት አነሳችው

‹‹አቤት››

‹‹የት ገባሽ…..?››

‹‹አለው ፈርቼ ቢሮዬ ቁጭ ብዬ ነው››

‹‹ምን ያስፈራሻል.…..?.››

‹‹እንዴ ድመት እኮ አይደለም ሰው ነው ያስገደላችሁኝ…..››

‹‹ማለቴ መግደልሽን  ማን ያውቃል..…..?እንደውም ስትፈሪና ስትንቀጠቀጪ የስራ ባለደረቦችሽ እንዳይጠረጥሩሽ…በተለይ ዶክተሩ እንዴት ሞተ ……..?ይሞታል ብለን አልገመትንም ነበር ሲል ሰምቼዋለሁ››

‹‹እ!! እንደዛ  አለ እንዴ…..? ››

‹‹አዎ ብሏል…ለማንኛውም አሁን ምን እናድርግ.››

‹‹ምን ለማድረግ አሰባችሁ?››

‹‹ሬሳውን አሁኑኑ ብትሰጡንና በጥዋቱ ቶሎ ብለን ብንቀብረው ጥሩ ነው፡፡››

‹‹ሬሳውንማ ላሰጣችሁ አልችልም …ጥዋት ነው መውሰድ የምትችሉት››

‹‹አይ አሁኑኑ መውሰድ አለብን… አሁን ሬሳ ሳጥን ገዝተው እንዲመጡ ሰዎች ልኬያለሁ…አንቺ ብቻ ደክተሩን አሳምነሽ እንዲፈርምልኝ አድርጊ…››

‹‹ዶክተሩ እኮ መሞቱን ብቻ ነው የሚያረጋግጥልህ….ሬሳውን በዚህ ምሽት እንድታወጣ የመፍቀድ ስልጣን ያላቸው  ግን ሌሎች ናቸው››

‹‹ሌሎቹን ተያቸው ..ዶክተሩ ብቻ ካስፈረምሽልኝ ካንቺ ምንም አልፈልገም…..ወደቤትሸ ሄደሽ ተረጋግተሸ በድል መተኛት ትችያለሽ…የስራ ኮንትራታችንን እዛ ላይ ይጠናቀቃል….››

‹‹እዛ ላይማ አይጠናቀቅም … መቶ ሺ ብር ጨምርልሻለው ብለኸኝ ነበር››

‹‹ሀይለኛ ብር ወዳድ  ልጅ ነሽ… አይዞሽ አረሳሁትም ግን እንደምታይኝ አሁን ሀዘን ላይ ነኝ ፡፡ ከሶስት ቀን በኃላ ያው እንደምንም መጽናናቴ  ስለማይቀር  አቀብልሻለሁ…››

‹‹ዋ እንዳትረሳ››

‹‹አረሳም አሁን ያልኩሽን ጨርሺና ደውይልኝ››
ስልኩ ተዘጋ……

ይቀጥላል

#ክፍል 40,,እንዲለቀቀ (10) ሰው ከስር ያለውን ሊንክ #Subscribe🔔ካረገ ይለቀቃል
https://youtube.com/@Weygud18

#Subscribe እያደረጋቹ ቤተሰቦች ተባበሩ #Subscriber
YouTube link👇
https://youtube.com/@Weygud18
በአስራ አምስተኛው ቀን እራሱን ለዋውጦ ጨለማን ተገን አድርጎ ሰፈሩ አካባቢ ሆነ ድርጅቱ ጋር ሄዶ  ለማየት ሞክሮ ነበር….ወንድሙ ሆነ ፍቅርኛው የየራሳቸውን ቤት ጥለው በቅርብ አስርቶት በነበረው  ባለአንድ ፎቅ መኖሪያ ቤት ውስጥ ተጠቃለው መግባታቸውን አረጋገጠ…
ውስጡ በጥላቻ እንኩትኩት አለ…ይህን ቤት እኮ ከመሰረቱ አንስቶ አጠናቆ እስኪያጠናቅቅ ድረስ ሰላምን ሙሽራ ሆና እቤቱ ስትገባ እያሰበ እና እያለመ ያም ሞራል ሆኖት ነበር ያገባደደው…እስከሚያውቀው ድረስ በጣም ነበር የሚያፈቅራት ….ከልብ ነበር የሚንከባከባት….መኪና ገዝቶ እስከመስጠት ድረስ ደርሷል..
ወንድሙንስ ቢሆን እራሱን እንዲችል እና የራሱ የሆነ ስራ እንዲኖረው ምን ያላደረገለት ነገር አለ.‹‹.ደግሞ ምንም ባላደርግለትስ…?ወንድሙ አይደለው እንዴ …..?ወንድምነት እንዲህ ቀላል ነገር ነው እንዴ……..?እንዴት ደጋግሞ ይገለኛል……..?ህይወቴን ነጥቆ…ንብረቴን ወርሶ… እጮኛዬን አግብቶ ምን አይነት ህሊና ነው ያለው…?
እንዲሁ ሲብሰለሰል ሰሚራም ስታፅናናው ቀናቶች እየነጎዱ እሱም ጥንካሬም እያገኘ ልብም ወደ ሰሚራ እየተሳበ መጣ…..
ሰሚራን ከሰላም ጋር  ሲያነፃፅራት  ግራ ግብት ይለዋል‹‹ያቺ እያወቀችኝ ስትስመኝ እና ስታቅፈኝ ኖራ ገደለችኝ..ይህቺ ምኔንም ሳወታውቀኝ ህይወቷን አደጋ ላይ ጥላ አዳነችኝ…ወይ የሰው ነገር…ሰው አኮ !! የሚባለው ለካ ለዚህ ነው…ሰውን እንዲህ ነው ተብሎ ቁርጥ ያለ ድምዳሜ ልንሰጠው አይቻልም..ሰው ደግ ነው ሰው ክፍ ነው፡፡ሰው መላዕክ ነው፤ ሰው ሰይጣን ነው፤ሰው ሞኝ ነው፤ ሰው ብልጥ ነው፤ሰው አዳኝ ነው ፤ሰው ገዳይ ነው…..››

     ይቀጥላል,,,,,,,,,

#ክፍል 41,,እንዲለቀቀ (10) ሰው ከስር ያለውን ሊንክ #Subscribe🔔ካረገ ይለቀቃል
https://youtube.com/@Weygud18

#Subscribe እያደረጋቹ ቤተሰቦች ተባበሩ #Subscriber
YouTube link👇
https://youtube.com/@Weygud18

መልካም ግዜ ተመኘሁ🙏
🎙ግሩፑን ለማግኘት
              👇👇👇

        @Mtshaf_bicha
        @Mtshaf_bicha
❤️ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
👉አሰተያየት ካላችሁ
📩 @Eyos18     አድርሱን
             📗📒📕📗📒📕
                Join&share
                  @EyosC1
       📚ማንበብ ባህላችን ይሁን📚
┄┉┉✽‌»‌🎶••✿••🎶»‌✽‌┉┉┄
📕ተአምረተ_ኬድሮን

#ክፍል_አርባ_አንድ

#ተከታታይ ልቦለድ

#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ

በ25ኛው ቀን ጥዋት ቁርስ ከበሉ በኃላ
‹‹ዛሬማታ ልሄድ ነው››
‹‹የት ነው የምትሄደው…..?››ደንገጥ ብላ ጠየቀችው ሰሚራ
‹‹ከከተማ ወጣ ብዬ  ትንሽ ራቅ ብዬ ምን ማድረግ እንዳለብኝ ማሰብ እፈልጋለሁ….››
‹‹ስለምንድነው የምታስበው..…..?ክፉ ነገር አይደለም አይደል…..?››
‹‹እኔ እንጃ …ለጊዜው ምንም የመጣልኝ ነገረ የለም..እንደገደሉኝ ልግደላቸው…ወይስ ይቅር ልበላቸው …..?የማውቀው ነገር የለም…ገንዘቤን ግን ልጅነቴን የሰዋሁበትና ብዙ ፈተና ያየሁበት ስለሆነ ሰባራ ሳንቲም እንደማልተውላቸው እርግጠኛ ነኝ..ምን አልባት እስከዛው በደንብ ቢደሰቱበት  ጥሩ ነው››
‹‹እንዴት አድርገህ ታስመልሳቸዋለህ……..?አሁን እኮ ንብረትህ በእነሱ እጅ ነው..በህይወት መኖርህን ካወቁ ባለ በሌለ  ኃይላቸው ነው አሳደው የሚያስገድሉህ››
‹‹አይዞሽ አታስቢ… እጠነቀቃለሁ….ለዛም ነው ከዚህ ከተማ ራቅ ብዬ በጽሞና ምን ማድረግ እንደምችል ማሰብ አለብኝ የምልሽ››
‹‹ካልክ እሺ ..ቆይ መጣሁ›› ብላ ከነበሩበት ሳሎን ተነስታ ወደመኝታ ቤቷ ከሄደች ከ5 ደቂቃ በኃላ ተመልሳ መጣችና ቼክ እጁ ላይ አስቀመጠችለት፣..ግራ ገብቶት አንዴ የሰጠችውን ቼክ አንዴ ደግሞ እሷን በማፈራረቅና በመገረም ሲያያት  ከቆየ በኃላ
‹‹ምንድነው ይሄ…..?››ጠየቃት
‹‹የራስህ ብር ነው..አንተን እንድገድልላቸው የከፈሉኝ ነው…ሁኔታዎችን እስቲስተካከሉልህ ለመንቀሳቀሻ ይሆንሀል››
‹እንዴ ምን አይነት ሰው ነሽ….?እንዲህ አይነት ሰው እኮ በዚህ ጊዜ አይገኝም››
‹‹አይ እንደምታስበኝ ደግ ሴት ሆኜ አይደለም..ለአንተ ብቻ ነው እንዲህ የሆንኩት..››
በንግግሯ ውስጡ ተነካና‹‹ለእኔ ለምን…..?››ጠየቃት
‹‹እኔ እንጃ….. ›አለችው
..ከተቀመጠበት ተነሳና ስሯ ተንበረከከ..ደነገጠች፡፡ አቀፋት …አንገቷ ሰር ገብቶ ሳማት…. ውርርር አደረጋት፣..አላቆመም… ወደታች አስጎንብሶ ግንባሯን …አይኖቾን… ጉንጮቾን በመጨረሻ ከንፈሯ ላይ ተጣበቀባት…አይኗን ከመጨፈን እና ከንፎሯን ከማነቃነቅ ውጭ ምንም ተቃውሞ አላሰማችም…ደስ የሚሉ እልፍ መሰል ሁለት ደቂቆች አለፉ….
የሚያደርገውን አድርጎ ከተቀመጠበት ተነስቶ ሲቆም እሷ አፍራ  አቀረቀረች…
የሰጠችውን ቼክ መልሶ ጉልበቷ ላይ እያስቀመጠላት..ይሄ ምን አልባት እኔን ለገደልሽበት ቢከፍሉሽም.. አንቺ ግን እኔን ለማዳን ለህክምና ይሄን ቤት ለመከራየት ላወጣሽው ወጪ መሸፈኛ ይሁንሽ…ውለታሽ ግን በዚህ ብር የሚመለስ ወይም የሚጣጣ ፍጽም አይደለም…በሕወቴም ጭምር ከፍዬ አልጨርሰውም››
‹‹ህይወትህን ስፈልግ ያኔ  ትከፍለኛለህ …አሁን ግን ከእኔ ይልቅ አንተ ነህ ችግር ላይ ያለህው …  ደግሞ ከራሴ ገንዘብ ምንም ያወጣሁት ነገር የለም…ከዚህ በተጫማሪ መቶ ሺ ብር ቦነስ ብለው ሰጥተውኝ ነበር…እርግጥ ከላዩ ላይ አንተን ለማሸሽ እና የሬሳ ሳጥኑን ቀይረው ለሰጡኝ አቶ ተካ 50 ሺ ብር ከፍያለሁ..ሌላውን 50 ሺብር   ደግሞ እስከአሁን እየተጠቀምኩበት ነው ፡፡››
‹‹አይዞሽ ለእኔ አትስቢ አልኩሽ እኮ …እነሱም ሆነ ማንም የማያውቀው 5 ሚሊዬን ብር ባንክ አለኝ…..በዛ እጠቀማለሁ፡፡››
‹‹ግን ባረብሽህ ምትሄድበት ይዘህኝ ብትሄድ …..?››
‹‹አረ ደስ ይለኛል..ስራሽን ብዬ እኮ ነው…..?››
‹‹ስራው ይደርሳል››
‹‹በያ ተዘጋጂ….መኪና እንከራይ ››
‹‹ወደየት ነው ግን ምንሄደው…..?››
‹‹እግራችን ወደመራን….››

   ይቀጥላል,,,,,,,,,

#ክፍል 42,,እንዲለቀቀ (10) ሰው ከስር ያለውን ሊንክ #Subscribe🔔ካረገ ይለቀቃል
https://youtube.com/@Weygud18

#Subscribe እያደረጋቹ ቤተሰቦች ተባበሩ #Subscriber
YouTube link👇
https://youtube.com/@Weygud18

መልካም ምሽት ተመኘሁ🙏
🎙ግሩፑን ለማግኘት
              👇👇👇

        @Mtshaf_bicha
        @Mtshaf_bicha
❤️ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
👉አሰተያየት ካላችሁ
📩 @Eyos18     አድርሱን
             📗📒📕📗📒📕
                Join&share
                  @EyosC1
       📚ማንበብ ባህላችን ይሁን📚
┄┉┉✽‌»‌🎶••✿••🎶»‌✽‌┉┉┄
📕ተአምረተ_ኬድሮን

#ክፍል_አርባ_ሁለት

#ተከታታይ ልቦለድ

በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ

የጊቢዋ አጸድ ውስጥ ባለ ወንበር ላይ ቁጭ ብላ የወፎችን ዝማሬ እና የዛፎችን ሽውሽውታ እየታዘበች በሀሳብ እየናወዘች ነው፡፡ያው በህይወቷ አዲስ ክስተት ተከስቷል … አንድ ሰው ላይ ለቀናቶች ሀሳቧ እንደተጣበቀ ነው….ያ ባሪያ ልጅ ልቧን ቅልጥ ሀሰቧን ውስውስ ነው ያደረገባት፡፡ሰሚራ ከምትባለው ፍቀረኛው ጋር ያለውን ታሪክ እና የፍቅር ትስሰር  ሙሉውን ታሪክ ለመጨረስ እራሱ አቅም አነሳት...ስለሱ ከማሰብ የሚያሰንፋት መስሎ እየተሰማት ነው….‹‹ለማንኛውም እስቲ  ታሪኩን ልጨርስ›› ብላ ተቀመጠች …ግን ታሪኩን ለመጨረስ  ንስሯ ያስፈልጋታል..እንደምታየው ደግሞ አሁን ጊቢ ውስጥ  ንስሯ አይታያትም …ብዙም ሳያስጠብቃት ከሄደበት ተመልሶ መጣ 
ቀጥታ ወደዛ ወደተለከፈችበት ታሪክ አመራች …አእምሯዋን ከንስሯ አዕምሮ ጋር በተለመደው መንገድ አቆራኘችው..አዎ አገኘዋቸው…ከከተማ እንውጣ ብለው ላንጋኖ ነው የሄድት …በሀይቁ ዳር በታነፀ ላውንጅ  የተዘጋ መኝታ ክፍል ውስጥ ናቸው፡፡
ህይወት ልክ እንደካርታ ጫወታ ነች…ይበወዝና ተጫዋች ለሆኑት  ኗዋሪዎቾ የሚታደል ዕጣ ፋንታ በሚሉት ምናባዊ ሀዲድ  የምትሸረብ…አጋጣሚ በተባለ የህይወት ሰንሰለታማ  ጉዞ ላይ በትክክለኛው ቦታ በትክክለኛው ጊዜ አንዱ ካንዱ በመገጣጠም መላተም እና በሌላ ገጽ ላይ  በሰከንድ ሽርፍራፊ ሰከንድ መዘግየት ተፈጥሮ ተፈላልጎም ሳይገናኙ  መተላለፍን በውስጧ የያዘች….
በጣርነው መጠን ማናገኝባት…ባመረትነው መጠን ማንሰበስብባት…በተመኘነው መንገድ ማንጓዝበት..እንደሎተሪ ዕጣ ብዙዎቻችን የምንከስርባት…የተወሰነው በማስተዛዘኛ የምንፅናናባት..ጥቂቶች ደግሞ እንደው ጠብታ  ላባቸውን በአልማዝ ተመንዝሮ እጃቸው ላይ የሚቀመጥላቸው …ውጥናቸውን አለም ጠቅላላ ተረባርቦ ከግብ የሚያደርስልቸው ከእርጥብ እድል ጋር የተፈጠሩ…ንግግራቸውን በደቂቃ አለም የሚያደምጥላቸው…እነሱ ለተከዙት አለም ተንሰቅስቆ የሚያለቅስላቸው …እንዲሁ መርቆ የፈጠራቸው አሉ፡፡ … እና ህይወት የካርታ ጫወታ ነች…የጫወታውን ህግ ግን ተፈጥሮዊ ብቻ አይደለም..ሰው ሰራሽም ጭምር ነው … 
ይሄንን ሀሳብ ያሰበችው ሰሚራ ነች ..ፍቅረኛዋ  መላኩ ደረት ላይ ጋደም ብላ እያሰላሰለች የምትገኘው፡፡እንዴት እንዲህ ልሆን ቻልኩ....?እንዴት ከበሽተኛዬ ጋር ፍቅር ውስጥ ገባሁ…...?አጋጣሚው ነው ወደዛ የገፋኝ ወይስ እራሴ ነኝ ፈቅጄ እና አስቤ ወደዚህ ደረቱ ላይ ወደተጋደምኩት ልጅ ልብ ውስጥ የገባሁት…...?
‹‹ምን እያሰብሽ ነው..?››ድንገት በጠየቃት ጥያቄ ለውስጥ ጥያቄዋ መልስ ሳታገኝ  አቋረጠችው፡፡
‹‹መቼ ጥለህኝ እንደምትሄድ እያሰብኩ ነው››አለችው…ለምን እንደዛ እንዳለችው ለራሷም አልተገለጸላትም… ..ምክንያም እያሰበች ያለችው ያንን እንዳልሆነ እሷና እግዚያብሄር ያውቃሉ….ሳታስብ ከንፈሯ ላይ የመጣላት ድንገታዊ መልስ የእውነት ስጋቷ አይደለም ማለት ግን አይቻልም…
‹‹የት ነው ጥዬሽ የምሄደው..?››
‹‹ወደኑሮህ ነዋ››
‹‹ኑሮ ማለት እኮ  የህይወት ደስታሽ የሚመረትበት ቦታ ነው….ማንም ሰው በህይወቱ የሚባክነው ያንን ቦታ ፍለጋ ነው…የደስታው ምንጭ የሚፈልቅበትን ጥግ ለማግኘት …የሰው ልጅ ስኬትም የሚለካው በዚህ ነው…እና እኔ እድለኛ ነኝ .ብዙም ሳለፋ በተዐምራዊ አጋጣሚ አንቺን አግኝቼያለሁ….እንዳገኘውሽ ያወቅኩት ደግሞ በአሁኑ ጊዜ በቃ ስትስቂ ልቤ ትቀልጣለች…ትንፋሽሽን ወደውስጤ ስስበው በሰውነቴ ውስጥ በስብሰው  ያበቃላቸው ሴሎቼ እንኳን መልሰው ህይወት ሲዘሩ ራሱ ይታወቀኛል…..ከጎኔ መኖርሽን ሳይ ዓለም ጠቅላላ ተሰብስባ ከእጄ የገባች ይመስለኝና ልቤ በኩራት አብጣ ልትፈነዳ ትደርሳለች..እና ከአንቺ ተለይቼ መሄድ ማለት ወደባዶነት ሸለቆ ተወርውሮ መከስከስ ማለት እንደሆነ ሚጠፋኝ ይመስልሻል …...?አሁን ባለሁበት ሁኔታ ከንቺ ውጭ ኑሮ ማለት ሲም ካርድ የሌለው ባዶ የሞባይል ቀፎ መሆን ማለት ነው…..››

ከትከት ብላ ሳቀች..ኪ…ኪ..ኪ…እንዴ ‹‹ነገሩን ሁሉ እኮ ስነጽሁፋዊ አደረከው…ከእኔ ከመገናኘትህ በፊት ነጋዴ ነበርኩ ብለሀኝ አልነበር እንዴ..?››

‹‹አዎ በጣም ጎበዝ ነጋዴ ነበርኩ…ምን ተፈጠረ..?››

‹‹አይ ንግግርህ የደራሲ እንጂ የነጋዴ አልመሰለኝ አለኛ…..››

‹‹አታውቂም እንዴ..? ፍቅር እና ችግር ያፈላስፋሉ እኮ….!!!››

‹‹አይ ጥሩ….ለማንኛውም የቀልድህንም ቢሆን በሰማሁት ነገር ደስ ብሎኛል….ምነው በተናገረው መጠን ሊያፈቅረኝ በቻለም ብዬ ተመኝቼያለሁ››

ከደረቱ ላይ ቀና አድርጎ አነሳትና እሱም ከተጋደመበት ቀና ብሎ ተቀመጠ… ወደእሷ ዞሮ አይን ዓይኗን እያየ‹‹አላመንሺኝም እንዴ ..? የምሬን ነው የተናገርኩት….በጣም ነው ያፈቀርኩሽ ..ወደፊት ማግባት የምፈልገው አንቺን ነው….የልጆቼ እናት ላደርግሽም እፈልጋለሁ….. ››
አንገቷን ወደእሱ ዘንበል አድርጋ እጆቾን በመዘርጋት ተጠመጠመችበት ..‹‹በጣም ነው የማፈቅርህ አንተን ስላገኘው እድለኛ ነኝ››
…..
‹‹እሺ አሁን ወጣ ብለን  ቢች ዳር ዘና እንበል…..››አላት በሀሳቡ ተስማማችና ተያይዘው ወጡ…
ላንጋኖ ሀይቅ ላይ ያረፈችው የማታዋ ጀንበር ልዩ ህብረቀለም እየረጨች ስትታይ ለአካባቢው ልዩ ውበት አልብሳዋለች…. ቢች ዳር ኳስ የሚጫወቱ አሉ..ሀይቅ ውስጥ ገብተው የሚዋኙን የሚንቦጫረቁም ጥቂት አይደሉም…… በአካባቢው ደስታ ተመርቶ የሚታደል ወይንም ከንፋሱ ጋር ተቀላቅሎ አየሩን እየሞላው በስፍራው ያለው ሰው ሁሉ እየማገው የሚፈግና የሚደሰት ይመስላል፡፡

‹‹ትዋኚያለሽ …..?››

‹‹አረ ይቅርብኝ …ዝምብለን እዚህ ሳሩ ላይ ቁጭ እንበልና  በማየት እንደሰት..ባይሆን ቆይቶ ከነሸጠኝ አብረን እንገባለን›› አለችውና ቁጭ አለች ..ተከትሎት ከጎኗ ቁጭ አለ…….

ይቀጥላል

#ክፍል 43,,እንዲለቀቀ (15) ሰው ከስር ያለውን ሊንክ #Subscribe🔔ካረገ ይለቀቃል
https://youtube.com/@Weygud18

#Subscribe እያደረጋቹ ቤተሰብ ስለምትሆኑ እናመሰግናለን #Subscriber
YouTube link👇
https://youtube.com/@Weygud18

መልካም ግዜ ተመኘሁ🙏
🎙ግሩፑን ለማግኘት
              👇👇👇

        @Mtshaf_bicha
        @Mtshaf_bicha
❤️ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
👉አሰተያየት ካላችሁ
📩 @Eyos18     አድርሱን
             📗📒📕📗📒📕
                Join&share
                  @EyosC1
       📚ማንበብ ባህላችን ይሁን📚
┄┉┉✽‌»‌🎶••✿••🎶»‌✽‌┉┉┄
📕ታምራተ_ኬድሮን

#ክፍል_አርባ_ሶስት

#ተከታታይ ልቦለድ

#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ

ሁለቱ ፍቅረኛሞች ከአካባቢው ተነስተው የተንቀሳቀሱት ከምሽቱ 2 ሰዓት አካባቢ ነበር…እያመሩ ያሉት ወደመኝታ ቤት ነበር..ልብስ ቀይረው ራት ለመብላት እና ምሽቱን ዘና ብለው ለማሳለፍ ወደ ሬስቶራንት ለመሄድ..ግን  መንገድ ላይ ያላሰቡት ሰው በዛፎችና በጭለማ የተሸፈነውን  ጠባብ  የእግር መንገድ ዘግቶ ሽጉጥ ደቅኖ ጠበቃቸው… መላኩ ቶሎ ብሎ የሰሚራን ክንድ ጨምድዶ ያዘና ጎትቶ ከጀርባው በማድረግ አሱ የግንብ ግድግዳ ሆኖ ከፊቷ ተገተረ…..
‹‹አይ አይ ….ካንተ በፊትማ እሷን ነው መግደል  የምፈልገው››
‹‹አይ እንደጀመርከኝ እኔኑ ጨርሰኝ….››
‹‹አይ መጀመሪያማ እንደህጻን ያታለለቺኝን ይቺን ጊንጥ ፊትህ ደፋትና አንተን አስከትላለሁ..››
‹‹ለመሆኑ እዚህ ድረስ እንዴት ተከትለኸን መጣህ..?››መላኩ  ነው ድንጋጤውን እንደምንም   ተቆጣጥሮ  በጣም የገረመውን እና ያልጠበቀው ነገር እንዴት ሊሆን እንደቻለ ለማወቅ የጠየቀው፡፡

‹‹እግዜር ነው እጄ ላይ የጣላችሁ..እኔማ ሀገር ሰላም ነው ብዬ ልዝናና ነበር እዚህ የመጣሁት
…ግን ሞቶ አልቅሼ በእጄ አፈር
አልብሼ ቀብሬዋለሁ ያልኩት ወንድሜ እዚህ ዘና ብሎ አለሙን ሲቀጭ አገኘሁት…..ለዛውም ገደልኩልህ ብላ 6መቶ ሺ ብሬን ቅርጥፍ አድርጋ ከበላች ቀጣፊ ሴት ጋር…››መለሰለት ሰሎሞን
መላኩ እየተንቀጠቀጠ መናገር ጀመረ‹‹ገራሚ ነህ …አንደኛ በዚህ አፍህ የእግዜያብሄርን ስም ማንሳትህ ትልቅ ድፍረት ነው..እግዚያብሄር እኮ ፍትህ ነው..እግዚያብሄር ፍቅር ነው..እግዜያብሄር የበጎነት የመጨረሻው ጥግ ነው…ታዲያ በምን ስሌት  እግዚያብሄር አንትን ረድቶህ እኛን አንተ እጅ ላይ ይጥለናል ብለህ ታስባለህ …..?ማይሆነውን…..!!!ደግሞ ገንዘቤን የምትለው…ገንዘቡ እኮ የእኔው ነው…ደግሞ እሷ እንደአንተ እና እንደዛች ሴት ከንቱ አትምሰልህ….ገንዘቡን የእኔ መሆኑን በመረዳት ሳትሰስት ሰታኛለች…››
‹‹በቃ ከዚህ በላይ ልፍለፋህን ልስማ  አልፈልግም …..አሁን አይኔ እያየ ሁለታችሁም በአንድ ሳጥን ተዳብላችሁ ትቀበራላችሁ..እዚህ የጀመራችሁት ፍቅር እዛ ያለከልካይ ትኮመኩሙታላችሁ…››ብሎ ወደነሱ የቀሰረውን ሽጉጡን ቀጭ ቀጭ አድርጎ አቀባበለ….ይሄ ቅጭልጭልታ ቀድሞ የተሰማው ለሰሚራ ጆሮ ነበር..ያው ሴት ከወንድ በላይ ንቁ አይደለች….ከሰማችው ድምጽ ጋር እኩል ተሸከርክራ መላኩን  ገፍታር ከፊቱ ተደቀነች.. ሞቱን ቀድማ ልትሞትለት….ተሳካላት…..በዛ ቅፅበት   ዶ..ዶ..የሚል አደንቋሪ ድምጽ ተሰማ  …ወዲያው የብዙ ሰው ጩኸት እና  የሚሮጡ የሰው ኮቴ …ከዛ ሰሚራ ዝልፍልፍ ብላ መላኩ  እጁ ላይ ገንደስ ስትል ይዟት ወደመሬት ሲወርድ ..ሁሉ ነገር የሚሆነው በደመነፍስ ነበር….
…ሰሚራ ድንገተኛ እና ያልታሰበ ከነበረው ከዛ አደጋ ከወራት  ህክምና በኃላ ዳነች…መላኩም ወንድሙንና  እና የበፊት ሚስቱን በግድያ ሙከራ እና በእምነት ማጉደል ከሶ በህግ ቁጥጥር ስር እንዲውሉ በማድረግ  ወህኒ እንዲወረወር አድርጎ ንብረቱን መልሶ ተቆጣጥሯል….አዎ እዚህ ድረስ ያሉ ነገሮች ጥሩና መልካም የሚመስሉ ነገሮች ነበሩ…እንግዲህ ይህ  ድርጊት የተከወነው ከአምስት አመት በፊት ነበር…

በመላኩ ወንድም በሰለሞን  ሽጉጥ ተተኩሶባት ፍቅረኛዋን ቀድማ በተመታችበት ወቅት ከተተኮሱባት ሁለት ሽጉጦች መካከል አንዱ ሽጉጥ በደረቷ ሌላው ደግሞ በጭነቅላቷ ነበር የገባባት…እና በወቅቱ በደረቷ የገባቸውን የጥይት ቀላሀ በቀላሉ ማውጣት ቢቻልም የጭንቅላቷን ማውጣት ግን በጣም አስቸጋሪ ሆኖ ነበር…፡፡
አስቸጋሪነቱ ጭንቅላቷን ቀዶ ጥይቷን  መዞ ማውጣቱ አይደለም….የከበደው ጥይቷ የተቀረቀረችበት ቦታ እንጂ… ጥይቷ ከወጣች የሰሚራ የጤና ሁኔታ በቋሚነት እንደሚበላሽ ….ትውስታዋ ሙሉ በሙሉ ሊጠፋ ከዛም አልፎ የማሰብ አቅሞንም እንደሚጎዳው ከፍተኛ ስጋት ስለጣለባቸው….ለጊዜው  ባለበት እንዲቆይ… በየጊዜው የቅርብ የህክምና ክትትል እንድታደርግና በሂደት የሚሆነውን ለማድረግ ተወሰኖ ነበር..
ለአንድ አመት  በየወሩ እየተማመላለሰች ህክምናዋ በመከታል በጥንቃቄ  ካሳለፈች በኃላ ምንም የሚሰማት እና የሚለወጥ ነገር ስላልነበረ ቀስ በቀስ እየተዘናጋችና ምንም አይፈጠረም በሚል እምነት ክትትሉን አቆመች ….
በዛን የጊዜ ክፍተት ውስጥ…መላኩ በንግዱ አለም ከበፊቱ የበለጠ ተሳክቶለት ከሰሚራ ጋር ያየነበረው የፍቅር ትስስር ይበልጥ እየጎመራ ሄዶ ወደጋብቻ ሊሸጋገር ወራቶች ሲቀሩት….ግን ከሁለት አመት ቆይታ በኃላ ድንገት ወድቃ  ሀኪም  ቤት ዳግመኛ ለመግባት ተገደደች…  ምርመራ ባደረገችበት ጊዜ በጭንቅላቷ መሀከላዊ ስፍራ የተቀረቀረችው ጥይት ብቻ ሳትሆን በፊት ያልነበረ ጎን ላይ  አስደንጋጭ እጢ ተፈጥሮ  ታየ..ሀኪሞቹ ተደናገጡ ..ተስፋ እንደሌላት እና ማድረግ የሚችሉት ብዙም ነገር እንደሌለ ለመላኩ ሲነግሩት አንጠልጥሎ ወደውጭ ሀገር ይዞት ሄደ….ግን የረፈደ ውሳኔ ነበር…ጥይቷ እንዲወጣላት ማድረግ ተቻለ ..እጢውም በጨረር ህክምና እንዲሞሞ ማድረግ ብዙም ከባድ አልነበረም…ይ ሁሉ ቢሆን ግን በህይወት ልትቆይ የምትችለው በዛ ቢባል ለቀጣዩ አንድ ወይም ሁለት አመት እንደሆነ አስምረው ነገረዋቸዋል…ከዛ በኃላ ወይ ትሞታለች ወይ ደግሞ በድን ሆና በህይወት እና በሞት መካከል ተንጠልጥላ ለአመታት ትኖራለች…..ሚሻለው ግን ወዲያው ብትሞት ነው…. የሀኪሞቹ ምክር ነበር፡፡ …የምርመራው ወጤቱ ለሁለቱም  ሰቅጣጭ ነበር…

እንግዲህ እነዚህ ፍቅረኛሞች …ሳቃቸው ከእንባ የተቀላቀለ፤ደስታቸው ከፍራቻ የተጋባ፤ተስፋቸው ጨለማ የገደበው ከሆነ እና በዚህ ሰቀቀን ውስጥ መኖር ከጀመሩ አመት አልፏቸዋል እና ንስሯ ባመጣላት ታሪክ መሰረት በቀደም የዋና ገንዳ ውስጥ ያገኘችው ፤የፈተነችው እና የፎከረችበት ወጣት ታሪክ እንደዚህ ነው…ታማኝ የሚሆነውም ለዚህች ፍቅረኛው ነው…..አግቢኝ እና ውለጂልኝም የሚላት ይችኑ በጀርመናዊዎቹና በአሜሪካኖቹ ሀኪሞች የ አመት ጊዜ ብቻ የተቆረጠላትን ወጣት  ነው….
ኬድሮን አሰበች‹‹እና ምን ላድርግ ….?እንዳለች ልተዋት….? ትውለድለትና ትሙት…. ከዛ እኔ ለእሱ ሚስት ለልጁ ደግሞ እናት ልሁን…..?ነው ወይስ ላድናት……..?›ከህሊናዋ ጋር ከባድ ፈተና ገባች፡፡በእርግጠኝነት   ንስሯ ከረዳት ለእሷ መዳኛ የሚሆን መድሀኒት ሌላ የአለም ጥግ ማሰስ ሳያስፈልጋት …ከዚህችው ከቅድስቲቷ የኢትዬጵያ ምድር  ቆፍር ቆፈር አድርጋ  ስር ማስ ማስ ፤ ቅጠል በጠስ በጠስ በማድረግ  ልታድናት ትችላለች..፡፡ግን  ለምን ታደርገዋለች…..?ለማንኛወም ጊዜ ወስዳ ልታሰብበት ከራሷ ጋር ተስማማች….

ይቀጥላል….

#ክፍል 44,,እንዲለቀቀ (15) ሰው ከስር ያለውን ሊንክ #Subscribe🔔ካረገ ይለቀቃል
https://youtube.com/@Weygud18

#Subscribe እያደረጋቹ ቤተሰብ ስለምትሆኑ እናመሰግናለን #Subscriber
YouTube link👇
https://youtube.com/@Weygud18
እሷም በመፍለቅለቅ እና ስጦታህን ከልቧ በደስታ  በመቀበል‹‹የእኔ ውድ….እዚህ ሰፍራ ከንተ ጋር አንድ ሳምንት እንኳን መኖር ዘላለም የመኖር ያህል ጣዕም ይሰጠኛል.. አፈቅርሀለው››ትልሀለች
‹‹ካፈቀርኝማ አግቢኝ››ትላታለህ
‹‹እንዲህ አድረገህልኝማ እንዴት እንቢ ልልህ እችላለሁ…..?ዛሬውኑ አገባሀለሀ…እዚህም ደሴት ላይ ምታምር ልጅ  ወልድልሀለሁ… ስሟንም ዘሀራ ትላታለህ  ..ትርጉሙም አበባ ማለት ነው››ትልህና ያልጠበቅከውን የምስራች ነግራህ ታስፈነድቅሀለች፡፡አንተም በሰማሀው ነገር   ሰክረህ ጮኸህ ስትጠመጠምባት‹‹..አረ አነቅከኝ …ምነካህ  …››ብላ ከጎንህ የተኛችው የእውነቷ አለም ሰሚራ ቀስቅሳ ነው ከእንቅልፍህም ከህልምህም ያፋታችህ…
ከተዘረፈጠበት ወለል..ዝልፍልፍ እንዳለ እየተጎተተ ተነሳና ሶፋው ላይ ተቀመጠ..ድክምክ ባለ እና እጅ የሰጠ በሚመስል  የተሸነፈ ድምጽ‹‹ይህንን እኮ ለሰሚራዬ እንኳን እ
አልነገርኳትም… ለብቻዬ አልሜ በውስጤ ብቻ ቀብሬ አስቀርቼው የነበረ  ፍቺውን በማብሰልሰል ላይ የነበርኩት  ጣፍጭ ህልሜ ነበር….እንዴት ልታውቂ ቻልሽ?››

‹‹ዋናው ማወቄ ነው…..አሁን እንዳድንልህ ትፈልጋለህ..?››

‹‹በጣም…አትቺይም እንጂ ከቻልሽ በጣም እድታድኚልኝ እፈልጋለሁ….››

‹‹ካዳንኩልህ ምን ታደርግልኛለህ…..?››መልሳ ወደ መነሻ ጥያቄዋ 

‹‹ህይወቴንም ከፈለግሽ..አንገቴን ቀንጥሼ ለመስዋዕትነት በሰሐን እንዲቀርብልሽ አደርጋለሁ  ››

‹‹ጥሩ ስጦታ ነው…..ግን አንገትህን አልፈልግም››

‹‹እሺ ሙሉ ንብረቴን ምንም ቤሳ ቤስቲ ሳትቀር ሰጥሻላሁ››

‹‹እሱንም አልፈልግም….እኔ በንብረት የምደሰት አይነት ሰው አይደለሁም››

‹‹እሺ ምን ትፈልጊያለሽ..?››

‹‹ሰሚራን  ከዳነች በኃላ ትተዋታለህ..ትተዋት እና እኔን ታገባለህ››

‹‹ዝም አለ…በቃ ዝም …..በድን የሆነ የሚጮህ ዝምታ….ድምፅ ያለው ዝምታ…..››

‹‹እ ምን አልከኝ..?››አለችው ዝምታው በውስጧ የፈጠረውን  ስቃይ መቋቋም ሲያቅታት ልትረብሸው ፈልጋ…

ይቀጥላል

#ክፍል 45,,እንዲለቀቀ (15) ሰው ከስር ያለውን ሊንክ #Subscribe🔔ካረገ ይለቀቃል
https://youtube.com/@Weygud18

#Subscribe እያደረጋቹ ቤተሰብ ስለምትሆኑ እናመሰግናለን #Subscriber
YouTube link👇
https://youtube.com/@Weygud18

መልካም ምሽት ተመኘሁ🙏
🎙ግሩፑን ለማግኘት
              👇👇👇

        @Mtshaf_bicha
        @Mtshaf_bicha
❤️ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
👉አሰተያየት ካላችሁ
📩 @Eyos18     አድርሱን
             📗📒📕📗📒📕
                Join&share
                  @EyosC1
       📚ማንበብ ባህላችን ይሁን📚
┄┉┉✽‌»‌🎶••✿••🎶»‌✽‌┉┉┄
‹‹እንዴ ታዲያ እንዲህ ምን ዝልፍልፍ አደረገህ..….?ሄጄ ቀንጥሼ ልምጣና የመልስ ጉዞችንን እንቀጥላ.››
አዕምሮዋ ላይ መልዕክት አስቀመጠላት..‹‹ልክ ከለሊቱ ስድስት  ሰዓት ላይ ነው መቀንጠስ ምትችይው….›››

ሞባይሏን አወጣችና አብርታ ሰዓቷን አየች..5፡20 ይላል
‹‹እና ገና 40 ደቂቃ መጠበቅ አለብን….?››

‹‹ የግድ ነው››

‹‹በቃ እንጠብቃለን…አንተ ግን  ምነው እንዲህ አዘንክ ደስ አለለህም….….?››

‹‹መዳኒቱን ጥለን እንሂድ››አለት..ያልጠበቀችው ምክረ-ሀሳብ ነው

‹‹እንዴ ለምን….? እዚህ ድረስ በዚህ ለሊት የለፋነው ለመድሀኒቱ አይደል እንዴ….?  ››

‹‹አዎ  ቢሆንም ጥለነው እንሂድ››

‹‹እንዴ ምን ነካህ .. ….?በዚህ አይነት ሁኔታ እስከዛሬ ብዙ ሰዎች አድነናል…አይደለም ከኢትዬጵያ ሱዳን ኤደን ባህረሰላጤ.. ኢራቅ ድረስ እኮ ሰውን ለማዳን የሚሆን መድሀኒት ፍለጋ ሄደን በስንት ልፋትና ጥረት አግኝተን ብዙ ሰው አድነን እናውቃለን..መድሀኒትን ያለበት ቦታ በእንደዚህ ሁኔታ ቀርበን ግን አንድም ቀን ትተነው እንመለስ ብለሀኝ አታውቅም››

‹‹ይሄ የተለየ ስለሆነ ነው››

‹‹ምንድነው የተለየ..….? ልጅቷን አያድናትም….?››

‹‹ያለምንም ጥርጥር ያድናታል…. ››

‹‹እና ታዲያ..….?ገባኝ ልጅቷን ከዳንኳት በኃላ ባሏን ስለምወስድባት አሳዝናህ ወይም እኔ ያልሆነ ነገረ እንዳልሰራ
ለመካላከል ነው አይደል..….?››

‹‹አይደለም….….?ይሄ ተክል የአባትሽ ዘመዶች በምድር ላይ የበተኑት ተክል ነው…ይሄንን ያየሽውን ተክል ማንም ሰው በዓይኑ ማየት አይችልም..››

‹‹እኔ እኮ እያየሁት ነው..››

‹‹አንቺ ያየሽው የአባትሽ ደም በውስጥሽ ስላለ ነው››

አባተሽ የሚለውን ቃል ለሁለተኛ ጊዜ ሲደግመው ነው ያስተዋለችው 

      ይቀጥላል

#ክፍል 46,,እንዲለቀቀ (15) ሰው ከስር ያለውን ሊንክ #Subscribe🔔ካረገ ይለቀቃል
https://youtube.com/@Weygud18

#Subscribe እያደረጋቹ ቤተሰብ ስለምትሆኑ እናመሰግናለን #Subscriber
YouTube link👇
https://youtube.com/@Weygud18

መልካም ምሽት ተመኘሁ🙏
🎙ግሩፑን ለማግኘት
              👇👇👇

        @Mtshaf_bicha
        @Mtshaf_bicha
❤️ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
👉አሰተያየት ካላችሁ
📩 @Eyos18     አድርሱን
             📗📒📕📗📒📕
                Join&share
                  @EyosC1
       📚ማንበብ ባህላችን ይሁን📚
┄┉┉✽‌»‌🎶••✿••🎶»‌✽‌┉┉┄
📕ታምራተ_ኬድሮን

#ክፍል_አርባ_ስድስት

#ተከታታይ ልቦለድ

#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ

‹‹የአባትሽ ዘመዶች ነው ያልከው….?››

‹‹አዎ የአባትሽ ወገኖች … ይሄንን ተክል በምድር ላይ  እንዲበቅል አድርገው ሲበትኑት ለመድሀኒትነት እንዲሆን አስበው አይደለም…››

‹‹እና ለምድነው….?››

‹‹አንቺን ለማግኘት….››ብሎ ጭራሽ ግራ አጋባት

‹‹እንዴት አድርገው ነው እኔን የሚያገኑኝ…….?ደግሞ የት ናቸው….?››

‹‹የት እንዳሉማ ታውቂለሽ….››

‹‹እና እንዴት ነው የሚያገኙኝ ….?››

‹‹ልክ  ያቺን ተክል ስትቀነጥሺ ቀጥታ መልእክቱ እነሱ ጋር ይደርሳል››

‹‹እወነትህን ነው….?››ውስጧ ፈነጠዘች..አባቷ የማግኘት ምኞት ሳታስበው አዘለላት..የእናቷን እውነት የማረጋጋጥ ፍላጎት…

‹‹እና አሪፍ ነዋ..ያለሁበትን ካወቁ ይመጣሉ አይደለ..….?አባቴም ይመጣል አይደል….?››ጠየቀችው

‹‹አይ አባትሽ በጥብቅ እስር ላይ ስላላ መምጣት አይችልም.. ወደዚህ ምድር በመጣ ጊዜ ሳይፈቀድለት  ከሰው ጋር በፍቅር በመቆራኘትና አንቺን ስለወለደ ይሄው ባንቺ እድሜ ሙሉ እንደታሰረ ነው››አንጀቷ ተላወሰ..በምድር ላይ ታስሮ ቢሆን ኖሮ  የፈጀውን ያህል   ይፍጅ  እንጂ   መንግስትንም ገልብጣ ቢሆን አባቷን ታስፈታው ነበር

‹‹እና ታዲያ ዘመዶቹም ቢሆን ይምጡ ምን  ችግር አለው….?››

‹‹ሚመጡት  አንቺን ለመውሰድ ነው››

ደስ አለት..ደነገጠችም ‹‹ወዴየት ነው የሚወስድኝ….?››

‹‹ወደራሳቸው አለም….››

‹‹እኔ መሄድ ካልፈለኩስ….?››
‹‹ፈለግሽም አልፈለግሽም ይወስዱሻል …ምንም አይነት ምደራዊ ኃይል አንቺን ከመውሰድ አያግዳቸውም….››

ለአምስት ደቂቃ በትካዜ  ውስጥ ገባች…ሌላ አለም የማየት ፍላጎት… አባቷን እና ዘመዶቹን የማወቅ ፍላጎት..ደግሞ ይህቺን ምድርስ….?

‹‹ቆይ ሄጄ ሁሉን ነገር ካየሁ በኃላ ተመልሼ ወደምድር መምጣት አልችልም….?››

‹‹አይመስለኝም… ብትመለሺም እንደዚህ ሆነሽ አይደለም…ሙሉ በሙሉ ተቀይረሽ.. ሙሉ በሙሉ እነሱን ሆነሽ..የእነሱን ተልዕኮ ለማስፈፀም ነው ሚሆነው.ያ በእነሱ ፍቃድ ላይ የተመሰረተ ነው.ከፈለጉ እስከወዲያኛው ዳግመኛ ምድርን ላትረግጪ ትችያለሽ፡፡››

‹‹በቃ ይሁን.. ለእኛም እዛ መኖር ይሻለናል..የተለየ ዓለም  እኮ አሪፍ ነው..ይቺን ዓለም እንደሆነ በተቻለ መጠን በርብረናታል…ምን ይቀርብናል….?››

‹‹እና ወሰንሽ››

‹‹አዎ ባክህ እንደውም አሪፍ እድል ነው››
እንግዲያው ተዘጋጂ… ከአምስት ደቂቃ በኃላ ሄደሽ መቀንጠስ ትችያለሽ..ከቀነጠስሽ በኃላ ግን አንድ ሳምንት ብቻ ነው በምድር የመቆየት እድል የሚኖርሽ… ልክ የዛሬ ሳምንት በዚህን ሰዓት ካለሽበት ቦታ መጥተው ይዘውሽ ይፈተለካሉ››

‹‹አንድ ሰምንት..አንድ ሳምንት ፈጠነ..ግን ቢሆንም ቀላል ቀን አይደለም….ብዙ ነገር እንሰራበታለን…እናቴን ሄደን እንሰናበታለን..የልጅነት ጎደኞቼን እሰናበታለሁ… አሪፍ ነው..አንድ ሳምንት ይበቃናል..››አለችና ወደተክሏ ተራመደች..
ደረሰችና ልክ ድፍን  6 ሰዓት ሲሆን  ከብሳናው ዛፍ ቅርንጫፎች መካከል  እጇን ዘረጋችውና ጨበጠችው… ቀነጥሰዋለሁ ስትል በእጇ ሟሞና እንደቅባት ተሙለጭልጮ ወደሰውነቷ ሲገባ ታወቀት… ደነገጠች የቀነጠስችው መስሏት ነበር… እጇ ላይ ግን ምንም ነገር የለም… እጇ  የተለየ ቀለም እያመጣ ነው ..ሀመራዊ እሳት መሰል ቀለም… በመላ ሰውነቷ እየተራወጣ ከተዳረሰ በኃላ አንዘርዝሮና አንቀጥቅጦት በአፏ የቴንስ መጫወቻ የምታክል ድብልብል እሳት ብልቅ ብሎ በመውጣት እንደሮኬት ተተኩሶ ወደሰማይ ተምዘገዘገ ..እያየችው  አየሩን ሰንጥቆ ተሰወረ..ግራ ጋባት …እንደምንም ለመረጋጋት እየሞከረች ወደንሰሯ አዕምሮ ተመለስችና ‹‹ምን እየሆነ ነው….?››ጠየቀችው
‹‹በቃ ጨርሰናል እንሄድ››
‹‹እንዴ መቀንጠስ አልቻልኩም እኮ ..እጄ ላይ ምንም የለም….?››
‹‹እጅሽ ላይ ምን ያደርግልሻል …ተክሉ እኮ በመላ ሰውነትሽ ገብቶ ተዋሀደሽ..አሁን መዳኒቱ ተክሉ ሳይሆን አንቺ ራስሽ ነሽ..በዚህ የሳምንት ጊዚ ውስጥ የፈለግሽውን ማዳንም የፈለከግሽውን መግደልም  ትችያለሽ..››

‹‹ደስ ሲል ››

‹‹ደስ አይልም…››አለና ከመጣ ጀምሮ ተዘፍዝፎበት ከነበረው ቋጥኝ ላይ ክንፉን አርገፍግፎ ተነሳን ማጅራቷን ይዞ ወደሰማይ ተምዘገዘገ  ….ወደጀርባዋ ዞረና ተጣበቀባት…  ወደ አዲስአባ ተመልሰው እቤታችን ሲደርሱ ከምሽቱ 8 ሰዓት አልፎ ነበር… …

‹‹ወይኔ ድክም ብሎኛል..ግን መድሀኒቱን ስላገኘን ከአባቴ ወገኖችም ጋር ልንገናኝ ስለሆነ ደስ ብሎኛል…አንተስ ደስ አላላህም….?››ለመተኛት ወደ አልጋዋ እያመራች ነበር ምትናገረው

‹‹በጣም ከፍቶኛል››አላት ንስሯ

ደነገጠች‹‹ለምን….?››

‹‹ከንቺ ጋር የምኖረው ..በህይወትም የምቆየው ለሳምንት ብቻ ስለሆነ››

በህይወቷ እንደዚህ አይነት ድንጋጤ ደንግጣ አታውቅም.‹‹.እንዴ የእኔ ንስር ሟች ፍጡር ነው እንዴ…….?›ብላ ለመጀመሪያ ጊዜ ያሰበችብት ጊዜ ነው

‹‹ጥዬህ የምሄድ መስሎህ ነው..አብረን እኮ ነው የምንሄደው››

‹‹ይዘሺኝ መሄድ አትቺይም››

‹‹ለምን….?››

‹‹እኔ መጀመሪያም ከዛ ነው የመጣሁት…ለአባትሽ ብዬ እና አሁን ተመልሼ ለመሄድ ፍፅም አይፈቀድልኝም፡፡››

‹‹በቃ ይቀራላ ..እስከዛሬ ካንተ  ጋር እንጂ ከእነሱ ጋር አልኖርኩ.. ምን  ያደርጉልናል እነሱ መቅረት ይችላሉ››

‹‹እሱማ ጊዜው አለፈ..ቅድም ከአፍሽ የወጣችው እሳት አነሱ ጋር መልዕክት ይዛ የምትሄድ ነች…ወደድሽም ጠላሽም አንቺን ይወስዱሻል..እኔ ደግሞ ካለአንቺ ህይወት የለኝም …ተነጥለሺኝ እንደሄድሽ ወዲያው በዛኑ ሰዓት እሞታለሁ..››

‹‹እንዴ  እሞታለሁ ማለት ምን ማለት ነው….?ይሄንን ታዲያ ተክሉን ከመቀንጠሴ በፊት ለምን አልነገርከኝም….?››

‹‹ውሳኔሽ በእኔ ላይ እንዲመሰረት ስላልፈለኩ ››

‹‹ያምሀል እንዴ . ….?.ካንተ ሚበልጥብኝ ነገር አለ…….?

ህይወቴ እኮ ነህ..››አበደች ጮህች ፕሮፌሰሩ ከእንቅልፋቸው ባነው በራፏን እስኪያንኮኩ ድረስ ግቢውን አተረማመችው …፡፡

     ይቀጥላል

#ክፍል 47,,እንዲለቀቀ (15) ሰው ከስር ያለውን ሊንክ #Subscribe🔔ካረገ ይለቀቃል
https://youtube.com/@Weygud18

#Subscribe እያደረጋቹ ቤተሰብ ስለምትሆኑ እናመሰግናለን #Subscriber
YouTube link👇
https://youtube.com/@Weygud18

መልካም ምሽት ተመኘሁ🙏
🎙ግሩፑን ለማግኘት
              👇👇👇

        @Mtshaf_bicha
        @Mtshaf_bicha
❤️ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
👉አሰተያየት ካላችሁ
📩 @Eyos18     አድርሱን
             📗📒📕📗📒📕
                Join&share
                  @EyosC1
       📚ማንበብ ባህላችን ይሁን📚
┄┉┉✽‌»‌🎶••✿••🎶»‌✽‌┉┉┄
​​‹‹እትዬ ሰሚራ ናቸዋ… ስንት ነገር ሲታሰብ… ለሰርጋቸው ሲዘጋጁ እንዲህ ባጭር ይቅሩ..….?ውይ ጋሼ በጣም ነው አንጀቴን የበሉት ..ተሳቀቁ፤እትዬስ አንዴ ለይቶላቸው ሊገላገሉ ነው እሷቸው ግን ጤነኛ ሰው የሚሆኑ አይመስለኝም፡፡››

ይህን ሁሉ እያወራ ሳሎኑ በራፍ ድረስ አደረሰታ እና የሳሎኑን በራፍ ከፍቶ አስገብቶ ወደኃላ ተመለሰ….ሳሎኑ ውስጥ በግምት ከ10 ያላነሱ  ፎጣ የለበሱ፤ ጋቢ የደረቡ ፤ የተቀመጡ፤ የሚንጓራደዱ ሰዎች ይታያሉ……

‹‹ዋው !!!ምን አይነት ሰዓት ደረስኩ….?››ስትል እራሷን ጠየቀች…በአይኗ መላኩን ብፈልግ ላየው አልቻልኩም ….እቤቱን ከዚህ በፊት በደንብ እደሚያውቅ ሰው ወደፎቅ የሚወስደውን ደረጃ የመቁጠር ያህል  በዝግታ እየረገጠች  ቀስ እያለች ሀንድሪሉን በአንድ እጇ ተደግፋ ወጣች….፡፡
ተራራ የመውጣት ያህል  ደከማት…. ስትደርስ መኝታ ቤቱ በራፍ ላይ ሁለት ወጣት ሴቶች ወገባቸውን በሻርፕ ጥፍንግ አድርገው አስረው በእንባ በመታጠብ እህህህ…. እያሉ በኮሪደሩ ላይ ይሽከረከራሉ…ዝም ብላ ችላ አለቻቸውና መኝታ ቤቱን ከፍታ ገባች…
ደረቷ ላይ ተደፍቶ ሲንሰቀሰቅ ነበር የደረሰችው…እሷ በቃ የለችም አምልጣቸዋለች….አንጀቴን በላኝ…‹‹አይዞህ›› ስለው ከተደፋበት ቀና ብሎ አየኝና
‹‹አይዞህ?ምን አይዞህ አለው…….?ጥላኝ ሄደች እኮ…ጨከነችብኝ..ብዙ ቃል ገብታልኝ ነበር..በቅርብ ቀን ድል ባለ ሰርግ ልንጋባ ቃል ገብታልኝ ነበር…ልጅ እደምተወልድልኝ ቃል ገብታለኝ ነበር..ቢያንስ 2 ዓመት እንደምትኖር ዓምኜ ነበር..ሀኪሞቹም እንደዛ ብለውኝ ነበር…››

‹‹አይዞህ… በቃ ተረጋጋ››

‹‹ተረጋጋ አትበይኝ…አንቺም እኮ ቃል ገብተሸልኝ ነበር…ግን ይሄው እሬሳዋን ከታቀፍኩ በኃላ ልታፌዥብኝ መጣሽ››

‹‹እስቲ ዞር በልልኝ››አለችው፡፡
የልጅቷን መሞት እና  የእሱን ሀዘን በማየቷ ምክንያት  ስምታ ይዛው የመጣችው ስካር በግማሽ ፐርሰንት በረደላት፡፡ 

‹‹ልነሳ….?ምን …በመገነዝ  ልትተባበሪኝ ነው..….?››ተነሳና ስሯ ቆሞ አፈጠጠባት፡፡

ገፍትራው እሱ በተነሳበት ቦታ ተተካችና ተቀመጠች ..እጇን ጭንቅላቷ ላይ አኖረችና አዕምሮዋን በመክፈት  ትኩረቷን ሰብስባ እጇን ግንባሯ ላይ አድርጋ የሚሆነውን መጠበቅ ጀመረቸ… ከ30 ሰክንድ በኃላ የእጇ ቀለሙ መቀየር እና ለሊት መዳወላቡ ላይ ተክሏን ስትቀነጥስ እዳጋጠማት  ሀመራዊ አይነት  ቀለም  ከውስጧ መፍለቅ ጀመረ ..
ከእሷ እጅ የፈለቀው ወደ ልጅቷ ጭንቅላት ሲገባና የእሷም በተመሳሳይ ሲቀየር ታየ…በዚህ አይነት ሁኔታ ለሁለት  ደቂቃ ያህል  ከቆየ በኃላ ጥቁር ጭስ የመሰለ ትነት ከጭንቅላቷ እየበነነ ወደቤቱ ኮርኒስ በመስገምገም በኖ መጥፋት ጀመር…ከዛ ህይወቷ ያለፈና  በድን የነበረችው ልጅ መንቀጥቀጥና መንዘፍዘፍ ጀመረች…ታአምር ተከሰተ…..
ከደቂቃዎች ቆይታ በኃላ  ልክ ከቀናት እንቅልፍ እንደናቃ ሰው አይኖቾን ገለጠችና አካባቢዋን መቃኘት ጀመረች…ፈገግ አለችና ቀና ብላ እንደሀውልት የተገተረውን መላኩን ተመለከተችው..አፉን እደከፈተና እነዛ ብርሀን የሚረጩ አይኖቾን እንደበለጠጣቸው በገረሜታ እያፈራረቀ ሲመለከታት አየችው…

‹‹የእኔ ፍቅር ምንድነው እየሆነ ያለው….?››አለችና በፍፅም ንቃት ከመኝታዋ ተነስታ አልጋው ጠርዝ ላይ ተቀምጠች…..ሶፊያ በጥርጣሬ እያየች‹‹አላወቅኩሽም ይቅርታ….?››ስትል ጠየቀቻት፡፡

‹‹አይ አታውቂኝም..ትንሽ አሞሽ ነበር…››

‹‹አረ ምንም የህመም ስሜት አይሰማኝም…እንደውም እንደዚህ ፍጽም ሰላማዊ የሆነ ስሜት ከተሰማኝ ዓመት አልፏታል ››

‹‹አዎ ትክክል ነሽ..ለማንኛውም እኔ ሀኪምሽ ነኝ..አሁን ስራዬን ስለጨረስኩ ልሂድ››ብላ ከተቀመጠችበት ተነሳችና ፊት ለፊቱ ተገትራ ቆመች…..ምን እንዳዛ እንዳስቆማት አታውቅም…

‹‹አደረግሺው..እንደፎከርሽው አደረግሽው››ብሎ በመፍለቅለቅ ተጠመጠመባት…እንደዛ ሲያደርግ ፍቅረኛዬ ምን ታስብ ይሆን….? ብሎ እንኳን መጨነቅ አልፈለገም….

እሷም እንዳቀፋት ጆሮው ላይ ተለጠፋችና በማንሾካሾክ‹‹አዎ አድርጌዋለሁ…..ዛሬውኑ ወደሀኪም ቤት ውሰዳትና አስመርምራት…ሙሉ በሙሉ መዳኗን ካረጋገጡልህ ያው በተስማማነው መሰረት በሶስት ቀን ውስጥ ቃልህን እንድትተገብር እፈልጋለሁ..የእቤቴ አድራሻ …››አለችና ከለበሰችው ጂንስ ሱሪዬ ኪስ ውስጥ ቢዝነስ ካርዷን አውጥታ የለበሰው ጃኬት ኪስ ውስጥ ከተተችለት…፡፡
በዝግታ ከእቅፉ አወጣትና በመገረም አፍጥጦ ያየት ጀመር….እሷም አይኖቾን ሳትሰብር አፍጥጣ አየችው …ደስታው  በኖ በአንዴ  አመድ ነፋቶበታል…እንደደነዘዘ ባለበት ቆመ፡፡

..‹‹ሰሚራም ምንድነው እየተካሄደ ያለው ….?››ብላ በጥርጣሬ የተለወሰ ጥያቄዋን ስትደረድር እና  እየተካሄደ ስላላው ነገር ይበልጥ ለማወቅ በጥያቄ ሁለቱንም ስታፋጥጥ… ሶፊያ ከቆመችበት ስፍራ እግሮቾን በማነቃነቅ  የተዘጋውን የመኝታ ቤት በራፍ ከፍታ ወጣች…..
ስትመጣ ከነበራት በተሻለ ፍጥነት   ደረጃውን እየተንደረደረች ወርዳ ሳሎኑን ሰንጥቃ  በመውጣት የግቢው የውጭ በራፍ ጋር ስትደርስ ቅልጥ ያለ የእልልታ ድምጽ እቤቱን ሲያደበላልቀው ሰማች……ፈገግ አለች..
‹‹ይህ  የእነዚህ ሰዎች ደስታ እኔን ምን እንዳስከፈለኝ ቢያውቁ እንዲህ እልል አይሉም ነበር…ግን ምንድነው ለመላኩ ብዬው የመጣሁት?አሁን አስቲ ምን ማድረጌ ነው ….?››ስትል እራሷን ታዘበች፡፡በተስማማነው መሰረት በሶስት ቀን ውስጥ ትከፍለኛለህ ማለቷን ማመን አልቻለችም፡ ..በዛ ላይ እኮ የቤቷን አድርሻ ጭምር  ሰጥታዋለች‹‹..እስቲ ይሄ ደስታው ለዛሬ እንኳን ሙሉ ቢሆንለት ምን ነበረበት..….?ገና ለገና እኔ ስቃይ ውስጥ ነኝ ብዬ ሌላውን ሰውም እንዲሰቃይ ማድረግ ነበረብኝ..….?ደግሞ ለሳምንት ዕድሜዬ እንደዚህ ክፉ መሆን ምን የሚሉት ልበ ጠጣርት ነው ….….?››እራሷን በራሷ ገሰፀች
የመኪናዋን ሞተር በማስነሳት ከአካባቢው በፍጥነት ተፈተለከቸ….

     ይቀጥላል

#ክፍል 48,,እንዲለቀቀ (20) ሰው ከስር ያለውን ሊንክ #Subscribe🔔ካረገ ይለቀቃል
https://youtube.com/@Weygud18

#Subscribe እያደረጋቹ ቤተሰብ ስለምትሆኑ እናመሰግናለን #Subscriber
YouTube link👇
https://youtube.com/@Weygud18

መልካም ምሽት ተመኘሁ🙏
🎙ግሩፑን ለማግኘት
              👇👇👇

        @Mtshaf_bicha
        @Mtshaf_bicha
❤️ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
👉አሰተያየት ካላችሁ
📩 @Eyos18     አድርሱን
             📗📒📕📗📒📕
                Join&share
                  @EyosC1
       📚ማንበብ ባህላችን ይሁን📚
┄┉┉✽‌»‌🎶••✿••🎶»‌✽‌┉┉┄
አይችልም››‹‹እማ እኔ እኮ የምታወሪውን ነገር አንድም ቀን ተጠራጥሬሽ አላውቅም…››

‹‹አመሰግናለሁ ልጄ…..….››ጎትታ ግንባሯን ደጋግማ ሳመቻት፡፡

‹‹ልጄ ለአባትሽ መልዕክት ታደርሺልኛለሽ….?››

‹‹አዎ.. ምን ልበልልሽ?››
‹‹ዕድሜዬን ሙሉ እሱን ብቻ ሳፈቅር እንደኖርኩ ንገሪልኝ…አንተ የከፈትከውን ጭኔን ሌላ ሰው እዲከፍተው ፈቅጄ በመሀከላችን የነበረውን ቅዱሱን  ፍቅራችንን ላሳንሰው ስላልፈለኩ እስከዛሬ በስምህ መልኩሼ እየኖርኩ ነው በይልኝ….እንደዛም በማድረጌ ከደስታ ውጭ አንድም ቀን ከፍቶኝ እንደማያውቅ ነግሪልኝ…ደግሞ ቆንጆና ብልህ ልጅ ስለሰጠኸኝ አመሰግናለሁ…መልሼ ለአንተ ስልክልህም ደስ እያለኝ ነው በይልኝ፡፡››

የእናትዬው ንግግር አንጀቷን አላወሰው‹‹…እሺ ያልሺኝን ሁሉ እነግረዋለሁ››አለቻት፡፡

መቼስ እሷ ብቻ ሳትሆን እሱም በእሷ እድሜ ሙሉ መስዋዕት እየከፈለ እንደሆነ እና በወገኖቹ እንደጥፋተኛ ተቆጥሮ  እስራት ላይ እንደሚገኝ ባታውቅም ይሄንን ነግራት ደስታዋን ልታደፈርሰው እና እሷ ከሄደችም በኃላ ያለውን ህይወቷን ወደ ትካዜና ሀዘን ልትቀይረው ስላልፈለገች አሳዛኙኝ የታሪክ ክፍል  ደበቀቻት..፡፡

‹‹ልጄ››እናቷ ጠራቻት፡፡

‹‹ወይ ሀርሜ››

‹‹አይዞሽ አታስቢ ንስርሽን እኔ እንከባከበዋለሁ..ማለቴ  በአንቺ ፋንታ እኔን ይንከባከበኛል››

‹‹እስቲ እናያለን››አለቻት ..አዎ እናቷ እንዳለቸው ቢሆን እሷም ደስ ይላት ነበር..ግን እንደዚህ አይነት ተስፋ ከንስሯ አላየችም….እና አሁን በዚህ ሰዓት  እናቷን ይሆናልም አይሆንምም ልተላት አልደፈረችም፡…..

             ይቀጥላል

#ክፍል 49,,እንዲለቀቀ (20) ሰው ከስር ያለውን ሊንክ #Subscribe🔔ካረገ ይለቀቃል
https://youtube.com/@Weygud18

#Subscribe እያደረጋቹ ቤተሰብ ስለምትሆኑ እናመሰግናለን #Subscriber
YouTube link👇
https://youtube.com/@Weygud18

መልካም ቀን ተመኘሁ🙏
🎙ግሩፑን ለማግኘት
              👇👇👇

        @Mtshaf_bicha
        @Mtshaf_bicha
❤️ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
👉አሰተያየት ካላችሁ
📩 @Eyos18     አድርሱን
             📗📒📕📗📒📕
                Join&share
                  @EyosC1
       📚ማንበብ ባህላችን ይሁን📚
┄┉┉✽‌»‌🎶••✿••🎶»‌✽‌┉┉┄
ሙሉ ጠርሙስ ጎርደን ጅን አዘዙ
‹‹አረ ልባችን ትፈነዳለች››አላት
አልመሰለችለትም …መጠጡ መጥቶም ለተወሰኑ ጊዜ ከዲጄው የሚለቀቀውን ለስለስ ያለ ሙዙቃ በተመስጦ እያዳመጡ እና ከራሳቸው ሀሳብ ጋር እየተብሰለሰሉ ቆዩ…. ሰላሳ የሚሆኑ  ደቂቃዎች በየራሳችን ዝምታ ወስጥ ቆይተዋል..ግን ድንገት ስትባንን መጠጡ ግማሽ ጠርሙስ ተጋምሷል..ደነገጠች ….እሷ የተቀዳላት ብርጭቆ ግማሹን እራሱ አላጋመሰችም ..አጅሬ ላካ እየለጋው ነበር..‹‹ወይ ከእኔ የባሰ መጠጥ የራበው ነው እንዴ የገጠመኝ .….?››ስትል አሰበች፡፡ደግሞ ሲያዩት ገና ብዙ የመጠጣት አቅሙ እንዳለው ያስታውቃል….እንግዲህ ምንም ማድረግ አይቻልም አንዳንድ ሰዎች እንዲህ ናቸው..፡፡ለእሷ እንዲህ መጠጡን መሳቡ ተመችቶታል..ብቻ እራሱን እስከመሳት ደርሶ ሰውነቱን ማዘዝ አያቅተው እንጂ ህሊናው እስኪቆለፍ ድረስ መጠጣቱ አሪፍ ነው ብላ አሰበች…‹‹እበላዋለሁ…ሌላ ተጽዕኖ ወስጥ ሳልከተው  በራሱ ፍላጎት አብሮኝ  እንዲያድር ማደረግ እፈልጋለሁ…እንደማንኛዋም ተራ ሴት ሆኜ ላሸነፈው  ነው የምፈልገው……ሰውኛ ማሸነፍ እንዲሆን …›ስትል እቅድ አወጣች፡

ድንገት ከመሬት ተነስታ‹‹ተጫወት›› አለችው፤

እሱም እንደመባነን አለና ‹‹እሺ …ባይዘወይ ኤርሚያስ እባላለሁ..››አላት

‹‹አሪፍ ስም ነው ..እኔን ሰፊ  በለኝ ››..
‹‹አይገርምም ማን ልበል ሳትይኝ እንዲሁ ከምድር ተነስቼ ኤርሚያስ አባላለሁ በማለት ከበሮ መደለቅ ምን የሚሉት እራስ ወዳድነት ነው..ኤርሚያስ ልባል ሚኪዬስ ለአንቺ ምን ይረባሻል፡፡ግን ያው ትረጂኛላሽ ብዬ አስስባለሁ…በመጀመሪያ እኔ በዚህች አለም ላይ ያለኝን ውክልና ለማሳወቅ ከስሜ መጀመር የግድ ይለኛል..ከስሜ ቀጥሎ ነው  ወደ ሌላ ጫወታ መግባት የምችለው ››

‹‹አረ ትክክል ነህ.. እንደውም እኮ  ገና እንደተገናኘን ነበር ስም መቀያየር የነበረብን ›› 

            ይቀጥላል

#ክፍል 50,,እንዲለቀቀ (10) ሰው ከስር ያለውን ሊንክ #Subscribe🔔ካረገ ይለቀቃል
https://youtube.com/@Weygud18

#Subscribe እያደረጋቹ ቤተሰብ ስለምትሆኑ እናመሰግናለን #Subscriber
YouTube link👇
https://youtube.com/@Weygud18

መልካም ምሽት ተመኘሁ🙏
🎙ግሩፑን ለማግኘት
              👇👇👇

        @Mtshaf_bicha
        @Mtshaf_bicha
❤️ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
👉አሰተያየት ካላችሁ
📩 @Eyos18     አድርሱን
             📗📒📕📗📒📕
                Join&share
                  @EyosC1
       📚ማንበብ ባህላችን ይሁን📚
┄┉┉✽‌»‌🎶••✿••🎶»‌✽‌┉┉┄
📕ተአምራተ_ኬድሮን

#ክፍል_ሃምሳ

#ተከታታይ ልቦለድ

#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ

‹‹ለማንኛውም ልድገምልሽ ኤርምያስ እባላለሁ…ለ15 ዓመት ያህል በማንዴላ ሀገር በሆነችው ደቡቡ አፍሪካ ጀሆንስበርግ ኖሬያለሁ… ወደሀገሬ ከተመለስኩ  ሁለት ዓመት ከግማሽ ሆኖኛል፡፡የ20ዓመት አፍላ ፍንዳታ ሆኜ ሄጄ የ35 ዓመት ሙሉ  ደንዳና ወጣት ሆኜ ተመለስኩ….››
‹‹አሀ ዲያስፖራ ነሀ….?››
‹‹አይ ዲያስፖራ ..!!! ‹ጽድቁ ቀርቶብኝ  በቅጡ በኮነነኝ ›ትላለች እናቴ… ለማንኛውም  እወነቱን ንገረኝ ካልሺኝ … በእነዛ ዓመታት ውስጥ በሰው ሀገር ላይ  ስዳክር ..ሞራሌን ከማንቆሻቆሽ…ሰው ሆኜ መፈጠሬን ከመጠየፍ እና ወጣትነቴ ላይ ጢቢ ጢቢ ከመጫወት ውጭ ምንም ያተረፍኩት ነገር አልነበረም…ብዙ ህልም በልቤ ብዙ ምኞት በውስጤ አጭቄ ነበር የተጓዘኩት …እርባነቢስ ሆኜ ባዶ እጄን በሀገሬ ለመሞት ብቻ ብዬ  ነበር የተመለስኩት …ይገርማል አይደል?
ሰው እንዴት ለመሞት ብሎ ከደብቡ አፍሪካ ድረስ ኪሎሜትሮችን አቆርጦ ይመጣል ትይኝ  ይሆናል..….?ለእኔ ግን ትርጉም ነበረው..››
‹‹ንገረኝ እስኪ ትርጉሙን…››ከሳዕታት ትርኪ ሚርኪ ወሬ እና መዛለል በኃላ ድንገት ምርር ወዳለ የህይወት ታሪክ ሀተታ መግባቱ አስደምሟታል አስደስቷታልም…አሁን እየነገራት  ያለውን ታሪክ እሱ ሳይነግራት እንደተለመደው  ወጭ እየጠበቀት ያለውን ንስሯን እንዲረዳት አድርጋ በዝርዝር ማወቅ ትችላለች..ግን አልፈለገችም …እንዲሁ እየጓጓችና ቀጥሎ ምን እንደሚናገር እየገመተች ቀጥታ ከራሱ አንደበት መስማቱ የሆነ የተለየ ስሜት ስለፈጠረባት ደስ ብሏታል…
ቀጠለ ‹‹በህይወቴ እያለሁ የመኖር ምኞቴ ሰልበው በድን አድርገውኝ …ወጣትነቴን ከንቱ አስቀርተውብኝ የመጨረሻውን ክስረት ማክሰራቸው ሳይበቃቸው …ከሞቴም በኃላ ክብር ስጋዬን  ለሀገራቸው ምድር  ልገብር …?አላደርገውም ፡፡ለዘላለም የባዕድ ሀገር አፈር ሆኜ መቅረት  አልፈለኩም  ..ይህ  መልካም አይደለም…ቢያንስ አገሬ እትብቴን በክብር በወርቃማ አፈሯ ውስጥ ቀብራ ከማንነቷ ጋር እንዳወሀደችው ሁሉ ስሞትም በድኔን በክብር ልትቀበለኝ እና ለዘላለም በጉያዋ ልትሸሽገኝ ይገባል..አዎ እንደዛ ነው መሆን ያለበት..በዛ ላይ እናቴን ለመጨረሻ ጊዜ ማየት እፈልጋለሁ… አያየኋት መሰናበት፤ስሮ በመኖር  እና እሷን መጦር ችዬ ላስደስታት  ባልታደልም… እጇ ላይ ሞቼ አልቅሳ ልትቀብረኝ እና እርሟን ለማውጣት እንድትችል ግን እድሉን ላመቻችላት ይገባል..አዎ ስመጣ እንደዛ ብዬ  እና እንደዛ ወስኜ ነበር …
‹‹ከዛስ….?››
‹‹ከደረስኩ ኋላማ … ቆይ ዛሬ ስል …ቆይ ትንሽ ልሰንብት ስል ..የመኖር ጉጉቴ ቀስ በቀስ ከሞተበት  እያንሰራራ እና እየተቀሰቀሰ መጣ..ምንም አግኝቼ አልነበረም ..ከእናቴ የማገኘው ተንሰፍሳፊ ፍቅር  እና ከጓደኞቼ የማገኘው ማፃናኛ …››
‹‹በጣም አሪፍ ታሪክ ነው ያለህ››
‹‹አዎ መራር የህይወት ገጠመኞች  ለሰሚው ወይም ለፅሀፊው ሳቢ ታሪክ ይወጣቸዋል…››
‹‹ከዛስ እንዴት ሀሳብህምን ሙሉ በሙሉ ልትቀይር ቻልክ….?››
‹‹አሁንም ሙሉ በሙሉ አልተውኩትም…አሁንም  የመሞት እቅዴ በውስጤ አለ…››
‹‹እሺ እንዴት ልታራዝመው ቻልክ….?››ጥያቄውን አስተካከለችለት፡፡
‹‹እንዴት መሰለሽ….ከዛ ከሰው ሀገር  በገንዘብም በመንፈስም ክስርስር ብዬ የመጣሁ ቢሆንም ብዙም ሳልቆይ ሚስኪን የልጅነት ጓደኞቼ  አዋጥተው አሁን የምጠቀምባትን ላዳ ገዝተው ሰጡኝ..በቃ የመሞት ሀሳቤን አራዘምኩት ..ለራሴ ሁለተኛ እድል ሰጠሁት..ቢያንስ ለጊዜው ሰርቼ ስጋዬን የማኖርበትን  ካገኘሁ አንድ ቀን ምን አልባት ሁለተኛውን የህይወት ምኞቴን በሆነ ተአምር ሊሳካልኝ ይችል ይሆናል…ብዬ ተስፋ አደረኩና መጨረሻውን እስከማይ ሁለት ዓመት ተኩል በሀገሬ ኖርኩ..ዘና ብዬ ለማንም ለምንም ሳልጨነቅ…ባሳኘኝ ሰዓት እየሰራሁ ሲያሰኘኝ ደግሞ እየተኛው..የእናቴን ሽሮ እየበላሁ ተስፋዬን በመጠበቅ እንሆ አለሁልሽ››
‹‹ምንድነው ተስፋህ..ማለቴ ይሳከልኛል ብለህ የምትጠብቀው….?››
‹‹የልጅነት ፍቅሬን… ..አንድ ቀን ቀና ብላ ታየኛለች የሚል ተስፋ..አንድ ቀን ከቄስ ትምህርት ቤት ጀምሮ እንደማፋቅራት እና ዕድሜዬን ሙሉ በልቤ ተሸክሜያት ስዞር እንደኖርኩ  ተረድታ በእቅፎ ታስገባኛለች ብዬ ተስፋ  በማድረግ..አንድ ቀን እጄ ትገባለች በሚል ተስፋ…..››

‹‹ወየው ጉዴ!!›አለኝች በውስጧ፡ በዚህ ቅርብ ጊዜ ውስጥ የምትቀርባቸውና የምትመኛቸው ወንዶች ሁሉ እንዴት እንዴት ሆኖና  ምንስ በሚሉት አጋጣሚ   እንደዚህ በፍቅር ስክር ያሉና የታወሩ ሆነው እንደሚገኙ ግልፅ ሊሆንላት አልቻለም...?‹‹ይሄኛውንስ ዛሬ አልምረውም…በፍጽም፡፡››ስትል ፎከረችው፡፡

‹‹ይቅርታ ሙሉ ታሪኩን እንድትነግረኝ እፈልጋለሁ….››

‹‹እየነገርኩሽ እኮ ነው …እየተረተርኩልሽ…..ሆድ ያባውን ብቅል ያወጣዋል አይደል የሚባለው››

‹‹አይ እዚህ አይደለም…እኔ ቤት እንሂድና ተረጋግተን እየጠጣን ታወራልኛለህ….አሁን ሆቴሉም ሊዘጋ መሰለኝ››

‹‹ይቻላል››ይከራከረኛል  ወይም ይቃወመኛል ብላ ነበር የጠበቀችው ..ቀድሟት ተነሳ ..ሂሳብ ከፍላ ተከተለችው …. እየተወለጋገድና እርስ በርስ እየተደጋገፉ ላደው ድረስ ሄድ ..ሹፌሩ ተቀብሏቸው እቤት ድረስ አደረሳቸውና የለሊቱን ግዳጅ ጨረሶ  ተለያቸው.. 
እሷም ዛሬ ለዛውም ከመሸ ያወቀችውን ባለ ላዳ ይዛው  ወደቤቷ ገባች…..

            ይቀጥላል

#ክፍል 51,,እንዲለቀቀ (10) ሰው ከስር ያለውን ሊንክ #Subscribe🔔ካረገ ይለቀቃል
https://youtube.com/@Weygud18

#Subscribe እያደረጋቹ ቤተሰብ ስለምትሆኑ እናመሰግናለን #Subscriber
YouTube link👇
https://youtube.com/@Weygud18

መልካም ምሽት ተመኘሁ🙏
🎙ግሩፑን ለማግኘት
              👇👇👇

        @Mtshaf_bicha
        @Mtshaf_bicha
❤️ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
👉አሰተያየት ካላችሁ
📩 @Eyos18     አድርሱን
             📗📒📕📗📒📕
                Join&share
                  @EyosC1
       📚ማንበብ ባህላችን ይሁን📚
┄┉┉✽‌»‌🎶••✿••🎶»‌✽‌┉┉┄
‹‹ቤተክርስትያን….? ጭራሽ ቤተክርስትያን…በፍጽም… የደረሰብኝ መከራ  ሁሉ በእግዚያብሄር ትዕዛዝና ፍላጎት  ነው የሆነው..እንዲህ የቀጣኝ እሱ ነው…..ፍፅሞ ወደቤቱ አልሄድም..››ብላ ተንገሸገሸች
ምርጫውን ወደራሷ መለስኩት‹‹እሺ የት ልውሰድሽ…….?››

‹‹-መጠጥ ቤት…››

‹‹አልተከራከርኳትም..ነዳሁት….እስከለሊቱ 5 ሰዓት ብትን እስክትል ድረስ  እስክትጠጣ ጠበቅኳት …ከዛ አዝዬ ማለት ይቻላል አቤቷ አስገብቼያት ደስ ብሎኝም ከፍቶኝም ወደቤቴ ገባሁ….ደስ ያለኝ ከስንት አመት በኃላ ከእሷ ጋር ማውራት፤ከእሷ ጋር ጊዜ ማሳለፍ በመቻሌ ነው…የከፋኝ በዚያ አይነት በእሷ ባልሆነ ሀዘን፤ በእሷ ባልሆነ ምሬት ውስጥ በተዘፈቀችበት ሰአት ስለገኘኋት ነው …..

‹‹ከዛስ እንዴት ሆነ….?››ስትል ጠየቀችው.. በታሪኩ ከመመሰጧ የተነሳ ምሽቱን  ሙሉ ጭኖን  የሚበላት  የነበረው  ክፉ አመሏ ራሱ ቀንሶላት ነበር።

            ይቀጥላል

#ክፍል 52,,እንዲለቀቀ 👍(5) ሰው ከስር ያለውን ሊንክ #Subscribe🔔ካረገ ይለቀቃል
https://youtube.com/@Weygud18

#Subscribe እያደረጋቹ ቤተሰብ ስለምትሆኑ እናመሰግናለን #Subscriber
YouTube link👇
https://youtube.com/@Weygud18

መልካም ምሽት ተመኘሁ🙏
🎙ግሩፑን ለማግኘት
              👇👇👇

        @Mtshaf_bicha
        @Mtshaf_bicha
❤️ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
👉አሰተያየት ካላችሁ
📩 @Eyos18     አድርሱን
             📗📒📕📗📒📕
                Join&share
                  @EyosC1
       📚ማንበብ ባህላችን ይሁን📚
┄┉┉✽‌»‌🎶••✿••🎶»‌✽‌┉┉┄
‹‹ኤርሚየስ››
‹‹ኤርሚያስ …እዚህ ጋር ታቆምልኝ..….?››
ዳር ያዝኩና አቆምኩላት…ወረደችና የመኪናዋን የኃላ ኮፈን ከፍታ ምንጣፍ በማውጣት አንድ ጠርሙስ ያልተከፈተ ውስኪ በመያዝ ከመኪናው እርቃ ወደአንድ ዘርፋፋ ቅርንጫፍ ወደተሸከመ ዛፍ ሄደችና ጥላው ባለበት አቅጣጫ ምንጣፍን አንጥፋ እንደቡዲስት መለኩሴ እግሮቾን አነባብራ  በመቀመጥ የጠርሙሱን ክዳኑን ተታግላ ከፈተችና አንዴ በመጎንጨት ወደ ፅሞናዋ ተመለሰች…..
እኔን  ልክ እንደ ግኡዙ  መኪናዋ ነበር የቆጠረችኝ… እስከመፈጠሬም እረስታኛለች…20 ለሚሆኑ ደቂቃዎች  ከመኪናው ሳልወርድ የተለያዩ ኤፍ. ኤም ጣቢያዎችን እየቀያየርኩ ሳረብሻት ለመቆየት ሞከርኩ… ከዛ በላይ ግን አልቻልኩም… መኪናውን ከፍቼ ወጣሁና በዝግታ እርምጃ ወደእሷ በመሄድ አንድ ሜትር ከእሷ ርቄ ከፊትለፊቷ  ሳር የለበሰ ሜዳ ላይ ቁጭ አልኩ……በሁለት ጉንጮቾ እንባዋ ያለምንም ድምጽ ትረጫዋለች….ደነገጥኩ…. ምን እንደምላትም ሊገለፅልኝ አልቻለም፡፡
‹-በህይወትህ መሞት ፈልገህ ግን ደግሞ እንዴት መሞት እንዳለብህ ግራ ገብቶህ ያውቃል….?፡፡››ስትል ጠየቀችኝ 

‹‹ብዙ ጊዜ አዎ…….?››መለስኩላት

‹‹እና እንዴት አደረግክ….?››

‹‹ቆይ ዛሬ…ቆይ ነገ…በገመድ ተንጠልጥዬ ብሞት ይሻላል ወይስ መድሀኒት ልጋት……….?ከፎቅ ላይ እራሴን ልፈጥፍጥ ወይስ የሚበር መኪና ውስጥ እራሴን ወርውሬ ይጨፍልቀኝ….? ብዬ ሳማርጥ በአንዱ መወሰን አቅቶኝ ስዋልል ቆይና ሁለት የምወዳቸው ሰዎች ወደአዕምሮዬ ሲመጡ ደግሞ እስኪ ቢያንስ ለእነሱ ስል  ብዬ  እታገሳለሁ..ከዛ ቀስ በቀስ ያ ስሜት ይጠፋል ወይም ይደበዝዛል…ቢያንስ ለጊዜውም ቢሆን ››
‹‹ለሁለት ሰዎች ስትል….?››


            ይቀጥላል

#ክፍል 53,,እንዲለቀቀ 👍(5) ሰው ከስር ያለውን ሊንክ #Subscribe🔔ካረገ ይለቀቃል
https://youtube.com/@Weygud18

#Subscribe እያደረጋቹ ቤተሰብ ስለምትሆኑ እናመሰግናለን #Subscriber
YouTube link👇
https://youtube.com/@Weygud18

መልካም ቀን ተመኘሁ🙏
🎙ግሩፑን ለማግኘት
              👇👇👇

        @Mtshaf_bicha
        @Mtshaf_bicha
❤️ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
👉አሰተያየት ካላችሁ
📩 @Eyos18     አድርሱን
             📗📒📕📗📒📕
                Join&share
                  @EyosC1
       📚ማንበብ ባህላችን ይሁን📚
┄┉┉✽‌»‌🎶••✿••🎶»‌✽‌┉┉┄
ነቃ ለማለት እዲረዳው  ክንፉን አርገፈገፈ …..የሳሎኑን በር ከፈተችለት… ከሶፋው ላይ ተንሳፎ ጭንቅላቷ ላይ አረፈ…ክንፉን እያማታ ከጭንቅላቷ ላይ ተነስቶ በሩን አልፎ ጭለማ ውስጥ ሰመጠ…..
ወደመኝታ ቤቷ ተመለሰችና  ወደአልጋው ሳይሆን  ወደ  ሻወር ቤት ገባች …

ሻወር ቤት ገብታ ሽንቷን ብቻ ሸንታ አልወጣችም..የሻወሩን ውሀ ከፈተችና ልብሷን አወላልቃ ገባችበት….አዎ በሆነ መንገድ መረጋጋት ፈልጋለች……. ‹‹ምንድነው ያጣሁት ነገር…….?.ከሁለት የተለያዩ  ፍጥሮች መፈጠሬ ስለፍቅር ያለኝን ስሜት አበላሽቶብኛል እንዴ….….?ለምንድነው እኔስ መላኩ  ሰሚራን ባፈቀረበት መጠን ላፈቅር  ማልችለው..….?ለምንድነው ይሄ አልጋዬ ላይ ሆኖ የሚጠብቀኝ ኤርምያስ ሰላምን ባፈቀራት መጠን በዚህ የህይወቴ ረጂም ጊዜ ሁሉ ቢያንስ ለአንድ ጊዜ እንኳን  ማፍቀር ያልቻልኩት….….?››በአዕምሮዋ እያተረማመሱ ያሉ ጥያቄዎች ነበሩ….

ውሃው ከላይ እየተወረወረ ሰውነቷ ላይ እያረፈ ነው..ዝም ብላ ቆማ በሀሳብ ውስጥ እየነሆለለች ነው….አሁን እነሱ ታሪካቸውን ለማንም ሰው ቢናገሩ ሰሚው ሰው ውስጡ በሀዘን ይተረማመሳል..እንባ አውጥቶም ሊያለቅስ እና  በዛም  መጠን ሊያዝንላቸው ይችላል…እሷ ግን ቀናችባቸው እንጂ ልታዝንላቸው አልቻለችም …ለምን በዚህ መጠን የማፍቀር ስሜት ከውስጧ መብቀል አቃተው…….?እንዴት ሰው በህይወት ዘመኑ ቢያንስ አንዴ በፍቅር ፍላፃ ልብ አይሰነጣጠቅም….?እንዴት በእድሜው አንዴ እንኳን በፍቅር እቅፍ አጥቶና ምቾት ነስቶት ሲነፈርቅ አይታይም…….?ለፍቅር መሸነፍ እኮ ድክመት አይደለም ሰዋዊነት እንጂ…..እሷ የወሲብ ረሀብ ያንን ተከትሎ የጭን መብላት አባዜ ብቻ ነው የሚያሰቃያት….ሙላት ያለው የፍቅር   ስሜት ሳታጣጥም ይህችን ምድር ልትለቅ አራት ቀን ቀራት ..!!!አራት ቀን ብቻ…

ይቀጥላል።

አብዛኞቻቹ ወይም ባጠቃላይ ማለት ይቻላል የአገልግሎት ክፍያ እየከፈላቹ አደለም ክፍያውም አንብባቹ ስትጨርሱ👇👇👇

#ክፍል 54,,እንዲለቀቀ 👍(15) ሰው ከስር ያለውን ሊንክ #Subscribe🔔ካረገ ይለቀቃል
https://youtube.com/@Weygud18

#Subscribe እያደረጋቹ ቤተሰብ ስለምትሆኑ እናመሰግናለን #Subscriber
YouTube link👇
https://youtube.com/@Weygud18

መልካም ምሽት ተመኘሁ🙏
🎙ግሩፑን ለማግኘት
              👇👇👇

        @Mtshaf_bicha
        @Mtshaf_bicha
❤️ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
👉አሰተያየት ካላችሁ
📩 @Eyos18     አድርሱን
             📗📒📕📗📒📕
                Join&share
                  @EyosC1
       📚ማንበብ ባህላችን ይሁን📚
┄┉┉✽‌»‌🎶••✿••🎶»‌✽‌┉┉┄
ሳቋ አመለጣት ..ከፊት ለፊቱ ቁጭ አለች……

‹‹ይሄውልህ…››ብላ የውስጧን ልትግረው ስትጀምር ባለ ላዳው ማለት ኤርሚያስ ሆዬ ከመኝታ ቤት ውልቅልቁ የወጣውን ሰውነቱን እየጎተተ ሳሎን ደረሰና ግራ በመጋባትና በድንጋጤ አንዴ እሱን አንዴ እሷን እያየ  ምን ማድረግ እንዳለበት ግራ በመጋባት ሲዋልል እሷንም ንግግሯን እንድታቆርጥ አደረገት ….

     ይቀጥላል።

አብዛኞቻቹ ወይም ባጠቃላይ ማለት ይቻላል የአገልግሎት ክፍያ እየከፈላቹ አደለም ክፍያውም አንብባቹ ስትጨርሱ👇👇👇

#ክፍል 55,,እንዲለቀቀ 👍(15) ሰው ከስር ያለውን ሊንክ #Subscribe🔔ካረገ ይለቀቃል
https://youtube.com/@Weygud18

#Subscribe እያደረጋቹ ቤተሰብ ስለምትሆኑ እናመሰግናለን #Subscriber
YouTube link👇
https://youtube.com/@Weygud18

መልካም ምሽት ተመኘሁ🙏
🎙ግሩፑን ለማግኘት
              👇👇👇

        @Mtshaf_bicha
        @Mtshaf_bicha
❤️ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
👉አሰተያየት ካላችሁ
📩 @Eyos18     አድርሱን
             📗📒📕📗📒📕
                Join&share
                  @EyosC1
       📚ማንበብ ባህላችን ይሁን📚
┄┉┉✽‌»‌🎶••✿••🎶»‌✽‌┉┉┄
‹‹እኔ ግን  አውቄያለሁ››
ሱሪውን ለብሶ ከላይ እራቃኑን እንደሆነ አጠገቡ ያለ ወንበር ላይ ቁጭ አለ‹‹እንዴት ልታውቂ ቻልሽ…..?እንኳን የእሷን  ታሪክ ይቅርና እኔን  ካወቅሽ እራሱ 24 ሰኣት አልሞላውም››
‹‹የፈለኩትን ነገር ማወቅ እችላለሁ…ንስሬ ከረዳኝ የፈለኩትን ነገር….››

‹‹አላምንሽም››

‹‹እሺ ጥቂት ደቅቃ ታገሰኝ ››አልኩና ወዲየው ትኩረቴን ወደንሰሬ በመመለስ ከአዕመሮው ጋር ተቆራኘው…..ለሶስት ደቆቃ ከቆየሁ በኃላ

‹‹እሺ ስማኝ …እንድታምነኝ አንተ ብቻ የምታውቀውን የራስህን ሚስጥር ነግራሀለው….ደቡብ አፍሪካ ለ2 ወር ታስረህ ነበር….ከሶስት ሴቶችና ከእንድ ተካልኝ ከሚባል ልጅ ጋር በደባልነት አንድ  ቤት ውስጥ ትኖሩ ነበር…ከሶስቱ ሴቶች  መካከል  ሁለቱን ሴቶች ታወጣቸው ነበር…..››

‹‹በቃ በቃ…..››

‹‹ያው እንድታምን ብዬ ነው…..››
‹‹አመንኩ እኮ …አደገኛ ጠንቆይ ነሽ….ምክንቱም ይሄንን ታሪኬን ለማንም ተናግሬ አላውቅም ..በተለይ የሁለቱ ሴቶችን ጋር ያለኝን ግንኝነት››

‹‹ምክንያቱም መንታ እህትአማቾች ስለሆኑ ትክክለኛ ስራ እንዳልሰራህ ስለሚሰማህ እና ፀፀት ስላለብህ..››ብላ ጨመረችለት፡፡

‹‹አዎ..ትክክል ነሽ…ግን አሁን ሰላም ምንድነው ችግሯ..ከፍቅረኛዋ ጋር ተጣልታ ነው…..?››

‹‹ፍቅረኛ የላትም….ማለቴ በፊት  ነበራት… ከተለያዩ ግን  አመት አልፏቸዋል…እረስታዋለች››

ፈገግ አለ‹‹ይሄንን በመስማቴ ደስ አለኝ….እሺ ሌላ ታዲያ ምን ሆና ነው…..? ስራ ተበላሽቶባት ነው..?››
‹‹ያለችበትን ችግር ምትገምተው አይደለም..››

‹‹እሺ ንገሪኛ..? ››

‹‹አባቷ ሞቶባት  ነው..››

መጀመሪያ ተደናግጦ ከተቀመጠበት ተነሳ..ከዛ መልሶ ቁጭ አለ..ለደቂቃ ተከዘ

‹‹እስከአሁን ያልሺው ሁሉ ትክክል ነው..ይሄ ግን የማይመስል ነው..አልነገርኩሽም እንዴ አንድ ሰፈር እኮ ነው የምንኖረው ..ዕድራችንም አንድ ነው….ቢያንስ እኔ ባልሰማ እናቴ ሰምታ ትነግረኝ ነበር..በዛ ላይ   እሷን የሀዘን ልብስ ለብሳ አያት ነበር ….››
‹‹አባቷ እንዲቀበሩባት ስለማትፈልግ ..መኝታ ቤቷ ውስጥ እንዳይበሰብሱ በማድረግ  ድብቃቸዋለች››

‹‹እንዴ!!!! ታዲያ ዝም ትያለሽ እንዴ....?እራሷን ብታጠፋስ....?ይሄንን ሁሉ ቀን የአባቷን እሬሳ ታቅፋ ለብቻዋ ስታድር ጄኒ ቢያጠናግራስ .. ..?እንዴ በቃ ብታብድስ…..?››ይሄን ሁሉ ሚናገረው በጥድፊያ ልብሱን እየለበሰና በተመሳሳይ ጊዜ ወደውጭ እየተንደረደረ ነው….እሷም ከኃላው  ኩስ ኩስ እያለች   ሚለውን ታዳምጣለች…

‹‹እውነት ከሆነ በጣም ነው የማዝንብሽ…..እንዳወቅሽ ልትነግሪኝ ይገባ ነበር…አንድም ሰከንድ ማባከን አልነበረብሽም ..አባቷን እንዴት እንደነፍሷ እንደምትወዳቸው ብታውቂ እንደዚህ ቸልተኛ አትሆኚም ነበር….››ወቀሳውን ሳያቆርጥ ከግቢው ወጥቶ በእግሩ ሊነካ ሲል…

‹‹ና በመኪና ላድርስህ….››ስትለው በደመነፍስ ተከተላትና ማጉረምረሙን ሳያቆርጥ  መኪና ውስጥ ገባ….ሞተሩን እስነስታ መንዳት ጀመረች..ፀጉሩን ይነጫል ….ጨንቅላቱን ይቀጠቅጣል..ከንፈሩን ይነክሳል
‹‹እንዲህ ከሆንክማ እንዴት ልንረዳት እንችላልን....?››አለችውት የእሱም ከቁጥጥር ውጭ መሆን አሳስቧት

‹‹እንዴት ልሁን ታዲያ …..?ሳለምዬ የአባቷን ሬሳ ታቅፋ አምስት ቀን ብቻዋን ባዶ ዝግ ቤት ውስጥ አድራለች እያልሺኝ እኮ ነው…››

‹‹እኮ አሁን ካለችበት ሁኔታ ይልቅ ወደፊት የሚከሰተው ነገር ይበልጥ ይጎዳታል… ስለዚህ እንዴት ልንረዳ እንደምንችል ለማሰብ ያንተ መረጋጋት ያስፈልጋል እያልኩህ ነው››

‹‹እሺ ንጂው…በእግዚያብሄር ፍጠኚ …ደግሞ ንስርሽ ከኃላ እየተከተለን ነው››

‹‹አዎ እሱ በጣም ያግዘናል…››

‹‹በፈጠረሽ …ምንም ነገር እንድትሆንብኝ እልፈልግም›››

‹‹አይዞህ…. ምንም አትሆንብህም…››

ከ25 ደቂቃ በኃላ ሳሪስ ደረሱ ..መኪናውን አቁመው ወደበራፍ  በመከተታል ተንደርደረው ደረሱ... ንስሯ ቀድሞ ግቢው ውስጥ ገባ..መጥሪያውን ተጫኑ..ደጋግመው  ተጫኑ…. እጃችን እስኪዝል በየተራ አንኳኩ ..ከውስጥ ከፋች ሊመጣ አልቻለም..

‹‹ትግስቴ አልቆል…  የግንቡን አጥር ዘለዬ  ልገባ ነው….››አላት በጭንቀት 

‹‹ግንቡ ላይ የተሰካውን የጠርሙስ ስብርባሪ እንዴት አድርገህ ታልፈዋለህ..?››

‹‹የራሱ ጉዳይ…የቆራረጠኝን ያህል ይቁረጠኝ… ››

‹‹ቆይ የተሻለ ዘዴ አለኝ ››አለችው
‹‹ምንድነው....?››

ንስሯን ጠራችው … ከገባበት ግቢ እየተመዝገዘገ መጣና  የፈለገችውን ሳትነግረው በመረዳት የለበሰችውን ልብስ አንገቷ አካባቢ በመንቁሯ ይዞ እያሽከረከረ ወደአየር ላይ ይዞት በመውጣት አጥሩን አሻግሮ ጊቤው ውስጥ ወለል ላይ አሳረፈት…  ከውስጥ የተቀረቀረውን በራፍ  ከፈተችለት…ኤርምያስ ተንደርድሮ ገባ..

‹‹ምን አይነት ተአምር ነው....?ምንድነሽ አንቺ..?›› እያለ ገፍትሯት ወደሳሎን ሮጠ… ሊያንኳኳ ሲሞክር ብርግድ ብሎ ተከፈተለት..ተከትላው ገባች..ወደየት እንደሚሄድ ግራ ገብቶት ሲደነጋገር ቀደመችውና ወደመኝታ ቤቱ አመራች..ምክንያቱም ቅድም ንስሯ በምናብ  እቤቱን በደንብ ስላስቃኛት ስለነበር  ታውቀዋለች..፡፡

መኝታ ቤት ሲገቡ …ሰላም ወለል ላይ ተዘርራ ግንባሯን ግዙፉ ፍሪጅ ላይ እስደግፋ በአንድ  እጇ የመጠጥ ጠርሙስ ጨብጣ በሌላ እጇ  የተለኮሰ ሲጋራ  ወደ ከንፈሯ በመላክ ወደውስጥ እየመጠጠች  ጭሱን  ወደውጭ እያትጎለጎለች  ትታያለች  …ከጎኖ 10 ሜትር የሚሆን የተጠቀለለ ሰማያዊ ሲባጎ ገመድ ይታያል….. ኤርምያስ ከእሷ ቀድሞ እሷንም ተራምዶ ወደፍሪጁ ሄደና ውስጡ ያለውን አየ…….

ወደኬድሮን በመዞር  ‹‹…እውነትሽን ነው…..››በማለት ከወገቡ ሽብርክ ብሎ ሰላም ጎን ወላሉ ላይ ተዘረፈጠ..እሷ በቃ ትንኝም በአካባቢዋ ያለ አልመሰላትም.. ፍጽም ደንዝዛለች…ጭርሱኑ ጠፍታለች…..


     ይቀጥላል።

አብዛኞቻቹ ወይም ባጠቃላይ ማለት ይቻላል የአገልግሎት ክፍያ እየከፈላቹ አደለም ክፍያውም አንብባቹ ስትጨርሱ👇👇👇

#ክፍል 56,,እንዲለቀቀ 👍(20) ሰው ከስር ያለውን ሊንክ #Subscribe🔔ካረገ ይለቀቃል
https://youtube.com/@Weygud18

#Subscribe እያደረጋቹ ቤተሰብ ስለምትሆኑ እናመሰግናለን #Subscriber
YouTube link👇
https://youtube.com/@Weygud18

መልካም ምሽት ተመኘሁ🙏
🎙ግሩፑን ለማግኘት
              👇👇👇

        @Mtshaf_bicha
        @Mtshaf_bicha
❤️ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
👉አሰተያየት ካላችሁ
📩 @Eyos18     አድርሱን
             📗📒📕📗📒📕
                Join&share
                  @EyosC1
       📚ማንበብ ባህላችን ይሁን📚
┄┉┉✽‌»‌🎶••✿••🎶»‌✽‌┉┉┄
‹‹በቃ አልቅሰሽ ቅበሪኝ….ከዛ በኃላ ሞተ የእያንዳንዱ ሰው ዕጣ ፋንታ መሆኑን አምነሽ ተቀበይና ወደ ህይወትሽ ተመለሺ…የራስሺኝ ሰው ፈልገሽ ኑሮሽን  ኑሪ….የእኔ በድን ታቅፈሽ እዚህ ቤት ባሳለፍሽው ስድስት ቀናት ውስጥ ስራ ላይ ብትሆኚ ኖሮ ሰንት ነፍስ  እንደምታታርፊ አስበሽዋል….… ?ስንት ያንቺን ክትትል የሚፈልጉ ህመምተኞችን እርግፍ አድረግሽ በመተውሽ  በያሉበት ምን ያህል እየተሰቃዩ እንደሆኑ ታውቂያለሽ….…?ያባትሽን መንፈስ ለዘላለም ለማስደሰት እውነታውን ተቀብለሽ  ፈገግ በይ ..በእኔ ስም የአዛውንቶችን ጤንነት ተንከባከቢ…እኔን እያሰብሽ ሞያሽን በጥንቃቄ እና በታማኝነት ስሪ..እያንዳንዱ ሰው ባንቺ እጅ ታከሞ በመዳኑ ተደስቶ ፈገግ ሲል  እኔም ባለሁበት  ፈገግ እንዳልኩ በማሰብ ውስጥሽ ሀሴት ታድርግ….›.

‹‹አዎ አባ እውነትህን ነው..እንዳልከው አደርጋለሁ››

‹‹ስለዚህ ተስማምተናል››

‹‹አዎ አባ ..ተስማምተናል››

‹‹በቃ ደህና ሁኚ ልሄድ ነው

‹‹አባ ከመሄድህ በፊት ››

‹‹እሺ ምንድነው…?››

‹‹ግን ገነት ነው ምትገባው አይደል…?››

‹‹አይ ልጄ..መች ሄድኩና አውቀዋለሁ ..ግን ምንም አይት ፍራቻ እየተሰማኝ አይደለም….እረፍትና እፎይታ ነው ዙሪያዬን የከበበኝ….የሚታየኝ  አንፀባራቂ ብርሀን እንጂ ፅልመት አይደለም….እና ፈጥኜ የመሄድ ፍላጎት ነው ያለኝ…ባከሽ ልጄ እንድዘገይ አታድርጊኝ..››

‹‹እሺ አባ ..አንድ የመጨረሻ ጥያቄ››

‹‹ምን ልጄ…?››

‹‹እማዬን ታገኛታለህ…?››

‹‹አዎ ልጄ ተስፍ አደርጋለሁ..በጣም መቸኮሌ አንድም ለዛ ይመስለኛል››

‹‹እንደምወዳትና በጣምም እንደናፈቀቺኝ ንገርልኝ››

‹‹እሺ ነገርልሻለሁ››
ደግሞ ቀኔ ደርሶ ወደእናንተ  ስመጣ ከእናንተ ጋር አብሬያችሁ መኖር ነው የምፈልገው››

‹‹እሺ ልጄ  እንዳልሽ…ደህና ሁኚልኝ…››

‹‹እሺ አባ ደህና ሁን››

     ይቀጥላል።

#ክፍል 57,,እንዲለቀቀ 👍(20) ሰው ከስር ያለውን ሊንክ #Subscribe🔔ካረገ ይለቀቃል
https://youtube.com/@Weygud18

#Subscribe እያደረጋቹ ቤተሰብ ስለምትሆኑ እናመሰግናለን #Subscriber
YouTube link👇
https://youtube.com/@Weygud18

መልካም ምሽት ተመኘሁ🙏
🎙ግሩፑን ለማግኘት
              👇👇👇

        @Mtshaf_bicha
        @Mtshaf_bicha
❤️ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
👉አሰተያየት ካላችሁ
📩 @Eyos18     አድርሱን
             📗📒📕📗📒📕
                Join&share
                  @EyosC1
       📚ማንበብ ባህላችን ይሁን📚
┄┉┉✽‌»‌🎶••✿••🎶»‌✽‌┉┉┄
ግን ክፋቱ በፈለግናት  ጊዜ ስለምናገኛት…በጣራናት ጊዜ ሮጣ ስራችን ስለምትገኝ ዋጋዋን ብዙም አናውቀው…. እንደድንገት ስትነጠለን  እና ከእጃችን ተንሸራታ ስናጣት ግን  አንድ ሰው ብቻ እንዳልነበረች ይገለጽልናል…መላ ዓለም እሷን እንደማይተካልን  ትምህርት እናገኛለን…ግን ትምህርት ቀድሞ ያጣኸው ነገር ወደፊት ዞሮ መጥቶ እንድታስተካክለው እድሉን ካላገኘህ ጥቅም የለውም..በደንብ ስትፀፀት እድትኖር ብቻ ነው የሚያግዝህ፡፡

ውሃም በቀላሉ ነው የምናገኘው..እኛ እራሱ በዋናነት የተሰራነው ከውሀ ነው ..ምድርም ሶስት እጆ ውሀ ነው….በቀላሉ ብቻ ሳይሆነ በርካሽም እናገኘዋለን.. ሰውነታችን ከየትኛውም መጠጥ በተሻለ በውሀ ይረካል…በውሃ ጤነኝነት ይሰማዋል…የውስጥ መጠማታችንን ብቻ ሳይሆን በአካልም መዛላችንን በውሀ ነው የምናክመው….ሰውነታንን የምንታጠበው የቆሸሸ ሰውነታችንን ለማጽዳት ብቻ አይደለም ውኃው በሰውነታችን ላይ ሲያርፍ መነፍስን የማረጋጋት እና የአዕምሮ ውጥረትን የማከም ኃይል ስላለው ነው…ግን ‹‹ወይ ስታጠብ ቀለል ይለኛል›› በማለት ያገኘነውን ጥቅም እናቃልለዋለን እንጂ ውሀ መድሀኒት ነው ብለን ዕውቅና መስጠት አንፈልግም ..ወሃ የደም ግፊት መድሀኒት ነው..ውሀ የኩላሊት መድሀኒት ነው…ውሃ የራስ ምታት መድሀኒት ነው…..ወሃ የበሽታዎች ሁሉ ፈውስ ነው…
‹‹የእኔ ውሃ ግን  አንቺ ነበርሽ…››አሏት እዝን እንዳሉ፡፡
‹‹ማለት……….?››አለቻቸው አሳዝነዋት፡፡
‹‹አዎ እኔ ጡረታ እስክወጣ ድረስ በዚህች ሀገር ላይ በጣም ስኬታማ ከሆኑ ጥቂት ሰዎች መካከል አንድ  ነኝ ብዬ አስብና እመፃደቅ ነበር….አምስት ስድስት ዲግሪዎች ስላሉኝ አንቱ የምባል ፕሮፌሰር ስለሆንኩ በቃ እታበይ ነበር….ልክ ጡረታ ስወጣ ግን ግማሽ ህይወት ብቻ ስኖር እንደነበር ተገለጽለኝ..እንደው ወደኃላ ተመልሶ የኖሩትን ህይወት ማስተካከል ቢቻል ካሉኝ ዲግሪዎች መካከል አንድን ብቻ አስቀርቼ ሌሎቹን በልጆች እና የልጅ ልጆች መቀየር ብችል ደስ ይለኝ ነበር..ከዛሬ 40 አመት በፊት አግብቼ ዛሬ የ35 ዓመት ልጅ እና የአምስት አመት የልጅ ልጅ ኖሮኝ ቢሆን ኖሮ በጣም ስኬታማ እና ሙሉ እሆን ነበር..ይሄን ቁጭቴን ባንቺ ነበር እየተፅናናው ለመኖር እውተረተር የነበረው…አሁን ግን….››
‹‹እንዲህ እማ አይዘኑ››
‹‹ተይኝ ልዘን…እነዛ ሁሉ ያገኘዋቸው ግኝቶች …እነዛ ሁሉ የተሸለምኮቸው ሽልማቶች እኔ ካለፍኩ በኃላ ማን ይረከባቸዋል..ማን ነው ሊኮራባቸው የሚችል የእኔ ሰው  ……….?
‹‹አሁን ወደኃላ ተመልሰው አድሉን ቢያገኙ እኮ መልሰው ተመሳሳዩን ነው የሚያደርጉት››
‹‹በፍጽም አላደርገውም..ህይወት ሚዛን መጠበቅ አላባት…እድሜሽን ሙሉ ገንዘብ ለማካበት ሰትባክኚ ቆይተሽ ካረጀሽ እና ጥርስሽ ከረገፈ በኃላ ልዝናና ብትይ አያምርብሽም… ደስታ ሚያመነጨው የሰውነትሽ ዕጢም እንዘይሙን ማምረት ስለሚያቆም አትቺይም….ወንደላጤ ሆነሽ ስትንዘላዘይ ኖረሽ በእኔ ዕድሜ ላግባ ብትይ እንዴት ተደርጎ..እንደው ሚስትዬዋ ተገኝታ ማግባት ቢቻል እንኳን እንዴት መውለድ ይቻላል..…….?ቢወለድ እራሱ የማያሳድጉትን ልጅ  እንዴት ….?ሁሉ ነገር በጊዜው ነው የሚያምረው››
‹‹እና እንዴት መሆን አለበት ይላሉ…….?››ጠየቀቻቸው
‹‹የተወሰነ መማር..የተወሰነ ገንዘብ መስራት… የተወሰን ቁጥር ያለው ቤተሰብ መመስረት…በቃ ከሁሉም የሚያስፈልገውን እና የምትጠቀሚበትን ያህል መውሰድ ነው…አየሽ አኔ አሁን ተማርኩ ከምላቸው ትምህርቶች መካከል ሁለቱን ዲግሪዎች ለአንድ ሰምንት እንኳን አልሰራሁባቸውም…እንዲሁ ለጉራ ካልሆነ በስተቀር  ያን ያህል ፋይዳ አልነበራቸውም …
በልተው እንደጨረሱ እጇን ታጥባ  እሳቸው ቢራቸውን እየጠጡ እሷ ደግሞ ወኃዋን ይዛ ወሬውን ቀጠሉ
‹‹እቤቱን እንግዲህ  ሰጥቼዎታለሁ…..››
‹‹አይ እንደዛማ አይሆንም ….እኔ እኮ ለራሴ የሚበቃ የጡረታ ብር አለኝ..ተከራይቼ ሌላ ቦታ እኖራለሁ..ቤቱ የሚገባወ ለዘመዶችሽ ነው..››
‹‹አይ ይሄ ቤት የሚገባው ለእናቴ ነበር..ግን እናቴ ከተወለደችበት አካባቢ ንቅንቅ ማለት አለትፈልግም….››
‹‹እንደዛ ከሆነ ይሸጥና ብሩን ይጠቀሙበታ››
‹‹አይዞት ለእሷ አያስቡ …በቂ የሆነ ብር ሰጣታለሁ..ይሄ ቤት ግን የሚሸጥ አይደለም…እሺ ጣሪያና ግድግዳው መሸጥ ቀላል ነው…እነዚህ ግቢውን የሞሉትን ዛፎች በስንት ብር ተምኜ ልሽጣቸው…?እነዚህ ዛፎቹን የወረሯቸውን በሺ የሚቆጠሩ ወፎች ስንት ስንት ብር ያወጣሉ...?ዝንጀሮዬን ስንት ልሽጠው..…?ጉሬዛዬንስ….?አዩ አንዳንድ ነገሮች ከሚሰጡት ጥቅም አንፃር ብቻ ሳይሆን ካለቸው ትርጉም  በመነሳት ዋጋ ሊወጣላቸው አይቻልም….አሁን ለአንድ ሀብታም ብሸጠው እኚ አሁን የጠቀስኩሎትን ሁሉ አንድ ሰምንት የሚያቆያቸው ይመስሎታል….?.ዛፎቹን ጨፍጭፎ መሬቱን ነፃ በማድረግ ፎቅ ነው ሚገነባበት…ወፎችስ እድሜ ለክንፋቸው በስደት  በመሸሽ  ነፍሳቸውን ለማቆት ይሞክራሉ..፤ሎሎቹስ….?

‹‹እሱስ ከባድ ነው››
‹‹ስለዚህ ቤቱ አይሸጥምም… ለሌላ ዘመድም ቢሆን ተላልፎ አይሰጥም…ይሄ ቦታ የሚገባው ለእርሷ ብቻ ነው..የእያንዳንዶን ዕጽዋት ሚስጥር የሚያውቁትና የሚረዱት እርሶ  ኖት… ስለዚህ የእርሶ ነው››
ፈገግ አሉ..
‹‹ምነው .. …….?ተሳሳትኩ እንዴ..…….?››አለቻቸው ፈገግታቸው የምፀት ስለነበረ ገርሞት
‹‹ስንት ዓመት ልኖር ብለሽ..…….?በተለይ አንቺ በሌለሽበት..ሁለት አመት ሶስት አመት..ከዛስ ያው የፈራሽው  መድረሱ አይቀርም..እነዚህ ሁሉ የለፋንባቸው ነገሮች አጥፊ እጅ መግባታቸው እና መውደማቸው አይቀሬ ነው…››
‹‹ስለዚህ አንድ ነገር እናድርጋ››
‹‹ምን…….?››
ከመቀመጫዋ ተነሳች..ንስሯ ለማድረግ የፈለገችውን ቀድሞ ገብቶታል ፤ ካለበት ዛፍ ላቆ ልክ ትሪኢት እደሚያሳይ የአየር ኃይል የጦር ጄት መገለባበጥ ጀመረ… እንዲህ የሚያደረግው ሲደሰት ነው…በስንት ቀኑ ፈታ አለ….. 
ወደእሳቸው ቀረበች… ግራ ገብቷቸው በዝምታ ያዩታል…. ከጀረባዋ ቆማ  ፀሎት እንደሚያደሰርስ   የፕሮቴስታንን ፓስተር ሁለት እጇን በጭንቅላታቸው ላይ ጫነችና አይኖቾን ጨፈነች…በፍጽም መመሰጥ ውስጥ ገባች….ቀስ እያለ ሰውነቷ ሲግል ይታወቃታል..አዎ ከልቧ ጀምሮ ኃይል እየተሰበሰብ በደምስሯ በመራወጥ ወደ እጆቾ እየፈሰሰ ነው…ከዛ ወደ ፕሮፌሰሩ ጭንቅላት መተላለፍ  ጀመረ…አይኖን የጨፈነች ቢሆንም እየሆነ ያለው ነገር ሁሉ ይታያታል… ኃይል የሞላው ሀመራዊ ቀለም  ከፕሮፌሰሩ ጭንቅላት አንስቶ ወደ አንገታቸው..ከዛም  ትከሻቸው እያለ ወደመላ ሰውነታቸው ተሰራጨ… መንዘፍዘፍ ጀመሩ….ኦ.. ሽበት የወረረው ነጭ ፀጉራቸው...ከግንባራቸው እየተነሳ ወደ መሬት ይረግፍ ጀመር…በዛው ቅፀበት ሌላ ደማቅ ጥቁር ሉጫ ፀጉር ከእያንዳንዱ የራስ ቅል ቀዳዳቸው በመብቀል ወደ ውጭ በመውጣት ጭንቅላታቸውን ሞላው…

ይቀጥላል
#ክፍል 58,,እንዲለቀቀ 👍(20) ሰው ከስር ያለውን ሊንክ #Subscribe🔔ካረገ ይለቀቃል
https://youtube.com/@Weygud18

#Subscribe እያደረጋቹ ቤተሰብ ስለምትሆኑ እናመሰግናለን #Subscriber
YouTube link👇
https://youtube.com/@Weygud18

መልካም ሰንበት ተመኘሁ🙏
የሆነው…›› ስትል እራሷን ጠየቀች፡ለመሄጃ 3 ደቂቃ ቀረው….ንስሩ ከነበረበት ጉቶ ጥቅልል ብሎ በመንሸራተት  መሬት ላይ ተዘረረ..እናቷም እሷም በደቂቃ ውስጥ ስሩ ደረሱ..አገላበጡት…ከአይኖቹ ደም እየፈሰሰ ነው…‹‹ወይኔ እማ ቅጠሉ….. ቅጠሉ ነው..መርዝ ነው የተጠቀመው..እማ ምን እናድርግ…?››የማሰቢያ ጊዜ ሳያገኙ ግቢያችን በሰማያዊ ብርሀን ተሞላ…ቀና ስትል በሰማይ ላይ ዲስክ መሳይ መንኮራኩር ብርሀን እየረጨች ሰማየ ሰማያትን በመሰንጠቅ እነሱ  ወዳሉበት አቅጣጫ እየወረደች ነው….መጡ ማለት ነው…መጡ መሰለኝ….ወይኔ ንስሬ….

  ተፈፀመ

#በአዲስ ታሪክ እንመለሳል‼️ ከተመቻችሁ 👍👍

ከስር ያለውን ሊንክ #Subscribe🔔ካረገ ይለቀቃል
https://youtube.com/@Weygud18

#Subscribe እያደረጋቹ ቤተሰብ ስለምትሆኑ እናመሰግናለን #Subscriber
YouTube link👇
https://youtube.com/@Weygud18

መልካም ምሽት ተመኘሁ🙏

🎙ግሩፑን ለማግኘት
              👇👇👇

        @Mtshaf_bicha
        @Mtshaf_bicha
❤️ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
👉አሰተያየት ካላችሁ
📩 @Eyos18     አድርሱን
             📗📒📕📗📒📕
                Join&share
                  @EyosC1
       📚ማንበብ ባህላችን ይሁን📚
┄┉┉✽‌»‌🎶••✿••🎶»‌✽‌┉┉┄