ፒያሳ መሃሙድ ጋ ጠብቂኝ
183K subscribers
279 photos
1 video
16 files
199 links
እዚህ Channel ላይ ያስተምራሉ ያዝናናሉ ብለን የምናስባቸውን
🎯ተከታታይ ልቦለድ
🎯ግጥም
🎯ወግ
🎯ፍልስፍና
🎯ምክር
🎯መነባንብ

#ማንኛውም አይነት ፅሁፎች📕 ከፈለጉ ይቀላቀሉን
የተለያዩ PDF መፅሐፍት ከፈለጉ @Eyosibooks
አስተያየት ካሎት👇👇
☎️• 0922788490

📩@Eyos18
Download Telegram
መልካም ግዜ ተመኘሁ🙏
🎙ግሩፑን ለማግኘት
              👇👇👇

        @Mtshaf_bicha
        @Mtshaf_bicha
❤️ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
👉አሰተያየት ካላችሁ
📩 @Eyos18     አድርሱን
             📗📒📕📗📒📕
                Join&share
                  @EyosC1
       📚ማንበብ ባህላችን ይሁን📚
┄┉┉✽‌»‌🎶••✿••🎶»‌✽‌┉┉┄
እሷም በመፍለቅለቅ እና ስጦታህን ከልቧ በደስታ  በመቀበል‹‹የእኔ ውድ….እዚህ ሰፍራ ከንተ ጋር አንድ ሳምንት እንኳን መኖር ዘላለም የመኖር ያህል ጣዕም ይሰጠኛል.. አፈቅርሀለው››ትልሀለች
‹‹ካፈቀርኝማ አግቢኝ››ትላታለህ
‹‹እንዲህ አድረገህልኝማ እንዴት እንቢ ልልህ እችላለሁ…..?ዛሬውኑ አገባሀለሀ…እዚህም ደሴት ላይ ምታምር ልጅ  ወልድልሀለሁ… ስሟንም ዘሀራ ትላታለህ  ..ትርጉሙም አበባ ማለት ነው››ትልህና ያልጠበቅከውን የምስራች ነግራህ ታስፈነድቅሀለች፡፡አንተም በሰማሀው ነገር   ሰክረህ ጮኸህ ስትጠመጠምባት‹‹..አረ አነቅከኝ …ምነካህ  …››ብላ ከጎንህ የተኛችው የእውነቷ አለም ሰሚራ ቀስቅሳ ነው ከእንቅልፍህም ከህልምህም ያፋታችህ…
ከተዘረፈጠበት ወለል..ዝልፍልፍ እንዳለ እየተጎተተ ተነሳና ሶፋው ላይ ተቀመጠ..ድክምክ ባለ እና እጅ የሰጠ በሚመስል  የተሸነፈ ድምጽ‹‹ይህንን እኮ ለሰሚራዬ እንኳን እ
አልነገርኳትም… ለብቻዬ አልሜ በውስጤ ብቻ ቀብሬ አስቀርቼው የነበረ  ፍቺውን በማብሰልሰል ላይ የነበርኩት  ጣፍጭ ህልሜ ነበር….እንዴት ልታውቂ ቻልሽ?››

‹‹ዋናው ማወቄ ነው…..አሁን እንዳድንልህ ትፈልጋለህ..?››

‹‹በጣም…አትቺይም እንጂ ከቻልሽ በጣም እድታድኚልኝ እፈልጋለሁ….››

‹‹ካዳንኩልህ ምን ታደርግልኛለህ…..?››መልሳ ወደ መነሻ ጥያቄዋ 

‹‹ህይወቴንም ከፈለግሽ..አንገቴን ቀንጥሼ ለመስዋዕትነት በሰሐን እንዲቀርብልሽ አደርጋለሁ  ››

‹‹ጥሩ ስጦታ ነው…..ግን አንገትህን አልፈልግም››

‹‹እሺ ሙሉ ንብረቴን ምንም ቤሳ ቤስቲ ሳትቀር ሰጥሻላሁ››

‹‹እሱንም አልፈልግም….እኔ በንብረት የምደሰት አይነት ሰው አይደለሁም››

‹‹እሺ ምን ትፈልጊያለሽ..?››

‹‹ሰሚራን  ከዳነች በኃላ ትተዋታለህ..ትተዋት እና እኔን ታገባለህ››

‹‹ዝም አለ…በቃ ዝም …..በድን የሆነ የሚጮህ ዝምታ….ድምፅ ያለው ዝምታ…..››

‹‹እ ምን አልከኝ..?››አለችው ዝምታው በውስጧ የፈጠረውን  ስቃይ መቋቋም ሲያቅታት ልትረብሸው ፈልጋ…

ይቀጥላል

#ክፍል 45,,እንዲለቀቀ (15) ሰው ከስር ያለውን ሊንክ #Subscribe🔔ካረገ ይለቀቃል
https://youtube.com/@Weygud18

#Subscribe እያደረጋቹ ቤተሰብ ስለምትሆኑ እናመሰግናለን #Subscriber
YouTube link👇
https://youtube.com/@Weygud18

መልካም ምሽት ተመኘሁ🙏
🎙ግሩፑን ለማግኘት
              👇👇👇

        @Mtshaf_bicha
        @Mtshaf_bicha
❤️ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
👉አሰተያየት ካላችሁ
📩 @Eyos18     አድርሱን
             📗📒📕📗📒📕
                Join&share
                  @EyosC1
       📚ማንበብ ባህላችን ይሁን📚
┄┉┉✽‌»‌🎶••✿••🎶»‌✽‌┉┉┄
‹‹እንዴ ታዲያ እንዲህ ምን ዝልፍልፍ አደረገህ..….?ሄጄ ቀንጥሼ ልምጣና የመልስ ጉዞችንን እንቀጥላ.››
አዕምሮዋ ላይ መልዕክት አስቀመጠላት..‹‹ልክ ከለሊቱ ስድስት  ሰዓት ላይ ነው መቀንጠስ ምትችይው….›››

ሞባይሏን አወጣችና አብርታ ሰዓቷን አየች..5፡20 ይላል
‹‹እና ገና 40 ደቂቃ መጠበቅ አለብን….?››

‹‹ የግድ ነው››

‹‹በቃ እንጠብቃለን…አንተ ግን  ምነው እንዲህ አዘንክ ደስ አለለህም….….?››

‹‹መዳኒቱን ጥለን እንሂድ››አለት..ያልጠበቀችው ምክረ-ሀሳብ ነው

‹‹እንዴ ለምን….? እዚህ ድረስ በዚህ ለሊት የለፋነው ለመድሀኒቱ አይደል እንዴ….?  ››

‹‹አዎ  ቢሆንም ጥለነው እንሂድ››

‹‹እንዴ ምን ነካህ .. ….?በዚህ አይነት ሁኔታ እስከዛሬ ብዙ ሰዎች አድነናል…አይደለም ከኢትዬጵያ ሱዳን ኤደን ባህረሰላጤ.. ኢራቅ ድረስ እኮ ሰውን ለማዳን የሚሆን መድሀኒት ፍለጋ ሄደን በስንት ልፋትና ጥረት አግኝተን ብዙ ሰው አድነን እናውቃለን..መድሀኒትን ያለበት ቦታ በእንደዚህ ሁኔታ ቀርበን ግን አንድም ቀን ትተነው እንመለስ ብለሀኝ አታውቅም››

‹‹ይሄ የተለየ ስለሆነ ነው››

‹‹ምንድነው የተለየ..….? ልጅቷን አያድናትም….?››

‹‹ያለምንም ጥርጥር ያድናታል…. ››

‹‹እና ታዲያ..….?ገባኝ ልጅቷን ከዳንኳት በኃላ ባሏን ስለምወስድባት አሳዝናህ ወይም እኔ ያልሆነ ነገረ እንዳልሰራ
ለመካላከል ነው አይደል..….?››

‹‹አይደለም….….?ይሄ ተክል የአባትሽ ዘመዶች በምድር ላይ የበተኑት ተክል ነው…ይሄንን ያየሽውን ተክል ማንም ሰው በዓይኑ ማየት አይችልም..››

‹‹እኔ እኮ እያየሁት ነው..››

‹‹አንቺ ያየሽው የአባትሽ ደም በውስጥሽ ስላለ ነው››

አባተሽ የሚለውን ቃል ለሁለተኛ ጊዜ ሲደግመው ነው ያስተዋለችው 

      ይቀጥላል

#ክፍል 46,,እንዲለቀቀ (15) ሰው ከስር ያለውን ሊንክ #Subscribe🔔ካረገ ይለቀቃል
https://youtube.com/@Weygud18

#Subscribe እያደረጋቹ ቤተሰብ ስለምትሆኑ እናመሰግናለን #Subscriber
YouTube link👇
https://youtube.com/@Weygud18

መልካም ምሽት ተመኘሁ🙏
🎙ግሩፑን ለማግኘት
              👇👇👇

        @Mtshaf_bicha
        @Mtshaf_bicha
❤️ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
👉አሰተያየት ካላችሁ
📩 @Eyos18     አድርሱን
             📗📒📕📗📒📕
                Join&share
                  @EyosC1
       📚ማንበብ ባህላችን ይሁን📚
┄┉┉✽‌»‌🎶••✿••🎶»‌✽‌┉┉┄
📕ታምራተ_ኬድሮን

#ክፍል_አርባ_ስድስት

#ተከታታይ ልቦለድ

#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ

‹‹የአባትሽ ዘመዶች ነው ያልከው….?››

‹‹አዎ የአባትሽ ወገኖች … ይሄንን ተክል በምድር ላይ  እንዲበቅል አድርገው ሲበትኑት ለመድሀኒትነት እንዲሆን አስበው አይደለም…››

‹‹እና ለምድነው….?››

‹‹አንቺን ለማግኘት….››ብሎ ጭራሽ ግራ አጋባት

‹‹እንዴት አድርገው ነው እኔን የሚያገኑኝ…….?ደግሞ የት ናቸው….?››

‹‹የት እንዳሉማ ታውቂለሽ….››

‹‹እና እንዴት ነው የሚያገኙኝ ….?››

‹‹ልክ  ያቺን ተክል ስትቀነጥሺ ቀጥታ መልእክቱ እነሱ ጋር ይደርሳል››

‹‹እወነትህን ነው….?››ውስጧ ፈነጠዘች..አባቷ የማግኘት ምኞት ሳታስበው አዘለላት..የእናቷን እውነት የማረጋጋጥ ፍላጎት…

‹‹እና አሪፍ ነዋ..ያለሁበትን ካወቁ ይመጣሉ አይደለ..….?አባቴም ይመጣል አይደል….?››ጠየቀችው

‹‹አይ አባትሽ በጥብቅ እስር ላይ ስላላ መምጣት አይችልም.. ወደዚህ ምድር በመጣ ጊዜ ሳይፈቀድለት  ከሰው ጋር በፍቅር በመቆራኘትና አንቺን ስለወለደ ይሄው ባንቺ እድሜ ሙሉ እንደታሰረ ነው››አንጀቷ ተላወሰ..በምድር ላይ ታስሮ ቢሆን ኖሮ  የፈጀውን ያህል   ይፍጅ  እንጂ   መንግስትንም ገልብጣ ቢሆን አባቷን ታስፈታው ነበር

‹‹እና ታዲያ ዘመዶቹም ቢሆን ይምጡ ምን  ችግር አለው….?››

‹‹ሚመጡት  አንቺን ለመውሰድ ነው››

ደስ አለት..ደነገጠችም ‹‹ወዴየት ነው የሚወስድኝ….?››

‹‹ወደራሳቸው አለም….››

‹‹እኔ መሄድ ካልፈለኩስ….?››
‹‹ፈለግሽም አልፈለግሽም ይወስዱሻል …ምንም አይነት ምደራዊ ኃይል አንቺን ከመውሰድ አያግዳቸውም….››

ለአምስት ደቂቃ በትካዜ  ውስጥ ገባች…ሌላ አለም የማየት ፍላጎት… አባቷን እና ዘመዶቹን የማወቅ ፍላጎት..ደግሞ ይህቺን ምድርስ….?

‹‹ቆይ ሄጄ ሁሉን ነገር ካየሁ በኃላ ተመልሼ ወደምድር መምጣት አልችልም….?››

‹‹አይመስለኝም… ብትመለሺም እንደዚህ ሆነሽ አይደለም…ሙሉ በሙሉ ተቀይረሽ.. ሙሉ በሙሉ እነሱን ሆነሽ..የእነሱን ተልዕኮ ለማስፈፀም ነው ሚሆነው.ያ በእነሱ ፍቃድ ላይ የተመሰረተ ነው.ከፈለጉ እስከወዲያኛው ዳግመኛ ምድርን ላትረግጪ ትችያለሽ፡፡››

‹‹በቃ ይሁን.. ለእኛም እዛ መኖር ይሻለናል..የተለየ ዓለም  እኮ አሪፍ ነው..ይቺን ዓለም እንደሆነ በተቻለ መጠን በርብረናታል…ምን ይቀርብናል….?››

‹‹እና ወሰንሽ››

‹‹አዎ ባክህ እንደውም አሪፍ እድል ነው››
እንግዲያው ተዘጋጂ… ከአምስት ደቂቃ በኃላ ሄደሽ መቀንጠስ ትችያለሽ..ከቀነጠስሽ በኃላ ግን አንድ ሳምንት ብቻ ነው በምድር የመቆየት እድል የሚኖርሽ… ልክ የዛሬ ሳምንት በዚህን ሰዓት ካለሽበት ቦታ መጥተው ይዘውሽ ይፈተለካሉ››

‹‹አንድ ሰምንት..አንድ ሳምንት ፈጠነ..ግን ቢሆንም ቀላል ቀን አይደለም….ብዙ ነገር እንሰራበታለን…እናቴን ሄደን እንሰናበታለን..የልጅነት ጎደኞቼን እሰናበታለሁ… አሪፍ ነው..አንድ ሳምንት ይበቃናል..››አለችና ወደተክሏ ተራመደች..
ደረሰችና ልክ ድፍን  6 ሰዓት ሲሆን  ከብሳናው ዛፍ ቅርንጫፎች መካከል  እጇን ዘረጋችውና ጨበጠችው… ቀነጥሰዋለሁ ስትል በእጇ ሟሞና እንደቅባት ተሙለጭልጮ ወደሰውነቷ ሲገባ ታወቀት… ደነገጠች የቀነጠስችው መስሏት ነበር… እጇ ላይ ግን ምንም ነገር የለም… እጇ  የተለየ ቀለም እያመጣ ነው ..ሀመራዊ እሳት መሰል ቀለም… በመላ ሰውነቷ እየተራወጣ ከተዳረሰ በኃላ አንዘርዝሮና አንቀጥቅጦት በአፏ የቴንስ መጫወቻ የምታክል ድብልብል እሳት ብልቅ ብሎ በመውጣት እንደሮኬት ተተኩሶ ወደሰማይ ተምዘገዘገ ..እያየችው  አየሩን ሰንጥቆ ተሰወረ..ግራ ጋባት …እንደምንም ለመረጋጋት እየሞከረች ወደንሰሯ አዕምሮ ተመለስችና ‹‹ምን እየሆነ ነው….?››ጠየቀችው
‹‹በቃ ጨርሰናል እንሄድ››
‹‹እንዴ መቀንጠስ አልቻልኩም እኮ ..እጄ ላይ ምንም የለም….?››
‹‹እጅሽ ላይ ምን ያደርግልሻል …ተክሉ እኮ በመላ ሰውነትሽ ገብቶ ተዋሀደሽ..አሁን መዳኒቱ ተክሉ ሳይሆን አንቺ ራስሽ ነሽ..በዚህ የሳምንት ጊዚ ውስጥ የፈለግሽውን ማዳንም የፈለከግሽውን መግደልም  ትችያለሽ..››

‹‹ደስ ሲል ››

‹‹ደስ አይልም…››አለና ከመጣ ጀምሮ ተዘፍዝፎበት ከነበረው ቋጥኝ ላይ ክንፉን አርገፍግፎ ተነሳን ማጅራቷን ይዞ ወደሰማይ ተምዘገዘገ  ….ወደጀርባዋ ዞረና ተጣበቀባት…  ወደ አዲስአባ ተመልሰው እቤታችን ሲደርሱ ከምሽቱ 8 ሰዓት አልፎ ነበር… …

‹‹ወይኔ ድክም ብሎኛል..ግን መድሀኒቱን ስላገኘን ከአባቴ ወገኖችም ጋር ልንገናኝ ስለሆነ ደስ ብሎኛል…አንተስ ደስ አላላህም….?››ለመተኛት ወደ አልጋዋ እያመራች ነበር ምትናገረው

‹‹በጣም ከፍቶኛል››አላት ንስሯ

ደነገጠች‹‹ለምን….?››

‹‹ከንቺ ጋር የምኖረው ..በህይወትም የምቆየው ለሳምንት ብቻ ስለሆነ››

በህይወቷ እንደዚህ አይነት ድንጋጤ ደንግጣ አታውቅም.‹‹.እንዴ የእኔ ንስር ሟች ፍጡር ነው እንዴ…….?›ብላ ለመጀመሪያ ጊዜ ያሰበችብት ጊዜ ነው

‹‹ጥዬህ የምሄድ መስሎህ ነው..አብረን እኮ ነው የምንሄደው››

‹‹ይዘሺኝ መሄድ አትቺይም››

‹‹ለምን….?››

‹‹እኔ መጀመሪያም ከዛ ነው የመጣሁት…ለአባትሽ ብዬ እና አሁን ተመልሼ ለመሄድ ፍፅም አይፈቀድልኝም፡፡››

‹‹በቃ ይቀራላ ..እስከዛሬ ካንተ  ጋር እንጂ ከእነሱ ጋር አልኖርኩ.. ምን  ያደርጉልናል እነሱ መቅረት ይችላሉ››

‹‹እሱማ ጊዜው አለፈ..ቅድም ከአፍሽ የወጣችው እሳት አነሱ ጋር መልዕክት ይዛ የምትሄድ ነች…ወደድሽም ጠላሽም አንቺን ይወስዱሻል..እኔ ደግሞ ካለአንቺ ህይወት የለኝም …ተነጥለሺኝ እንደሄድሽ ወዲያው በዛኑ ሰዓት እሞታለሁ..››

‹‹እንዴ  እሞታለሁ ማለት ምን ማለት ነው….?ይሄንን ታዲያ ተክሉን ከመቀንጠሴ በፊት ለምን አልነገርከኝም….?››

‹‹ውሳኔሽ በእኔ ላይ እንዲመሰረት ስላልፈለኩ ››

‹‹ያምሀል እንዴ . ….?.ካንተ ሚበልጥብኝ ነገር አለ…….?

ህይወቴ እኮ ነህ..››አበደች ጮህች ፕሮፌሰሩ ከእንቅልፋቸው ባነው በራፏን እስኪያንኮኩ ድረስ ግቢውን አተረማመችው …፡፡

     ይቀጥላል

#ክፍል 47,,እንዲለቀቀ (15) ሰው ከስር ያለውን ሊንክ #Subscribe🔔ካረገ ይለቀቃል
https://youtube.com/@Weygud18

#Subscribe እያደረጋቹ ቤተሰብ ስለምትሆኑ እናመሰግናለን #Subscriber
YouTube link👇
https://youtube.com/@Weygud18

መልካም ምሽት ተመኘሁ🙏
🎙ግሩፑን ለማግኘት
              👇👇👇

        @Mtshaf_bicha
        @Mtshaf_bicha
❤️ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
👉አሰተያየት ካላችሁ
📩 @Eyos18     አድርሱን
             📗📒📕📗📒📕
                Join&share
                  @EyosC1
       📚ማንበብ ባህላችን ይሁን📚
┄┉┉✽‌»‌🎶••✿••🎶»‌✽‌┉┉┄
​​‹‹እትዬ ሰሚራ ናቸዋ… ስንት ነገር ሲታሰብ… ለሰርጋቸው ሲዘጋጁ እንዲህ ባጭር ይቅሩ..….?ውይ ጋሼ በጣም ነው አንጀቴን የበሉት ..ተሳቀቁ፤እትዬስ አንዴ ለይቶላቸው ሊገላገሉ ነው እሷቸው ግን ጤነኛ ሰው የሚሆኑ አይመስለኝም፡፡››

ይህን ሁሉ እያወራ ሳሎኑ በራፍ ድረስ አደረሰታ እና የሳሎኑን በራፍ ከፍቶ አስገብቶ ወደኃላ ተመለሰ….ሳሎኑ ውስጥ በግምት ከ10 ያላነሱ  ፎጣ የለበሱ፤ ጋቢ የደረቡ ፤ የተቀመጡ፤ የሚንጓራደዱ ሰዎች ይታያሉ……

‹‹ዋው !!!ምን አይነት ሰዓት ደረስኩ….?››ስትል እራሷን ጠየቀች…በአይኗ መላኩን ብፈልግ ላየው አልቻልኩም ….እቤቱን ከዚህ በፊት በደንብ እደሚያውቅ ሰው ወደፎቅ የሚወስደውን ደረጃ የመቁጠር ያህል  በዝግታ እየረገጠች  ቀስ እያለች ሀንድሪሉን በአንድ እጇ ተደግፋ ወጣች….፡፡
ተራራ የመውጣት ያህል  ደከማት…. ስትደርስ መኝታ ቤቱ በራፍ ላይ ሁለት ወጣት ሴቶች ወገባቸውን በሻርፕ ጥፍንግ አድርገው አስረው በእንባ በመታጠብ እህህህ…. እያሉ በኮሪደሩ ላይ ይሽከረከራሉ…ዝም ብላ ችላ አለቻቸውና መኝታ ቤቱን ከፍታ ገባች…
ደረቷ ላይ ተደፍቶ ሲንሰቀሰቅ ነበር የደረሰችው…እሷ በቃ የለችም አምልጣቸዋለች….አንጀቴን በላኝ…‹‹አይዞህ›› ስለው ከተደፋበት ቀና ብሎ አየኝና
‹‹አይዞህ?ምን አይዞህ አለው…….?ጥላኝ ሄደች እኮ…ጨከነችብኝ..ብዙ ቃል ገብታልኝ ነበር..በቅርብ ቀን ድል ባለ ሰርግ ልንጋባ ቃል ገብታልኝ ነበር…ልጅ እደምተወልድልኝ ቃል ገብታለኝ ነበር..ቢያንስ 2 ዓመት እንደምትኖር ዓምኜ ነበር..ሀኪሞቹም እንደዛ ብለውኝ ነበር…››

‹‹አይዞህ… በቃ ተረጋጋ››

‹‹ተረጋጋ አትበይኝ…አንቺም እኮ ቃል ገብተሸልኝ ነበር…ግን ይሄው እሬሳዋን ከታቀፍኩ በኃላ ልታፌዥብኝ መጣሽ››

‹‹እስቲ ዞር በልልኝ››አለችው፡፡
የልጅቷን መሞት እና  የእሱን ሀዘን በማየቷ ምክንያት  ስምታ ይዛው የመጣችው ስካር በግማሽ ፐርሰንት በረደላት፡፡ 

‹‹ልነሳ….?ምን …በመገነዝ  ልትተባበሪኝ ነው..….?››ተነሳና ስሯ ቆሞ አፈጠጠባት፡፡

ገፍትራው እሱ በተነሳበት ቦታ ተተካችና ተቀመጠች ..እጇን ጭንቅላቷ ላይ አኖረችና አዕምሮዋን በመክፈት  ትኩረቷን ሰብስባ እጇን ግንባሯ ላይ አድርጋ የሚሆነውን መጠበቅ ጀመረቸ… ከ30 ሰክንድ በኃላ የእጇ ቀለሙ መቀየር እና ለሊት መዳወላቡ ላይ ተክሏን ስትቀነጥስ እዳጋጠማት  ሀመራዊ አይነት  ቀለም  ከውስጧ መፍለቅ ጀመረ ..
ከእሷ እጅ የፈለቀው ወደ ልጅቷ ጭንቅላት ሲገባና የእሷም በተመሳሳይ ሲቀየር ታየ…በዚህ አይነት ሁኔታ ለሁለት  ደቂቃ ያህል  ከቆየ በኃላ ጥቁር ጭስ የመሰለ ትነት ከጭንቅላቷ እየበነነ ወደቤቱ ኮርኒስ በመስገምገም በኖ መጥፋት ጀመር…ከዛ ህይወቷ ያለፈና  በድን የነበረችው ልጅ መንቀጥቀጥና መንዘፍዘፍ ጀመረች…ታአምር ተከሰተ…..
ከደቂቃዎች ቆይታ በኃላ  ልክ ከቀናት እንቅልፍ እንደናቃ ሰው አይኖቾን ገለጠችና አካባቢዋን መቃኘት ጀመረች…ፈገግ አለችና ቀና ብላ እንደሀውልት የተገተረውን መላኩን ተመለከተችው..አፉን እደከፈተና እነዛ ብርሀን የሚረጩ አይኖቾን እንደበለጠጣቸው በገረሜታ እያፈራረቀ ሲመለከታት አየችው…

‹‹የእኔ ፍቅር ምንድነው እየሆነ ያለው….?››አለችና በፍፅም ንቃት ከመኝታዋ ተነስታ አልጋው ጠርዝ ላይ ተቀምጠች…..ሶፊያ በጥርጣሬ እያየች‹‹አላወቅኩሽም ይቅርታ….?››ስትል ጠየቀቻት፡፡

‹‹አይ አታውቂኝም..ትንሽ አሞሽ ነበር…››

‹‹አረ ምንም የህመም ስሜት አይሰማኝም…እንደውም እንደዚህ ፍጽም ሰላማዊ የሆነ ስሜት ከተሰማኝ ዓመት አልፏታል ››

‹‹አዎ ትክክል ነሽ..ለማንኛውም እኔ ሀኪምሽ ነኝ..አሁን ስራዬን ስለጨረስኩ ልሂድ››ብላ ከተቀመጠችበት ተነሳችና ፊት ለፊቱ ተገትራ ቆመች…..ምን እንዳዛ እንዳስቆማት አታውቅም…

‹‹አደረግሺው..እንደፎከርሽው አደረግሽው››ብሎ በመፍለቅለቅ ተጠመጠመባት…እንደዛ ሲያደርግ ፍቅረኛዬ ምን ታስብ ይሆን….? ብሎ እንኳን መጨነቅ አልፈለገም….

እሷም እንዳቀፋት ጆሮው ላይ ተለጠፋችና በማንሾካሾክ‹‹አዎ አድርጌዋለሁ…..ዛሬውኑ ወደሀኪም ቤት ውሰዳትና አስመርምራት…ሙሉ በሙሉ መዳኗን ካረጋገጡልህ ያው በተስማማነው መሰረት በሶስት ቀን ውስጥ ቃልህን እንድትተገብር እፈልጋለሁ..የእቤቴ አድራሻ …››አለችና ከለበሰችው ጂንስ ሱሪዬ ኪስ ውስጥ ቢዝነስ ካርዷን አውጥታ የለበሰው ጃኬት ኪስ ውስጥ ከተተችለት…፡፡
በዝግታ ከእቅፉ አወጣትና በመገረም አፍጥጦ ያየት ጀመር….እሷም አይኖቾን ሳትሰብር አፍጥጣ አየችው …ደስታው  በኖ በአንዴ  አመድ ነፋቶበታል…እንደደነዘዘ ባለበት ቆመ፡፡

..‹‹ሰሚራም ምንድነው እየተካሄደ ያለው ….?››ብላ በጥርጣሬ የተለወሰ ጥያቄዋን ስትደረድር እና  እየተካሄደ ስላላው ነገር ይበልጥ ለማወቅ በጥያቄ ሁለቱንም ስታፋጥጥ… ሶፊያ ከቆመችበት ስፍራ እግሮቾን በማነቃነቅ  የተዘጋውን የመኝታ ቤት በራፍ ከፍታ ወጣች…..
ስትመጣ ከነበራት በተሻለ ፍጥነት   ደረጃውን እየተንደረደረች ወርዳ ሳሎኑን ሰንጥቃ  በመውጣት የግቢው የውጭ በራፍ ጋር ስትደርስ ቅልጥ ያለ የእልልታ ድምጽ እቤቱን ሲያደበላልቀው ሰማች……ፈገግ አለች..
‹‹ይህ  የእነዚህ ሰዎች ደስታ እኔን ምን እንዳስከፈለኝ ቢያውቁ እንዲህ እልል አይሉም ነበር…ግን ምንድነው ለመላኩ ብዬው የመጣሁት?አሁን አስቲ ምን ማድረጌ ነው ….?››ስትል እራሷን ታዘበች፡፡በተስማማነው መሰረት በሶስት ቀን ውስጥ ትከፍለኛለህ ማለቷን ማመን አልቻለችም፡ ..በዛ ላይ እኮ የቤቷን አድርሻ ጭምር  ሰጥታዋለች‹‹..እስቲ ይሄ ደስታው ለዛሬ እንኳን ሙሉ ቢሆንለት ምን ነበረበት..….?ገና ለገና እኔ ስቃይ ውስጥ ነኝ ብዬ ሌላውን ሰውም እንዲሰቃይ ማድረግ ነበረብኝ..….?ደግሞ ለሳምንት ዕድሜዬ እንደዚህ ክፉ መሆን ምን የሚሉት ልበ ጠጣርት ነው ….….?››እራሷን በራሷ ገሰፀች
የመኪናዋን ሞተር በማስነሳት ከአካባቢው በፍጥነት ተፈተለከቸ….

     ይቀጥላል

#ክፍል 48,,እንዲለቀቀ (20) ሰው ከስር ያለውን ሊንክ #Subscribe🔔ካረገ ይለቀቃል
https://youtube.com/@Weygud18

#Subscribe እያደረጋቹ ቤተሰብ ስለምትሆኑ እናመሰግናለን #Subscriber
YouTube link👇
https://youtube.com/@Weygud18

መልካም ምሽት ተመኘሁ🙏
🎙ግሩፑን ለማግኘት
              👇👇👇

        @Mtshaf_bicha
        @Mtshaf_bicha
❤️ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
👉አሰተያየት ካላችሁ
📩 @Eyos18     አድርሱን
             📗📒📕📗📒📕
                Join&share
                  @EyosC1
       📚ማንበብ ባህላችን ይሁን📚
┄┉┉✽‌»‌🎶••✿••🎶»‌✽‌┉┉┄
አይችልም››‹‹እማ እኔ እኮ የምታወሪውን ነገር አንድም ቀን ተጠራጥሬሽ አላውቅም…››

‹‹አመሰግናለሁ ልጄ…..….››ጎትታ ግንባሯን ደጋግማ ሳመቻት፡፡

‹‹ልጄ ለአባትሽ መልዕክት ታደርሺልኛለሽ….?››

‹‹አዎ.. ምን ልበልልሽ?››
‹‹ዕድሜዬን ሙሉ እሱን ብቻ ሳፈቅር እንደኖርኩ ንገሪልኝ…አንተ የከፈትከውን ጭኔን ሌላ ሰው እዲከፍተው ፈቅጄ በመሀከላችን የነበረውን ቅዱሱን  ፍቅራችንን ላሳንሰው ስላልፈለኩ እስከዛሬ በስምህ መልኩሼ እየኖርኩ ነው በይልኝ….እንደዛም በማድረጌ ከደስታ ውጭ አንድም ቀን ከፍቶኝ እንደማያውቅ ነግሪልኝ…ደግሞ ቆንጆና ብልህ ልጅ ስለሰጠኸኝ አመሰግናለሁ…መልሼ ለአንተ ስልክልህም ደስ እያለኝ ነው በይልኝ፡፡››

የእናትዬው ንግግር አንጀቷን አላወሰው‹‹…እሺ ያልሺኝን ሁሉ እነግረዋለሁ››አለቻት፡፡

መቼስ እሷ ብቻ ሳትሆን እሱም በእሷ እድሜ ሙሉ መስዋዕት እየከፈለ እንደሆነ እና በወገኖቹ እንደጥፋተኛ ተቆጥሮ  እስራት ላይ እንደሚገኝ ባታውቅም ይሄንን ነግራት ደስታዋን ልታደፈርሰው እና እሷ ከሄደችም በኃላ ያለውን ህይወቷን ወደ ትካዜና ሀዘን ልትቀይረው ስላልፈለገች አሳዛኙኝ የታሪክ ክፍል  ደበቀቻት..፡፡

‹‹ልጄ››እናቷ ጠራቻት፡፡

‹‹ወይ ሀርሜ››

‹‹አይዞሽ አታስቢ ንስርሽን እኔ እንከባከበዋለሁ..ማለቴ  በአንቺ ፋንታ እኔን ይንከባከበኛል››

‹‹እስቲ እናያለን››አለቻት ..አዎ እናቷ እንዳለቸው ቢሆን እሷም ደስ ይላት ነበር..ግን እንደዚህ አይነት ተስፋ ከንስሯ አላየችም….እና አሁን በዚህ ሰዓት  እናቷን ይሆናልም አይሆንምም ልተላት አልደፈረችም፡…..

             ይቀጥላል

#ክፍል 49,,እንዲለቀቀ (20) ሰው ከስር ያለውን ሊንክ #Subscribe🔔ካረገ ይለቀቃል
https://youtube.com/@Weygud18

#Subscribe እያደረጋቹ ቤተሰብ ስለምትሆኑ እናመሰግናለን #Subscriber
YouTube link👇
https://youtube.com/@Weygud18

መልካም ቀን ተመኘሁ🙏
🎙ግሩፑን ለማግኘት
              👇👇👇

        @Mtshaf_bicha
        @Mtshaf_bicha
❤️ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
👉አሰተያየት ካላችሁ
📩 @Eyos18     አድርሱን
             📗📒📕📗📒📕
                Join&share
                  @EyosC1
       📚ማንበብ ባህላችን ይሁን📚
┄┉┉✽‌»‌🎶••✿••🎶»‌✽‌┉┉┄
ሙሉ ጠርሙስ ጎርደን ጅን አዘዙ
‹‹አረ ልባችን ትፈነዳለች››አላት
አልመሰለችለትም …መጠጡ መጥቶም ለተወሰኑ ጊዜ ከዲጄው የሚለቀቀውን ለስለስ ያለ ሙዙቃ በተመስጦ እያዳመጡ እና ከራሳቸው ሀሳብ ጋር እየተብሰለሰሉ ቆዩ…. ሰላሳ የሚሆኑ  ደቂቃዎች በየራሳችን ዝምታ ወስጥ ቆይተዋል..ግን ድንገት ስትባንን መጠጡ ግማሽ ጠርሙስ ተጋምሷል..ደነገጠች ….እሷ የተቀዳላት ብርጭቆ ግማሹን እራሱ አላጋመሰችም ..አጅሬ ላካ እየለጋው ነበር..‹‹ወይ ከእኔ የባሰ መጠጥ የራበው ነው እንዴ የገጠመኝ .….?››ስትል አሰበች፡፡ደግሞ ሲያዩት ገና ብዙ የመጠጣት አቅሙ እንዳለው ያስታውቃል….እንግዲህ ምንም ማድረግ አይቻልም አንዳንድ ሰዎች እንዲህ ናቸው..፡፡ለእሷ እንዲህ መጠጡን መሳቡ ተመችቶታል..ብቻ እራሱን እስከመሳት ደርሶ ሰውነቱን ማዘዝ አያቅተው እንጂ ህሊናው እስኪቆለፍ ድረስ መጠጣቱ አሪፍ ነው ብላ አሰበች…‹‹እበላዋለሁ…ሌላ ተጽዕኖ ወስጥ ሳልከተው  በራሱ ፍላጎት አብሮኝ  እንዲያድር ማደረግ እፈልጋለሁ…እንደማንኛዋም ተራ ሴት ሆኜ ላሸነፈው  ነው የምፈልገው……ሰውኛ ማሸነፍ እንዲሆን …›ስትል እቅድ አወጣች፡

ድንገት ከመሬት ተነስታ‹‹ተጫወት›› አለችው፤

እሱም እንደመባነን አለና ‹‹እሺ …ባይዘወይ ኤርሚያስ እባላለሁ..››አላት

‹‹አሪፍ ስም ነው ..እኔን ሰፊ  በለኝ ››..
‹‹አይገርምም ማን ልበል ሳትይኝ እንዲሁ ከምድር ተነስቼ ኤርሚያስ አባላለሁ በማለት ከበሮ መደለቅ ምን የሚሉት እራስ ወዳድነት ነው..ኤርሚያስ ልባል ሚኪዬስ ለአንቺ ምን ይረባሻል፡፡ግን ያው ትረጂኛላሽ ብዬ አስስባለሁ…በመጀመሪያ እኔ በዚህች አለም ላይ ያለኝን ውክልና ለማሳወቅ ከስሜ መጀመር የግድ ይለኛል..ከስሜ ቀጥሎ ነው  ወደ ሌላ ጫወታ መግባት የምችለው ››

‹‹አረ ትክክል ነህ.. እንደውም እኮ  ገና እንደተገናኘን ነበር ስም መቀያየር የነበረብን ›› 

            ይቀጥላል

#ክፍል 50,,እንዲለቀቀ (10) ሰው ከስር ያለውን ሊንክ #Subscribe🔔ካረገ ይለቀቃል
https://youtube.com/@Weygud18

#Subscribe እያደረጋቹ ቤተሰብ ስለምትሆኑ እናመሰግናለን #Subscriber
YouTube link👇
https://youtube.com/@Weygud18

መልካም ምሽት ተመኘሁ🙏
🎙ግሩፑን ለማግኘት
              👇👇👇

        @Mtshaf_bicha
        @Mtshaf_bicha
❤️ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
👉አሰተያየት ካላችሁ
📩 @Eyos18     አድርሱን
             📗📒📕📗📒📕
                Join&share
                  @EyosC1
       📚ማንበብ ባህላችን ይሁን📚
┄┉┉✽‌»‌🎶••✿••🎶»‌✽‌┉┉┄
📕ተአምራተ_ኬድሮን

#ክፍል_ሃምሳ

#ተከታታይ ልቦለድ

#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ

‹‹ለማንኛውም ልድገምልሽ ኤርምያስ እባላለሁ…ለ15 ዓመት ያህል በማንዴላ ሀገር በሆነችው ደቡቡ አፍሪካ ጀሆንስበርግ ኖሬያለሁ… ወደሀገሬ ከተመለስኩ  ሁለት ዓመት ከግማሽ ሆኖኛል፡፡የ20ዓመት አፍላ ፍንዳታ ሆኜ ሄጄ የ35 ዓመት ሙሉ  ደንዳና ወጣት ሆኜ ተመለስኩ….››
‹‹አሀ ዲያስፖራ ነሀ….?››
‹‹አይ ዲያስፖራ ..!!! ‹ጽድቁ ቀርቶብኝ  በቅጡ በኮነነኝ ›ትላለች እናቴ… ለማንኛውም  እወነቱን ንገረኝ ካልሺኝ … በእነዛ ዓመታት ውስጥ በሰው ሀገር ላይ  ስዳክር ..ሞራሌን ከማንቆሻቆሽ…ሰው ሆኜ መፈጠሬን ከመጠየፍ እና ወጣትነቴ ላይ ጢቢ ጢቢ ከመጫወት ውጭ ምንም ያተረፍኩት ነገር አልነበረም…ብዙ ህልም በልቤ ብዙ ምኞት በውስጤ አጭቄ ነበር የተጓዘኩት …እርባነቢስ ሆኜ ባዶ እጄን በሀገሬ ለመሞት ብቻ ብዬ  ነበር የተመለስኩት …ይገርማል አይደል?
ሰው እንዴት ለመሞት ብሎ ከደብቡ አፍሪካ ድረስ ኪሎሜትሮችን አቆርጦ ይመጣል ትይኝ  ይሆናል..….?ለእኔ ግን ትርጉም ነበረው..››
‹‹ንገረኝ እስኪ ትርጉሙን…››ከሳዕታት ትርኪ ሚርኪ ወሬ እና መዛለል በኃላ ድንገት ምርር ወዳለ የህይወት ታሪክ ሀተታ መግባቱ አስደምሟታል አስደስቷታልም…አሁን እየነገራት  ያለውን ታሪክ እሱ ሳይነግራት እንደተለመደው  ወጭ እየጠበቀት ያለውን ንስሯን እንዲረዳት አድርጋ በዝርዝር ማወቅ ትችላለች..ግን አልፈለገችም …እንዲሁ እየጓጓችና ቀጥሎ ምን እንደሚናገር እየገመተች ቀጥታ ከራሱ አንደበት መስማቱ የሆነ የተለየ ስሜት ስለፈጠረባት ደስ ብሏታል…
ቀጠለ ‹‹በህይወቴ እያለሁ የመኖር ምኞቴ ሰልበው በድን አድርገውኝ …ወጣትነቴን ከንቱ አስቀርተውብኝ የመጨረሻውን ክስረት ማክሰራቸው ሳይበቃቸው …ከሞቴም በኃላ ክብር ስጋዬን  ለሀገራቸው ምድር  ልገብር …?አላደርገውም ፡፡ለዘላለም የባዕድ ሀገር አፈር ሆኜ መቅረት  አልፈለኩም  ..ይህ  መልካም አይደለም…ቢያንስ አገሬ እትብቴን በክብር በወርቃማ አፈሯ ውስጥ ቀብራ ከማንነቷ ጋር እንዳወሀደችው ሁሉ ስሞትም በድኔን በክብር ልትቀበለኝ እና ለዘላለም በጉያዋ ልትሸሽገኝ ይገባል..አዎ እንደዛ ነው መሆን ያለበት..በዛ ላይ እናቴን ለመጨረሻ ጊዜ ማየት እፈልጋለሁ… አያየኋት መሰናበት፤ስሮ በመኖር  እና እሷን መጦር ችዬ ላስደስታት  ባልታደልም… እጇ ላይ ሞቼ አልቅሳ ልትቀብረኝ እና እርሟን ለማውጣት እንድትችል ግን እድሉን ላመቻችላት ይገባል..አዎ ስመጣ እንደዛ ብዬ  እና እንደዛ ወስኜ ነበር …
‹‹ከዛስ….?››
‹‹ከደረስኩ ኋላማ … ቆይ ዛሬ ስል …ቆይ ትንሽ ልሰንብት ስል ..የመኖር ጉጉቴ ቀስ በቀስ ከሞተበት  እያንሰራራ እና እየተቀሰቀሰ መጣ..ምንም አግኝቼ አልነበረም ..ከእናቴ የማገኘው ተንሰፍሳፊ ፍቅር  እና ከጓደኞቼ የማገኘው ማፃናኛ …››
‹‹በጣም አሪፍ ታሪክ ነው ያለህ››
‹‹አዎ መራር የህይወት ገጠመኞች  ለሰሚው ወይም ለፅሀፊው ሳቢ ታሪክ ይወጣቸዋል…››
‹‹ከዛስ እንዴት ሀሳብህምን ሙሉ በሙሉ ልትቀይር ቻልክ….?››
‹‹አሁንም ሙሉ በሙሉ አልተውኩትም…አሁንም  የመሞት እቅዴ በውስጤ አለ…››
‹‹እሺ እንዴት ልታራዝመው ቻልክ….?››ጥያቄውን አስተካከለችለት፡፡
‹‹እንዴት መሰለሽ….ከዛ ከሰው ሀገር  በገንዘብም በመንፈስም ክስርስር ብዬ የመጣሁ ቢሆንም ብዙም ሳልቆይ ሚስኪን የልጅነት ጓደኞቼ  አዋጥተው አሁን የምጠቀምባትን ላዳ ገዝተው ሰጡኝ..በቃ የመሞት ሀሳቤን አራዘምኩት ..ለራሴ ሁለተኛ እድል ሰጠሁት..ቢያንስ ለጊዜው ሰርቼ ስጋዬን የማኖርበትን  ካገኘሁ አንድ ቀን ምን አልባት ሁለተኛውን የህይወት ምኞቴን በሆነ ተአምር ሊሳካልኝ ይችል ይሆናል…ብዬ ተስፋ አደረኩና መጨረሻውን እስከማይ ሁለት ዓመት ተኩል በሀገሬ ኖርኩ..ዘና ብዬ ለማንም ለምንም ሳልጨነቅ…ባሳኘኝ ሰዓት እየሰራሁ ሲያሰኘኝ ደግሞ እየተኛው..የእናቴን ሽሮ እየበላሁ ተስፋዬን በመጠበቅ እንሆ አለሁልሽ››
‹‹ምንድነው ተስፋህ..ማለቴ ይሳከልኛል ብለህ የምትጠብቀው….?››
‹‹የልጅነት ፍቅሬን… ..አንድ ቀን ቀና ብላ ታየኛለች የሚል ተስፋ..አንድ ቀን ከቄስ ትምህርት ቤት ጀምሮ እንደማፋቅራት እና ዕድሜዬን ሙሉ በልቤ ተሸክሜያት ስዞር እንደኖርኩ  ተረድታ በእቅፎ ታስገባኛለች ብዬ ተስፋ  በማድረግ..አንድ ቀን እጄ ትገባለች በሚል ተስፋ…..››

‹‹ወየው ጉዴ!!›አለኝች በውስጧ፡ በዚህ ቅርብ ጊዜ ውስጥ የምትቀርባቸውና የምትመኛቸው ወንዶች ሁሉ እንዴት እንዴት ሆኖና  ምንስ በሚሉት አጋጣሚ   እንደዚህ በፍቅር ስክር ያሉና የታወሩ ሆነው እንደሚገኙ ግልፅ ሊሆንላት አልቻለም...?‹‹ይሄኛውንስ ዛሬ አልምረውም…በፍጽም፡፡››ስትል ፎከረችው፡፡

‹‹ይቅርታ ሙሉ ታሪኩን እንድትነግረኝ እፈልጋለሁ….››

‹‹እየነገርኩሽ እኮ ነው …እየተረተርኩልሽ…..ሆድ ያባውን ብቅል ያወጣዋል አይደል የሚባለው››

‹‹አይ እዚህ አይደለም…እኔ ቤት እንሂድና ተረጋግተን እየጠጣን ታወራልኛለህ….አሁን ሆቴሉም ሊዘጋ መሰለኝ››

‹‹ይቻላል››ይከራከረኛል  ወይም ይቃወመኛል ብላ ነበር የጠበቀችው ..ቀድሟት ተነሳ ..ሂሳብ ከፍላ ተከተለችው …. እየተወለጋገድና እርስ በርስ እየተደጋገፉ ላደው ድረስ ሄድ ..ሹፌሩ ተቀብሏቸው እቤት ድረስ አደረሳቸውና የለሊቱን ግዳጅ ጨረሶ  ተለያቸው.. 
እሷም ዛሬ ለዛውም ከመሸ ያወቀችውን ባለ ላዳ ይዛው  ወደቤቷ ገባች…..

            ይቀጥላል

#ክፍል 51,,እንዲለቀቀ (10) ሰው ከስር ያለውን ሊንክ #Subscribe🔔ካረገ ይለቀቃል
https://youtube.com/@Weygud18

#Subscribe እያደረጋቹ ቤተሰብ ስለምትሆኑ እናመሰግናለን #Subscriber
YouTube link👇
https://youtube.com/@Weygud18

መልካም ምሽት ተመኘሁ🙏
🎙ግሩፑን ለማግኘት
              👇👇👇

        @Mtshaf_bicha
        @Mtshaf_bicha
❤️ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
👉አሰተያየት ካላችሁ
📩 @Eyos18     አድርሱን
             📗📒📕📗📒📕
                Join&share
                  @EyosC1
       📚ማንበብ ባህላችን ይሁን📚
┄┉┉✽‌»‌🎶••✿••🎶»‌✽‌┉┉┄
‹‹ቤተክርስትያን….? ጭራሽ ቤተክርስትያን…በፍጽም… የደረሰብኝ መከራ  ሁሉ በእግዚያብሄር ትዕዛዝና ፍላጎት  ነው የሆነው..እንዲህ የቀጣኝ እሱ ነው…..ፍፅሞ ወደቤቱ አልሄድም..››ብላ ተንገሸገሸች
ምርጫውን ወደራሷ መለስኩት‹‹እሺ የት ልውሰድሽ…….?››

‹‹-መጠጥ ቤት…››

‹‹አልተከራከርኳትም..ነዳሁት….እስከለሊቱ 5 ሰዓት ብትን እስክትል ድረስ  እስክትጠጣ ጠበቅኳት …ከዛ አዝዬ ማለት ይቻላል አቤቷ አስገብቼያት ደስ ብሎኝም ከፍቶኝም ወደቤቴ ገባሁ….ደስ ያለኝ ከስንት አመት በኃላ ከእሷ ጋር ማውራት፤ከእሷ ጋር ጊዜ ማሳለፍ በመቻሌ ነው…የከፋኝ በዚያ አይነት በእሷ ባልሆነ ሀዘን፤ በእሷ ባልሆነ ምሬት ውስጥ በተዘፈቀችበት ሰአት ስለገኘኋት ነው …..

‹‹ከዛስ እንዴት ሆነ….?››ስትል ጠየቀችው.. በታሪኩ ከመመሰጧ የተነሳ ምሽቱን  ሙሉ ጭኖን  የሚበላት  የነበረው  ክፉ አመሏ ራሱ ቀንሶላት ነበር።

            ይቀጥላል

#ክፍል 52,,እንዲለቀቀ 👍(5) ሰው ከስር ያለውን ሊንክ #Subscribe🔔ካረገ ይለቀቃል
https://youtube.com/@Weygud18

#Subscribe እያደረጋቹ ቤተሰብ ስለምትሆኑ እናመሰግናለን #Subscriber
YouTube link👇
https://youtube.com/@Weygud18

መልካም ምሽት ተመኘሁ🙏
🎙ግሩፑን ለማግኘት
              👇👇👇

        @Mtshaf_bicha
        @Mtshaf_bicha
❤️ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
👉አሰተያየት ካላችሁ
📩 @Eyos18     አድርሱን
             📗📒📕📗📒📕
                Join&share
                  @EyosC1
       📚ማንበብ ባህላችን ይሁን📚
┄┉┉✽‌»‌🎶••✿••🎶»‌✽‌┉┉┄
‹‹ኤርሚየስ››
‹‹ኤርሚያስ …እዚህ ጋር ታቆምልኝ..….?››
ዳር ያዝኩና አቆምኩላት…ወረደችና የመኪናዋን የኃላ ኮፈን ከፍታ ምንጣፍ በማውጣት አንድ ጠርሙስ ያልተከፈተ ውስኪ በመያዝ ከመኪናው እርቃ ወደአንድ ዘርፋፋ ቅርንጫፍ ወደተሸከመ ዛፍ ሄደችና ጥላው ባለበት አቅጣጫ ምንጣፍን አንጥፋ እንደቡዲስት መለኩሴ እግሮቾን አነባብራ  በመቀመጥ የጠርሙሱን ክዳኑን ተታግላ ከፈተችና አንዴ በመጎንጨት ወደ ፅሞናዋ ተመለሰች…..
እኔን  ልክ እንደ ግኡዙ  መኪናዋ ነበር የቆጠረችኝ… እስከመፈጠሬም እረስታኛለች…20 ለሚሆኑ ደቂቃዎች  ከመኪናው ሳልወርድ የተለያዩ ኤፍ. ኤም ጣቢያዎችን እየቀያየርኩ ሳረብሻት ለመቆየት ሞከርኩ… ከዛ በላይ ግን አልቻልኩም… መኪናውን ከፍቼ ወጣሁና በዝግታ እርምጃ ወደእሷ በመሄድ አንድ ሜትር ከእሷ ርቄ ከፊትለፊቷ  ሳር የለበሰ ሜዳ ላይ ቁጭ አልኩ……በሁለት ጉንጮቾ እንባዋ ያለምንም ድምጽ ትረጫዋለች….ደነገጥኩ…. ምን እንደምላትም ሊገለፅልኝ አልቻለም፡፡
‹-በህይወትህ መሞት ፈልገህ ግን ደግሞ እንዴት መሞት እንዳለብህ ግራ ገብቶህ ያውቃል….?፡፡››ስትል ጠየቀችኝ 

‹‹ብዙ ጊዜ አዎ…….?››መለስኩላት

‹‹እና እንዴት አደረግክ….?››

‹‹ቆይ ዛሬ…ቆይ ነገ…በገመድ ተንጠልጥዬ ብሞት ይሻላል ወይስ መድሀኒት ልጋት……….?ከፎቅ ላይ እራሴን ልፈጥፍጥ ወይስ የሚበር መኪና ውስጥ እራሴን ወርውሬ ይጨፍልቀኝ….? ብዬ ሳማርጥ በአንዱ መወሰን አቅቶኝ ስዋልል ቆይና ሁለት የምወዳቸው ሰዎች ወደአዕምሮዬ ሲመጡ ደግሞ እስኪ ቢያንስ ለእነሱ ስል  ብዬ  እታገሳለሁ..ከዛ ቀስ በቀስ ያ ስሜት ይጠፋል ወይም ይደበዝዛል…ቢያንስ ለጊዜውም ቢሆን ››
‹‹ለሁለት ሰዎች ስትል….?››


            ይቀጥላል

#ክፍል 53,,እንዲለቀቀ 👍(5) ሰው ከስር ያለውን ሊንክ #Subscribe🔔ካረገ ይለቀቃል
https://youtube.com/@Weygud18

#Subscribe እያደረጋቹ ቤተሰብ ስለምትሆኑ እናመሰግናለን #Subscriber
YouTube link👇
https://youtube.com/@Weygud18

መልካም ቀን ተመኘሁ🙏
🎙ግሩፑን ለማግኘት
              👇👇👇

        @Mtshaf_bicha
        @Mtshaf_bicha
❤️ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
👉አሰተያየት ካላችሁ
📩 @Eyos18     አድርሱን
             📗📒📕📗📒📕
                Join&share
                  @EyosC1
       📚ማንበብ ባህላችን ይሁን📚
┄┉┉✽‌»‌🎶••✿••🎶»‌✽‌┉┉┄
ነቃ ለማለት እዲረዳው  ክንፉን አርገፈገፈ …..የሳሎኑን በር ከፈተችለት… ከሶፋው ላይ ተንሳፎ ጭንቅላቷ ላይ አረፈ…ክንፉን እያማታ ከጭንቅላቷ ላይ ተነስቶ በሩን አልፎ ጭለማ ውስጥ ሰመጠ…..
ወደመኝታ ቤቷ ተመለሰችና  ወደአልጋው ሳይሆን  ወደ  ሻወር ቤት ገባች …

ሻወር ቤት ገብታ ሽንቷን ብቻ ሸንታ አልወጣችም..የሻወሩን ውሀ ከፈተችና ልብሷን አወላልቃ ገባችበት….አዎ በሆነ መንገድ መረጋጋት ፈልጋለች……. ‹‹ምንድነው ያጣሁት ነገር…….?.ከሁለት የተለያዩ  ፍጥሮች መፈጠሬ ስለፍቅር ያለኝን ስሜት አበላሽቶብኛል እንዴ….….?ለምንድነው እኔስ መላኩ  ሰሚራን ባፈቀረበት መጠን ላፈቅር  ማልችለው..….?ለምንድነው ይሄ አልጋዬ ላይ ሆኖ የሚጠብቀኝ ኤርምያስ ሰላምን ባፈቀራት መጠን በዚህ የህይወቴ ረጂም ጊዜ ሁሉ ቢያንስ ለአንድ ጊዜ እንኳን  ማፍቀር ያልቻልኩት….….?››በአዕምሮዋ እያተረማመሱ ያሉ ጥያቄዎች ነበሩ….

ውሃው ከላይ እየተወረወረ ሰውነቷ ላይ እያረፈ ነው..ዝም ብላ ቆማ በሀሳብ ውስጥ እየነሆለለች ነው….አሁን እነሱ ታሪካቸውን ለማንም ሰው ቢናገሩ ሰሚው ሰው ውስጡ በሀዘን ይተረማመሳል..እንባ አውጥቶም ሊያለቅስ እና  በዛም  መጠን ሊያዝንላቸው ይችላል…እሷ ግን ቀናችባቸው እንጂ ልታዝንላቸው አልቻለችም …ለምን በዚህ መጠን የማፍቀር ስሜት ከውስጧ መብቀል አቃተው…….?እንዴት ሰው በህይወት ዘመኑ ቢያንስ አንዴ በፍቅር ፍላፃ ልብ አይሰነጣጠቅም….?እንዴት በእድሜው አንዴ እንኳን በፍቅር እቅፍ አጥቶና ምቾት ነስቶት ሲነፈርቅ አይታይም…….?ለፍቅር መሸነፍ እኮ ድክመት አይደለም ሰዋዊነት እንጂ…..እሷ የወሲብ ረሀብ ያንን ተከትሎ የጭን መብላት አባዜ ብቻ ነው የሚያሰቃያት….ሙላት ያለው የፍቅር   ስሜት ሳታጣጥም ይህችን ምድር ልትለቅ አራት ቀን ቀራት ..!!!አራት ቀን ብቻ…

ይቀጥላል።

አብዛኞቻቹ ወይም ባጠቃላይ ማለት ይቻላል የአገልግሎት ክፍያ እየከፈላቹ አደለም ክፍያውም አንብባቹ ስትጨርሱ👇👇👇

#ክፍል 54,,እንዲለቀቀ 👍(15) ሰው ከስር ያለውን ሊንክ #Subscribe🔔ካረገ ይለቀቃል
https://youtube.com/@Weygud18

#Subscribe እያደረጋቹ ቤተሰብ ስለምትሆኑ እናመሰግናለን #Subscriber
YouTube link👇
https://youtube.com/@Weygud18

መልካም ምሽት ተመኘሁ🙏
🎙ግሩፑን ለማግኘት
              👇👇👇

        @Mtshaf_bicha
        @Mtshaf_bicha
❤️ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
👉አሰተያየት ካላችሁ
📩 @Eyos18     አድርሱን
             📗📒📕📗📒📕
                Join&share
                  @EyosC1
       📚ማንበብ ባህላችን ይሁን📚
┄┉┉✽‌»‌🎶••✿••🎶»‌✽‌┉┉┄
ሳቋ አመለጣት ..ከፊት ለፊቱ ቁጭ አለች……

‹‹ይሄውልህ…››ብላ የውስጧን ልትግረው ስትጀምር ባለ ላዳው ማለት ኤርሚያስ ሆዬ ከመኝታ ቤት ውልቅልቁ የወጣውን ሰውነቱን እየጎተተ ሳሎን ደረሰና ግራ በመጋባትና በድንጋጤ አንዴ እሱን አንዴ እሷን እያየ  ምን ማድረግ እንዳለበት ግራ በመጋባት ሲዋልል እሷንም ንግግሯን እንድታቆርጥ አደረገት ….

     ይቀጥላል።

አብዛኞቻቹ ወይም ባጠቃላይ ማለት ይቻላል የአገልግሎት ክፍያ እየከፈላቹ አደለም ክፍያውም አንብባቹ ስትጨርሱ👇👇👇

#ክፍል 55,,እንዲለቀቀ 👍(15) ሰው ከስር ያለውን ሊንክ #Subscribe🔔ካረገ ይለቀቃል
https://youtube.com/@Weygud18

#Subscribe እያደረጋቹ ቤተሰብ ስለምትሆኑ እናመሰግናለን #Subscriber
YouTube link👇
https://youtube.com/@Weygud18

መልካም ምሽት ተመኘሁ🙏
🎙ግሩፑን ለማግኘት
              👇👇👇

        @Mtshaf_bicha
        @Mtshaf_bicha
❤️ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
👉አሰተያየት ካላችሁ
📩 @Eyos18     አድርሱን
             📗📒📕📗📒📕
                Join&share
                  @EyosC1
       📚ማንበብ ባህላችን ይሁን📚
┄┉┉✽‌»‌🎶••✿••🎶»‌✽‌┉┉┄
‹‹እኔ ግን  አውቄያለሁ››
ሱሪውን ለብሶ ከላይ እራቃኑን እንደሆነ አጠገቡ ያለ ወንበር ላይ ቁጭ አለ‹‹እንዴት ልታውቂ ቻልሽ…..?እንኳን የእሷን  ታሪክ ይቅርና እኔን  ካወቅሽ እራሱ 24 ሰኣት አልሞላውም››
‹‹የፈለኩትን ነገር ማወቅ እችላለሁ…ንስሬ ከረዳኝ የፈለኩትን ነገር….››

‹‹አላምንሽም››

‹‹እሺ ጥቂት ደቅቃ ታገሰኝ ››አልኩና ወዲየው ትኩረቴን ወደንሰሬ በመመለስ ከአዕመሮው ጋር ተቆራኘው…..ለሶስት ደቆቃ ከቆየሁ በኃላ

‹‹እሺ ስማኝ …እንድታምነኝ አንተ ብቻ የምታውቀውን የራስህን ሚስጥር ነግራሀለው….ደቡብ አፍሪካ ለ2 ወር ታስረህ ነበር….ከሶስት ሴቶችና ከእንድ ተካልኝ ከሚባል ልጅ ጋር በደባልነት አንድ  ቤት ውስጥ ትኖሩ ነበር…ከሶስቱ ሴቶች  መካከል  ሁለቱን ሴቶች ታወጣቸው ነበር…..››

‹‹በቃ በቃ…..››

‹‹ያው እንድታምን ብዬ ነው…..››
‹‹አመንኩ እኮ …አደገኛ ጠንቆይ ነሽ….ምክንቱም ይሄንን ታሪኬን ለማንም ተናግሬ አላውቅም ..በተለይ የሁለቱ ሴቶችን ጋር ያለኝን ግንኝነት››

‹‹ምክንያቱም መንታ እህትአማቾች ስለሆኑ ትክክለኛ ስራ እንዳልሰራህ ስለሚሰማህ እና ፀፀት ስላለብህ..››ብላ ጨመረችለት፡፡

‹‹አዎ..ትክክል ነሽ…ግን አሁን ሰላም ምንድነው ችግሯ..ከፍቅረኛዋ ጋር ተጣልታ ነው…..?››

‹‹ፍቅረኛ የላትም….ማለቴ በፊት  ነበራት… ከተለያዩ ግን  አመት አልፏቸዋል…እረስታዋለች››

ፈገግ አለ‹‹ይሄንን በመስማቴ ደስ አለኝ….እሺ ሌላ ታዲያ ምን ሆና ነው…..? ስራ ተበላሽቶባት ነው..?››
‹‹ያለችበትን ችግር ምትገምተው አይደለም..››

‹‹እሺ ንገሪኛ..? ››

‹‹አባቷ ሞቶባት  ነው..››

መጀመሪያ ተደናግጦ ከተቀመጠበት ተነሳ..ከዛ መልሶ ቁጭ አለ..ለደቂቃ ተከዘ

‹‹እስከአሁን ያልሺው ሁሉ ትክክል ነው..ይሄ ግን የማይመስል ነው..አልነገርኩሽም እንዴ አንድ ሰፈር እኮ ነው የምንኖረው ..ዕድራችንም አንድ ነው….ቢያንስ እኔ ባልሰማ እናቴ ሰምታ ትነግረኝ ነበር..በዛ ላይ   እሷን የሀዘን ልብስ ለብሳ አያት ነበር ….››
‹‹አባቷ እንዲቀበሩባት ስለማትፈልግ ..መኝታ ቤቷ ውስጥ እንዳይበሰብሱ በማድረግ  ድብቃቸዋለች››

‹‹እንዴ!!!! ታዲያ ዝም ትያለሽ እንዴ....?እራሷን ብታጠፋስ....?ይሄንን ሁሉ ቀን የአባቷን እሬሳ ታቅፋ ለብቻዋ ስታድር ጄኒ ቢያጠናግራስ .. ..?እንዴ በቃ ብታብድስ…..?››ይሄን ሁሉ ሚናገረው በጥድፊያ ልብሱን እየለበሰና በተመሳሳይ ጊዜ ወደውጭ እየተንደረደረ ነው….እሷም ከኃላው  ኩስ ኩስ እያለች   ሚለውን ታዳምጣለች…

‹‹እውነት ከሆነ በጣም ነው የማዝንብሽ…..እንዳወቅሽ ልትነግሪኝ ይገባ ነበር…አንድም ሰከንድ ማባከን አልነበረብሽም ..አባቷን እንዴት እንደነፍሷ እንደምትወዳቸው ብታውቂ እንደዚህ ቸልተኛ አትሆኚም ነበር….››ወቀሳውን ሳያቆርጥ ከግቢው ወጥቶ በእግሩ ሊነካ ሲል…

‹‹ና በመኪና ላድርስህ….››ስትለው በደመነፍስ ተከተላትና ማጉረምረሙን ሳያቆርጥ  መኪና ውስጥ ገባ….ሞተሩን እስነስታ መንዳት ጀመረች..ፀጉሩን ይነጫል ….ጨንቅላቱን ይቀጠቅጣል..ከንፈሩን ይነክሳል
‹‹እንዲህ ከሆንክማ እንዴት ልንረዳት እንችላልን....?››አለችውት የእሱም ከቁጥጥር ውጭ መሆን አሳስቧት

‹‹እንዴት ልሁን ታዲያ …..?ሳለምዬ የአባቷን ሬሳ ታቅፋ አምስት ቀን ብቻዋን ባዶ ዝግ ቤት ውስጥ አድራለች እያልሺኝ እኮ ነው…››

‹‹እኮ አሁን ካለችበት ሁኔታ ይልቅ ወደፊት የሚከሰተው ነገር ይበልጥ ይጎዳታል… ስለዚህ እንዴት ልንረዳ እንደምንችል ለማሰብ ያንተ መረጋጋት ያስፈልጋል እያልኩህ ነው››

‹‹እሺ ንጂው…በእግዚያብሄር ፍጠኚ …ደግሞ ንስርሽ ከኃላ እየተከተለን ነው››

‹‹አዎ እሱ በጣም ያግዘናል…››

‹‹በፈጠረሽ …ምንም ነገር እንድትሆንብኝ እልፈልግም›››

‹‹አይዞህ…. ምንም አትሆንብህም…››

ከ25 ደቂቃ በኃላ ሳሪስ ደረሱ ..መኪናውን አቁመው ወደበራፍ  በመከተታል ተንደርደረው ደረሱ... ንስሯ ቀድሞ ግቢው ውስጥ ገባ..መጥሪያውን ተጫኑ..ደጋግመው  ተጫኑ…. እጃችን እስኪዝል በየተራ አንኳኩ ..ከውስጥ ከፋች ሊመጣ አልቻለም..

‹‹ትግስቴ አልቆል…  የግንቡን አጥር ዘለዬ  ልገባ ነው….››አላት በጭንቀት 

‹‹ግንቡ ላይ የተሰካውን የጠርሙስ ስብርባሪ እንዴት አድርገህ ታልፈዋለህ..?››

‹‹የራሱ ጉዳይ…የቆራረጠኝን ያህል ይቁረጠኝ… ››

‹‹ቆይ የተሻለ ዘዴ አለኝ ››አለችው
‹‹ምንድነው....?››

ንስሯን ጠራችው … ከገባበት ግቢ እየተመዝገዘገ መጣና  የፈለገችውን ሳትነግረው በመረዳት የለበሰችውን ልብስ አንገቷ አካባቢ በመንቁሯ ይዞ እያሽከረከረ ወደአየር ላይ ይዞት በመውጣት አጥሩን አሻግሮ ጊቤው ውስጥ ወለል ላይ አሳረፈት…  ከውስጥ የተቀረቀረውን በራፍ  ከፈተችለት…ኤርምያስ ተንደርድሮ ገባ..

‹‹ምን አይነት ተአምር ነው....?ምንድነሽ አንቺ..?›› እያለ ገፍትሯት ወደሳሎን ሮጠ… ሊያንኳኳ ሲሞክር ብርግድ ብሎ ተከፈተለት..ተከትላው ገባች..ወደየት እንደሚሄድ ግራ ገብቶት ሲደነጋገር ቀደመችውና ወደመኝታ ቤቱ አመራች..ምክንያቱም ቅድም ንስሯ በምናብ  እቤቱን በደንብ ስላስቃኛት ስለነበር  ታውቀዋለች..፡፡

መኝታ ቤት ሲገቡ …ሰላም ወለል ላይ ተዘርራ ግንባሯን ግዙፉ ፍሪጅ ላይ እስደግፋ በአንድ  እጇ የመጠጥ ጠርሙስ ጨብጣ በሌላ እጇ  የተለኮሰ ሲጋራ  ወደ ከንፈሯ በመላክ ወደውስጥ እየመጠጠች  ጭሱን  ወደውጭ እያትጎለጎለች  ትታያለች  …ከጎኖ 10 ሜትር የሚሆን የተጠቀለለ ሰማያዊ ሲባጎ ገመድ ይታያል….. ኤርምያስ ከእሷ ቀድሞ እሷንም ተራምዶ ወደፍሪጁ ሄደና ውስጡ ያለውን አየ…….

ወደኬድሮን በመዞር  ‹‹…እውነትሽን ነው…..››በማለት ከወገቡ ሽብርክ ብሎ ሰላም ጎን ወላሉ ላይ ተዘረፈጠ..እሷ በቃ ትንኝም በአካባቢዋ ያለ አልመሰላትም.. ፍጽም ደንዝዛለች…ጭርሱኑ ጠፍታለች…..


     ይቀጥላል።

አብዛኞቻቹ ወይም ባጠቃላይ ማለት ይቻላል የአገልግሎት ክፍያ እየከፈላቹ አደለም ክፍያውም አንብባቹ ስትጨርሱ👇👇👇

#ክፍል 56,,እንዲለቀቀ 👍(20) ሰው ከስር ያለውን ሊንክ #Subscribe🔔ካረገ ይለቀቃል
https://youtube.com/@Weygud18

#Subscribe እያደረጋቹ ቤተሰብ ስለምትሆኑ እናመሰግናለን #Subscriber
YouTube link👇
https://youtube.com/@Weygud18

መልካም ምሽት ተመኘሁ🙏
🎙ግሩፑን ለማግኘት
              👇👇👇

        @Mtshaf_bicha
        @Mtshaf_bicha
❤️ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
👉አሰተያየት ካላችሁ
📩 @Eyos18     አድርሱን
             📗📒📕📗📒📕
                Join&share
                  @EyosC1
       📚ማንበብ ባህላችን ይሁን📚
┄┉┉✽‌»‌🎶••✿••🎶»‌✽‌┉┉┄
‹‹በቃ አልቅሰሽ ቅበሪኝ….ከዛ በኃላ ሞተ የእያንዳንዱ ሰው ዕጣ ፋንታ መሆኑን አምነሽ ተቀበይና ወደ ህይወትሽ ተመለሺ…የራስሺኝ ሰው ፈልገሽ ኑሮሽን  ኑሪ….የእኔ በድን ታቅፈሽ እዚህ ቤት ባሳለፍሽው ስድስት ቀናት ውስጥ ስራ ላይ ብትሆኚ ኖሮ ሰንት ነፍስ  እንደምታታርፊ አስበሽዋል….… ?ስንት ያንቺን ክትትል የሚፈልጉ ህመምተኞችን እርግፍ አድረግሽ በመተውሽ  በያሉበት ምን ያህል እየተሰቃዩ እንደሆኑ ታውቂያለሽ….…?ያባትሽን መንፈስ ለዘላለም ለማስደሰት እውነታውን ተቀብለሽ  ፈገግ በይ ..በእኔ ስም የአዛውንቶችን ጤንነት ተንከባከቢ…እኔን እያሰብሽ ሞያሽን በጥንቃቄ እና በታማኝነት ስሪ..እያንዳንዱ ሰው ባንቺ እጅ ታከሞ በመዳኑ ተደስቶ ፈገግ ሲል  እኔም ባለሁበት  ፈገግ እንዳልኩ በማሰብ ውስጥሽ ሀሴት ታድርግ….›.

‹‹አዎ አባ እውነትህን ነው..እንዳልከው አደርጋለሁ››

‹‹ስለዚህ ተስማምተናል››

‹‹አዎ አባ ..ተስማምተናል››

‹‹በቃ ደህና ሁኚ ልሄድ ነው

‹‹አባ ከመሄድህ በፊት ››

‹‹እሺ ምንድነው…?››

‹‹ግን ገነት ነው ምትገባው አይደል…?››

‹‹አይ ልጄ..መች ሄድኩና አውቀዋለሁ ..ግን ምንም አይት ፍራቻ እየተሰማኝ አይደለም….እረፍትና እፎይታ ነው ዙሪያዬን የከበበኝ….የሚታየኝ  አንፀባራቂ ብርሀን እንጂ ፅልመት አይደለም….እና ፈጥኜ የመሄድ ፍላጎት ነው ያለኝ…ባከሽ ልጄ እንድዘገይ አታድርጊኝ..››

‹‹እሺ አባ ..አንድ የመጨረሻ ጥያቄ››

‹‹ምን ልጄ…?››

‹‹እማዬን ታገኛታለህ…?››

‹‹አዎ ልጄ ተስፍ አደርጋለሁ..በጣም መቸኮሌ አንድም ለዛ ይመስለኛል››

‹‹እንደምወዳትና በጣምም እንደናፈቀቺኝ ንገርልኝ››

‹‹እሺ ነገርልሻለሁ››
ደግሞ ቀኔ ደርሶ ወደእናንተ  ስመጣ ከእናንተ ጋር አብሬያችሁ መኖር ነው የምፈልገው››

‹‹እሺ ልጄ  እንዳልሽ…ደህና ሁኚልኝ…››

‹‹እሺ አባ ደህና ሁን››

     ይቀጥላል።

#ክፍል 57,,እንዲለቀቀ 👍(20) ሰው ከስር ያለውን ሊንክ #Subscribe🔔ካረገ ይለቀቃል
https://youtube.com/@Weygud18

#Subscribe እያደረጋቹ ቤተሰብ ስለምትሆኑ እናመሰግናለን #Subscriber
YouTube link👇
https://youtube.com/@Weygud18

መልካም ምሽት ተመኘሁ🙏
🎙ግሩፑን ለማግኘት
              👇👇👇

        @Mtshaf_bicha
        @Mtshaf_bicha
❤️ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
👉አሰተያየት ካላችሁ
📩 @Eyos18     አድርሱን
             📗📒📕📗📒📕
                Join&share
                  @EyosC1
       📚ማንበብ ባህላችን ይሁን📚
┄┉┉✽‌»‌🎶••✿••🎶»‌✽‌┉┉┄
የሆነው…›› ስትል እራሷን ጠየቀች፡ለመሄጃ 3 ደቂቃ ቀረው….ንስሩ ከነበረበት ጉቶ ጥቅልል ብሎ በመንሸራተት  መሬት ላይ ተዘረረ..እናቷም እሷም በደቂቃ ውስጥ ስሩ ደረሱ..አገላበጡት…ከአይኖቹ ደም እየፈሰሰ ነው…‹‹ወይኔ እማ ቅጠሉ….. ቅጠሉ ነው..መርዝ ነው የተጠቀመው..እማ ምን እናድርግ…?››የማሰቢያ ጊዜ ሳያገኙ ግቢያችን በሰማያዊ ብርሀን ተሞላ…ቀና ስትል በሰማይ ላይ ዲስክ መሳይ መንኮራኩር ብርሀን እየረጨች ሰማየ ሰማያትን በመሰንጠቅ እነሱ  ወዳሉበት አቅጣጫ እየወረደች ነው….መጡ ማለት ነው…መጡ መሰለኝ….ወይኔ ንስሬ….

  ተፈፀመ

#በአዲስ ታሪክ እንመለሳል‼️ ከተመቻችሁ 👍👍

ከስር ያለውን ሊንክ #Subscribe🔔ካረገ ይለቀቃል
https://youtube.com/@Weygud18

#Subscribe እያደረጋቹ ቤተሰብ ስለምትሆኑ እናመሰግናለን #Subscriber
YouTube link👇
https://youtube.com/@Weygud18

መልካም ምሽት ተመኘሁ🙏

🎙ግሩፑን ለማግኘት
              👇👇👇

        @Mtshaf_bicha
        @Mtshaf_bicha
❤️ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
👉አሰተያየት ካላችሁ
📩 @Eyos18     አድርሱን
             📗📒📕📗📒📕
                Join&share
                  @EyosC1
       📚ማንበብ ባህላችን ይሁን📚
┄┉┉✽‌»‌🎶••✿••🎶»‌✽‌┉┉┄
📍አንዳንዴ ምን ሆነሀል ስትባል የማትመልሰው ብዙ መሆን አለ። ለመናገር የማይመች ለመተው የማይቀል ብዙ ስሜት አለ ..ለአንተ የከበደ ለሌላው የቀለለ ነገር አለ ።

💡እንዴ ይሄ እኮ ቀላል ነው ይሄ እኮ አያስጨንቅም በሚባል ቃል የሚሸነፍ ለአንተ/አንቺ ግን የከበደ ስሜት አለ ።
ምን ሆነሀል ስትባል ምንም ብለክ የምታልፈው ውስጥህ ብቻ የምታንሸራሽረው እያዳመጥክ የምትታመምበት ። ከባድ ስሜት አለ ከባድ.......

✔️ምናልባት የምትፈልገው ስፍራ ላይ አልተቀመጥክ ወይንም የምትመኘውን ነገር አላገኘህ ይሆናል፣ ቢሆንም ተስፋ አትቁረጥ ፣ ተስፋ የመኖር ምክንያት ነውና፣

እየኖርን ነው አይደል? በሰው ሳይሆን በፈጣሪ!!
ትላንት የኖርነው ህይወት በነበር ይተካል፣
ሰዎችም ኖረው ነበሩ ይባላሉ፣
ፈጣሪን ግን ነበር ብለን አናወራውም ፤ ያለና የሚኖር ፣ በዛሬያችን ,በነጋችን አልፎም በዘላለም ውስጥ ኗሪ ነው ።
" የትላንት ነበሮቻችን በእሱ መኖር ተረስተዋል"

እናም  ወዳጄ

✔️አትድከም ፣ አትዘን ። ማንያውቃል ሸክምህ ህመምህ ሁሉ ተራግፎ ሌላ ሰው ሆነህ ትነሳ ይሆናል። ያለን ፈጣሪ እንኳን በአንድ ሙሉ ቀንና ሌሊት፣ በቅጽበት ጊዜ ዉስጥም ብዙ ተዓምር ይሠራል።

💡ንፋስ የማይወዘዉዘው ዛፍ የለም። ችግር ፣ ፈተና ፣ ሀሳብ ወስዶ የማይመልሰው ሰዉም የለም። እንዲህም ሆኖ የማይወድቅ ዛፍ አለ። በፈተና የሚፀና የሚበረታ ሰዉም አለ። ዐሳብህ ጉልበትህ ሥሮችህ ታክቶዋቸው በደከሙ ጊዜ ልብህ ብቻ ፈጣሪን ይዞ ይበርታ።


🚨በYouTube አማራጭ ይቀላቀሉን!
❇️SUBSCRIBE NOW
https://youtube.com/@Weygud18
https://youtube.com/@Weygud18

መልካም ግዜ 🙏

🎙ግሩፑን ለማግኘት
              👇👇👇

        @Mtshaf_bicha
        @Mtshaf_bicha
❤️ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
👉አሰተያየት ካላችሁ
📩 @Eyos18     አድርሱን
             📗📒📕📗📒📕
                Join&share
                  @EyosC1
       📚ማንበብ ባህላችን ይሁን📚
┄┉┉✽‌»‌🎶••✿••🎶»‌✽‌┉┉┄
💚ህይወት ከእናንተ ትጠብቃለች!

ዶ/ር ቪክቶር ፍራንክል (Dr. Victor Frankl) ይባላል። በ20ኛው ክፍለ ዘመን የነበረ ኦስትሪያዊ ታዋቂ ኒዎሮሎጂስት (Neurologist) እና ሳይኮሎጂስት (psychologist) ነው። በህይወትና የህይወትን ትርጉም በማግኘት ዙሪያ በሚያነሳቸው ሀሳቦችና አስተምህሮዎች ይታወቃል። በአንድ ወቅትም እንዲህ ብሎ ነበር፦ "ለምን እንደሚኖሩ ለማያውቁና ከህይወት ምንም ለማይጠብቁ ሰዎች ህይወት በእራሷ ከእነርሱ ሌላ ነገር እነደምትጠብ ማሳወቅ በጣም አስፈላጊ ነው።" የህይወት አላማችሁን ፍለጋ ብዙ ዋጋ ብትከፍሉም ላታገኙት ትችላላችሁ፣ ለዘመናት ስታደርጉት የነበራችሁት ነገር የሆነ ጊዜ ስትነቁ ትርጉም አልባ ሊሆንባችሁ ይችላል፣ ከዚህም በላይ ከእራሳችሁና ከህይወታችሁ ምንም የተሻለ እሴትን መጨመር የሚችል ነገር መጠበቅ ታቆሙ ይሆናል። ነገር ግን ይሔንን አስተውሉ። እናንተ በሰውኛ አዕምሮ አስባችሁ፣ አውጥታችሁ አውርዳችሁ ደክሟችሁና ሰልችታችሁ ያላገኛችሁት የህይወት ትርጉም ዝም ብላችሁ ስትኖሩና እያንዳንዱን ሃላፊነታችሁን ስትወጡ በሒደት ወደ እናንተ ይመጣል። እናንተ የምትኖሩት ህይወት አለ፣ ህይወት ደግሞ እንድትኖሯት የምትፈልግበት መንገድ አለ።

አዎ! ህይወት ከእናንተ ትጠብቃለች! እናንተ በህይወታችሁ ውስጥ ትርጉምን እንደምትፈለጉ ሁሉ ህይወታችሁም ከእናንተ አንድ የተለየና የእናንተ መገለጫ የሆነ ልዩ ነገር ትጠብቃለች። የህይወት አላማን ለማግኘት መውጣት መውረድ፣ እራስን ማታገልና ማስጨነቅ አያስፈልግም። አንዳንድ ክስተቶች እራሳቸው ፍሰት አላቸው፣ ሲጨመቁ ከሚያወጡት መልካም ነገር ይልቅ እንዲሁ በራሳቸው ሲፈሱና በኡደታቸው ሲጓዙ የሚያመጡት ውጤት ይበልጥ ትርጉም ይሰጣል። የትኛውም ትልቅ ነገር መነሻው ትንሽ ነው። "ህይወት ትርጉም አልሰጥ አለችኝ" ከማለት ይልቅ "ህይወት ከእኔ ምን ትጠብቃለች?" ብሎ መጠየቅ ብዙ የተደበቁ አቅማችንን እንድናወጣ ያግዘናል። በየትኛውም ዘርፍ ሊሆን ይችላል፣ በምንም ስራ ውስጥ ሊሆን ይችላል በእኛና በእኛ ብቻ መሞላት የሚችል ክፍተት አለ። ተምረን፣ አውቀን፣ ተረድተንና አስተውለን ወይም በተፈጥሮ በተሰጠን የተለየ ክህሎት ይህንን ክፍተት መሙላት አንችላለን። ዓለማችን በችግር የተሞላች ነች፣ ወረድ ስንል አህጉራችን ውስጥ የችግር መዓት አለ፣ ከዛም ወረድ ስንል ሀገራችን ውስጥ ብዙ ያልተፈቱ እንቆቅልሾች አሉ።

አዎ! ጀግናዬ..! ከምታየውና ከምትሰማው ችግርና ክፍተት ውስጥ ለአንተ የትኛው ጎልቶ ይታይሃል? የትኛውን ለመቅረፍ የቀረብክ ይመስልሃል? በየትኛው ላይ ብትሰማራ ነፍስህ የምትረካ ይመስልሃል? ትንሽ ጊዜ አስብ፣ ለተወሰነ ጊዜ አቅድ፣ በቀጣይ ግን ቀጥታ ትግበራውን ጀምር። ብዙ ሰው የማያየውን ነገር ማየት ስትችል ብቻ ከሰዎች የተለየ አዲስ ነገር ማከናወን ትችላለህ። ህይወትን በዓላማ መኖር ውስጥ እይታ፣ ዝግጁነት፣ ቆራጥነትና የተግባር ሰው መሆን በጣም አስፈላጊዎች  ጥበቦች ናቸው። እይታህ የምትሔድበትን አቅጣጫ ያጠራልሃል፣ ዝገጁነት በማንኛው ሰዓት ወደ ተግባር እንድትገባ ያደርግሃል፣ ቆራጥነት ከሃሳብ በላይ ተግባር ላይ እንድታተኩር ያደርግሃል፣ የተግባር ሰው መሆን ደግሞ በውድቀትና በስህተት ውስጥ አያሳለፍና እያስተማረ ለላቀው ውጤት ያበቃሃል። ቀላል፣ የተረጋጋና ትርጉም ያለው ህይወት ለመኖር እንቅስቃሴዎችህን ሁሉ ትግል አታድርገው። የዓለምን ክፍተት ፈልግ፣ ከፍላጎትህ ጋር አቆራኘው፣ እርሱን ለመሙላትም እንቅስቃሴህን ጀምር


🚨በYouTube አማራጭ ይቀላቀሉን!
❇️SUBSCRIBE NOW👇👇👇
https://youtube.com/@Weygud18
https://youtube.com/@Weygud18

መልካም ምሽት ተመኘሁ🙏

🎙ግሩፑን ለማግኘት
              👇👇👇

        @Mtshaf_bicha
        @Mtshaf_bicha
❤️ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
👉አሰተያየት ካላችሁ
📩 @Eyos18     አድርሱን
             📗📒📕📗📒📕
                Join&share
                  @EyosC1
       📚ማንበብ ባህላችን ይሁን📚
┄┉┉✽‌»‌🎶••✿••🎶»‌✽‌┉┉┄
“ደሃ እያለሁ ለምን የድህነቴን ምንጭ አላጣራም?”
*
በ10ሺ ዶላር የተገዛ የወርቅ ጫማ ፣በአልማዝ የተለበጠና 100ሺ ዶላር የተገዛ ሮሌክስ ሰዓት፣ 200ሺ ዶላር ያወጣ ሜርሴዲዝ ቤንዝ ካሉት በርካታ የቅንጦት እቃዎች ጥቂቶቹ ናቸው፡፡

ይህ ሰው የደቡብ ሱዳን ዜጋ ሲሆን በአንድ ወቅት የሀብቱን ምንጭ መንገግስት ለማጣራት ሲሞክር ሀብቱን ሰብስቦ ከሀገሩ አመለጠ፡፡

ታዲያ ይሄን ለምን እንዳደረገ ሲጠየቅ የመለሰው መልስ ሳቅን የሚያጭር ነበር፡፡

የመለሰው መልስ እንዲህ የሚል ነበር…“ደሃ እያለሁ ለምን መንግስት የድህነቴን ምንጭ አላጣራም?”

የአነጋጋሪውን ቢሊየነር ታሪክ በተከታዩ ቪዲዮ ይመልከቱት…

🚨በYouTube አማራጭ ይቀላቀሉን!
❇️SUBSCRIBE NOW👇👇👇
https://youtube.com/@Weygud18
https://youtube.com/@Weygud18

  መልካም ምሽት ተመኘሁ🙏

🎙ግሩፑን ለማግኘት
              👇👇👇

        @Mtshaf_bicha
        @Mtshaf_bicha
❤️ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
👉አሰተያየት ካላችሁ
📩 @Eyos18     አድርሱን
             📗📒📕📗📒📕
                Join&share
                  @EyosC1
       📚ማንበብ ባህላችን ይሁን📚
┄┉┉✽‌»‌🎶••✿••🎶»‌✽‌┉┉┄
ለውብ ቀን

ከዛ በላይ ናችሁ!

ማንም ምንም ይበላችሁ እናንተ ከዛ በላይ ናችሁ፣ ማንም ሰራችሁን ያጣጥል ስራችሁ ግን ከማንም ስራ በላይ ነው፣ ማንም በኑሯችሁ ይፈር ኑሯችሁ ግን ከማንም ኑሮ በላይ ነው፣ ማንም ከፊታችሁ ቆሞ እንደማትችሉ ይንገራችሁ አቅማችሁ ግን ከንግግሩ በላይ ነው። ከውጪ የሚመጣው ጫና ይቅርና በውስጣችሁ እንኳን የሚመላለሰው የገዛ ሃሳባችሁ ከእናንተ በላይ አይደለም። እራሳችሁን በጥራት የምትመለከቱባት የግል መነፅር አላችሁ፣ ለእራሳችሁ የምትሰጡት ቦታ አላችሁ። ውድድራችሁ ከሰዎች ንግግር ወይም ከውስጥ ጩሀታችሁ ጋር ሳይሆን ለእራሳችሁ ከሰጣችሁት ቦታ ጋር እንደሆነ አስተውሉ። ብለሃትንና ጥበብን ትምህርት ቤት ገብታችሁ አትማሩም። እውቀትን ታወሩት ይሆናል ጥበብና ብለሃት ግን በየቀኑ የምትኖሯቸው ናቸው። ጥበበኞች የማይጠቅማቸውን ንግግር አይሰሙም፣ ብልሆች ከጩሀት በላይ በሳል ንግግር ይገዛቸዋል። በየጊዜው ይማራሉ፣ እራሳቸውን በእውቀት መሰረት ላይ ያንፃሉ፣ መንፈሳቸው ጠንካራ ነው፣ ልብና አዕምሯቸው ቅርብ ለቅርብ ናቸው፣ ስለራሳቸው ሚዛናዊ ሀሳብን በማሰብ ይታወቃሉ፣ በእራሳቸው ያምናሉ ከእራሳቸው ጋር ስለሚያወሩት እያንዳንዱ ነገር በሚገባ ይጠነቀቃሉ።

አዎ! እናንተ ከዛ በላይ ናችሁ! ሳትኖሩ ከሚወራባችሁ፣ በጆሯችሁ ከሰማችሁት፣ አዕምሯችሁ ደጋግሞ ከሚነግራችሁ አሉታዊ ማንነት በላይ ናችሁ። ህይወታችሁ በመዳፋችሁ ነች። የትኛውንም ወደ አዕምሯችሁ የሚገባውን አሉታዊ ሀሳብ የማገድ መብት አላችሁ፣ የትኛውንም በአዕምሯችሁ ውስጥ የሚመላለሰውን መጥፎ ሀሳብ ጠራርጎ የማውጣት አቅሙ አላችሁ። የሰዎችን ሀሳብ በማሳደድ አትጠመዱ፣ ስለሚወራባችሁ ነገር ብዙ አትጨነቁ። "ሰዎች ስለእኔ ምን አሉ ሳይሆን እኔ ስለእራሴ ምን እላለሁ?" ብላችሁ ጠይቁ። በማንኛውም ሰዓት በምንም አይነት ሁኔታ ውስጥ እራሳችሁን ልታገኙ ትችላላችሁ፣ በየትኛውም ሰዓት ያልጠበቃችሁት ስፍራ ልትገኙ ትችላላችሁ። ይህም ሁኔታ የህይወታችሁ አንድ አካል እንጂ የህይወታችሁ መጨረሻ እንዳልሆነ አስተውሉ። ሁሉም ነገር በፍጥነት ይቀየራል፣ የትኛውም ከባድ ስሜት እንደ ንፋስ ያልፋል። በተፈጥሮ የደስታችን ጊዜ አጭር የመከራችን ወቅት ግን ረጅም እንደሆነ ልናስብ እንችላለን። ነገር ግን ልዩነቱን ያመጣው አስተሳሰባችን እንጂ በእርግጥም የጊዜው ርዝመት ተለያይቶ አይደለም።

አዎ! ጀግናዬ..! ከየትኞቹም ከባድ ሁኔታዎችህ በላይ ስለመሆንህ አትጠራጠር። የሚሆነው ይሆናል፣ የሚቀረው ይቀራል፣ የምትባለውን ትባላለህ፣ የሚሰጥህ ስም ይሰጥሃል በስተመጨረሻ ግን ህይወት በእራሷ አቅጣጫ ስትቀጥል ትመለከታለህ። አንተ ተስፋ ቆርጠህ ካልቆምክ ምንም የሚቆም የህይወት ፍሰት የለም። ብዙዎች ሰዎችን ሰምተው ባሉበት ቆመው ቀርተዋል፣ ብዙዎች ለራሳቸው በሰጡት መጥፎ ስም ምክንያት ህይወታቸውን ፈተና አድርገውታል። የምትሰማውም ሆነ የምታየው ነገር ሁሉ እውነት እንደሆነ መቀበል አቁም። እውነት የእምነት ቅጂ ነው። ጉዳዩ የሚያወራው ወይም የሚያሳይህ ሰው ሳይሆን የእራስህ አቀባበል ነው። ሀሳብ ሰውን ይገነባል፣ ሀሳብ ሰውን ያፈራርሳል። ማንም የማይገባበት የግል ዓለም እንዳለህ እወቅ። ያንተ ዓለም ያንተ ብቻ ነው። ከማንም ዓለም አያንስም ከማንም ዓለም አይበልጥም። በልብህ ያኖርከውን ያንኑ እምነት በገሃድ አውጥቶ ያሳይሃል። የግል ዓለምህን ጠብቅ። የማንም ሀሳብ ገብቶ እንዳይረብሸው ተጠንቀቅለት። በህይወት አጋጣሚ ከተገኘህበት ሁኔታ የተሻለ ስፍራ እንደምታደርሰው ቃል ግባለት።

🚨በYouTube አማራጭ ይቀላቀሉን!
❇️SUBSCRIBE NOW👇👇👇
https://youtube.com/@Weygud18
https://youtube.com/@Weygud18

#መልካም ቀን

🎙ግሩፑን ለማግኘት
              👇👇👇

        @Mtshaf_bicha
        @Mtshaf_bicha
❤️ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
👉አሰተያየት ካላችሁ
📩 @Eyos18     አድርሱን
             📗📒📕📗📒📕
                Join&share
                  @EyosC1
       📚ማንበብ ባህላችን ይሁን📚
┄┉┉✽‌»‌🎶••✿••🎶»‌✽‌┉┉┄
ለውብ ቀናችን

👍ከዚህ ይበልጣል!

አንዳንድ ሃሳቦች ሃሳብ ብቻ ናቸው፤ አንዳንዶችም ቅዠት ሊሆኑ ይችላሉ። ደጋግመህ ታስበዋለህ ነገር ግን ልታደርገው አትሞክርም፤ ደጋግሞ ይታይሃል፣ ይመጣብሃል ነገር ግን በእውን ልታየው አልቻልክም። ጀርባህ ብዙ ታሪክ፣ ኋላህ ብዙ እንቆቅልሽ፣ ብዙ ሸክም ይኖራል። በምንም ተዓምር በእንቆቅልሽ ማንነት፣ ባልተፈታ ታሪክ ታጅበህ ወደፊት መጓዝ፣ ሃሳብህን መኖር፣ እቅድህን መፈፀም፣ ህልምህን መኖር ሊቀልህ አይችልም። ምንም እንኳን መጠኑና አይነቱ ቢለያይም ሁሉም ሰው በህይወት አጋጣሚ በህመም ውስጥ ያልፋል፤ በስቃይ ይፈተናል፤ በግል አጣብቂኝ ውስጥ ይወድቃል፤ ደፋ ቀና ይላል፣ ይታገላል። የተደላደለ ህይወት ለማግኘት ብዙ ርቀት መጓዝ ይኖርበታል፤ ብዙ መሰናክሎችን ማለፍ ይጠበቅበታል፤ መወጣት የማይፈልገውን ሃላፊነት መወጣት ይጠበቅበታል።

አዎ! ጀግናዬ..! ሃላፊነትህ ቢልቅም፣ ተጠያቂነትህ ቢበዛም፣ ችግሮችህ ቢወሳሰቡም ህይወትህ ግን ከዚህ ይበልጣል፤ መቆየትህ ከዚህ ሁሉ ይልቃል። የሚሆኑ የማይመስሉ ታሪኮች ሊከሰቱ ይችላሉ፣ አጣብቂኞቹ ሊደራረቡ ይችላሉ፣ ፍላጎትና አሁናዊው አቅምህ ሊለያዩ ይችላሉ፣ ምኞትህና የጀመርከው መንገድም ሊራራቁ ይችላሉ። ነገር ግን በዚህ መሃልም ቢሆን መዳረሻህ አንድና አንድ ነው፤ በአዎንታዊነት ዘርፍ ከፍ ማለት፤ ጠቃሚ፣ ችግር ፈቺና አንተ የመጣህበት ከባድ መንገድ ላይ ያሉ ሰዎችን ማብቃት፣ መደገፍና አቅጣጫውን መጠቆም። የሆነው ቢሆንም የሚበልጠው ላይ ማተኮር ይኖርብሃል፤ እውነታውን ተቀብሎ መቆም ሳይሆን ወደፊት መጓዝ፣ መሰናክሎችን ተሻግሮ የተሻለውን ህይወት መፍጠር ይጠበቅብሃል።

አዎ! በጊዜ ብዛት የተገለጡ፣ ጊዜ ወዳንተ ያመጣቸው ጉዳዮች ፈቺው ጊዜያቸው ነው፤ የሚያቀላቸው እራሱ አምጪው አምላክ ነው። ፅናትህ እስከ ጥግ ሲሆን እንቆቅልሾችህ ይፈታሉ፤ ትዕግስትህ ሲበዛ የላቀውን ብለሃት ትጎናፀፋለህ። በደረሰብህ ጉዳይ ፈጥነህ ብይን አትስጥ፤ እራስህ ላይ ለመፍረድ፣ ማንነትህን ለመተቸት፣ መንገድህን ለማንቋሸሽ አትቸኩል። ሁሉም ሰው የተመረጠለት መንገድ በእርሱ በመራጩ በእግዚአብሔር ዘንድ ትክክልና እንከን አልባ ነው። ሁኔታህን መቃወም፣ ገጠመኞችህን መተቸት፣ በመጣህበት መንገድ ማፈር ከአምላክህ መቃረን፣ ፈጣሪህን መተቸትና በስራው ማፈር እንደሆነ እወቅ። መሰራት ባለብህ መንገድ ትሰራለህ፤ ብቁ መሆን በሚገባህ አቅጣጫ ብቁ ትሆናለህ። ዋናው ስቃይና ውድቀትህ ሳይሆን ዳግም መነሳትና የፈለክበት ስፍራ መድረስህ ነው።

🚨በYouTube አማራጭ ይቀላቀሉን!
❇️SUBSCRIBE NOW👇👇👇
https://youtube.com/@Weygud18
https://youtube.com/@Weygud18

#መልካም ቀን💚💛

🎙ግሩፑን ለማግኘት
              👇👇👇

        @Mtshaf_bicha
        @Mtshaf_bicha
❤️ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
👉አሰተያየት ካላችሁ
📩 @Eyos18     አድርሱን
             📗📒📕📗📒📕
                Join&share
                  @EyosC1
       📚ማንበብ ባህላችን ይሁን📚
┄┉┉✽‌»‌🎶••✿••🎶»‌✽‌┉┉┄