ፒያሳ መሃሙድ ጋ ጠብቂኝ
183K subscribers
280 photos
1 video
16 files
200 links
እዚህ Channel ላይ ያስተምራሉ ያዝናናሉ ብለን የምናስባቸውን
🎯ተከታታይ ልቦለድ
🎯ግጥም
🎯ወግ
🎯ፍልስፍና
🎯ምክር
🎯መነባንብ

#ማንኛውም አይነት ፅሁፎች📕 ከፈለጉ ይቀላቀሉን
የተለያዩ PDF መፅሐፍት ከፈለጉ @Eyosibooks
አስተያየት ካሎት👇👇
☎️• 0922788490

📩@Eyos18
Download Telegram
😎ጠላፊዎቹ

#ክፍል_ሃምሳ

#በኬንፎሌት

#ትርጉም_ወንዳየሁ_ንጉሴ



ናንሲ ሌኔሃን በተከራየችው አይሮፕላን በካናዳ ጠረፍ ላይ ስትበር ለችግሯ መፍትሄ ታያት፡ ወንድሟን መርታት ብቻ ሳይሆን አባቷ
ካስቀመጡላት የህይወት መርህ መውጣት ትፈልጋለች፡ ከመርቪን ጋር
መሆንም ትፈልጋለች፡ ሆኖም የጫማ ፋብሪካውን ትታ መርቪንን ተከትላ
እንግሊዝ ሃገር ሄዳ ብትኖር እንደ ዳያና የባሏን እጅ መጠበቅ የሰለቻት
ሚስት መሆኗ ነው፡

ናት ሪጅዌይ ኩባንያውን በተሻለ ዋጋ እንደሚገዛና በጄኔራል ቴክስታይል ጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ ከፍተኛ የኃላፊነት ቦታ እንደሚሰጣት ነግሯታል፡ ጄኔራል ቴክስታይልስ ደግሞ አውሮፓ ውስጥ ባብዛኛው በተለይም እንግሊዝ ውስጥ በርካታ ፋብሪካዎች አለው፡፡ ናት ሪጅዌይ ደግሞ ጦርነቱ ካላበቃ ፋብሪካዎቹን መጎብኘት አይችልም፡፡ ስለዚህ እሷ የፋብሪካ
ዎቹን የአውሮፓ የበላይ ሀላፊነት ቦታ ይሰጣታል፡፡ ይህ ደግሞ በራሱ
ከመርቪን ጋር ለመሆንና ስራ መስራት የሚያስችላት በመሆኑ ጥሩ ነው፡

መፍትሄው ጥሩ ይመስላል፡፡ አንድ የሚያስፈራ ነገር አውሮፓ ጦርነት ውስጥ ስላለች ልትሞት ትችላለች፡፡ ናንሲ ይህን ስታወጣና ስታወርድ
መርቪን ባህሩ ላይ የቆመውን አይሮፕላናቸውን አሳያት፡፡
መርቪን ከአይሮፕላኑ ጋር በሬዲዮ መገናኛ ለመገናኘት ቢሞክርም ምንም ምላሽ አላገኘም፡፡ ናንሲ አይሮፕላኗ ስታንዣብብ አዕምሮዋ ውስጥ የሚመላለሰውን ነገር ተወችው፡፡ ምንድን
ምንድን ነው የተፈጠረው?
አይሮፕላኑ ውስጥ አሉ? አይሮፕላኑ ሲታይ ምንም አልተጎዳም፡፡ ሆኖም
የሰው ዘር ያለበት አይመስልም፡፡

መርቪን ‹‹ምናልባትም ችግር ደርሶባቸው ከሆነ አርፈን ብናያቸው›› አለ፡፡ ናንሲ በመስማማት ራሷን ነቀነቀች፡፡

‹‹የመቀመጫ ቀበቶሽን በደምብ እሰሪ፡፡ ባህሩ ማዕበል ያለበት ስለሆነ
ስናርፍ ይንገጫገጫል፡››
ፓይለታቸው እንደ ፈረስ የሚጋልበው ባህር ላይ አይሮፕላናቸውን
አሳረፈ፡ ናንሲ እንደገመተችው ማዕበሉ አስቸጋሪ አልነበረም፡፡
አንድ የሞተር ጀልባ ከአይሮፕላኑ ጋር ታስሯል፡፡ ትልቁ አይሮፕላን በር ላይ አንድ ሰው እጁን ያውለበልባል። ከዚያም እነ መርቪን አይሮፕላናቸውን ከግዙፉ አይሮፕላን ጋር አሰሩት፡፡

ኔድ ‹‹እኔ አይሮፕላኔ ውስጥ እቆያችኋለሁ›› አለ ‹‹እናንተ ውጡ አይሮፕላኑ ምን ችግር እንደደረሰበት አጣሩ›› አላቸው፡፡

‹‹እኔም እመጣለሁ›› አለች ናንሲ፡፡

መርቪን መጀመሪያ ወደ አይሮፕላኑ ዘለለና ለናንሲ እጁን ዘረጋላት፡

በሩ ላይ የቆመውን ሰው ‹‹ምንድን ነው የተፈጠረው?›› ሲል ጠየቀው፡

‹‹ነዳጅ ስላለቀባቸው ነው ባህሩ ላይ ያረፉት›› ሲል መለሰ፡፡

‹‹በሬዲዮ መገናኛ ላገኛቸው ሞክሬ ነበር፡፡

ሰውዬውም ‹‹ወደ ውስጥ ግባ›› አለው፡

መርቪን ከገባ በኋላ ‹‹ምንድን ነው ችግሩ?›› ሲል ጠየቀ፡

‹‹አይሮፕላኑ ድንገት ነው ያረፈው›› አለ ወጣቱ ሰው ‹‹እኛ አሳ አጥማጆች ነን ስለዚህ ችግሩን ለማጣራት መጥተን ነው››

‹ካፒቴኑን እጠይቀዋለሁ›› አለ መርቪን፡፡

ወጣቱ ሰው በአለባበሱ አሳ አጥማጅ አይመስልም፡፡ ክራቫት አድርጓል፡፡
ናንሲ ሁኔታው አሳቃት፡፡

ወደ ውስጥ ገብተው ሲመለከቱ መምበሪ በደም ተለውሶ ወለሉ ላይ
ተዘርግቷል፡፡ አፏን ያዘች በድንጋጤ
‹ወይ አምላኬ! ምንድን ነው ችግሩ?›› ሲል መርቪን ጠየቀ ከኋላቸው ያለው ወጣቱ ሰው ‹‹ቀጥሉ ወደፊት›› አለ በቁጣ፡

ናንሲ ዞር ብላ ስታየው ሰውዬው ሽጉጥ ደግኗል፡፡ ‹‹አንተ ነህ እንዲህ ያደረከው?›› ስትል ጠየቀች
‹‹አፍሽን ዝጊና ቀጥ ብለሽ ሂጂ›› አላት፡፡

መብል ክፍል ውስጥ ገቡ፡፡
ሌሎች ሶስት ሽጉጥ የያዙ ሰዎች አሉ፡፡ አዛዣቸው የሚመስል አራተኛ
ሰው ቆሟል፡፡ ትንሹ ልጅ ከመርቪን ሚስት ኋላ ቆሞ ጡቷን ይጎነትላል፡
መርቪን ይህንን ሲያይ ተናደደ፡፡ ሶስተኛው ሰው የአይሮፕላኑ ተሳፋሪ
የሆነው ሉተር ሲሆን በፕሮፌሰር ሃርትማን ላይ ሽጉጡን ደግኗል፡
ካፒቴኑና የበረራ መሀንዲሱ ኤዲ የሚያደርጉት ጠፍቷቸው ዓይናቸውን
ያቁለጨልጫሉ፡ በርካታ ተሳፋሪዎች ወምበራቸው ላይ እንደተቀመጡ
ሲሆን ወለሉ ላይ የብርጭቆና የሰሃን ስብርባሪ ይታያል፡፡ ናንሲ ዙሪያውን ስታማትር በፍርሃት የተዋጠችው ማርጋሬት አይኗ ገባች፡፡
‹‹ላቭሴይ አምላክ ፊቱን አዙሯል፡፡ አይሮፕላን በምንፈልግበት ጊዜ
ደርሰህልናል፡ እኔን ቪንቺኒንና የእሱን ሰዎች በአይሮፕላን ይዘኸን ትሄዳለህ፡ ኤዲ ዲኪንማ ፖሊስ እጅ ሊጥለን ወጥመድ ሲያሰናዳልን ነው
የከረመው›› አለ ሉተር፡
መርቪን ከመገላመጥ በስተቀር ምንም መልስ አልሰጠውም፡፡

ባለመስመር ሱፍ ልብስ የለበሰው ሰው ‹‹የባህር ኃይል ወታደሮች
መጥተው ችግር ከመፍጠራቸው በፊት እንሂድ፡፡ ትንሹ ልጅ አንተ ላቭሌይን ይዘህ ና፡፡ ገርል ፍሬንዱ እዚሁ ትቆይ›› አለ፡፡
‹‹እሺ ቪኒ›› አለ ትንሹ ልጅ፡፡
ናንሲ ምን እየተካሄደ እንደሆነ ባታውቅም ወደኋላ መቅረት ግን አልፈለገችም፡፡ መርቪን ችግር ውስጥ የሚገባ ከሆነ ከጎኑ ትሆናለች፡፡

ቪንቺኒ ሌላ ትዕዛዝ ሰጠ፡፡ ‹‹ሉተር አንተ ሳይንቲስቱን ይዘህ ና፡›› ወደ ጆ ዞር አለና ‹‹በመጨረሻ ቆንጆዋን ሴት ይዘህ ና›› ሲል ትዕዛዝ ሰጠ፡፡

ሰውየው ዳያና ላቭሴይ ላይ ሽጉጡን ደግኖ ‹‹እንሂድ›› አላት እሷ ግን ከቦታዋ ንቅንቅ አልልም አለች፡፡ ናንሲ ሌላ ጥያቄ ጭንቅላቷ ውስጥ አጫረ፡ ዳያናን ለምንድን ነው የሚወስዷት? በኋላ ግን መልሱ ተከሰተላት
ጆ ቀጠለና በሽጉጡ አፈሙዝ የዳያናን ጡት ወጋ ሲያደርገው ጮኸች፡፡

‹‹ቆይ እስቲ›› አለ መርቪን፡፡

ሁሉም እሱ ላይ አፈጠጡ፡፡

‹ሁላችሁንም በአይሮፕላን እወስዳችኋለሁ። ነገር ግን አንድ ነገር ማሟላት አለባችሁ›› አላቸው

ቪንቺኒም ‹‹አፍህን
ዝጋና ተንቀሳቀስ፡፡ ምንም ቅድመ  ሁኔታ ማስቀመጥ አትችልም›› አለው፡፡

መርቪን እጁን ዘረጋና ‹‹እንግዲያውስ ግደሉኝ›› አለ፡፡

ናንሲ በፍርሃት ጮኸች፡
እነዚህ ሰዎች የሚዳፈራቸውን ሰው
ከመግደል ወደኋላ የሚሉ አይደሉም መርቪን  አላወቃቸውም አለች በሆዷ

‹‹ምንድነው ቅድመ ሁኔታው?›› ሲል ጠየቀ ሉተር

መርቪን ወደ ዳያና
አመለከተና ‹‹እሷ እዚሁ ትቆይ›› አለ ጆ በንዴት መርቪን ላይ አፈጠጠ፡፡

‹‹አንፈልግህም ብዙ የፓን አሜሪን ፓይለቶች ሞልተዋል፡፡ እነሱም
እንዳንተ ማብረር ይችላሉ›› አለ ቪንቺኒ፡

‹‹ሁሉም እንደዚህ አይነት ጥያቄ ሊያነሱ ይችላሉ›› አለ መርቪን፡፡
‹‹ጠይቋቸው ጊዜ ካላችሁ፡፡›› ወሮበሎቹ እነሱን ያመጣው ፓይለት መኖሩን እንዳላወቁ ተገንዝቧል፡

‹‹ሴትዬዋን ተዋት›› አለ ሉተር፡፡

ጆ በንዴት ፊቱ ቀላ፡፡

‹‹ለምን?››

‹‹እሷን ተዋት›› ሲል ጮኸ ሉተር፡፡ ‹‹እኔ ገንዘብ የከፈልኩህ ሃርትማንን እንድታፍንልኝ ነው እንጂ ሴት እንድትደፍርልኝ ነው እንዴ››

‹‹ሉተር ልክ ነው ጆ፡ በኋላ ሌላ ሴት ታገኛለህ›› አለው ቪንቺኒም:

‹‹እሺ›› አለ ጆ፡

ዳያና በእፎይታ አለቀሰች።

‹‹ጊዜ የለንም ከዚህ እንውጣ›› ሲል ቪንቺኒ አዘዘ፡፡

ናንሲ ‹መርቪንን ዳግመኛ አየው ይሆን?› አለች በሃሳቧ
ከውጭ ክላክስ ተሰማ፡፡ የጀልባው ነጂ ነው ክላክስ ያደረገው።
😎ጠላፊዎቹ

#ክፍል_ሃምሳ_አንድ

#የመጨረሻው ክፍል

#በኬንፎሌት

#ትርጉም_ወንዳየሁ_ንጉሴ


ጎረምሳውና ጆ ውሃ ውስጥ እየሰጠሙ ስታይ ጮኸች፡፡
ወጣቱ ልጅ ወደ ላይ ለመውጣት ሲሞክር ጆ ደግሞ ህይወቱን ለማትረፍ ወጣቱን ወደ ታች ይጎትታል፡፡ በጣም አስፈሪ ሁኔታ ነው የሚታየው፡፡
ማርጋሬት መጮኋን ሰምቶ ሉተር በመስኮት ተመለከተና ‹‹ባህሩ ውስጥ ወድቀዋል››› ሲል ጮኸ በጭንቀት፡፡

‹‹እነማ ናቸው?›› አለ ቪንቺኒ፡፡

‹‹ጎረምሳውና ጆ›› አለ ሉተር፡

የጀልባው ነጂ ገመድ ቢወረውርላቸውም ሁለቱ ሰዎች አላዩትም፡፡ እነሱ
የሚይዙትን አጥተው በፍርሃት ውሃ ውስጥ እየተንቦራጨቁ ሲሆን ጆ
ጎረምሳውን ልጅ ወደ ባህሩ ውስጥ እየደፈቀው ነው፡፡

‹‹እባክህ እርዳቸው›› አለ ሉተር እሱም በፍርሃት እየተንቀጠቀጠ፡፡

‹‹ምን?›› አለቪንቺኒ ‹‹ምንም ልንረዳቸው የምንችለው ነገር ያለ
አይመስለኝም፡ እነሱም ራሳቸውን ለማዳን አቅም የላቸውም፡፡›› በመጨረሻም
ሁለቱን ሰዎች ጨካኙ ባህር ሰለቀጣቸው፡

‹‹እንዴት ሊሆን ቻለ?›› ሲል ጠየቀ ሉተር ‹‹በመጀመሪያ ውሃ ውስጥዐእንዴት ሊወድቁ ቻሉ?››

‹‹ምናልባት የሆነ ሰው ገፍቷቸው ይሆናል›› አለ ቪንቺኒ፡

‹‹ማን?››

‹‹እዚህ አይሮፕላን ውስጥ የሆነ ሌላ ሰው ይሆናል፡›› ማርጋሬት የሁለቱን ሰዎች ንግግር ስትሰማ ስለነበር ሄሪ ሊሆን ይችላል› ስትል
ገመተች፡ ሄሪ ጀልባው ውስጥ ይኖር ይሆን?
ፖሊሶቹ አይሮፕላኑን
ሲፈትሹ እሱ የሆነ ቦታ ተደብቆ አይሮፕላኑ ባህሩ ላይ ሲያርፍ ከተደበቀበት
ወጥቶ ይሆን? ሁለቱን ወሮበሎች ውሃ ውስጥ ገፍቶ የጨመራቸው እሱ
ይሆን? እያለች መልስ የሌለው ጥያቄ በአዕምሮዋ ተጉላላ፡፡

በኋላ ደግሞ ወንድሟ ትዝ አላት ፔርሲ የወሮበሎቹ ጀልባ ከአይሮፕላኑ ጋር በሚታሰርበት ጊዜ ነው የጠፋው፡፡ ‹ምናልባትም መጸዳጃ ቤት ሄዶ ግርግሩ እስኪያልቅ እዚያው ሊቆይ አስቦ ይሆናል› አለች በሆዷ፡
እሱ ደግሞ እንዲህ አይነት ባህሪ የለውም፡፡ እሱ እንደውም ሁሉን ነገር
ለማወቅ ስለሚፈልግ ችግር አይፈራም፡፡

ሉተር ‹‹ሁሉ ነገር ከእጃችን እየወጣ ነው ምን ብናደርግ ይሻላል?›› ሲል ጠየቀ፡

‹‹አሁን በመጣችው አይሮፕላን እንሄዳለን እንዳቀድነው፡፡ አንተ፣ እኔና
ሳይንቲስቱ›› አለ ቪንቺኒ፡ ‹‹መንገዳችንን ሊያሰናክል የሚሞክር ሰው ካለ
በሆዱ ጥይት ልቀቅበት፡ አሁን ረጋ ብለን እንውጣ፡፡››
ማርጋሬት ወሮበሎቹ ፔርሲን ደረጃው ላይ ያገኙትና በሆዱ ጥይት
ይለቁበታል ብላ ሰጋች፡
ሶስቱ ሰዎች ከምግብ ቤቱ ሲወጡ የፔርሲ ድምጽ ከበስተኋላቸው
ተሰማ፡፡ ድምጹንም ከፍ አድርጎ ‹‹እንዳትነቃነቁ!›› አለ፡፡
ፔርሲ ቪንቺኒ ላይ ሽጉጡን መደገኑን ስታይ ማርጋሬት ዓይኗን ማመን አቃታት፡፡ የሽጉጡን አፈሙዝ አይታ ካፒቴኑ ከኤፍ.ቢ.አዩ ሰውዬ
ላይ የነጠቀው መሆኑን ገመተች፡

ቪንቺኒ ቀስ ብሎ ወደ ፔርሲ ዞረ፡፡

ማርጋሬት የወንድሟ ህይወት አደጋ ላይ ቢሆንም በፔርሲ ኮራች፡፡

የመብል ክፍሉ በሰው
ተሞልቷል፡፡ ከቪንቺኒ ኋላ ማርጋሬት ከተቀመጠችበት አጠገብ ሉተር በሃርትማን ላይ ሽጉጡን ደግኗል፡ በሌላኛው በኩል ናንሲ፣ መርቪን፣ ዳያና፣ ኤዲ እና ካፒቴኑ ቆመዋል ቪንቺኒ ፔርሲን ዘለግ ላለ ጊዜ አየውና ‹‹ልጅ ከዚህ ጥፋ›› አለው፡፡

‹‹ሽጉጥህን ጣል!›› ሲል ፔርሲ አዘዘ፡፡

በመሃል አንድ ጥይት ጮኸች፡፡ የጥይቱ ድምጽ ጆሮ ያደነቁራል፡
ማርጋሬት ጩኸቷን አቀለጠችው: ማን ማን ላይ እንደተኮሰ አላወቀችም:: ፔርሲ ምንም አልሆነም፡፡ ትንሽ ቆይቶ ቪንቺኒ ከደረቱ ላይ ደም እየተንፎለፎለ ተንገዳገደና መሬት ዘፍ አለ፡፡ በዚህ ጊዜ ቦርሳው
ሲወድቅ ተበረገደና ብሮቹ በደም ታጠቡ፡

ፔርሲ ቪንቺኒን ሲያይ ሽጉጡን ጣለ፡፡ ደንግጧል፡
ሁሉም ሰው ሽጉጥ የያዘው የመጨረሻው ወሮበላ ላይ አፍጧል፡

ካርል ሃርትማን በተፈጠረው
ሁኔታ ከተዘናጋው ሉተር መንጭቀው ራሳቸውን ነጻ አደረጉና መሬት ያዙ ማርጋሬት ሳይንቲስቱን ይገድላቸዋል ብላ ሰግታለች ፔርሲንም እንዲሁ፡ ነገር ግን ወዲያው የሆነው ግን
አስደንግጧታል፡፡

ሉተር አፈፍ አድርጎ ያዛት፡ ከወንበሯ ጎትቶ አነሳትና ጭንቅላቷ ላይ ሽጉጡን ደገነባት፡፡ በዚህ ጊዜ ሁሉም በድንጋጤ በድን ሆኑ።

ማርጋሬት ፍርሃት ስለገባት መንቀሳቀስ መጮህ አልቻለችም፡ የሉተር
ሽጉጭ ጭንቅላቷን እየወጋት ነው፡ ሉተር ራሱ ይንቀጠቀጣል፡፡ ከዚያም
ሳይንቲስቱን ‹‹ውጣና ጀልባ ውስጥ ግባ፡፡ ትዕዛዜን ካልፈጸምክ ልጅቷ
ጭንቅላት ላይ ጥይት እቀረቅርበታለሁ›› አለ፡፡
ወዲያው ፍርሃቷ ሲለቃት ታወቃት፡፡ ሉተር  ብልህ መሆኑን ተገንዝባለች፡፡ ሽጉጡን ሃርትማን ላይ ደግኖ ቢሆን ኖሮ ሃርትማን ግደለኝ ጀርመን አገር ከምመለስ ሞቴን እመርጣለሁ› እንደሚሉ እርግጠኛ ሆኗል፡ አሁን ግን የእሷ ህይወት አደጋ ላይ ነው፡ ሃርትማን ምናልባት
ህይወታቸውን ለመስጠት ዝግጁ ይሆኑ
ይሆናል፡፡

ሃርትማን ቀስ ብለው ተነስተው ቆሙ፡፡

ሁሉም ነገር በማርጋሬት ላይ የተጣለ ነበር፡ ራሷን ሰውታ ማዳን ትችላለች፡ ሆኖም ይህ አድራጎት ጥሩ አይደለም፡፡ እሷም ይህን አደርጋለሁ ብላ አልጠበቀችም፡፡ ለዚህ ራሴን አላዘጋጀሁም፡፡ ማድረግ አልችልም› አለች
በሆዷ፡
ከአባቷ ጋር ዓይን ላይን ግጥም አሉ፡፡ አባቷ በጣም ደንግጠዋል ሲያበሻቅጧት እንደኖሩ ምን ያህል
አቅመቢስ እንደሆነች ጦሩንም ተቀላቅላ አንድ ቀን እንኳን እንደማትቆይ
የነገሯት ሁሉ ትዝ አላት፡፡
አባቴ ያለው እውነት ይሆን?› አለች ለራሷ፡
ስለዚህ አንድ ነገር ማድረግ እንዳለባት ወሰነች፡፡ ሉተር ሊገላት ይችላል ነገር ግን አንድ ነገር ከማድረጉ በፊት ሌሎች ሰዎች ዘለው ይረባረቡበታል ጊዜው እየሄደ ነው፤ አንድ ነገር ማድረግ አያቅተኝም, አለች በሆዷ፡

ከዚያም ‹‹ሁላችሁም ደህና ሁኑ›› አለች፡፡ አፍታም ሳይቆይ የሄሪን ድምጽ ከኋላዋ ሰማች፡፡

‹‹ሚስተር ሉተር ጠላቂው መርከብህ ደርሷል›› አለ፡፡

ሁሉም ሰው በአይሮፕላኑ መስኮት ተመለከተ፡፡ ማርጋሬት ሄሪ በተናገረው ነገር ሉተር ልቡ መወሰዱን አወቀች፡፡ ከዚያ አንድ ጥይት ጮኸች፤ እሷ ግን ምንም አልሆነችም፡፡ ሁሉም አንድ ጊዜ ተንቀሳቀሰ፡፡ ኤዲ ዘለለና እንደ ተቆረጠ ዛፍ ሉተር ላይ ወደቀበት፡፡ ሄሪ የሉተርን ሽጉጥ
መንጭቆ ወሰደ፡፡

ፔርሲ ወደ ማርጋሬት ሄደና አቀፈችው፡፡ ‹‹አንተ ግን ደህና ነህ?››ቸ ስትል ጠየቀችው፡፡

‹‹አዎ ይመስለኛል››
‹‹በጣም ጎበዝ ነህ››
‹‹አንቺም እንዲሁ››
‹አዎ እኔ ጎበዝ ነኝ አለች ለራሷ፡
ፀጥ ብሎ የቆየው ተሳፋሪ ሁሉ በአንድ ጊዜ ተንጫጫ፡፡ በዚህ ጊዜ
ካፒቴኑ ‹‹ፀጥታ እባካችሁ ዝም በሉ›› አለ፡፡
ማርጋሬት ዙሪያውን ቃኘች፡፡
ሉተር ኤዲ እና ሄሪ ላዩ ላይ ወጥተውበት ከመሬቱ ላይ እንደተደፋ ነው፡፡ አይሮፕላኑ ውስጥ ያንዣበበው አደጋ ተወግዷል፡ ሃርትማንና
ሉተርን ሊወስድ የመጣው ጠላቂ መርከብ ተንሳፎ ይታያል፡

ካፒቴኑም የባህር ኃይል መርከብ በቅርብ ርቀት ይታያል፡ ‹‹ጠላቂ
መርከብ እዚህ እንዳለ የሬዲዮ መልእክት እናስተላልፋለን፡፡››
‹‹ቤን›› ሲል ተጣራ፡
‹‹አቤት ጌታዬ›› አለ የሬዲዮ ኦፕሬተሩ ‹‹የጠላቂው መርከብ አዛዥ
ሬዲዮ መልእክት ማስተላለፋችንን ካወቀ ወደ እኛ ሊተኩስ እንደሚችል
ተገንዝበኸዋል?›› አለ ቤን፡፡

‹‹ደህና ይቅር›› አለ ካፒቴኑ ‹‹ተሳፋሪዎቻችን እስካሁን የደረሰባቸው መከራ
ይበቃል፡››
ጠላቂው መርከብ መግቢያው እንደተዘጋ ነው አዛዡ  አንድ ነገር
ይሆናል ብሎ እየጠበቀ ነው፡፡

‹‹ቤከር አንድ ያልተያዘ ወሮበላ  ይቀረናል፡ እዚህ እንዲመጣ እፈልጋለሁ፡፡ የጀልባዋ ነጂ፡ ኤዲ ሂድና ቪንቺኒ እንደሚፈልገው ንገረው አለው
📕ተአምራተ_ኬድሮን

#ክፍል_ሃምሳ

#ተከታታይ ልቦለድ

#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ

‹‹ለማንኛውም ልድገምልሽ ኤርምያስ እባላለሁ…ለ15 ዓመት ያህል በማንዴላ ሀገር በሆነችው ደቡቡ አፍሪካ ጀሆንስበርግ ኖሬያለሁ… ወደሀገሬ ከተመለስኩ  ሁለት ዓመት ከግማሽ ሆኖኛል፡፡የ20ዓመት አፍላ ፍንዳታ ሆኜ ሄጄ የ35 ዓመት ሙሉ  ደንዳና ወጣት ሆኜ ተመለስኩ….››
‹‹አሀ ዲያስፖራ ነሀ….?››
‹‹አይ ዲያስፖራ ..!!! ‹ጽድቁ ቀርቶብኝ  በቅጡ በኮነነኝ ›ትላለች እናቴ… ለማንኛውም  እወነቱን ንገረኝ ካልሺኝ … በእነዛ ዓመታት ውስጥ በሰው ሀገር ላይ  ስዳክር ..ሞራሌን ከማንቆሻቆሽ…ሰው ሆኜ መፈጠሬን ከመጠየፍ እና ወጣትነቴ ላይ ጢቢ ጢቢ ከመጫወት ውጭ ምንም ያተረፍኩት ነገር አልነበረም…ብዙ ህልም በልቤ ብዙ ምኞት በውስጤ አጭቄ ነበር የተጓዘኩት …እርባነቢስ ሆኜ ባዶ እጄን በሀገሬ ለመሞት ብቻ ብዬ  ነበር የተመለስኩት …ይገርማል አይደል?
ሰው እንዴት ለመሞት ብሎ ከደብቡ አፍሪካ ድረስ ኪሎሜትሮችን አቆርጦ ይመጣል ትይኝ  ይሆናል..….?ለእኔ ግን ትርጉም ነበረው..››
‹‹ንገረኝ እስኪ ትርጉሙን…››ከሳዕታት ትርኪ ሚርኪ ወሬ እና መዛለል በኃላ ድንገት ምርር ወዳለ የህይወት ታሪክ ሀተታ መግባቱ አስደምሟታል አስደስቷታልም…አሁን እየነገራት  ያለውን ታሪክ እሱ ሳይነግራት እንደተለመደው  ወጭ እየጠበቀት ያለውን ንስሯን እንዲረዳት አድርጋ በዝርዝር ማወቅ ትችላለች..ግን አልፈለገችም …እንዲሁ እየጓጓችና ቀጥሎ ምን እንደሚናገር እየገመተች ቀጥታ ከራሱ አንደበት መስማቱ የሆነ የተለየ ስሜት ስለፈጠረባት ደስ ብሏታል…
ቀጠለ ‹‹በህይወቴ እያለሁ የመኖር ምኞቴ ሰልበው በድን አድርገውኝ …ወጣትነቴን ከንቱ አስቀርተውብኝ የመጨረሻውን ክስረት ማክሰራቸው ሳይበቃቸው …ከሞቴም በኃላ ክብር ስጋዬን  ለሀገራቸው ምድር  ልገብር …?አላደርገውም ፡፡ለዘላለም የባዕድ ሀገር አፈር ሆኜ መቅረት  አልፈለኩም  ..ይህ  መልካም አይደለም…ቢያንስ አገሬ እትብቴን በክብር በወርቃማ አፈሯ ውስጥ ቀብራ ከማንነቷ ጋር እንዳወሀደችው ሁሉ ስሞትም በድኔን በክብር ልትቀበለኝ እና ለዘላለም በጉያዋ ልትሸሽገኝ ይገባል..አዎ እንደዛ ነው መሆን ያለበት..በዛ ላይ እናቴን ለመጨረሻ ጊዜ ማየት እፈልጋለሁ… አያየኋት መሰናበት፤ስሮ በመኖር  እና እሷን መጦር ችዬ ላስደስታት  ባልታደልም… እጇ ላይ ሞቼ አልቅሳ ልትቀብረኝ እና እርሟን ለማውጣት እንድትችል ግን እድሉን ላመቻችላት ይገባል..አዎ ስመጣ እንደዛ ብዬ  እና እንደዛ ወስኜ ነበር …
‹‹ከዛስ….?››
‹‹ከደረስኩ ኋላማ … ቆይ ዛሬ ስል …ቆይ ትንሽ ልሰንብት ስል ..የመኖር ጉጉቴ ቀስ በቀስ ከሞተበት  እያንሰራራ እና እየተቀሰቀሰ መጣ..ምንም አግኝቼ አልነበረም ..ከእናቴ የማገኘው ተንሰፍሳፊ ፍቅር  እና ከጓደኞቼ የማገኘው ማፃናኛ …››
‹‹በጣም አሪፍ ታሪክ ነው ያለህ››
‹‹አዎ መራር የህይወት ገጠመኞች  ለሰሚው ወይም ለፅሀፊው ሳቢ ታሪክ ይወጣቸዋል…››
‹‹ከዛስ እንዴት ሀሳብህምን ሙሉ በሙሉ ልትቀይር ቻልክ….?››
‹‹አሁንም ሙሉ በሙሉ አልተውኩትም…አሁንም  የመሞት እቅዴ በውስጤ አለ…››
‹‹እሺ እንዴት ልታራዝመው ቻልክ….?››ጥያቄውን አስተካከለችለት፡፡
‹‹እንዴት መሰለሽ….ከዛ ከሰው ሀገር  በገንዘብም በመንፈስም ክስርስር ብዬ የመጣሁ ቢሆንም ብዙም ሳልቆይ ሚስኪን የልጅነት ጓደኞቼ  አዋጥተው አሁን የምጠቀምባትን ላዳ ገዝተው ሰጡኝ..በቃ የመሞት ሀሳቤን አራዘምኩት ..ለራሴ ሁለተኛ እድል ሰጠሁት..ቢያንስ ለጊዜው ሰርቼ ስጋዬን የማኖርበትን  ካገኘሁ አንድ ቀን ምን አልባት ሁለተኛውን የህይወት ምኞቴን በሆነ ተአምር ሊሳካልኝ ይችል ይሆናል…ብዬ ተስፋ አደረኩና መጨረሻውን እስከማይ ሁለት ዓመት ተኩል በሀገሬ ኖርኩ..ዘና ብዬ ለማንም ለምንም ሳልጨነቅ…ባሳኘኝ ሰዓት እየሰራሁ ሲያሰኘኝ ደግሞ እየተኛው..የእናቴን ሽሮ እየበላሁ ተስፋዬን በመጠበቅ እንሆ አለሁልሽ››
‹‹ምንድነው ተስፋህ..ማለቴ ይሳከልኛል ብለህ የምትጠብቀው….?››
‹‹የልጅነት ፍቅሬን… ..አንድ ቀን ቀና ብላ ታየኛለች የሚል ተስፋ..አንድ ቀን ከቄስ ትምህርት ቤት ጀምሮ እንደማፋቅራት እና ዕድሜዬን ሙሉ በልቤ ተሸክሜያት ስዞር እንደኖርኩ  ተረድታ በእቅፎ ታስገባኛለች ብዬ ተስፋ  በማድረግ..አንድ ቀን እጄ ትገባለች በሚል ተስፋ…..››

‹‹ወየው ጉዴ!!›አለኝች በውስጧ፡ በዚህ ቅርብ ጊዜ ውስጥ የምትቀርባቸውና የምትመኛቸው ወንዶች ሁሉ እንዴት እንዴት ሆኖና  ምንስ በሚሉት አጋጣሚ   እንደዚህ በፍቅር ስክር ያሉና የታወሩ ሆነው እንደሚገኙ ግልፅ ሊሆንላት አልቻለም...?‹‹ይሄኛውንስ ዛሬ አልምረውም…በፍጽም፡፡››ስትል ፎከረችው፡፡

‹‹ይቅርታ ሙሉ ታሪኩን እንድትነግረኝ እፈልጋለሁ….››

‹‹እየነገርኩሽ እኮ ነው …እየተረተርኩልሽ…..ሆድ ያባውን ብቅል ያወጣዋል አይደል የሚባለው››

‹‹አይ እዚህ አይደለም…እኔ ቤት እንሂድና ተረጋግተን እየጠጣን ታወራልኛለህ….አሁን ሆቴሉም ሊዘጋ መሰለኝ››

‹‹ይቻላል››ይከራከረኛል  ወይም ይቃወመኛል ብላ ነበር የጠበቀችው ..ቀድሟት ተነሳ ..ሂሳብ ከፍላ ተከተለችው …. እየተወለጋገድና እርስ በርስ እየተደጋገፉ ላደው ድረስ ሄድ ..ሹፌሩ ተቀብሏቸው እቤት ድረስ አደረሳቸውና የለሊቱን ግዳጅ ጨረሶ  ተለያቸው.. 
እሷም ዛሬ ለዛውም ከመሸ ያወቀችውን ባለ ላዳ ይዛው  ወደቤቷ ገባች…..

            ይቀጥላል

#ክፍል 51,,እንዲለቀቀ (10) ሰው ከስር ያለውን ሊንክ #Subscribe🔔ካረገ ይለቀቃል
https://youtube.com/@Weygud18

#Subscribe እያደረጋቹ ቤተሰብ ስለምትሆኑ እናመሰግናለን #Subscriber
YouTube link👇
https://youtube.com/@Weygud18

መልካም ምሽት ተመኘሁ🙏
🎙ግሩፑን ለማግኘት
              👇👇👇

        @Mtshaf_bicha
        @Mtshaf_bicha
❤️ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
👉አሰተያየት ካላችሁ
📩 @Eyos18     አድርሱን
             📗📒📕📗📒📕
                Join&share
                  @EyosC1
       📚ማንበብ ባህላችን ይሁን📚
┄┉┉✽‌»‌🎶••✿••🎶»‌✽‌┉┉┄
📕ተአምራተ_ኬድሮን

#ክፍል_ሃምሳ_አንድ

#ተከታታይ ልቦለድ

#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ

መኝታ ቤቷ ገብታ ልብሷን ከቀያየረች በኋላ የጀመሩትን አይነት መጠጥ  አምጥታ ለሁለቱም ቀዳችና ወደጫወታቸውን እዲመለሱ ተመቻቸች..

‹‹እሺ አሁን ካቆምክበት ጀምርልኝ››

‹‹ምን….? ››አለት ሁሉን ነገር የረሳው ይመስላል

‹‹ታሪክህን እየነገርከኝ ነበር››

‹‹እ..አዎ…ግን የት ላይ  ነበር ያቆምኩት….?››

‹‹ስለፍቅረኛህ ጀምረህልኝ ነበር..በህይወት የምትኖርበት ምክንያት እሷን አንድ ቀን አገኛት ይሆናል በሚል ጉጉት ምክንያት እንደሆነ ነግረኸኝ ነበር ያቆምከው››

‹‹አዎ….አይገርምሽም …

እስከጥቂት ቀናት ድረስ እኮ ምንም አይነት ተስፋ አልነበረኝም…››
‹‹ቆይ ጠይቀሀት እንቢ ብላህ ነው….?››

‹‹አረ መጠየቅ…ትቀልጂያለሽ እንዴ ….?ቀና ብዬ እንኳን ሰላምታ ልሰጣት ድፍረቱ የለኝም.››

‹‹ግን እኮ እንደዛ አይነት ሰው አትመስልም..በጣም ደፋር ግልጽ እና በራስ መተማመን ያለህ ሰው ነህ››አለችው ከልቧ..

‹‹እኔም እንደዛ ነኝ ብዬ አምናለሁ..ፍቅር የሚባለው ነገር ግን ዋና ባህሪው ያልሆንሺውን ሆነሽ እንድትገኚ ማድረግ ይመስለኛል…እጅግ ክፉ የነበርሽው ሰው በፍቅር ውስጥ ስትሆኚ ስጋዬን ግፈፉት እስከማለት ድርስ የሚደርስ ደግነት ያጓናጽፍሻል….ደንዳናና ኮስታራ የነበርሽው፤አልቃሽና ተርበትባች ሆነሽ ቁጭ….ፍቅር እንደዛ  አይነት በሽታ ነው፡፡››

‹‹ቢሆንም ….ይህን ያህል ካፈቀርካት የሆነ ነገር ማድረግ ነበረብህ ..ለመሆኑ የት ነው የምትኖረው….?››

‹‹የሚገርመው እሱ ነው..በእሷ ቤት እና በእኔ ቤት መካከል ያለሁ እርቀት ግማሽ ኪሎ ሜትር አይሆንም…. ሁለታችንም ሳሪስ  በአንድ ሰፍር ተወልደን እዛው አንድ ሰፈር ያደግን ነን…ቤተሰቦቻን የአንድ እድር አባል ሆነው፤አንድ የጽዋ ማህበር መስርተው ዕድሜያቸውን በጉርብትና  የኖሩ ናቸው….አንድ ቄስ ትምህር ቤትፊደል መቁጠር ጀምረን   .አብረን ኤለመንተር የገባን የእድሜ እኩዬች ነን››

‹‹ይገርማል!!››

‹‹እውነትሽን ነው በጣም ይገርማል…. ከ1ኛ ክፍል አንስቶ እስከ አስረኛ ክፍል አብረን ነበር  የተማርነው…በተለይ ዘጠነኛ ክፍል አንድ ወንበር ላይ ነበር የምንቀመጠው…ግን በወቅቱ እኔ  ግማሽ ልቤ ነበር ክፍል ውስጥ የሚገኘው… እሷ ደግሞ አካሏም ነፍሶም ትምርቱ ላይ የተጣበቀ ነበር፡፡ግን የሚያመሳስለን አንድ ነገር ቢኖር  ሁለታችንም ተአምር ካልተፈጠረ በስተቀር ከትምህርት ቤት አንቀርም ነበር..››

‹‹ለምን ….?››አለችው ገለጻው ገርሞት

‹‹እሷ ለትምህርት ባላት ፍቅር የተነሳ እኔ   ደግሞ ለእሷ ካለኝ ፍቅር  የተነሳ….››

አሳቃት….ብርጭቆውን አንስቶ ከተጎነጨለት በኃላ ቀጠለ

‹‹እሷ እንደማንኛውም የክፍል ጓደኛ ግን ደግሞ ከዛም ትንሽ ከፍ ባለ የሰፈር ልጅነት እና አብሮ አደግነት ነው የምትቀርበኝ…እኔ ደግሞ በዚህ አለም ላይ ሁለት ሴቶች ብቻ ናቸው ያሉኝ.. እናቴ እና እሷ ብቻ..በቃ..ያኔ  አብሬት በምማርበት  በዛ ጊዜ ብቻ አልነበረም እንደዛ የሚሰማኝ.. አገር ለቅቄ  በስደትም እያለው እንደዛ ነበር  እምነቴ…የሆነች ሴት በሆነ ነገሮቾ ትንሽም እንኳን ከእሷ ጋር ካልተመሳሰለችልኝ..የሆነ የእሷን ነገር እንዳስታውስ  ካላደረገችኝ አንድ ደቂቃም ላወራት ወይም አጠገቧ ልቀመጥ አይቻለኝም….ከአስር አመት መለያየት በኃላ ከ10 ዓመት ናፍቆት በኃላ እሷን እና እናቴን አንዴ አይቼ ለመሞት ወስኜ  ወደሀገሩ ስመጣ…እሷን በተመለከተ ጭራሽ ተስፋ የሚያስቋርጥ ነገር ነው ያጋጠመኝ…፡፡አፍላ ልጃገረድ ገና አጎጠጎጤ ሆና ጥያት የሄድኳት  ልጅ አድጋና ፈክታ ሙሉ ሴት ሆና ጠበቀችኝ…፡፡የ10ኛ ክፍል ተማሪ ሆና የተለየኋት  ልጅ ዶክተር ተብላ ትልቅ ሆስፒታል ውስጥ ትልቅ  ባለሞያ ሆና አገኘኋት..እና የሩቅ ህልሜ የነበረችው ልጅ ጭራሽ መቼም የማትፈታ ቅዠቴ እንደሆነች አሰብኩ…ሳያት በሩቅ መሸሽ ጀመርኩ፡፡ድንገት መንገድ ላይ ስንገጣጠም እንኳን   ቅንድቤን ከፍ ዝቅ በማድረግ አንገቴን አቀርቅሬ  ሰላምታ  ለመስጠት ከመሞከር ውጭ እሷ እንኳን ለሰላምታዬ አፀፋውን መመለሷ እና አለመመለሷን  እርግጠኛ ሆኜ አላውቅም፡፡ይህቺ ልጅ የእኔ ልጅነቴ ነች….የሩቅ እሩቅ ትዝታዬ …ብዙ ብዙ ለሊቶች በህልሜ ያየኋት… ብዙ ብዙ ታሪክ ያጫወተችኝ….ብዙ ብዙ ነገር ያወጋኋት…ያወጋችኝ..፡፡እንደዛ ብቻ ሳይሆን ደጋግሜ ያገባኋት…ብዙ ብዙ ልጆች የወለደችልኝ…ብዙ የሳምኳት፤ ብዙ የሳመችኝ…ብዙ ያፈቀርኳት፤ብዙ የወደደቺኝ…ግን ሁሉም በህልሜ የሆነ ነበር …››

‹‹ምን አይነት ፍቅር ነው..ስል አሰብኩ ደግሞ ከዚህች ልጅ ጋር የሚያመሳስለኝ አንድ ነገር ይኖር  ይሁን .. ….?አዎ መኖርማ አለበት ….እደዛ ቢሆን ነው ይሄን ሁሉ ሰዓት አብሮኝ ያሳለፈው…እቤቴ ድረስ ተከትሎኝ በለሊት የመጣው…አዎ እንደዛ ቢሆን ነው ሚስጥሩን ዘክዝኮ የሚነግረኝ…››ስትል የራሷን ግምት ወሰደች…ግምቷ እውነት ሆኖ  እስከአልጋ መዋደቅና መዋሰብ ድረስ ያደርሷቸው እንደሆነ አሁንም በውስጧ እያሳላሳላች ነው ፡
ቀጠለ እሱ…‹‹እና ይገርምሻል ከሶስት ቀን በፊት  ያልጠበቅኩት አጋጣሚ ተከሰተ…››

‹‹ምን ተከሰተ….?››

‹‹ወደሀገሬ ከተመለስኩ ከሁለት ዓመት ተኩል በኃላ   ትናንት….ድብር እና ጭፍግግ ብሎኝ ሰፈር ላዳዬ  አቁሜ እኔም ላዳዬ  ውስጥ ወንበሬን ወደኃላ ለጥጬ መፅሀፍ በማንበብ በተመስጦ ላይ እያለሁ...በሀይለኛው የላዳው የኃላዋ በራፍ ሲንኳኳ የሆነ  የእብድ ድርጊት መስሎኝ  በርግጌ ተነሳሁና  አንገቴን በመስኮት አስግጌ  ወደ ኃላው ተመለከተኩ…

‹‹እንዴ ሰላም…!!!!!››

‹‹ክፈትልኝ››

‹‹እሺ ››ተረብትብቼ ከፈትኩላት..ተስፈንጥራ ገባች…የሆነ ሰው ከኃላ እያባረራት ይመስላል..ፀጉሯ ሁሉ ጭብርር ብሏል…የአይኖቾ ደም መልበስ ምን አልባት ለቀናት ስታለቅስ እንደቆየች ምስክር ናቸው…..አለባበሶም እንደነገሩ እና ያልታሰበበት ነው….››የአመታት ህልሜ የሆነች ልጅ በእንዲህ አይነት ያልታሰበበት አጋጣሚ ላዳዬ ውስጥ ትገባለች ብዬ እንኳን ማሰብ አልሜ እንኳን አላውቅም…..

‹‹ንዳው ››አለችኝ
ህልም ውስጥ ያለሁ ነበር የመሰለኝ ፡፡ ትዛዞን ተቀብዬ  …ሞተሬን አንቀሳቀስኩ እና  ነደሁት

‹‹-የትኛው ፖሊስ ጣቢያ እንሂድ….?››ጠየቅኳት

‹‹የምን ፖሊስ ጣቢያ….?›› አለችን ግራ በመጋባት

-‹‹አይ እንዲሁ ነገር ስራሽን ስገመግመው  የሆንሽው ነገር ያለ ስለመሰለኝ ነው..››

‹‹ሆኜያለሁ...አዎ የሆነ ነገር ሆኜያለሁ… መች አልሆንኩም አልኩህ …ግን ወደ  ፖሊስ ጣቢያ መሄድ ምን ይፈይድልኛል..….?››አለቺኝ.‹‹ይቅርታ እሺ የት ልወስድሽ..….?››አልኳት
በመለማመጥ..እወነቴን ነው በዛች ላዳ ጆሀንስበርግ  አድርሰኝ ብትለኝ እንኳን እድሜ ልክ ይውሰድብኝ እንጂ እንቢ አልላትም…በምን አቅሜ…በእሷ መታዘዝ እኮ ለእኔ እድል ነው…የአለምን ህዝብ አጥፋልኝ ብትለኝ እንኳን ባልችልም  ከመሞከር ወደኃላ አልልም፡፡ 
‹‹እኔ እንጃ የሆነ ሰው እንደእኔ ሲሆን የት ነው የሚሄደው..….?ወይም የት ነው መሄድ ያለበት..››በቀላሉ ልመልሰው የማልችለውን ውስብስብና  ግራአጋቢ ጥያቄ ጠየቀችኝ ‹‹እኔ እንጃ ምን አልባት ቤተክሪስትያን ልውሰድሽ….?››ይሻል የመሰለኝን አማራጭ አቀረብኩላት ፡
📕ታምራተ_ኬድሮን

#ተከታታይ ልቦለድ

#ክፍል_ሃምሳ_ሁለት

#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ

‹‹ከተለየኋት በኋላ ስለእሷ ማሰብ ላቆም አልቻልኩም ነበር..እንዴት አድርጌ ከዚህ ሀዘን ላወጣት  እችላለሁ….?እንዴት አድርጌ ላግዛት እችላለሁ….? የግድ አባቷ እስኪመጡ መጠበቅ የለብኝም..አባቷ ስል አባቷ ብቻ አይደሉም እናቷም ጭምር.. ጓደኛዋም ጭምር እንደሆኑ መላ ሰፈሩ ያውቃል..ብቻቸውን ነው ያሳደጎት….እድሜ ልኳን ከአባቷ ተለይታ ኖራ አታውቅም..ይሄንን ማንም ያውቃል…ዩኒቨርሲቲ ጎንደር ደርሷት መለያየት ግድ በሆነበት ጊዜ እንኳን  እሷ ከአንተ ተለይቼ መሄድ ስለማልችል ትቼዋለሁ ስትል..አባቷም እውነትሽን ነው አንቺ ትምህርትሽን ከምትተይ እኔ አብሬሽ ሄዳለሁ በማለት…ስራቸውን ከአዲስ አበባ ወደ ጎንደር በመቀየር አብረዋት ዘምተዋል…ይህ ሀገር የሚያውቀው ሀቅ ነው……..አሁን አባቷ ለጉዳይ ወደውጭ ሀገር እንደሄዱ ነግራኛለች….ስጨነቅ አንግቼ  በማግስቱ ያለውን ቀንም በተመሳሳይ መሸበር አሳለፍኩ

…..ግን……?››

ድንገት ንግሩን አቋረጥኩትና ‹‹አልደከመህም መኝታ ቤት ሄደን አልጋ ላይ አረፍ ብለን የቀረውን ትጨርስልኝ….?››አለችው  

‹‹በቀላሉ  ያልቃል ብለሽ ነው….?››

‹‹እንሞክረው….?››

ደስ እንዳሽ ብሎ ብርጭቆውን ይዞ ተነሳ.. ቀድማው ወደመኝታ ቤት አመራች፤ እየተንጋዳገደ ከኃላ ተከተላት….የእሱና የሰላም የፍቅር ታሪክ ብቻ ሳይሆን የእሷ እና የእሱንም መጨረሻ እንዴት እንደሚጠናቃቅ ማወቅ አጓጓት
///

መኝታ ቤት ገብተው አልጋ ላይ ጎን ለጎን ትራስ በመደገፍ ጋደም ብለው ከተመቻቹ በኃላ ወሬውን ካቆሙበት ቀጠሉ፡፡

‹‹እና እንደነገርኩሽ በእሷ ጉዳይ ስጨነቅ አድሬ ስጨነቅ ውዬ …ከእንደገና መልሼ መጥፎ ለሊት ካሳለፍኩ በኃ
ኋላ ዛሬ ጥዋት ስልኬ ጠራ …አነሳሁት‹‹ሄሎ››

‹‹ሄሎ››

‹‹ማን ልበል….?››ስል ጠየቅኩ፡፡

‹‹ትናንት ማታ ያደረስከኝ ልጅ ነኝ..ቁጥርህን ከተውክልኝ ካርድ ላይ አግኝቼው  ነው››አለቺኝ.…

እንደዛ በፍጥነት ትደውልልኛለች ብዬ አላሳብኩም ነበር..ትናንትና ስልክ ቁጥሬን ፅፌ ትቼላት ሰወጣ ለምን አልባቱ ብዬ ነበር..ምን አልባት በዛ ስካር ውስጥ  ሆና የሰጠኋትን ወረቀት ቀዳዳም ቆሻሻ ቅርጫት ውስጥ ልትጥለው ትችላላች የሚልም ግምት ነበርኝ..እና ደወለችልኝ ..ለዛውም ገና በጥዋት4 ሰዓት…እንደደረስኩ መኪናዬን ዳር አስይዤ  አቆምኩና ወርጄ የውጩን በራፍ እንኳኳሁ…ከፈተችልኝ….

‹‹እሺ ደህና ነሽ ግን….?››
ጥያቄዬን ችላ ብላ ‹‹አሁን እየጠበቅኩህ ነው ና››አለችኝ 

‹‹አቤት….?››አልኳት ይበልጥ እንድታብራራልኝ ፈልጌ 
እሷ እቴ ስልኩን  ጆሮዬ ላይ ጠረቀመችው

‹‹ይህቺ ልጅ ጤናም የላትም እንዴ . ….?.››አልኩና የላዳዬን ሞተር በማስነሳት ወደቤቷ ተፈተለኩ..እንዴ እሷ ና ብላኝ እንዴት እዘገያለሁ….?፡፡ 

‹‹ታዲያ እቤት ስትሄድ አገኘሀት….?››ኬድሮን ነች የጠየቀችው በእጇ ከያዘችው ብርጭቆ መጠጥ አንዴ እየተጎነጨች
‹‹አዎ ..እንደደረስኩ መኪናዋን ዳር አስይዤ  አቆምኩና ወርጄ የውጩን በራፍ እንኳኳው…እራሷ ከፈተችልኝ….ጉስቁልናዋ እንዳለ ነበር..ስልችት ብሏታል…የሆነ ልቧን ስብብርብረ ያደረገው ነገር እንዳለ እርግጠኛ ነኝ..እንደውም የፍቅር ነገር ይመስለኛል….››

‹‹እሺ ማን ነበረ ስምህ….?›› አለችኝ ግድ የለሽ እና አናዳጅ በሆነ የድምጽ ቅላፄ….አይገርምሽም ዕድሜሽን ሙሉ ያመለክሽው ልጅ… ስንት ቀን እና ሌት የናፈቃሽው እና በትዝታው የተሰቃየሽለት ልጅ -ማን ነበር ስምሽ ሲልሽ…..….?

በውስጥሽ  የሚፈጥረው ስሜት ግማሽ ህልውናሽ  የመደምሰስ አይነት ነው …..እመኚኝ በጣም ነው የሚያመው …እሷ ግን ለእኔ የስሜት መጎዳት ቁብ ሳይኖራት፤.መልሴንም ለመስማት ትግስት አጥታ ወደትዕዛዞ ተሸጋገረች

‹‹ካላስቸገርኩህ የሆነ ቦታ ትወስደኛለህ…….?››

‹‹የፈለግሺው ባታ …ተዘጋጂና ነይ መኪና ውስጥ እጠብቅሻለሁ››ብዬ ወደላዳዬ ፊቴን አዞርኩ‹‹አይ ላዳህን ወደግቢው አስገባት እና አቁማት.. በእኔ መኪና ነው የምንሄደው፤ ከከተማ ወጣ ማለት ነው የፈለግኩት…..››አለቺኝ፡
ግራ ግብት እንዳለኝ ወደኃላዬ ተመለስኩና ላዳዬ ውስጥ ስገባ እሷ ደግሞ የውጩን በራፍ ከፈተችልኝ…ወደ ጊቢ ውሰጥ አስገባኋትና ሚጢጢ ላዳዬን  ግዙፍ የእሷ ላንድኩሩዘር መኪና ጎን አቆምኳትና ሞተሩን አጥፍቼ ወጣሁ… በሩን ዘግቼ ቆምኩ..
‹‹እሷ ወደሳሎን ተመልሳ እየገባች ነበር…ደግሞ የሰውነቷ ቅርፅ ከቁመቷ ጋር ያለው ምጣኔ እንዴት አባቱ ያምር ነበር መሰለሽ…..5 ደቂቃ ሳትቆይ ተመልሳ ወጣችና የሳሎኑን በራፍ መቆለፍ ጀመረች ….በእጇ ካንጠለጠለችው ቦርሳ በስተቀር ምንም  የያዘችውም ሆነ የቀየረችው ነገር አልነበረም… እንደነበረችው ነው ተመልሳ የመጣችው..ዝንጥንጥ ብላ የምትመጣ መስሎኝ ነበር..ግን በለበሰችው ቱታ ሱሪ እና ቲሸረት ነው አሁንም ያለችው..ስሬ እንደደረሰች ከቦርሳዋ ውስጥ ቁልፍ አወጣችና ወረወረችልኝ …በአየር ላይ ቀለብኩና ወደመኪናዋ ተንቀሳቀስኩ…..ሞተሩን እስነስቼ ከግቢሁ ከወጣሁ በኋላ አቁሜ ጠበቅኳት… የውጩውን በራፍ  በመዝጋት እና በመቆለፍ መጣችና ጋቢና  በመግባት ከጎኔ ትቀመጣለች ብዬ ስጠብቅ  የኃላውን በራፍ ከፍታ ገባች……››

‹‹ምነው እዚህ አይሻልሽም….?›› ልላት ነበር ..ግን አንደበቴን ማላቀቅ አልቻልኩም…በእስፖኪዬ ወደኃላ ተመለከትኳት ….ግማሽ እሷነቷ ሞቶ ግማሽ እሷነቷ ብቻ በህይወት እና በሞት መካከል ያለ ይመስላል..ልክ እኔ  ለመሞት ወደሀገሬ ልግባ ብዬ በወሰንኩበት በዛ ጭለማ ጊዜ የነበርኩበትን ሁኔታ አስታወሰችኝ ….

‹‹ሰላም ወዴት ነው የምንሄደው..….?››ብዬ ጠየቅኳት

‹‹አቤት›› አለችኝ እንደመባነን ብላ
‹‹ወዴት ልንዳው ነው ያልኩሽ….?››

‹‹ወደ ፈለከው…. ግን ከከተማ ውጭ እና ፀጥ ያለ ቦታ ይሁን እንጂ ወደየትም ይሁን …..››
‹‹እሺ››
‹‹ግን ስሜን መቼ ነው የነገርኩህ….….?ሰላም ብለህ የጠራህኝ መሰለኝ….?››

‹‹ነግረሺኝ አይደለም…››

‹‹እና እንዴት  አወቅከው…..….?››

‹‹አውቄውም አይደለም…ሰላም ማለት ለእድሜ ልኬ ያፈቀርኳት..አሁንም ድረስ የማፈቅራት ከህጻንነቴ ጀምሮ የማውቃት ፤መቼም ልረሳት የማልችላት  ልጅ ስም ነው…እና ያው ፍቅሯ ጅል አደርርጎኛል መሰለኝ ብዙ ሴቶችን ሰላም ብዬ መጥራት እወዳለሁ…››አልኳት….ሽሙጤ ሳይገባት….ፈገግ አለችና‹‹ ይገርማል እንደአጋጣሚ የእኔም ስም ሰላም ነው››አለችኝ 

‹‹አውቃለሁ››

‹‹ማለት›….?›››መልሶ  ግር ብሏት

‹‹በመልክም በጣም ትመሳሰላላችሁ ልልሽ ፈልጌ ነው››
ዝም አለች….በጦር ኃይሎች አድርገን በ18 ማዞሪያ ታጥፈን በአንቦ መስመር አሸዋ ሜዳን አቆርጠን ወደቡራዬ ተጓዝን…እሷ እውነትም እንዳለችው ወደየትም ብነዳው ግድ ያላት አትመስልም ነበር..አይኗን በመኪናው መስታወት ወደውጭ ልካ በየመንገዱ ዳር ያለውን ትዕይንት ምታይ ትመስላለች ….ግን አታይም እሳቤዋም እይታዋም ከውስጧ ጋር እንደሆነ ያስታውቃል…ብራዩንም አለፍን ፣እኔም አላቆምኩም እሷም አቁም አላለችኝ…ግን ጊንጪ ልንደርስ ኪሎ ሜትሮች ሲቀረን  የሆነ ለጥ ያለ ሜዳ ጋር ስንደርስ…..‹‹ይቅርታ ማን ነበር ስምህ...….?››ስትል ከሳዕታት ዝምታ በኃላ አብሻቂ ጥያቄ ለሁለተኛ ጊዜ ጠየቀችኝ….
📕ታምራተ_ኬድሮን

#ተከታታይ ልቦለድ

#ክፍል_ሃምሳ_ሶስት

በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ



‹‹አዎ…እናቴ እና ሰላም ያልኩሽ የማፈቅራት ልጅ ትዝ ሲሉኝ››
-‹‹በዛ ሰዓት ላይ ሁለቱም ባይኖሩ ኖሮ…..መቼም እንዳማታገኛቸው እርግጠኛ ሆነህ ቢሆን ኖሮስ….?››ዘግናኝ ጥያቄ ጠየቀችኝ

‹‹እኔ እንጃ…እንዳልሞት የሚያደርገኝ ምንም ምክንያት የሚኖር አይመስለኝም››ስል በታማኝነት መለስኩላት፡፡

‹‹ለምን….?››ጠየቀችኝ
‹‹ሁለቱ መላ አለሜ ናቸው…እነዚህ የነገርኩሽ ሁለቱ ሴቶች እና ሌላው ዓለም እኔንም ጨምሮ በሌላ ሚዛን ቢሆን ሚዛን ሚደፉት እነሱ ናቸው…..ስለዚህ እነሱ  የሌሉበት  ዓለም ምን ይረባኛል…››

‹‹አየህ ትክክል ብለሀል..እኔ አሁን ያለሁበት ሁኔታ አንተ አንደገለጽከው ነው…እስከአሁን እራሱ ለምን እንደቆየሁ አላውቅም…….?››ብላ የሆነ አዲስ ነገር እንደተገለጽላት ተመራማሪ  ፈገግ ብላ ከተቀመጠችበት  ተነሳች ‹‹ እንሂድ ›› ብላ ጠርሙሷን ይዛ ምንጣፉን ባለበት ጥለ መራመድ ጀመረች…

-‹‹እንዴ ወዴት….? ››

‹‹ወደቤት ….ወደቤት መልሰኝ››

ደነገጥኩ…. ሳላስበው የማይሆን ነገር እንደተናገርኩ ገባኝ…ገደል አፋፍ ላይ ያለን ሰው ከኃላ መግፋት አይነት የቀሺም ሰው ተግባር ነው የሰራሁት..

‹‹ምንጣፉስ..››

ግዴለሽ በሆነ የድምፅ ቃና‹‹ከፈለከው ያዘው›› አለችኝ፡፡ጠቅለል ጠቅለል አደረኩና ወስጄ ኮፈን ውስጥ ከተትኩት፡፡ከዛ ወደመኪናው ገባሁና ወደኃላ አዙሬ የመልስ ጉዞ ….ብራዩ እንደደረስን የሆነ ነገር ማድረግና አሁን ካለችበት ስሜት እንድትዘናጋ ማድረግ እንዳለብኝ   ወሰንኩ…

‹‹..በጣም አመመኝ..››አልኳት …ቀና ብላ አየችኝና ምንም ሳትናገር መልሳ ወደ ሃሳቧ ተመለሰች…..መኪናዋን ወደዳር አውጥቼ አቆምኩ

‹‹ምነው….?››ኮስተር ብላ

‹‹ሆዴን ቆረጠኝ ››

‹‹ማለት….?››

‹‹እኔ እንጃ እራበኝ መሰለኝ..ከነጋ ምንም አልቀመስኩም… ለዛ ይሆናል..ረሀብ ደግሞ አልችልም››

‹‹እና ምን ይሻላል ….?››አለች እንደመበሳጨት ብላ

‹‹በቃ እኔ ሳልበላ መንዳት አልችልም….››

‹‹እሺ ጥሩ  ቁልፉን ስጠኝ…. እኔ ጊዜ ማባከን አልፈልግም …አንተ ብላና በትራንስፖርት ና››የሚል ሀሳብ አቀረበች

‹‹ለምን የሚሆን ጊዜ ነው ማባካን የማትፈልጊው….?››ስል ጠየቅኳት፡፡

‹‹እቤት ተመልሼ በፍጥነት ማድረግ ያለብኝ ነገር አለ››

‹‹እሺ ነይ…አልኩና ቁልፉን ነቅዬ ከመኪናው ወረድኩ.. እሷም ካለችበተ የኋላ ወንበር ወርዳ ወደጋቢናው ስታመራ ፈጠን ብዬ ሁሉንም በር ጠረቀምኩትና ቁልፍን እያንቀጫጨልኩ   በአካባቢው ወደአለ ሆቴል ጉዞ ጀመርኩ

‹‹ምን እያደረክ ነው….?››

‹‹ምሳ በልቼ እቤትሽ አደርስሻለሁ..አንቺ ስለጠጣሽ መንዳት አትችይም…››

‹‹ምኑ ነህ..….?አሁን ለአንድ ቀን ባትበላ አትሞት…ደግሞ ብትሞትስ ከመኖር ምን ሲገኝ…››

‹‹ግድ የለም.. ልብላና አብሬሽ እሞታለሁ››

‹‹መቀለድህ  ነው..….?››ተከተለችኝና ከፊት ለፊቴ ወንበር ስባ ተቀመጠች…ምግብ አዘዝኩ እስኪመጣ ወሬ ጀመርን 
‹‹በነገራችን ላይ አባትሽን በቅርብ አይቼው አላውቅም..?››

‹‹የለም››

‹‹የት ሄዱ….?››

‹‹ወደ ውጭ ሄዷል››

‹‹አሀ …ለዛ ነዋ እንዲህ ዓለም ድብልቅልቅ ያለችብሽ….?››

‹‹እንዴት እንዲህ ልትል ቻልክ….?››

‹‹በአባትሽ እና በአንቺ መካከል ያለውን ግንኙነት እና ቀረቤታ እኮ ሙሉ ሰፈሩ ነው የሚያውቀው.. እንኳን እኔ ቀርቶ የዛሬ አመት እዛ ሰፍር የገባ ሰው ሳይቀር ያውቃል…››

‹‹አንዴ አንተም እኛ ሰፈር በቅርብ የገባህ መስሎኝ….  ባልሳሳት ሁለት  አመት ..ከዛ ይበልጥሀል..?››

‹‹የእውነትሽን ነው..አታውቂኝም….?›› በእድሜዬ  ከደነገጥኩት በበለጠ መጠን ደንግጬና ተሸማቅቄ ጠየኳት

‹‹ማለት አንተ ታውቀኛለህ እንዴ….?››

……የምመልሰው ነገር ሲጠፋኝ  ሳቅኩ

‹‹የሚያስቅ ነገር ተናገርኩ እንዴ…››

‹‹አይ ታውቀኛለህ ስትይ ገርሞኝ ነው….ራስህን ታውቃለህ ወይ ብለሽ ብትጠይቂኝ ይሻላል..ግንባርሽ ላይ ያለውን ስንጥቅ ጠባሳ ምን እንደሆነ ልንገርሽ…….?››

‹‹እንዴት ልትነግረኝ ትችላለህ..….?

እሱ እኮ እፃን ሆኜ የሆነ ነገር ነው››

‹‹አዎ ቄስ ትምህርት ቤት አባ ገብረክርስቶስ ጋር ስንማር ድብብቆሽ በምንጫወትበት ጊዜ ልትደበቂ ስትሮጪ  አደናቅፎች ወድቀሽ ብረት ግንባርሽን ሰንጥቆሽ አይደል…?››

አይኖቾ ፈጠጡ ‹‹እንዴ !!!አዎ ትክክል ነህ ..ማነህ አንተ….?..››

‹‹ኤርሚያስ››

‹‹ኤርሚያስ ..ኤርሚያስ እንዴ ኤርሚያስ ካሳ እንዳትሆን……….?››የሆነ የቆየ ህልም የማስታወስ ያህል ተደንቃ

‹‹አዎ ነኝ››

‹‹ታዲያ በጣም እኮ ነው የተቀያየርከው…አረጀህ… በጣም…ደግሞ ከሀገር  ወጥተህ አልነበር…..….?››

‹‹ኦዋ ሁለት  ዓመት አለፈኝ  ተመልሼ   ከመጣሁ..››

‹‹እና ይሄን ሁሉ ጊዜ   ሳታናግረኝ…….?››

‹‹እኔ እንጃ እንደመጣው ጥሩ ስሜት ላይ ስላልነበርኩ ላናግርሽ ጉልበቱ አልነበረኝም….››

‹‹ትክክል አልሰራህም…ጓደኛች ነበርን አይደል….….?.››መገረሟ ሳይገታ የታዘዘው ምግብ መጣ..እሷ ለምግቡ  ደንታም ሳይሰጣት ብላክ ሌብል ታመጣልኝ አለችው አስተናጋጁን….

‹‹አይቻልም..››አልኳት ቆፈጠን ብዬ
‹‹ለምን…….?ዝም በለውና አምጣልኝ ››አምጣላት …ግን ከበላሽ ነው የምትጠጪው..

‹‹አረ ባክህ ››

‹‹እውነቴን ነው››

‹‹እሺ ..››አለች.. እየቆነጠረች ከምግቡ ለመቅመስ ሞከረች እኔ እየለመንኩም እያስገደድኩም አንድ ሶስት ደህና ጉርሻ አጎረስኳት…
ከዛ መጠጧን ጀመረች ‹‹….ይገርማል  ..ዱርዬ ነበርክ እኮ …አሁን የተለየ እና የተረጋጋ ሰው ሆነሀል››

‹‹ምን ታደርጊዋለሽ ህይወት ትገራሻለች… ኑሮ ይሞርድሻል…መከራ ያስተካክልሻል ወይም ያበላሽሻል፡፡››

‹‹ለምን አንተም አትጠጣም….?››

‹‹ጥሩ ሀሳብ ነው..ግን መኪናውን ማን ይነዳል…….?››

‹‹ግድ የለም ..የሆነ መላ እንፈልጋለን..….?››ልክ ቅድም ላንቺ ታዝዤ አብሬሽ መጠጣት እንደጀመርኩ ..ለእሷም ተስማምቼ አዘዝኩ …የልጅነት ነገር ምንም ሳይነሳ የቀረ ትውስታ የለም..ከማስበው በላይ ስለልጅነታችን ታስታውሳለች…ያ ደግሞ ደስታ ፈጠረብኝ….እሷም ከነበረችበት ስሜት በሆነ ጠብታ ቢሆንም የመረጋጋት ሁኔታ  ታየባት
ተመልሰን ቅድም ለቀነው ወደወጣነው ቤት የሄድን
 
‹‹እየተቆነጠረ የሚመጣው ውስኪ ሊያረካን ስላልቻለ..ሙሉውን አዘዝን…››

ኬድሮን ቆይ ቆይ ..››ብላ አስቋመችው 

‹‹ምነው ደከመሽ..እንተኛ?››

‹‹አይ አንዴ ሽንቴን….›› አለችና ከመኝታዋ ወርዳ ወደሽንት ቤት ሳይሆን ወደሳሎን ሄደች….ይህቺ ታሪኳ ለሊቱን ሙሉ የተነገረላት  ፍቅረኛው የሆነ ችግር ላይ እንደሆነች እየተሰማት ነው ..አዎ ስሜቷ እየነገራት ነው….ለዚህ ነው ወደሳሎን የሄደችው …ንስሯን ፈልጋ..‹‹አይ የኔ ነገር ..››አለች . የዚህ ባለ ላዳ ታሪክ ንስሯንም እንድትዘናጋ ስላደረጋት እራሷን ታዘበች…ሳሎን ሶፋ ላይ ኩርምት እንዳለ ተኝቷል….አስነሳችው….‹‹ ‹‹አብሮኝ ያለው ልጅ ፍቅረኛ..ማለቴ የሚወዳት ልጅ ችግር ላይ ትመስለኛለች..አሁኑኑ ሄደህ ያለችበትን ሁኔታ አጣራልኝና  ና…አሁኑኑ……ትንሽ ከዘገየን የሚረፍድብን ይመስለኛ…››
📕ተአምራተ_ኬድሮን

#ተከታታይ ልቦለድ

#ክፍል_ሃምሳ_አራት

በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ


የንስሯ ጭንቅላቷ ላይ ማረፍ ነበር ከእንቅልፏ ያባነናት….በመከራ አይኗን ገልጣ ዙሪያዋን ስትቃኝ እራሷን  እዛው ቅድም የተዘረረችበት ወለል ላይ እርቃኗን አገኘችው….ባለ ላደውም የሞተ እስኪመስል ድረስ ትንፋሹ ጠፍቶ እግሮቾ  መካከል ጭንቅላቱን ቀብሮ በተመሳሳይ እርቃኑን ተዘርሯል ….ቀስ ብላ ከላዮ ላይ ገልበጥ  አደረገችውና እና እራሷን በማላቀቅ  ሾልካ ወደ ሻወር በመሄድ ለ5 ደቅቃ ውሃ በላይዋ ላይ አፈሰሰችና..
ከዛ ወደመኝታ  ቤቷ ተመልሳ ቢጃማ ለበሰችና ባለ ላዳውን እንደምንም እየጎተተችም እየደገፈችውም ወስዳ አልጋው ላይ በማስተኛት ብርድልብስ ካለበስችው በኋላ ወደሳሎን አመራች…..ንስሯም ተከተላት..፡፡
አዎ ሊነጋ  መሆኑን ከውጭ የሚሰማውን የወፎች  ዝማሬ በማዳመጥ ተረዳች …ሳሎኖ እንደደረሰች ተስተካክላ ከተቀመጠች በኋላ ንስሯ ያየውን  እንዲያሳየት… ያወቀውን እንዲያሳውቃት አዕምሮዋን ከእሱ ጋ አቆራኘችው…
ሰላምና አባቷ…ፍቅራቸው ከአባትና ከልጅም የዘለል አይነት ነው..ኤርምያስ እንዳለው እናትም አባትም ወንድምም እህትም ሆነው ነው ያሳደጎት…ግን አሁን ስላለችበት ሁኔታ ብቻ ያለውን ታሪክ ከንስሯ በተረዳችው የሚከተለውን ነው
ቀጥታ ቤታቸው ገባች… መኝታ ቤት ወደመሰላት ክፍል ተጓዘች… አዎ ትክክል ነች ያልተነጠፈ እና የተዝረከረከ አልጋ … አልጋው ላይ የተዘረረች ውብ ለጋ  ሀዘን የሰበራት ወጣት ተኝታለች…..ወለሉ ጠቅላላ በመጠጥ ጠርሙሶች እና በተበታተኑት ልብሶች ተሞልቷል..አንድ ግዙፍ  አራት መአዘን  ፍሪጅ አልጋውን ተደግፎ   ይታያል…ትኩረቷን ወደፍሪጁ አመዘነበት… ውስጡን አየችው… .ህልም ውስጥ ነኝ እንዴ ያስብላል… …ነጭ ሱፍ ለብሶ ነጭ ሸሚዝና ቀይ ከረባት ያደረገ  እንቅልፍ የተኛ የሚመስል ሰው ፍሪጅ ውስጥ ይታያል.. ..አባቷ ነው ….የሰላም አባት..አሁን የሆነ ነገር የገባት ነው..ልጅቷ እንደጠረጠረችውም  አደጋ ላይ ነች…ሰላም አባቷን አጥታለች..ሰላም አባቷን መሬት ውስጥ ቀብራ ለዘላላም ለመለየት ድፍረቱንም ጭካኔውንም ለማግኘት አልቻለችም….
/////
ነገሩን በዝርዝር ለመረዳት  አምስት ቀን ወደኃላ እንመለስ 
እንደማንኛውም ቀን እየተጎራረሱ እራት በሉ…እያተሳሳቁ ዜናና ፊልም አዩ…አራት ሰዓት አካባቢ ወደመኝታቸው አመሩ….ሰላም አባቷን መኝታ ቤት አስገብታ እንዲተኙ ካደረገች  በኃላ ግንባራቸውን ስማ ተሰናብታ ወደመኝታዋ ልትሄድ ስትል

‹‹ሰላሜ››ሲሉ ጠሯት

‹‹አቤት አባ›››

‹‹አብረሺኝ ተኚ››
ዘላ አልጋው ላይ ወጣችን ብድርብሱን ገልጣ ከውስጥ በመግባት እቅፋቸው ውስጥ ገባች…..ይህ አዲስ ነገር አይደለም..ተለያይተው ከሚተኙበት ይልቅ አንድ ላይ የሚተኙባቸው ቀናቶች የበዙ ነበሩ..ሁለቱም ትንሽ ሲከፋቸው ወይንም አመም ሲያደርጋቸው..ወይንም እንዲሁ ለብቻ መተኛት ሲደብራቸው ዛሬ እኔ ጋር ትተኚ..?ዛሬ አብረሀኝ ትተኛ..? እየተባባሉ አንድ ቀን እሷ ክፍል አንድ ቀን እሳቸው ክፍል ይተኛሉ..እና የተለመደ ነው፡፡
ችግሩ ንጊ ላይ ከእንቅልፏ ባና ከእቅፋቸው ስትወጣ ነበር የተፈጠረው….እጃቸውን ከሰውነቷ ላይ ሳታነሳ በተለየ ሁኔታ ቀዘቀዛት…..ቀስ ብለ ወጣችና አየቻቸው..ጸጥ ያለ ፊት ነበር..ዝም ያለ ፊት…እጇን ወደ አንገታቸው ላከች ….ትንፋሽ አልባ ሆነዋል..

‹‹አባዬ ..አባዬ›› ወዘወዘቻቸው…ጮኸች……..ወደመኝታ ቤቷ  በሩጫ ሄደችና የልብ ማዳመጫ መሳሪዋን አመጣች…ምንም  የለም..?…ጮኸች…ሁሉ ነገር ረፍዶ ነበር..ፀሀይ በጠለቀችበት ቀርታ ነበር…ጨረቃ በደመናው ሙሉ በሙሉ ተሸንፋ ከስማ ነበር…ምጽአት ደርሶ  ነጋሪት እየተጎሰመ እና መለከት እየተነፋ ነበር…..
አባቷ እርግጥ ህመም ላይ ከነበሩ ወራት አልፏቸዋል….ግን እየተንከባከበቻቸው እና በትክክል የህክምና ክትትል እያደረገችላቸው ነበረ…ምንም የተለየ እና ለሞት የሚያሰጋ ምልክት አልተመለከተችም….የት ጋር ነው የተሸወደችው…..?ማወቅ አልቻለችም…፡፡ ለሳዕታት እሬሳውን ላይ ተኝታ ስትነፈርቅ ቆየች…ስልክ ደውላ ለወዳጆቾ ልትናገር ፈለገችና መደወል ከጀመረች በኃላ መልሳ ተወችው

‹‹አባቴን ልቀብር…..?አባቴንም ፈጽሞ አልቀብርም…….ለሳዕታት ካሰበች በኃላ ወሰነች‹‹..አብሬው እሞታለሁ..ግን ለመሞት እስክቆርጥ ድረስ እሱም አይቀበርም›› አለችና…ባላት የህክምና እውቀት በመጠቀም ሬሳው እንዳይበሰብስ አድርጋ በባለመስታወት ፍሪጅ ውስጥ በማድረግ መኝታ ቤት ውስጥ ሬሳውን ደብቃ አስቀመጠች….እና ይሄ ነው የሚያስጨንቃት…እና በዚህ ጊዜ ነበር ኤርምያስ ላዳ ውስጥ የገባችው….ይሄን ችግር ነበር እሱ ሊያውቅና ሊረዳላት ያልቻለው…..በዚህ ከቀጠለች  በጥቂት ቀናት ውስጥ ወይ አዕምሮዋ ተነክቶ ጨርቋን ጥላ ይለይላታል ወይንም እዛው መኝታ ቤት ውስጥ እራሷን አጥፍታ ከአባቷ ጋር ወደመቃብር ትጓዛለች..ከሁለቱ የተለየ የነገ ዕጣ ፋንታ የላትም….
ንስሯ ይዞላት የመጣው ታሪክ ይሄ ነው..በእውነት ልብ የሚነካ ታሪክ ነው…‹‹እና እንዴት ልረዳት እችላለሁ…...?›ስትል እራሷን ጠየቀች፡መቼስ ምንም  ተአምረኛ ብትሆን ከሞተ  አራት ቀን የሆነው እና በፍሪጅ ውስጥ በቅዝቃዜ የደረቀ ሬሳን  ህይወቱን ካሄደችበት መልሳ በማዋሀድ ነፍስ  ልትዘራበት አትችልም…ይሄ የማይቻል ነው… ቢሆንም ቢያንስ ልጅቷ የአባቷን ሞት አምና እንድትቀበል እና እንድትቀብረው…ከዛም እንድትጽናና የሚያስችል አንድ ዘዴ መዘየድ እንዳለባት ተሰማት…አዎ ያንን ማድረግ ትፈልጋለች…
ሀሳቧን ሰብስባ ውሳኔ ላይ ሳትደርስ በፊት የሳሎኗ  በራፍ ተንኳኳ..ግራ ገባት …በዚህ ጥዋት ማን ነው የሚያንኳኳው .. ..?ገና አንድ ሰዓት እንኳን አልሆነም፡፡

‹‹…ማነው..?››ከተቀመጠችበት ሳትነሳ

‹‹እኔ ነኝ ..››

የፕሮፌሰር ድምጽ ነው..ተነሳችና ከፈተችላቸው‹‹እንዴ ፕሮፌሰር..በጥዋት እንዴት ተነሱ..?››

‹‹አረ ጨርሶውኑም አልተኛሁም…ከሰው ጋር ስለሆንሽ ነው እንጂ  ለሊቱን አብሬሽ ስጫወት ማደር ነበር የፈለግኩት››

‹‹ምነው በሰላም..?››

‹‹እኔ እንጃ ብቻ  ትናፍቂኛለሽ…ከፍቶኛል››

‹‹እንዴ ፕሮፌሰር..እስቲ ግቡ››

‹‹አሁን አልገባም.. በኋላ ግን እፈልግሻልሁ››

‹‹ለምን አይገቡም..?››

‹‹አይ አሁን እንግዳ ይፈልግሻል››

‹‹ማንን እኔን....?››ግራ ገብቷት 

‹‹አዎ አንቺን››ብለው ከበራፍ ላይ ገለል ሲሉ ከጀርባቸው በአዕምሮዋ ውስጥም የሌለ ሰው ብቅ አለ…አንድ ጥቁር ሻንጣ በእጁ አንጠልጥሎ አንገቱን ደፍቶ ቋማል..ፕሮፌሰሩ  ወደክፍላቸው ተመለሱ….

‹‹እንዴ መላኩ ..ምነው ሰላም አይደለህም እንዴ....?ሰሚራን አመማት እንዴ..?››

‹‹አረ እሷስ ደህና ነች››

‹‹ታዲያ ምነው በለሊት....?››እስቲ ግባ ብላ ወደውስጥ ገብቶ እንዲቀመጥ አደረገችው…

‹‹ምን ሆንክ..?››ፊት ለፊቱ ቆማ በገረሜታ እያየቸችው ዳግመኛ የመጣበትን ምክንያት ጠየቀችው፡፡

‹‹ምን ያልሆንኩት ነገር አለ..አሸንፈሻል …ሰሚርን አስመርምሬያታለሁ..ሙሉ በሙሉ ጤነኛ ሆናለች..››

‹‹አሪፍ ነዋ .ታዲያ ደስ አላለህም..?››

‹‹አዎ ብሎኛል…››
‹‹እና ታዲያ አሁን ለምን መጣህ..?››

‹‹ስምምነታችንን ላከብር ነዋ..በሶስት ቀን ውስጥ ትተሀት ካልመጣህ ብለሽ ፎክረሻ አድራሻሽን ሰጥተሸኝ ነበር  እኮ..የሆነ ነገር ለማድረግ ኃይል እንዳለሽ አሳይተሸኛል…እንቢ ብዬ በዛው ብቀር ደግሞ ፍቅሬን  መልሰሽ በሽተኛ ብታደርጊብኝስ..?››
😎ተአምራተ_ኬድሮን

#ተከታታይ ልቦለድ

#ክፍል_ሃምሳ_አምስት

በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ

‹‹ልሄድ ነበር››አላት ሚለው ጠፍቶት..አንዴ ኬድሮንን  አንዴ ከፊት ለፊቴ የተቀመጠውን መላኩን እያየ

‹‹አይ መኝታ ቤት ተመልሰህ ትጠብቀኝ..አብረን ነው ምንወጣው››

ግር አለው‹‹ይቅርታ አልሰማሁሽም..?››

‹‹እሱን ልሸኝና እመጣለሁ …መኝታ ቤት ተመልሰህ ጠብቀኝ…››

ባለማመን ወደኋላው ዞረና.. ወደመኝታ ቤት ተመለሰ

ከመላኩ ፊት ላይ ግራ የመጋባት  ጥያቄ  ስላነበበች‹‹ባለቤቴ ነው..?›› አለችና  ሳይጠይቃት መለሰችለት….

‹‹እንዴ….ባለቤቴ…ታዲያ እኔን…....?››

‹‹እኔ ለቀልድ ነበር እደዛ ያልኩህ ..የእውነት ታዳርገዋለህ አላልኩም ነበር…..››ከተቀመጠበት ተነስቶ ተንደርድሮ ጉንጯን እያገላባጠ ሞጨሞጫት

‹‹በእውነት በጣም ነው ደስ ያለኝ…በቃ ሁለቴ ህይወት ሰጥተሸኝል….ሰሚርን  አዳንሺልኝ አሁን ደግሞ ነፃነቴን ስትሰጪኝ››

‹‹አይ ግድ የለም››አለችና ከእቅፉ እየወጣች…ጭምቅ አርጎ ሲያቅፈትና ሲስማት መተንፈስ አቅቶት ነበር…በቃ በሽታዋ ሁሉ ሊነሳባት እና ሀሳቧን ልትቀይር ትንሽ  ነበር የቀራት….. 

እንደመደንገጥ አለና ወደመኝታ ቤቱ ገልመጥ በማለት ሲስማት ማንም እንዳላየው ለማጣራት ሲሞክር በቆረጣ አይታ ለራሷ ፈገግ አለች   ..‹‹በቃ ልሂድ.. ሌላ ቀን ከሰሚር ጋር መጥተን እንጠይቅሻለን ….በቃ ዘመድ እንሆናለን..››እያለ ይዞ የመጣውን ሻንጣ ይዞ ለመሄድ አንጠልጠሎ ተዘጋጀ፡፡

‹‹ሰላም በልልኝ..ግን እኔን ለመጠየቅ አትልፉ.. ዛሬ ለሊት ወደውጭ ልበር ነው….››ስትል ዋሸችው

‹‹ዉይ !!!ምነው?በሰላም..?››እንደመደንገጥ ብሎ፡፡

‹‹አይ በሰላም ነው …ቤተሰብ እዛ ስለሆነ እዛ ለመኖር ነው››

‹‹እሺ በቃ እግዜር ካንቺ ጋር ይሁን …ዕድሜ ልክ ከፍዬ የማልጨርሰው ውለታሽ አለብኝ ››እያለ ሳሎኑን ባለማመን  ለቆ ወጣ……

‹‹ምን ያህል መስዋዕትነት እንደከፈልኩልህ ብታውቃው..ባንተ ምክንያት ይህቺን አለምና ንስሬንም ጭምር እንደአጣሁ ብትሰማ›› ስትል አሰበች

….ይህን ሁሉ ልትነግረው ያልፈለገችው ቢያንስ በስተመጨረሻ ጥሩ ልሁንለት ብላ ነው ….በፀፀት ያልደፈረሰ የፍቅር ህይወት ይገባዋል ብላ ስላሰበች ነው….አሁን  የእነሱን ሰሚራ ለማዳን የሆነችውን እና  ያጣችውን ዘርዝራ ባታወራው ከማዘን በስተቀር ለእሷ ምንም አይፈይድላትም..በእሱ ህይወት ላይ ግን ቁጭትን ይፈጥርበታል…..ደስታው ላይ ደመና ያጠላል…. ያንን አስባ ነው እውነቱን የደበቀችው፡፡
/////

ሀሳቧን ሰብስባ ቀጥታ ወደመኝታ ቤቴ ሄደች…. ስትደርስ ባዶ ነው..ግራ ገባት….‹‹ እንዴ በጓሮ በር ሾልኮ ፈረጠጠ እንዴ..? ››ብላ ሳታሰላስል ከሻወር ቤት የውሃ መንሾሾት ድምጽ ሰማችና ወደ እዛው ሄደች..ደረሰችና ብርግድ አድርጋ  ከፈተችው…. ድንገት መሳሪያ እንደተደቀነበት ምርኮኛ ኩም ብሎ ደነገጠ..እጆቹን የተንዘላዘለ እንትኑ ላይ ሸፈናቸው….
‹‹አረ ልቀቀው ..ለሊቱን  እስክጠግብ እኮ ሳየው ነው ያደርኩት››

‹‹እብድ ነሽ..አስደነገጥሸኝ እኮ …››አለና ቀስበቀስ ለቀቀው
‹‹ህፃን ሆነህ እናትህ በቂቤ በደንብ ያሹልህ እና ይጎትቱልህ ነበር እንዴ..? ›› 

‹‹‹ምን እንዲሆን ነው የምትጎትትልኝ..?››

‹‹እንዲህ እንዲንጀላጀል ነዋ….ሜትር ከምናምን እንዲሆንልህ››

‹‹ትቀልጂያለሽ..ቆይ ማን ነበር ሰውዬው… ውሽማሽ መስሎኝ እኮ ተበላሁ ብዬ ነበር››

‹‹አይደለም ዘመዴ ነው…እንዴት ነው እኔም አወላልቄ ልግባ እንዴ..?››

‹‹ወዴት....?››

‹‹ወደሻወር ነዋ..እጠበኝ ልጠብህ››

‹‹ኸረ በፈጠረሽ..ስወደሽ እንዳታደርጊው››

ሳቋ አመለጠት‹‹እንዴ !!ይሄን ያህል…...?››

‹‹እንዴ…እሳት እኮ ነሽ…እኔ እንጃ የዛሬ ወር ድረስ ተከፍቶ ባገኝ እንኳን ለመክደን አልሞክርም…እንዴት እንዴት አይነት የወሲብ ጥብብ ነው..የሆነ ህልም ውስጥ እኮ ነው ያስገባሺኝ..በአየር ላይ ሁሉ እየተንሳፈፍኩ ይመስለኛል…አሁን ሳስበው ደግሞ እንዴት በአየር ላይ መንሳፈፍ ይቻላል እላለው....?ከግድግዳ ጋር ግን እዳጣበቅሺኝ በእርግጠኝነት አውቃለሁ..ግን አጥንቶቼ ስብርባራቸው ለምን እንዳልወጣ እንቆቅልሽ ነው የሆነብኝ…ብቻ ግራ ተጋብቻለሁ.፡፡እኔ በህይወት ፍቅር እንጂ ያጣሁት የወሲብ ችግር ገጥሞኝ አያውቅም….ቁጥራቸውን ከማላስታውሳቸው ሴቶች ጋር ወሲብ ፈጽሜያለሁ..በአንድ ለሊት ስድስት ሰባቴ …ግን ከንቺ ጋር ያደረኩት አንድ ዙር ወሲብ እድሜ ልኬን ከደረኩት ጋር የማይነፃፀር እና የተለየ ነው››

‹‹ወሲብ ደጋግመን የምፈፅመው ለምን እንደሆነ ታውቃልህ..?››

‹‹እኔ እንጃ››

‹‹እኔ ግን ስገምት ..ለኮፍ ለኮፍ ከሆነ ወዲያው ወዲያው ያምርሀል…በሁለት ደቂቃ በራፍ ላይ ደፍቶ ተልኮውን የሚያጠናቅቅ  ሰውና በ20  ደቂቃ  ውስጠ ውስጥ በርብሮ ግዳጁን ያጠናቀቀ እኩል መልሶ አያሰኛቸውም….ለዛ ነው ››
‹‹ይሁንልሽ ››አለና የሻወሩን ውሃ ዘግቶ… ፎጣውን አገለደመና ከሻወሩ ቤት ወጣ …ተከተለችውና አልጋው ጠርዝ ላይ ቁጭ አለች፡፡

‹‹እሺ ቁርስ ትጋብዘኛለህ አይደል..?››አለቸው

‹‹አንቺን ለመሰለች ቆንጆ እንኳን ቁርስ አራሴንስ ብጋብዝሽ ቅር አይለኝም..››

‹‹እራስህንማ  እንዴት ልትጋብዘኝ ትችላለህ…..?››

‹‹ለምን አልችልም..?››ሲል ጠየቃት  ኮስተር ብሎ

‹‹እኔ ልቡን ለሌላ ሰው ጠቅልሎ ያስረከበና ቀፎውን ብቻ ያለ ሰው ምን ያደርግልኛል…....?››

‹‹አይ የምታወሪው ስለ ሰላም ከሆነ ተስፋ  ቆርጬያለሁ….አሁን የምፈለገው ምን እንደሆነች ብቻ አውቄ ልረዳት ነው…ያንን ማድረግ  ከቻልኩ ይበቃኛል…ካዛ….››

‹‹ከዛ ምን…..?››

‹‹እኔ እንጃ… የላዳ ሹፌር ነው ብለሽ ካልናቅሺኝ በጣም ነው ያፈቀርኩሽ..?››

‹‹ያፈቀርኩሽ ስትል..?››
‹‹ያፈቀርኩሽ ነዋ..በጣም ነው የተመቸሺኝ ….የሆነ የማላውቀውን አለም ነው ያሳየሺኝ…ላጣሽ አልፈልግም….››

‹‹ስለእኔ ምንም እኮ አታውቅም....?››

‹‹ማወቅ አልፈልግም..አንቺ ብቻ እሺ በይኝ እንጂ…..››ንግግሩን ሳይጨርስ ንስሯ እየበረረ የመኝታ ቤቱን በር በርግዶ  በመግባት  እንደቀናተኛ አባ ወራ አልጋ ላይ ተኮፍሶ  ጉብ አለ….

ይሄንን በድንገት ያየው ባለ ላዳው ከተቀመጠበት በርግጎ ወድቆ ነበር..

‹‹አይዞህ አይዞህ…›››ሳቋ እያመለጣት
‹‹አይዞህ….!!›

‹‹የማታው ንስር አይደል..?››

‹‹አዎ ነው››

‹‹ምን ይሰራል  እዚህ..?››
‹‹እዚህ ምን ትሰራለህ ..?ብሎ መጠየቅ ያለበት እሱ ነው..ምክንያም እሱ የገዛ ቤት ውስጥ ነው ያለው››

‹‹ማታ የእኔ ነው ያልሺው እወነትሽን ነው እንዴ..?››

‹‹አይ የእኔ አይደለም..እኔ ነኝ የእሱ….››

‹‹እኔ እንጃ ግራ ይገባል..››እያለ ልብሱን መልበስ ጀመረ……..
‹‹ሰላምን እንድትረዳት ልናግዝህ እንችላለን››አልኩት  

‹‹ልናግዝህ ስትይ....?አንቺና ማን..?››

‹‹እኔና ንስሬ››

ፈገግ አለ….‹‹ትቀልጂብኛለሽ አይደል..?››

‹‹የምሬን ነው…›

‹‹አንቺ እሺ ይሁን …ይሄ እንስሳ እንዴት አድርጎ ነው የሚረዳኝ..ደግሞስ አንቺስ ብትሆኚ በምን መልኩ ልትረጀኝ ትችያለሽ .. ..?እኔ እንኳን ገና ችግሯን  ማወቅ አልቻልኩም››
📕ተአምራተ_ኬድሮን

#ተከታታይ ልቦለድ

#ክፍል_ሃምሳ_ስድስት

#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ

ወደቀልቧ እስክትመለስ እና መኝታ ቤቷ ውስጥ ያልጋበዘቻችው ሰዎች እንደገቡ ለመገንዘብ ከአንድ ሰዓት በላይ ወሰደባት ….

‹‹እንዴት ብትደፍረኝ ነው ግን ሰተት ብለህ መኝታ ቤቴ ድረስ  ሚስትህን ይዘህ የገባኸው……?.›

ኤርሚያስ ግራ ተጋባ … ተርበተበተ……‹‹ይቅርታ..ማለት ሚስቴ አይደለችም…. አላውቃትም..ይቅርታ ማለቴ አውቃታለሁ ግን ይሄውልሽ እሷ….››
አቋረጠችው ‹‹…ውጣልኝ …ውጡልኝ..››ጭንቅላቷን በእጆቾ ይዛ ጩኸቷን ለቀቀችው….

‹‹እሺ እንወጣለን..አንቺ ብቻ ተረጋጊ… እንወጣለን…ይሄው እየወጣን ነው…››የሚያደርገው ጠፍቶት ክፍሉን ለቆ ለመውጣት ወደበራፉ ፊቱን አዞረ…

ኬድሮን‹‹አባትሽን ላገናኝሽ ነው የመጣሁት››አለቻት

ከተቀመጠችበት ወንበር ንቅንቅ ሳትልል
ከትከት ብላ ሳቀች..የምፀት ሳቅ…..የእብደት ሳቀ..የንዴት ሳቅ

‹‹እንዴት አድርገሽ ነው ከሞተው አባቴ ጋር ምታገናኚኝ….…?ነው ወይስ ከበድኑ ነው ልታገኛኚኝ ያሰብሺው…..አመሰግናለሁ በድኑ በእጄ ስለሆነ አትልፊ  ….››

‹‹አይ እዲያናግርሽ ማድረግ እችላለሁ››

‹‹እንዲያናግረሽ አልሽ…..ኤርሚያስ ምን በድዬሀልው..…?››አለችው ወደእሱ ዞራ

እየተርበተበተ‹‹..ሰላም አንቺ ምን በወጣሽ.. አረ ምንም አልበደልሺኝም  …ለምን እንደዛ ልትይ ቻልሽ…?››

‹‹እንዴ ያንተ ሳያንስ ሌላ ሰው ይዘህ መጥተህ እድታሾፍብኝ ታደርጋለህ……?በሀዘኔ እንዴት ታላግጣላችሁ….…?በቁስሌ እንዴት ጨው ትነሰንሳላችሁ…?ይሄ ምን አይነት ጭካኔ ነው …?…››

‹‹አረ በፍፅም እንደዛ አይደለም….አንቺን ለመርዳት እንጂ ሌላ ምንም አላማ የለንም››

‹‹እና ታዲያ እንዴት ነው ከአባቴ የምታገናኘኝ……?.››

‹‹እሱን አንዴት እንደሆነ አላውቅም ..ግን ታደርገዋለች ››አለ አንዴ ኬድሮንን አንዴ ሰላምን በማፈራረቅ እያየ
ልታስረዳት ሞከረች‹‹እመኚኝ  የሙት መንፈስ ማናገር እና ከሚወዶቸው ሰዎች  ጋር የማገናኘት ችሎታ አለኝ…መቼስ ስለዚህ ጉዳይ ሰምተሸ አታውቂም  ለማለት አቸገራለው….››

‹‹ሰምቼማ አውቃለው..በመጽሀፍ ቅዱስ ላይም አንብቤያው..ግን ..››>

‹‹ምንም ግን የለም…››ብላ ንስሯን እንዲመጣ በአዕምሮዬ መልዕክት አስተላለፍችለት ….. ክንፉን እየማታ መጣና  አልፎን ፈሪጁ ላይ ጉብ  ሲል  ሰላም  በድንጋጤ ተንደርድራ ልትሰፍርበት ስትል ቦታ ቀየረና አመለጣት….

‹‹አባቴን ..አግዙኝ…. አባቴን አንዳይነካብኝ››

‹‹አይዞሽ የእኔ ንስር ነው ..ምንም አያደርግም…››

‹‹እርግጠኛ ነሽ ……?አባቴን አይነካውም…?››አለች… በእሷ ግምት የኬድሮን ንስር  የአባቷን በድን አካል ለመዘንጠል ይዳዳል ብላ ነው

‹‹እንዴ ንስር የሞተ ነገር እንደማይነካ አታውቂም…››

‹‹አላውቅም››አለች

‹‹እኔም አላውቅም ››በማለት ድጋፍ ሰጣት  ኤልያስ

ማብራሪያዬን በኩራት ቀጠልኩ ‹‹ንስር ኩሩ ነው…እራሱ አባሮ… እራሱ ታግሎ …እራሱ ገድሎ ካልሆነ ነክች አያደርግም…ለማንኛውም አሁን ተዘጋጂ ቁጭ በይ ››….ቁጭ አለች…
‹‹ይሄሁልሽ አሁን ንስሬ ያግዘኝና ከአባትሽ መንፈስ ጋር አገናኝሻለሁ...ማለት የእኔን አንደበት ተጠቅመው አባትሽ ቀጥታ ያናግሩሻል..በእኔ አንደበት በራሳቸው ድምፅ››

‹‹እሺ››

‹‹ኤርምያስ አንተ ደግሞ ካለህበት እንዳትነቃነቅ..ምንም የሚረብሽ ነገር ካለ ትኩረቴን ስለሚበታን መሀል ላይ ግንኙነቱ ሊቋረጥ ይችላል››

‹‹አረ በፍጽም ይሄው ንቅንቅ አልልም..ትንፋሼ እራሱ አይሰማም››አለና በተቀመጠበት ጭብጥብጥ አለ

ሁሉም ነገር ዝግጁ መሆኑን ሳታረጋግጥ አዕምሮዋን ከንሰሯ ጋር አገናኘቸው..ለደቂቃዎች ተመሰጠች …ይሄን ነገር ከዚህ በፊት አድርጋው አታውቅም ‹‹..ግን ማድረግ አያቅተኝም›ስትል በራሷ ተማመነች….አዎ ንስሯ የአባቷን ነፍስ ካለችበት እንድትመጠ እየጋበዘ  ነው..ወይ ብዙም አላስቸገራትም ….ቀጥታ አባትዬው በኬድሮን አንደበት ልጃቸውን ማናገር ጀመሩ……

‹‹ልጄ ሰላሜ…››

ባለማመን መለሰች‹‹ወይ አባዬ..››ተንደርድራ ሬሳውን እያየች
‹‹እዛ ለምን ትፍልጊኛለሽ….…?አይ ልጄ ስጋዬ ውስጥ አይደለሁም.. …ግን ደግሞ ወደዘላለም ማረፊያዬም መሄድ አልቻልኩም..ከሁለቱም ሳልሆን በአየር ላይ ተንጠልጥዬ አለሁልሽ፡፡

‹‹ምነው አባዬ……? እኔ ልሰቃይልህ…..እኔ በአየር ላይ ለዘላለም ተንጠልጥዬ ልቅር››

‹‹አይ ለምን ልጄ…? ለምን..…?ለአንቺማ ይሄ አይገባም…ትቼሽ ስለሄድኩ ይቅርታ ልጄ..ምን ላድርግ የአማላክ ጥሪ ነው….እባክሽ ልጄ ከዚህ በላይ እንድሰቃይ አታድርጊኝ…››

‹‹እንዴ አባዬ እኔ አንተን ማሰቃየት…?››

‹‹አዎ እናቴ… እዚህ እቤቴ ውስጥ በድን አካሌን ታቅፈሽ እንደዚህ ሆነሽ እንዴት እፎይ ብዬ ወደዘላለም የሚወስደኝን  መንገዴን እቀጥላለሁ..…?አልችልም ልጄ ..አካሌ መሬት ሳይገባ ነፍሴ ወደአምላኮ ልትሄድ ይከብዳታል..ልጄ እባክሽ በአምላክ  ስራ ጣልቃ አትግቢ..››

‹‹እንዴት አባ……? እንዴት ጣልቃ ገባሁ……?.››

‹‹እንዴ ሞትን የፈጠረውን አምላክ  እኮ እየተቃወምሽው ነው..ተሳስተሀል እያልሺው ነው››

‹‹አዎ ተሳስቷልማ..እንዴት አንድ አባቴን ይነጥቀኛል..…?እንዴት ባዶዬን ያስቀረኛል….…?.››

‹‹አየሽ ልጄ …ሞት እርግጥ በጥፋታችን ምክንያት የተሸለምነው ቅጣታችን ነው…ይሁን እና በዚህ ምድር ለመኖር እስከመጣን  ድረስ   ሞታችንም በጣም አስፈላጊ ነው..››

‹‹እንዴት አባ .. …?ሞት ደግሞ እንዴት ነው ጠቃሚ የሚሆነው.?››

እግዜር ፈጥሮ ምድር ላይ ቢረሳንስ ምን ይውጠናል….…?አርጅተን መንቀሳቀስ አቅቶን እቤት እስክንቀር…. ቆዳችን እስኪጨማደድ እና  ወበታችን እስኪረግፍ ድረስ አልወስዳችሁም ቢለን ማነው የሚጎዳው……?.ጥርሳችን ረግፎ ገንፎ እንኳን  ማኘክ እስኪያቅተን ቢተወን …አይናችን ለግሞ  የልጅ ልጆቻችንን ከጎረቤቶቻችን ልጆች መለየት እስኪያቅተን ..መኝታ ቤታችን ከሽንት ቤታችን መለየት እስኪሳነን ድረስ ኑሩ ብንባል ሽልማት ነው ቅጣት…ዕርግማን ነው ምርቃት…?››

‹‹እንዴ አባዬ.. …!!!አንተ እኮ ገና ነህ …ሰባ አመት እንኳን አልሆነህም..…?››

‹‹እኮ እግዚያብሄር ይወደኛል ማለት ነዋ..…?ምላሴ ጣዕም መለየት ሳይሳነው፤አይኖቼ ማንበብ ሳያቆሙ ፤እግሮቼ ላምሸው ከዘራ ሳልይዘ አስታወሶኛል…››

‹‹ግን እኮ አባ እኔን ጥለህ ነው የሄድከው…?››

‹‹የሞት መጥፎው ክፍል ያ ነው….አዎ ሁልግዜ የሆነ ነገር ጥለሽ መሄድሽ አይቀርም…ማንም ቢሆን ከዚህ ምድር ሲሰናበት የሆነ ነገር በጅምር ጥሎ መሄዱ የሆነ የሚወደውን ሰው ሳይሰናበት ማምለጡ ያለ እና ግዳጅም ነው….እና ልጄ አንቺ አፈር ካላቀመሺኝ እና በሀዘን መቆራመድሽን እስካላቆምሽ ድረስ ጉዞዬን መጀመር አልችልም… ብጀምርም ቶሎ አልደርስም..ሀዘንሸ ወደኃላ ይስበኛል….ለቅሶሽ  መንገዴን እያጨቀየው ያዳልጠኝ እና አላላውስ ይለኛል…..››

‹‹አባ አረ እኔ እንዲህ የበደልኩህ አልመሰለኝም…?››

‹‹በደልሺኝ እኮ አላልኩም.. ግን  በቃ..አንዳንዴ መሆን ያለበት ነገር እንዲሆን መተው ነው..ታግለሽ ልታሸኝፊው ከማትችይው ነገር ጋር መታገል  ከድካም ውጭ እርባን ያለው ውጤት አያስገኝም ››

‹‹እና ምን ላድርግ አባ…?››
❇️ተአምረተ_ኬድሮነ

#ተከታታይ ልቦለድ

#ክፍል_ሃምሳ_ሰባት

በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ


ቫይብሬት ላይ የተደረገ ሞባይል ስልክ ላይ ሲደወል እንዳለ ንዝረት ተንቀጠቀጥችና አዕምሮዋን ከንስሯ ጋር አላቀቀች…
ሰላም ወደኬድሮን ተንደርድራ መጥታ እግሯ ሰር ድፍት አለችና‹‹በጣም አመሰግናለሁ….እግዜር ይስጥሽ››

‹‹ተነሺ ..እኔን አታመስግኚ…እሱ በጣም ስለለመነኝ ነው እንዲህ ያደረኩልሽ…››አለቻት

‹‹ኤርሚ እግዜር ይስጥልኝ….አንተንም በጣም  ነው የማመስግንህ..ምን አይነት ሰላም በውስጤ እንደተሰራጨ አትገምትም››አለች ወደመቀመጫዋ ተመልሳ በመቀመጥ

‹‹በነጋራችን ላይ በጣም ነው የሚያፈቅርሽ …እንደነገረኝ ከሆነ ከልጅነቱ ጀምሮ አንቺን ሲያፈቅርሽ ነው የኖረው….አንድም ቀን አንቺን ማፍቀር አቁሞ አያውቅም..ግን በኑሮ ደራጃ ስለምትለያዩ እሺ አትለኝም የሚል ፍራቻ በውስጡ ስላለ  ካንቺ ሲሸሽ ነው የኖረው››አፈረጠችለት

ባለማመን አንዴ ኬድሮንን አንዴ እሱን በማፈራረቅ ማየት ጀመረች..ኤርምያስም የተቀመጠበት ወንበር ላይ አንገቱን ወደወለሉ እንደደፋ ሚገባበት ጠፍቶታል እጆቹን እያፍተለተለ ነው…

‹‹አላውቅም ነበር…ኤርምያስ እኔን ማፍቀር….…?››

‹‹አዎ….ኤርምያስ አንቺን…››

‹‹እሺ ጥሩ ነው…አሁን ምን እናደርግ …ኤርሚ እርዳኝ ለእድር ሰዎች ንገራቸው…አባቴ ዛሬውኑ እንዲቀበር እፈልጋለሁ….››

‹‹አረ እሺ… ችግር የለውም… አሁኑኑ ነግሬያቸው ልምጣ …ስልካቸውን ስለማላውቅ እናቴ ጋር ሂጄ …››ብሎ ተነሳ 

ኬድሮን የተለየ ሀሳብ አመጣች‹‹ቆይ መጀመሪያ የሬሳ ሳጥን እንግዛና አባትሽኝ  በሳጥኑ ውስጥ በማድረግ  ማዘጋጀት አለመብን..አሁን ዕድርተኛው መጥተው ጓደኞቸው ተሰብስበው እንገንዝ ማለታቸው አይቀርም …እንደዛ ከሆነ ደግሞ ሌላ ሀሚት ላይ ይጥልሻል…በህግም ሊያስጠረጥርሽ ይችላል››

‹‹ታዲያ ምን እናድርግ››አለች ግራ ገብቷትና ያለሳበችውን ነገር ስላነሳው ደንግጣ

‹‹ግድ የለም እኔና ኤርሚ ሳጥኑን ይዘን እንምጣ..ሁሉንም ከጨረስን  ብኃላ ለሌላው ሰው እንናገራለን….››

‹‹አስቸገርኮችሁ አይደል…?›› 

‹አረ አትጨነቂ …እኔን እንደእህትሽ ቁጠሪኝ… ኤሪሚም  ያው ያንቺው ነው..››አለችና ምትናገረው ጠፍቷት በመቁለጭለጨ ላይ ሳለች የደነዘዘውን ኤርሚያስን ይዛው ወጣች…

መኪናው ውስጥ ገብተን የሬሳ ሳጥን ወደሚሸጥበት ቦታ  እያመሩ ሳለ…

‹‹ምን አይነት ተአምር ነው ያደረግሽው……?.››ሲል ጠየቀት

‹‹ያው ላንተ ስል ነው››

‹‹በጣም ነው የማመሰግንሽ….ግን  እንደማፈቅራት ለእሷ ባትነግሪያት ጥሩ ነበር››

‹‹ለምን…?››

‹‹ያው አንደኛ መንገሩ ምንም ውጤት አይኖረውም ሁለተኛ እኔ እና አንቺ……››

‹‹አይ እኔና አንቺ የሚባል ነገር የለም…አኔን እርሳኝ…እኔ ሁለት ቀን ብቻ ነው የቀረኝ..››

‹‹ምን ለመሆን…?››

‹‹ለመብረር…››

‹‹እንዴ የት አሜሪካ ወይስ አውሮፓ……?››

‹‹በለው ከሁለት አንዱ….ስለዚህ እሷኑ ጠበቅ አድርግ.ደግሞ በትክክል ይሳካልሀል….

እንደምታፈቅራት ስነግራት የልቧን ምት በደንብ ታዝቤያለሁ. ዋናው ከዚህ ሀዘን እስክትወጣ ከስሯ አትለይ …….

‹‹እንዴ ወዴት ነው የምለየው….ከእሷ የሚበልጥ ምን ሌላ ጉዳይ ይኖረኛል››

‹‹ምንም ››

‹‹አንቺ ልትበሪ መሆንሽን መስማቴ  ግን ቅር አሰኝቶኛል››

‹‹እኔን እርሳኝ አልኩህ እኮ››

‹‹እኮ እንዴት አድርጌ ልርሳሽ…?››
/////

የሰላምን አባት የቀብር ሁኔታ ካመቻቸችና ከተጠናቀቀ በኃላ ሁለቱንም አንድ ላይ ከለቀስተኞች ጋር ጥላቸው እናም በውስጧ ለመጨረሻ ጊዜ ተሰናብታቸው መልካሙን ሁሉ እየተመኘችላቸው ወደቤቷ ነው የተመለሰችው…ድክምክም ብሏት ነበር…ግቢውን አስከፍታ ስትገባ ግን ድካሟን ሁሉ ከላዮ የሚያበንላት አስደሳች ሁኔታ ነው የጠበቃት…

ግቢው መሀል ላይ ባለች ክፍት ቦታ ጠራጴዛ እና ወንበር ወጥቷል፤…ጠረጵዛው በልዩ ሌዩ ምግቦችና መጠጦች ተሞልቷል …ከዛ አልፎ ዙሪያው በየጥጋጥጉና በየቦታው የዛፍ ቅርንጫፎች ላይም ሳይቀር የተለያዩ የምግብና የፍራፍሬ አይነቶች ተቀምጠዋል…የተለያዩ ጥራጥሬዋች በየቦታው ተበትኗል….በጊቤዋ ውስጥ ያሉ እንስሳት ብቻ ሳይሆኑ እንግዳ የሆኑ ወፎች ሳይቀሩ ግቢውን ወረውት የተበተነላቸውን ጥራጥሬ በደስታ ይለቅማሉ… ጦጣና ዝንጆሮዎቾም ሙዙን እየላጡ ይውጣሉ …የማይፈነጭ እና የማያስካካ ፍጥረት በግቢው አይታይም..  የሆነ እንስሳት አግብቶ ሌሎቹ ሠርግ ተጠርተው አሼሼ ገዳሜ ላይ ያሉ ነው የሚመስለው….ሌላው ይቅር እያንዳንዱ  ተክል   ስሩ ተኮትኩቶና አፈር ታቅፎ ውሃ ጠግቦ እስኪተፋ ድረስ ጠጥቶ ይታያል….በቃ በግቢው አንድም ያልተደሰተ ፍጥረት አልነበረም..ይሄ ሁሉ በፕሮፌሰሩ የተደረገው እነሱ በተደሰቱበት መጠን እኔ እንደምደሰት በደንብ ስለሚያውቁ ነው፡፡

‹‹አትመጪም…  ይሆን ብዬ በስጋት ላይ ነበርኩ …እንኳን በሰላም መጣሽ››አሏት ከእድሜ ጫና የተነሳ ያጎበደድት ፕሮፌሰር…

‹‹አይ እፈልግሻለሁ ብለውኝ የለ..…….?በዛ ላይ  አንድ ቀን ብቻ ነው የቀረኝ …ማታ ወደ እናቴ  እሄዳለሁ.አዎ ነገ ሙሉውን ቀን ከእሷዋ ጋር ነው ማሳለፍ የምትፈልገው………››

‹‹ጥሩ ጥሩ..ነይ እዚህ ጋር ቁጭ በይ›› ብለው ምግብ በሞላበት ጠረጴዛ ዙርያ ከበው ከተቀመጡ ወንበሮች ውስጥ አንድን ሳቡላት… አመስግና ተቀመጠች፡፡

የእጅ ውሀ አመጡላት …‹‹አረ እራሴ እታጠባለሁ›› ብላ በራሷ ተጣበች… ሳሀን ስባ ምንም እንኳን የምግብ ፍላጎት ባይኖራትም እሷቸውን ለማስደሰት ስትል ብቻ መብላት ጀመረች… እሳቸውም ከፊት ለፊቷ ተቀምጠው በስስት እያዮት መመገብ ጀመሩ…

‹‹የሚጠጣ ምን ልቅዳልሽ…….?››

‹‹ውሀ ››

‹‹ወይን ወይም ሌላ ነገር አይሻልሽም…….?››ካለወትሮዋ ዉሀ ማለቷ አስገርሞታል

‹‹አይ ውሀ ነው የምፈልገው….››

‹‹እሺ ካልሽ ››ብለው ውሀ ቀዱላት፡፡

‹‹ጋሼ በዚህ ምድር በኖርኩበት ዓመት የተረዳሁት ነገር ቢኖር  ምድር መተኪያ የሌላቸው ሁለት ነገሮች መታዳሏን ነው ….አዎ  እናትና ውሃ የዚህ ዓለም ሁለት ልዩዎች  ናቸው…››

‹‹እንዴት ልጄ..…….?እንዴት እንደዛ ተረዳሽ…?››

‹‹እናታችን መጀመሪያ ገነታችን ነች..ከተፈጠርንበት ቀን አንስቶ እስክንወለድበት ቀን ድረስ በእናታችን መሀፀን ውስጥ ገነታዊ ኑሮ ነበር የምነኖረው… ያ ስፍራ ሁሉ ነገር በፍፅምና  እንከን አልባ  ስፍራ  ነበር..ሁላችንም ከዛ ያለፍላጎታችን ተገፍትረን ስንወጣ(ስንወለድ) እሪ ብለን ለቅሶችንን የምንለቀው  ምን እንዳጣን በደመነፍስ ስለሚገባን ነው…አዳም እና ሄዋን በሰሩት ሀጥያት ከገነት ወደምድር ተባረሩ የሚባለው ሌላ አይደለም ከእናት መህፀን ወደምድር ተገፍትሮ መውጣት ነው…ከዛ በኋላም ቢሆን  እናት ምን ጊዜም እናት እንደሆነች ነው ምትቀጥለው… እንዳላረጀን እና እንዳላበቃልን የሚሰማን እናታችን በሰላሳ አመታችንም እንደ ህፃን ስትቆጣን ስናይ ነው..ጭንቅላታችንን ስትዳብስልን…ተይ አንቺ ልጅ ብርድ ይመታሻል ስትለን  ነው፡፡
📕ተአምረተ_ኬድሮን

#ተከታታይ ልቦለድ

#ክፍል_ሃምሳ_ስምንት

በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ


ለዓመታት ጎብጦ እና አጎንብሶ የነበረ ትከሻቸው ቋቋቋቋቋ የሚል ድምጽ እያሰማ በመላቀቅ መቃናት ጀመረ…የተጨማደደ እና ተኮመታትሮ የነበረ ቆዳቸው ልክ የሽማግሌ ገፃ-ባህሪ ለመጫወት ጭንብል አጥልቆ እንደነበረ አክተር  ከፊታቸው ተሞሽልቆ በመነሳት መሬት ወደቀ…
ወዲያው መለስተኛ አውሎ ንፋስ ተነሳና እየተሸከረከረ መጥቶ እዚህም እዛም በዙሪያችን የወደቀውን የፕሮፌሰሩን የተወገደ አካል ከአካባቢው ጠራርጎ በአየር ላይ ተሸክሞ ሄደ ..
ከዛ…. ሁሉ ነገር እንዳሰበችው እንደሆነ ካረጋገጠች በኃላ እጆቾን ከጭንቅላታቸው አነሳችና…ወደመቀመጫዋ ተመልሳ ተቀመጠች…

አየቻቸው‹‹…..እንዴት አባቱ የሚያምር ጎረምሳ ሆኖል›ስትል እራሷ በሰራችው ተአምር እራሷ ተደነቀች   …‹‹ውይ እነዛ የአባቴ ዘመዶች መተው ሚወስዱኝ ባይሆን  ኖሮ ይሄን  ፊት ለፊቴ የተቀመጠውን ቆንጅዬ  ጎረምሳ አግብቼ  መኖር ነበር….›ስትል የምፀት ፈግታ ፈገግ አለች፡
ፕሮፌሰሩ ቀስ እያለ ከሰመመኑ ነቃ…
‹‹ወይ ልጄ ምድነው ያደረግሺኝ…….?ራስ ምታቴ እና ጭንቀቴ እኮ ለቆኝ ሄደ››
‹‹አሞህ ነበር እንዴ…….?››
‹‹ምን አልሽኝ…….?››ግራ ተጋብተው
‹‹ ይቅርታ አሞት ነበር እንዴ…….? ለማለት ፈልጌ ነው››
‹‹አንቺን አልረብሽሽም ብዬ ነው እንጂ እንደምትሄጄ ከሰማሁበት ቀን አንስቶ ጤናም የለኝ ነበር..››
‹‹አይ እንኳን ተሸሎት››
‹‹አረ መሻል ብቻ አይደልም …››ንግግራቸውን ሳይጨርሱ አይናቸው እጃቸው ላይ አረፈ..ተጨማዶ ና ተሸብሽቦ የነበረ እጃቸው አሁን በለግላጋ  ጣት እና ለስላሳ ቆዳ ተሸፍኖ ሲያዩት ማመን አልቻሉም… ግራ በመገባት እና  ባለማመን በጃኬታቸው ሸፈኑት..መልሰው ገለጡ…
‹‹ቆይ መጣሁ›› ብለው….ትተዋት ወደቤት በፍጥነት መራመድ ጀመሩ…ከኃላ ተከተለቻቸው…ቀጥታ ወደመኝታ ቤታቸው ሄደው የቁምሳጥናቸው መስታወት ፊት ለፊት  ነው የቆሙት….
‹‹የምን ታአምር ነው.…….?.እኔ የት ሄድኩ……….?ማን ነው ይሄ..…….?እኔ ማነኝ…….…….? ››ፊታቸውን እየዳበሱ ለፈለፉ…
መልስ መስጠት ጀመረች‹‹አሁን የ30 ዓመት ወጣት ሆነዋል..ማለት ሆነሀል፡፡…የሚፀፀቱበት ምንም ነገር የለም..ቀጣይ 45 ዓመት ተሰጥቶታል …. ስዚህ ቅድም እንዳሉት ሚዛናዊ ኑሮ ይኑሩበት..ማለቴ ኑርበት…››
‹‹ምን ጉድ ነው….…….?እኔ ወጣት…አንደገና መወለድ እኮ ነው…….?››
‹‹አዎ ነው..ልክ እንደንስር እንደገና የመታደስ ዕድል..››አለቻቸውና ቤታቸው ለቅቄ ወደራሴ ቤት አመራሁ ..ወደ እናቴ ለመሄድ ልዘጋጅ
////
ንጋት ላይ ነው ጉዞ የጀመሩት፡፡የንጋቱን ቀዝቃዛ አየርን  እየማጉ ሰማዩን ሰንጥቀው ቁልቁል የኢትዬጵያን ደቡባዊዉን መልካ ምድር እየቃኙ እየተጓዙ ነው፡፡እስኪ ትንሽ ከላይ ሆነው ቁልቁል ወደታች ሳያዩ ከፊል ኢትዬጵያ ምን እንደምትመስል አብረናቸው እንመልከት፡

ኢትዬጵያ 12 ታሪካዊ ቅርሶችን በዩኒስኮ በዓለም አቀፍ ቅርስነት አስመዝግባለች፡፡እነዚህም፤ የአክሱም ሀውልቶች፣ የላሊበላ አብያተክርቲያናት፣ የጎንደር ፋሲል ቤተመንግስት፤የሰሜን ብሄራዊ ፓርክ፣ የኮንሶ ሰው ሰራሽ መልካዓ ምድር፣ የጢያ ትክል ድንጋዮች፣የታችኛው አዋሽና የታችኛው ኦሞ ሸለቆ፣ የመስቀል ደመራ፣ የሲዳማ ፊቼ ጨንበላላ፣ የኦሮሞ የገዳ ሥርአት ናቸው። ሌሎችም ለማስመዝገብ   ላይ ያለ አሉ  በዩኔስኮ እንዲመዘገቡ በእቅድ ደረጃ የተያዙ ቅርሶችም እንደ የባሌ ተራራዎች ብሄራዊ ፓርክ፣ የድሬ ሼክ ሁሴን መስጊድ፣ የሶፍ ኦመር ዋሻ፣ የጌዲዩ ሰው ሰራሽና የተፈጥሮ መልከዓምድር፣ የመልካ ካንቱሬ የአርኪዮሎጂ ስፍራዎች ናቸው። በማይጨበጥ ባህላዊ ቅርስነት ደግሞ የአማራና የትግራይ የሻዳይና የአሸንዳ በዓላት የጥምቀት በዓል ይጠቀሳሉ። 
ኢትዬጳያ ግን ለቱሪስት ኢነደስትሪው ግብአት የሚሆኑ ሀብቶቾ እነዚህ ብቻ አይደሉም…ሀገሪቱ እራሱ ሙሉ በሙሉ በዩንሰኮ ቅርስነት ብትመዘገብ አያንስባትም…ግን በዛ መጠን የሚያስብ በዛም መጠን የሚሰሩ ልጆች ወልዳ አለማሳደጎ በጣት የሚቆጠሩትን ብቻ ማስመዝገብ ችላለች፡፡

ይገርማችኋል ይህቺ ሀገር ሙሉ ነች፡፡ሙሉ ስላችሁ ለምሳሌ አየር ፀባዮ  ደጋ ጥቂት ፈቅ ስትሉ ወይና ደጋ ..ብዙም ሳትርቁ ቆላ ታገኛላችሁ፡፡ይሄ ድንቅና መድሎ ያለበት የተፈጥሮ ስጦታ ነው…መልካ ምድሯን ስንመለከት  ለጥ ያለ ሜዳ…ደግሞ ቀጥ ያለ ተራራ..እሱ ሲገርማችሁ ጭው ያለ ገደል…በሌላ ጎኑ እንደጣባ አህያ የተራቆተ መሬት…እንደ ደብረብርሀን የሱፍ በግ ጥቀጥቅ ያለ ጫካ…ኩሬ ሀይቅ ወንዝ….አቤት እነዛ አሜሪካኖቹ ይሄን መልካ ምድር ከዚህ የተመጣጠነ ምግብ ከሆነ አየሯ ጋ ቢያገኙት.. አቤት ይሮፖዎች ያ በቆፈን የሚያኮራምት በረዶ ገላግሎቸው እንዲህ ሚዛኑን የጠበቀ አየር ቢያድላቸው ምን ያህል ተአምራዊ ህይወት ይኖሩ ነበር.. ተፈጥሮ ሚዛኗን የምትጠብቅበት የራሷ ቀመር አለት መሰለኝ ለእነሱ ሀብት ከቆፈን ጋር ስታድል ለእኛ ምርጥ አየር ከችጋር ጋር.. ያስቃል….እነሱ በቱሪስት ሆነው መልካምድሯን አይተው ለመደሰት እና አይሯን ምገው ሀሴት ለማድረግ ምቾት ባለው አይሮፕላን መጥተው ገንዘባቸውን ከስክሰው ከረምረም ብለው ይመለሳሉ..እኛ በስደት መልክ ከችግር ለመላቀቅ በእግር ተጉዘን በባህር ተጉዘን ሀገራቸው እንገባና ጉልበታችንን አንጠፍጥፈን አንገታችንን ደፍተን ስንባዝን ስንባዝን እንኖርና በዛው የውሀ ሽታ ሆነን እንቀራለን የእነሱ አንድ ነፍስ በእኛ ስንት ነፍስ እንደሚመነዘር ስሌቱ አይታወቅም ..ምን አልባት የብራችን ምንዛሬ ወይም ዋጋ ልዩነትን ያህል የነፍሳችንም ዋጋ ልዩነት ይኖረው ይሆናል…

….ይሄን ሁሉ ይምታስበው.ይሄን ሁሉ የምትመኘው በአየር ላይ ሆና ንስሯ ጀርባ ላይ ተጣብቆ ነው እየተጓዙ ያሉት… 

ያው ሰው በተፈጥሮ በመጨረሻው የህይወቱ ማብቂያ ሰዓት ቁጭት ውስጥ መግባቱ እና ፀፀቱን መናዘዙ ተለመደ አይደል..እሷም ያው በግማሽም ሰው በመሆኗ መጠን ከሰውም ኢትዬጵያዊ ስለሆነች ያው ያ ደግሞ ክርስቶስም ለስጋው አደላ የእንደሚባለው ለእሷም ለዘመዶቿ ተቆጭታ ነው እንጂማ የእሷ የአባቷ ዘመዶች በምድራዊ ዕውቀት የማይመዘን ብቃት እንዳላቸው ታውቃለች፡፡

ለማንኛውም አሁን ደሎ ደርሰዋል…ግን ቀጥታ ወደእናቷ ቤት መሄድ አልፈለገችም ..በመጀመሪያ ያደገችበትን ጫካ ልትሰናበት ፈለገች..መቼስ የደሎመና ጫካ ጫካ ብቻ አይደልም …ውስጡ  የቡና ተክል የተሰገሰገበት ነው..ልጅ ሆነው እንጨት ለቀማ ከእኩዬቾ ጋር ስትሰማራ ከቡናው ተክል ድፍኑን ሸምጥጠውን ይመጡት ነበር..የቡና ተክል ጥሬ ሆኖ ድፍን አረንጓዴ ነው …እየበሰለ ሲሄድ ቢጫ እየሆነ ይመጣል በስተመጨረሻ ሙሉ ብስል  ሆኗል የሚባለው ሙሉ ቀይ ሲሆን ነው..ታዲያ በዛን ጊዜ ፍሬውን ቀፈው ይመጣሉ…ቀዩ የቡና ገለፈት በወስጡ የያዘው ፈሳሽ ልዩ ጣዕም አለው….ሌላው የሚገርማት ይሄ አሁን ከላይ ወደታች የማታየው የደሎ ጫካ ወይም ሀራና ደን የመንግስት ነው…በውስጡ ከደኑ ጋ ተሰባጥሮ ሚገኘው የቡና ተክል ደግሞ የግለሰብ ነው….የኢትዬጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲህ ተዋህደው በስምም ሲጠቀሙ በዚህ ደን ብቻ ነው ያየችው፡፡