TIKVAH-ETHIOPIA
1.43M subscribers
55.6K photos
1.39K videos
200 files
3.74K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#CBE
ግብርዎን በሲቢኢ ብር መተግበሪያ እንዴት ይከፍላሉ?
=======
ለአዲስ አበባ፣ ድሬዳዋ እና ሶማሌ ክልል ግብር ከፋዮች

ከግብር ሰብሳቢው ተቋም
• የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር፣
• የገንዘብ መጠን እና
• የክፍያ ማዘዣ ቁጥር የያዘ መልእክት ሲደርስዎት

የሲቢኢ ብር መተግበሪያዎን በመክፈት ቅደም ተከተሉን ጠብቀው ግብርዎን በቀላሉ ይክፈሉ፡፡

የሲቢኢ ብር መተግበሪያን ለማውረድ፡

• Android፡ https://play.google.com/store/apps/details?id=prod.cbe.birr
• IOS፡ https://apps.apple.com/us/app/cbebirr/id1600841787

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
ሁሌም የሚተማመኑበት ባንክ!
***
የፌስቡክ እና የቴሌግራም ገፆቻችንን ይቀላቀሉ!  
• Facebook፡- https://www.facebook.com/combanketh  
• Telegram፡- https://t.me/combankethofficial
#CBE

በቲክቶክ ያግኙን!
*********
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን ትክክለኛ የቲክቶክ ገጽ (https://www.tiktok.com/@combankethiopia) በመከተል ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃ ያግኙ!
********
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
ሁሌም የሚተማመኑበት ባንክ!
#CBE

በአዲስ መልክ!
****
የነበሩትን አ
ሻሽሎ፣
በርካታ አዳዲስ ነገሮችን አካቶ፣
ለአጠቃቀም ቀሎ፣
ፍጥነት እና ምቾት ጨምሮ፣
በአዲስ መልክ በቀረበው የሲቢኢ ብር መተግበሪያ ይጠቀሙ!
****

አሁኑኑ ወደ
Google Play ወይም App Store በመግባት የሲቢኢ ብር መተግበሪያዎን ያዘምኑ/ ይጫኑ!
• ለአንድሮይድ ስልኮች፡
https://play.google.com/store/apps/details?id=prod.cbe.birr

• ለአፕል ስልኮች፡
https://apps.apple.com/us/app/cbebirr/id1600841787

*** 
የፌስቡክ እና የቴሌግራም ገፆቻችንን ይቀላቀሉ!  
• Facebook፡- https://www.facebook.com/combanketh  
• Telegram፡- https://t.me/combankethofficial
#CBE
በቀጥታ ወደ ወዳጅ ዘመድዎ ሂሳብ!
EthioDirect
===========
በኢትዮ-ዳይሬክት ከውጭ ሀገር ገንዘብ መላኪያ መተግበሪያ የማስተር ወይም የቪዛ ካርድዎን ተጠቅመው በማንኛውም ጊዜና ቦታ በሞባይል ስልክዎ ቀጥታ ወደ ወዳጅ ዘመድዎ ሂሳብ መላክ ይችላሉ፡፡
#ቀላል #ፈጣን #አስተማማኝ #ነፃ
===========
የEthioDirect የሞባይል መተግበሪያ ከPlay Store ወይም  App Store በማውረድ  አገልግሎቱን ይጠቀሙ።
• ለአንድሮይድ ስልኮች
https://play.google.com/store/apps/details?id=com.combanketh.ethiodirect
• ለአፕል ስልኮች
https://apps.apple.com/us/app/ethiodirect/id1602064491

***  
የፌስቡክ እና የቴሌግራም ገፆቻችንን ይቀላቀሉ!  
• Facebook፡- https://www.facebook.com/combanketh  
• Telegram፡- https://t.me/combankethofficial
#CBE

እጥፍ ወለድ....
********
ከባህር ማዶ ገንዘብ ሲላክልዎ፤
አዲሱን የውጭ ሐዋላ የቁጠባ ሂሳብ ይክፈቱ!

• ከመደበኛው ሂሳብ እጥፍ ወለድ ያስገኛል ፣
• ለውጭ ሀገር ጉዞዎ ቅድሚያ የውጪ ምንዛሬ አገልግሎት እና
• የሞባይል ካርድ ስጦታም ያገኛሉ ።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
ሁሌም የሚተማመኑበት ባንክ!
***********

የፌስቡክ እና የቴሌግራም ገፆቻችንን ይቀላቀሉ!
• Facebook፡- https://www.facebook.com/combanketh
• Telegram፡- https://t.me/combankethofficial
#CBE

CashGo (ካሽ ጎ) - ከውጭ ሀገራት ገንዘብ መላኪያ የሞባይል መተግበሪያ
===========================
በሞባይል ስልክዎ አማካኝነት ቪዛና ማስተር ካርድዎን በመጠቀም

• ከውጭ ሀገር በቀጥታ ወደ ወዳጅ ዘመድዎ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሂሳብ ወይም ወደ ሲቢኢ ብር ሂሳብ መላክ ይችላሉ፣ አሊያም
• ተቀባዩ ከ1900 በላይ በሚሆኑት የባንካችን ቅርንጫፎች መቀበል ይችላሉ!
**************
የCashGo ሞባይል መተግበሪያን ከ Play Store ወይም App Store በማውረድ ይጠቀሙ።

• ለአንድሮይድ ስልኮች
https://play.google.com/store/apps/details?id=com.bankofabyssinia.cashgo&hl=en&gl=US

• ለአፕል ስልኮች
https://apps.apple.com/us/app/cashgo/id1559346306
#CBE

በአዲስ መልክ!
****
የነበሩትን አ
ሻሽሎ፣
በርካታ አዳዲስ ነገሮችን አካቶ፣
ለአጠቃቀም ቀሎ፣
ፍጥነት እና ምቾት ጨምሮ፣
በአዲስ መልክ በቀረበው የሲቢኢ ብር መተግበሪያ ይጠቀሙ!
****

አሁኑኑ ወደ
Google Play ወይም App Store በመግባት የሲቢኢ ብር መተግበሪያዎን ያዘምኑ/ ይጫኑ!
• ለአንድሮይድ ስልኮች፡
https://play.google.com/store/apps/details?id=prod.cbe.birr

• ለአፕል ስልኮች፡
https://apps.apple.com/us/app/cbebirr/id1600841787

*** 
የፌስቡክ እና የቴሌግራም ገፆቻችንን ይቀላቀሉ!  
• Facebook፡- https://www.facebook.com/combanketh  
• Telegram፡- https://t.me/combankethofficial
የነዳጅ ክፍያዎን በሲቢኢ ብር በቀላሉ ይፈፅሙ!
**********
አዲስ በተሻሻለው የሲቢኢ ብር መተግበሪያ የነዳጅ ክፍያን መፈፀም እጅግ ቀሏል፡፡

የነዳጅ ቀጂውን ስልክ ቁጥር፣ የሚገዙትን የነዳጅ መጠን እና አይነት እንዲሁም ታርጋ ቁጥርዎን በማስገባት ብቻ ክፍያውን በቀላሉ መፈፀም ይችላሉ!
**********
የሲቢኢ ብር መተግበሪያን ለማውረድ/ለማዘመን፡

• ለአንድሮይድ ስልኮች፡ https://play.google.com/store/apps/details?id=prod.cbe.birr
• ለአፕል ስልኮች፡ https://apps.apple.com/us/app/cbebirr/id1600841787

#CBE #cbebirr #fuel #payment
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፤ የዲጂታል ባንክ አግልግሎት ሙሉ በሙሉ መጀመሩን ገለጸ። ባንኩ ፤ በሲስተም ችግር ምክንያት ፦ - በቅርንጫፎች፥ - በኢንተርኔት ባንኪንግ፥ - በሞባይል ባንኪንግ፥ እንዲሁም በሲቢኢ ብር የአገልግሎት መቋረጥ አጋጥሞ እንደነበር አስውሷል። በቅርንጫፍ እና በኤቲኤም የሚሰጡ አገልግሎቶች ቀደም ብለው መጀመራቸውን ገልጾ አሁን ደግሞ በዲጂታል የሚሰጡ የባንክ አገልግሎቶች…
#Update #CBE #NBE

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ትላንት ባጋጠመው ችግር የደንበኞች መጉላላትን ጨምሮ የደረሱ #ጉዳቶች ስለመኖራቸው ተነግሯል።

ጉዳቶቹ ምርመራ ተደርጎ ወደፊት ለህብረተሰቡ ይገለጻሉ ነው የተባለው።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መጋቢት 7 በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዲጂታል ባንክ  ስርዓት ላይ ያጋጠመውን ችግርና የአገልግሎት መቋረጥ በተመለከተ ዛሬ መግለጫ አውጥቷል።

" ባንኮች በሥርዓቶቻቸዉ ላይ በየጊዜዉ የደህንነት ፍተሻ እንዲሁም የማሻሻያ ሥራዎችን ያከናዉናሉ " ያለው ብሔራዊ ባንክ ፤ " በሥርዓቶቹ ላይ በሚከናወን ለዉጦችና ፍተሻዎች የባንኮች አገልግሎት አልፎ አልፎ ሊቋረጥ ይችላል " ብሏል።

በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በትናንትና ዕለት የተከሰተዉ የአገልግሎት መቋረጥ ከዚሁ ጋር የተያያዘ መሆኑን #አረጋግጫለሁ ሲል ገልጿል።

ችግሩ ከተከሰተበት ሰዓት አንስቶ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን የባንኩን እና የደንበኞቹን ደህንነት ለማረጋገጥ ከፍተኛ ክትትል ሲያደርግ እንደቆየና በተደረገው ርብርብ አገልግሎቶች እንዲመለሱ መደረጉን ጠቁሟል።

ብሔራዊ ባንክ በዚሁ መግለጫ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ባጋጠመው ችግር #ጉዳቶች እንደደረሱ ጠቁሟል።

ስለ ጉዳቶቹ በዝርዝር ያለው ነገር ባይኖርም አስፈላጊው ምርመራ ተደርጎ ወደፊት ለህዝብ ይገለጻል ብሏል።

በተፈጠረው ችግር የደንበኞች መጉላላትም መከሰቱን አመላክቷል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በፋይናንስ ተቋማት ላይ በየጊዜዉ ክትትልና ቁጥጥር እንደሚያደርግ አመልክቶ በአሁኑ ጊዜ በሀገሪቱ ያሉ በሁሉም የፋይናንስ ተቋማት የሚገኙ የፋይናንስ ሥርዓቶች ደህንነቸዉ የተጠበቀ ነው ብሏል።

" ህብረተሰቡ ያለምንም ስጋት የፋይናንስ አገልግሎቶችን መጠቀም መቀጠል ይችላል " ሲል አሳውቋል።

የፋይናንስ ተቋማትም የሥርዓቶቻቸዉን ደህንነትና ቀልጣፋነት ይበልጥ ለማሳደግ የቴክኖሎጂ ተለዋዋጭ ባህርይ በማየት በቀጣይነት መሥራት እንደሚኖርባቸዉ #ጥብቅ_ማሳሰቢያ ሰጥቷል።

@tikvahethiopia
#CBE

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሰሞኑን " በሲስተም መበላሸት " ምክንያት አጋጥሞት ከነበረው ሁኔታ ጋር በተያያዘ ያሉ ጉዳዮች ላይ ከጥቂት ደቂቃዎች በኃላ በዋና መ/ቤቱ መግለጫ እንደሚሰጥ ገልጿል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#CBE

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዝዳንት አቶ አቤ ሳኖ ምን አሉ ?

- " ችግሩ የተከሰተው አንድ ሂሳብ ማስታረቅ ቅልጥፍና እንዲያመጣ ታስቦ የተሰራ የሲስተም ማሻሻያ ሲተገበር ስህተት በመፈጠሩ ነው። የተፈጠረው ስህተት ለሌቦች ቀዳዳ ከፍቶ ነበር። "

- " የሲስተም ማሻሻያው የተተገበረው አርብ መጋቢት 6/2016 ዓ.ም ከምሽቱ 3 ሰዓት አካባቢ ነበር። ከሌሊቱ 8 ሰዓት አካባቢ ችግር እንዳለ ሊለይ ችሏል። ይህን ተከትሎም አንዳንድ የተጠረጠሩ አገልግሎቶች እንዲቋረጡ ተደርጓል። ይህም ሆኖ ሙሉ በሙሉ ችግሩ ስላልቆመ ሁሉም የዲጂታል ባንክ ስርዓቶች እንዲቋረጡ ተደርጎ ነበር። "

- " ባንኩ ችግሩ በተከሰተበት ወቅት ከ490 ሺህ በላይ የገንዘብ ልውውጥ ተካሂዷን። ሌሊቱን ሙሉ ግብይት ሲፈጸምባቸው የነበረባቸው የባንክ ሂሳቦች በሙሉ እስኪጣራ ድረስ #እንዲታገድ ተደርጓል። "

- " በቀጣይ ከፍተኛ እና ያልተገባ ግብይት የፈጸሙ አካላትን እየለየን ለህግ የማቅረብ ስራ ይሰራል። "

- " የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በወንጀሉ ዋነኛ ተዋናይ መሆናቸው አሳዝኖናል። በየአካባቢው ያሉ የዲስትሪክት ኃፊዎች በየአካባው ከሚገኝ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመቀናጀት ተማሪዎች የወሰዱትን ገንዘብ #እንዲመልሱ እየተደረገ ነው። "

- " ከተፈጠረው ችግር ጋር ተያይዞ አጠቃላይ የደረሰው ጉዳት ላይ ምርመራ እየተደረገ ነው። የችግሩ መሰረታዊ መንስዔ እና ያስከተለውን ጉዳትም ምርመራው ሲጠናቀቅ ይፋ ይደረጋል። "

- " ባንኩ ላይ የደረሰው ጉዳት ባንኩ ካለው ሀበት እና አቅም አንጻር የጎላ ተጽእኖ የለውም፤ ከደንበኞች ሂሳብ ጋርም አይገናኝም። " #አልአይን

@tikvahethiopia
መተግበሪያዎን ሲቢኢ ብር ላይ ያስቀምጡ
በቀላሉ በርካታ ደንበኞች ዘንድ ይድረሱ!

#CBE #cbebirr #apps #digitalbanking
*************
የሲቢኢ ብር መተግበሪያ ማስፈንጠሪያ፡

• ለአንድሮይድ ስልኮች፡ https://play.google.com/store/apps/details?id=prod.cbe.birr
• ለአፕል ስልኮች፡ https://apps.apple.com/us/app/cbebirr/id1600841787
TIKVAH-ETHIOPIA
CBE Name.pdf
#CBE

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቀሪ ገንዘብ ያልመለሱ ገንዘቡን እንዲመልሱ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ሰጠ።

ቀሪ ገንዘብ ያልመለሱ ግለሰቦችን ስም ዝርዝርም ይፋ አድርጓል።

ባንኩ ችግር ገጥሞት በነበረበት ወቅት በህገወጥ መንገድ ገንዘብ የወሰዱ እስከ ቅዳሜ መጋቢት 14 ቀን 2016 ዓ.ም. ተመላሽ እንዲያደርጉ አሳስቦ ነበር።

በዚህ መሰረት 9281 የሚሆኑ ግለሰቦች በተሰጠው ጊዜ ገደብ ተጠቅመው የወሰዱትን ገንዘብ ሙሉ በሙሉ መልሰዋል ብሏል።

5166 ግለሰቦች ባንኩ የሰጠውን ዕድል በመጠቀም ያላግባብ የወሰዱትን ገንዘብ በከፊል ተመላሽ ያደረጉ ቢሆንም እስከ ዛሬ ድረስ ቀሪውን ገንዘብ አልመለሱም ሲል ገልጿል።

ባንኩ ወደ ቀጣዩ #ሕጋዊ እርምጃ ከማለፉ በፊት ቀሪውን ገንዘብ እንዲመልሱ እስከ ቅዳሜ መጋቢት 21 ቀን 2016 ዓ.ም ከቀኑ 11 ሰዓት ድረስ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ሰጥቷል።

ገንዘቡን የማይመልሱ ከሆነ በባንኩ በኩል ቀጣይ ሕጋዊ እርምጃ እንደማይኖር አረጋግጧል።

እስከተጠቀሰው ቀን ገንዘቡን #የማይመልሱ ካሉ የተለያዩ የመገናኛ ብዙኃን ዘዴዎችን በመጠቀም ፦
- ሙሉ ስማቸው
- ፎቷቸው
- በሕገ ወጥ መንገድ ገንዘብ በመውሰድ ወንጀል መጠርጠራቸውን በመግለፅ ለሚመለከታቸው የሕግ አካላትና ተቋማት ይገለጻል ለሕዝብም ይፋ ይደረጋል ብሏል።

ከሕግ አካላት እና ከሚመለከታቸው ተቋማት ጋር በመተባበር ቀጣይ #የወንጀል፣ የፍትሐ ብሔር እና የአስተዳደር ሕጋዊ እርምጃዎችም እንደሚወሰዱ በጥብቅ አስጠንቅቋል።

ስም ዝርዝሩን በዚህ መልከቱ ፦ https://t.me/tikvahethiopia/86375

@tikvahethiopia
ኮንሰርት፣ ባዛር ሲያዘጋጁ
ፊልም/ቲያትር ሲያቀርቡ
የሚታይ የሚጎበኝ ሲኖርዎት
የመግቢያውን ትኬት
እኛ እንሽጥልዎት!
https://www.facebook.com/combanketh
https://t.me/combankethofficial
**********
በሲቢኢ ብር መተግበሪያ የትኬት ሽያጭ አገልግሎት
በቀላሉ ሚሊዮኖች ጋር ይደርሳሉ!

#CBE #cbebirr #apps #digitalbanking
*************
የሲቢኢ ብር መተግበሪያ ማስፈንጠሪያ፡

• ለአንድሮይድ ስልኮች፡ https://play.google.com/store/apps/details?id=prod.cbe.birr
• ለአፕል ስልኮች፡ https://apps.apple.com/us/app/cbebirr/id1600841787
TIKVAH-ETHIOPIA
#CBE የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቀሪ ገንዘብ ያልመለሱ ገንዘቡን እንዲመልሱ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ሰጠ። ቀሪ ገንዘብ ያልመለሱ ግለሰቦችን ስም ዝርዝርም ይፋ አድርጓል። ባንኩ ችግር ገጥሞት በነበረበት ወቅት በህገወጥ መንገድ ገንዘብ የወሰዱ እስከ ቅዳሜ መጋቢት 14 ቀን 2016 ዓ.ም. ተመላሽ እንዲያደርጉ አሳስቦ ነበር። በዚህ መሰረት 9281 የሚሆኑ ግለሰቦች በተሰጠው ጊዜ ገደብ ተጠቅመው የወሰዱትን…
#CBE

ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፤ #የራሳቸውን_ያልሆነውን ገንዘብ ከባንኩ ወስደው ሙሉ በሙሉ ያልመለሱ (በከፊል የመለሱ) 5166 ግለሰቦች የሚቀረውን ብር እንዲመልሱ የሰጠው የመጨረሻ ቀነ ገደብ ዛሬ ቅዳሜ 11:00 ላይ ያበቃል።

ባንኩ ፤ ገንዘቡን #የማይመልሱ ካሉ የተለያዩ የመገናኛ ብዙኃን ዘዴዎችን በመጠቀም ፦
- ሙሉ ስማቸው
- ፎቷቸው
- በሕገ ወጥ መንገድ ገንዘብ በመውሰድ ወንጀል መጠርጠራቸውን በመግለፅ ለሚመለከታቸው የሕግ አካላትና ተቋማት እንዲሁም ለህዝብ እንደሚያሳውቅ አሳስቦ ነበር።

ባንኩ ከቀናት በፊት ፤ ገንዘብ ወስደው ጭራሽ ያልመለሱ 565 ደንበኞቹንና በከፊል መልሰው የሚቀር ገንዘብ ያልመለሱ 5166 ደንበኞቹን ስም ዝርዝር ይፋ ማድረጉ ይወሳል።

በሌላ በኩል ፤ አንዳንድ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የወሰዱትን እና ወደ ግል ባንኮች ያዘዋወሩትን ገንዘብ በዲጂታል መንገድ ወደ ንግድ ባንክ ቢመልሱም ገንዘብ ካልመለሱት ጋር ስማቸው መውጣቱን በመግለፅ ንግድ ባንክ ማስተካከያ እንዲያደርግ ጠይቀዋል።

ንግድ ባንክ ዓርብ በመጋቢት 6 / 2016 ለሊት በ25,761 ደንበኞች ከ801 ሚሊዮን ብር በላይ ገንዘብ እንደተወሰደበት ከዛ ውስጥ 622 ሚሊዮን ያህሉን ማስመለሱን ከ4 ቀን በፊት መግለጹ ይወቃል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#CBE

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ምን አለ ?

መጋቢት 7 / 2016 ዓ/ም ባጋጠመው የሲስተም ችግር ምክንያት ያለአግባብ የገንዘብ ልውውጥ እንደነበር ፤ በዚህም በርካታ ግለሰቦች በጥሬ ገንዘብ እንዲሁም በዲጂታል የክፍያ አማራጮች የወሰዱትን የገንዘብ ልክ እየመለሱ እንደሆነ ገልጿል። 

ነገር ግን አንዳንድ ግለሰቦች የወሰዱትን ገንዘብ ወደ #ቤቲንግ (የስፖርት ውርርድ) ተቋማት በማዛወራቸው መመለስ እንደተቸገሩ ጥቆማ እንደሰጡት ገልጿል።

ገንዘቡን ተመላሽ ማድረግ እንዲቻል ወደ ቤቲንግ ተቋማት የራሳቸው ያልሆነ ገንዘብ ያዘዋወሩ አቅራቢያቸው በሚገኝ የባንኩ ቅርንጫፍ በመገኘት ለዚሁ የተዘጋጀውን ቅጽ በመሙላት እንዲያመለክቱ አሳስቧል።

ባንኩ ገንዘብ ወስደው ሙሉ ሙሉ ያልመለሱ (በከፊል የመለሱ) ቀሪ ያልመለሱትን ገንዘብ እንዲመልሱ በማለት ለ5,166 ደንበኞቹ የሰጠው የመጨረሻ ማሳስቢያ ዛሬ ቅዳሜ አብቅቷል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#AU #Fraud #CBE

ቀሲስ በላይ መኮንን ከአፍሪካ ኅብረት ኦፊሳላዊ የክፍያ ሰነድ ጋር ተመሳስለው የተዘጋጁ የተለያዩ ሐሰተኛ የክፍያ ሰነዶችን በመጠቀም ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የአፍሪካ ኅብረት የባንክ ሒሳብ ወደ ሌላ የባንክ ሒሳብ #ከ6_ሚሊዮን_ዶላር_በላይ (367 ሚሊዮን ብር) ለማዘዋወር ሲሞክሩ ነው በቁጥጥር ሥር ውለዋል።

ፍድር ቤት ቀርበውም ለፖሊስ ተጨማሪ ቀን ተሰጥቷል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዜዳንት አቶ አቤ ሳኖ ምን አሉ ?

" በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ካለው የአፍሪካ ህብረት ሒሳብ የወጣ ገንዘብ የለም።

አንድ ሰው ሀሰተኛ ሰነዶችን ተጠቅሞ ለማውጣት ቢሞክርም እዛው በቦታው ላይ ተይዟል።

የማጭበርበር ሃሳብና ገንዘብ ለመውሰድ ጥረት ቢደረግም ማክሸፍ ችለናል። ይህንን የሞከሩት ሰዎች በፖሊስ ቁጥጥር ስር ናቸው። እኔ የማውቀው ይህን ብቻ ነው።

በመሰረቱ ጥሬ ገንዘብ በውጭ ምንዛሪ ሊሰጥ አይችልም። አጭበርባሪው መጥቶ  ሲጠይቅ ይህን እንኳን አያውቅም ነበር።

ሰውዬው እዚህ ሀገር የዶላር አካውንት ከሌለው ገንዘቡ ቢተላለፍም የትም ውስጥ ሊገባ አይችልም።

አጭበርባሪዎች በየቀኑ ነው ወደ ባንካችን የሚመጡት ፤ ባንክ ስለምንሰራ ይህ የተለመደ ነው። ነገር ን ሁሌም የማጭበርበር ድርጊቶቹ ከመሳካታቸው በፊት እንደርስባቸዋለን። ለፍርድም እናቀርባቸዋለን።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፥ የደንበኞቹን ሒሳቦች የመጠበቅ ኃላፊነት አለበት ያንን እያደረግን ነው። የአፍሪካ ህብረት እስካሁን ድረስ በይፋ ቅሬታ አላቀረበብንም። "

ስማቸው እንዲገለጽ ያልፈለጉ የአፍሪካ ኅብረት ምንጭ ምን አሉ ?

"የእኛ ሒሳብ ላይ መሰል ማጭበርበር ሲያጋጥም ይህ ለሶስተኛ ጊዜ ነው።

አሁን ላይ ማጭበርበሩ #በተከበሩ_ሰዎች አማካኝነት እየተሞከረ ነው። ይህ ደግሞ በጣም አስጨንቆናል። አንድ ቀን ባለስልጣናት ተመሳሳይ ነገር ላለማድረጋቸው ምንም አይነት ዋስትና የለንም።

እምነት እያጣን ነው። ስለዚህ ኢትዮጵያ ውስጥ ለደሞዝ አነስተኛ መጠን ያለው ፎሬክስ (የውጭ ምንዛሬ) ለመያዝ ወስነናል።

ይህን መሰሉ ሁኔታ የድርጅቱን ገንዘብ በውጭ ማቆየት እንድናስብ እያስገደደን ነው። "

https://telegra.ph/The-Reporter-04-21 #ሪፖርተር_ጋዜጣ

@tikvahethiopia
" በታሪኬ ከታክስ በፊት ከፍተኛውን ትርፍ አግኝቻለሁ " - ንግድ ባንክ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ2016 በጀት ዓመት 135.4 ቢሊዮን ብር አጠቃላይ ገቢ ማግኘቱን አሳውቋል።

በዚህ ዓመት ከታክስ በፊት የተገኘው 25.6 ቢሊዮን ብር ትርፍ እንደሆነ እና በባንኩ ታሪክ ከፍተኛው ሆኖ መመዝገቡን ገልጿል።

የባንኩ አጠቃላይ የተቀማጭ ገንዘብ መጠን ከ1.17 ትሪሊዮን ብር የተሻገረ መሆኑን ተናግሯል።

የባንኩ የደንበኞች ቁጥር ደግሞ ከ45 ሚሊዮን በላይ እንደሆነ አመልክቷል።

የተበላሸ ብድር ክምችቱ 2.6% መደረሱም ገልጿል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፥ ከ218 ቢሊዮን ብር በላይ የብድር አገልግሎት ማቅረቡን ጎልጾ 91% ወይም ብር 198 ቢሊዮን የሚበልጠው ለግሉ ሴክተር የተለቀቀ ብድር እንደሆነ አሳውቋል።

#CBE #Ethiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
በንግድ ባንክ ዛሬ የውጭ ምንዛሬ እንዴት ዋለ ? በባንኩ የውጭ ምንዛሬ በተለይ የዶላር ዋጋ ከትላንት ከሰዓቱ የተለየ አልነበረም። ዶላር ትላንትና ከሰዓት ሲገዛ እና ሲሸጥ በነበረበት ዛሬም በዛው ውሏል። አንድ ዶላር መግዣው 80 ብር ከ0203 ሳንቲም ፤ መሸጫው 81 ብር ከ6207 ሳንቲም ሆኖ ውሏል። ዩሮም ዛሬ ከትላንቱ ያን ያህል ልዩነት አልነበረውም። መግዣው 86 ብር ከ63 ሳንቲም መሸጫው 88 ብር…
#Update

ለነገ አርብ የውጭ ምንዛሬ ዋጋ ጨምሯል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የነገ አርብ ምንዛሬ ዋጋን ዛሬ ምሽት ይፋ አድርጓል።

በዚህም አንዱ የአሜሪካን ዶላር መግዣው 83 ብር ከ9413 ሳንቲም ፤ መሸጫው 85 ብር ከ6201 ሳንቲም እንዲሆን ቆርጧል።

ፓውንድ ስተርሊንግም በእጅጉ ጨምሯል። መግዣው 101 ብር ከ9101 ሳንቲም ፤ መሸጫው 103 ብር ከ9483 ሆኖ ይውላል ብሏል።

ዩሮም ጨምሯል። መግዣው 90 ብር ከ5307 ሳንቲም መሸጫው 92 ብር ከ3413 ሳንቲም እንደሚሆን አሳውቋል።

የUAE ድርሃም በተመሳሳይ ጨምሯል። አንዱ ድርሃም ነገ በ20 ብር ከ4557 ሳንቲም እየተገዛ ፤ በ20 ብር ከ8648 ሳንቲም ይሸጣል ብሏል።

#TikvahEthiopia #CBE #Floatingexchangerate

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ለነገ አርብ የውጭ ምንዛሬ ዋጋ ጨምሯል። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የነገ አርብ ምንዛሬ ዋጋን ዛሬ ምሽት ይፋ አድርጓል። በዚህም አንዱ የአሜሪካን ዶላር መግዣው 83 ብር ከ9413 ሳንቲም ፤ መሸጫው 85 ብር ከ6201 ሳንቲም እንዲሆን ቆርጧል። ፓውንድ ስተርሊንግም በእጅጉ ጨምሯል። መግዣው 101 ብር ከ9101 ሳንቲም ፤ መሸጫው 103 ብር ከ9483 ሆኖ ይውላል ብሏል። ዩሮም ጨምሯል።…
#Update

ዶላር መሸጫው ከ100 ብር አለፈ።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የነገ ቅዳሜ ምንዛሬ ዋጋን ዛሬ ምሽት ይፋ አድርጓል።

በዚህም አንዱ የአሜሪካን ዶላር መግዣው 95 ብር ከ6931 ሳንቲም ፤ መሸጫው 101 ብር ከ4347 ሳንቲም እንዲሆን ቆርጧል።

ፓውንድ ስተርሊንግም በእጅጉ ጨምሯል። መግዣው 116 ብር ከ6881 ሳንቲም ፤ መሸጫው 123 ብር ከ6894 ሆኖ ይውላል ብሏል።

ዩሮም እጅግ በጣም ጨምሯል። መግዣው 104 ብር ከ4107 ሳንቲም መሸጫው 110 ብር ከ6754 ሳንቲም እንደሚሆን አሳውቋል።

የUAE ድርሃም በተመሳሳይ ጨምሯል። አንዱ ድርሃም ነገ በ23 ብር ከ3201 ሳንቲም እየተገዛ ፤ በ24 ብር ከ7194 ሳንቲም ይሸጣል ብሏል።

#TikvahEthiopia #CBE #Floatingexchangerate

@tikvahethiopia