TIKVAH-ETHIOPIA
1.49M subscribers
56.5K photos
1.41K videos
203 files
3.84K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ለኮሮና ቫይረስ በፍጥነት ክትባት ይገኝለት ይሆን ?

በአሜሪካ የጤና ተቋም CDC በኃላፊነት የሚሰሩት ዶክተር ኤርሚያስ በላይ #ETHIOTUBE ላይ ቀርበው ይህን ተናግረዋል ፦

ክትባትን ለመፍጠር ብዙ ሰዎች በተለያዩ ሀገሮች ብዙ ስራ እየሰሩ ነው ያለው። ይሄ ክትባት ሊገኝ እንደሚችል ብዙ ተስፋ አለኝ። በቫይረስ ጥቃት ለሚመጡ በሽታዎች ክትባት ማግኘት በአብዛኛው ጊዜ ብዙ አይከብድም። የሚከብድባቸው ሆኔታዎችም ግን አሉ።

የኢንፉሌንዛ ቫይረስን ብንመለከት በተመሳሳይ ሁኔታ ነው የሚተላለፈው፤ ለኢንፉሌንዛ ቫይረስ ክትባት በየአመቱ ይሰራል። ለዚህኛውም ቫይረስ ክትባት እንደሚገኝለት #ተስፋ አደርጋለሁ። ግን ይሄን ክትባት ለማግኘት ብዙ ጊዜ ይወስዳል። ከ8-12 #ወራት ሊወስድ ይችላል።

ቫይረሱ ቢጠቃ በክትባት ሊሸነፍ የሚችልበትን ቦታ ማግኘት ያስፈልጋል፤ ይሄ በላብራቶሪ ጥናት ከተደረገ በኃላ ለዛ ክትባት ተዘጋጅቶ በእንስሶች ውስጥ ሙከራ ማድረግ ይፈልጋል፣ ከዛም በሰዎች ላይ ጥናት ማድረግ ያስፈልጋል፣ ከዛም ቁጥሩ በዛ ያለ ህዝብ ላይ ይሄ ክትባት ከበሽታው መከላከል መቻሉ ማረጋገጥ ያስፈልጋል። ይሄ ሁሉ ሂደት ረጅም ጊዜ ይወስዳል።

አንዴ በጥናት ከተረጋገጠ በኃላ እንኳን ለብዙ ሰዎች እንዲሆን አድርጎ በስፋት ማምረት እንኳን ብዙ ጊዜ ይወስዳል። ቢያንስ ቢያንስ ሁለትና ሶስት ወራት ሊወስድ ይችላል። ስለዚህ ክትባት ማግኘቱን ቀላል ነገር ተደርጎ ቢታሰብም ለግለሰቦች እንዲባዛ አድርጎ ማቅረቡ በጣም ጊዜ ይወስዳል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ኮቪድ-19 ክትባትም ሆነ መድሃኒት የለውም!

በመዘናጋት ከፍተኛ ዋጋ እንዳንከፈል በድጋሚ አደራ ለማለት እንወዳለን። በአሁን ሰዓት ለኮሮና ቫይረስ በሽታ [ኮቪድ-19] ምንም የተረጋገጠ ክትባትም ሆነ መድሃኒት የለውም።

በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች የምትሰሟቸው መረጃዎች በስራ ላይ ያሉ እጅግ በጣም ጊዜ የሚፈልጉ ናቸው። አሁን ያለው ብቸኛው መድሃኒት የጤና ባለሞያዎችን ምክር ማዳመጥ ነው።

ከሰሞኑን በአሜሪካ የጤና ተቋም CDC በኃላፊነት የሚሰሩት ዶክተር ኤርሚያስ በላይ ይህን ማለታቸው አይዘነጋም ፦ "...ለዚህኛው ቫይረስ [ለኮቪድ-19] ክትባት እንደሚገኝለት ተስፋ አደርጋለሁ። ግን ይሄን ክትባት ለማግኘት ብዙ ጊዜ ይወስዳል። ከ8-12 #ወራት ሊወስድ ይችላል።"

በተለያዩ ባልተጨበጡ መረጃዎች ፣ እንዲሁም በሂደት ላይ ባሉ የምርምር ስራዎች ዙሪያ የሚወጡ መረጃዎችን በመስማት የስፔን እና ጣልያን አሁን ደግሞ የአሜሪካ ዜጎች እየከፈለቱ ያለውን ዋጋ እንዳንከፍል አደራ።

እራሳችንን እንጠብቅ፤ የምንባለውን እናድምጥ!

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#REPOST

ለኮሮና ቫይረስ በፍጥነት ክትባት ይገኝለት ይሆን ?

በአሜሪካ የጤና ተቋም CDC በኃላፊነት የሚሰሩት ዶክተር ኤርሚያስ በላይ #ETHIOTUBE ላይ ቀርበው ይህን ተናግረዋል ፦

ክትባትን ለመፍጠር ብዙ ሰዎች በተለያዩ ሀገሮች ብዙ ስራ እየሰሩ ነው ያለው። ይሄ ክትባት ሊገኝ እንደሚችል ብዙ ተስፋ አለኝ። በቫይረስ ጥቃት ለሚመጡ በሽታዎች ክትባት ማግኘት በአብዛኛው ጊዜ ብዙ አይከብድም። የሚከብድባቸው ሆኔታዎችም ግን አሉ።

የኢንፉሌንዛ ቫይረስን ብንመለከት በተመሳሳይ ሁኔታ ነው የሚተላለፈው፤ ለኢንፉሌንዛ ቫይረስ ክትባት በየአመቱ ይሰራል። ለዚህኛውም ቫይረስ ክትባት እንደሚገኝለት #ተስፋ አደርጋለሁ። ግን ይሄን ክትባት ለማግኘት ብዙ ጊዜ ይወስዳል። ከ8-12 #ወራት ሊወስድ ይችላል።

ቫይረሱ ቢጠቃ በክትባት ሊሸነፍ የሚችልበትን ቦታ ማግኘት ያስፈልጋል፤ ይሄ በላብራቶሪ ጥናት ከተደረገ በኃላ ለዛ ክትባት ተዘጋጅቶ በእንስሶች ውስጥ ሙከራ ማድረግ ይፈልጋል፣ ከዛም በሰዎች ላይ ጥናት ማድረግ ያስፈልጋል፣ ከዛም ቁጥሩ በዛ ያለ ህዝብ ላይ ይሄ ክትባት ከበሽታው መከላከል መቻሉ ማረጋገጥ ያስፈልጋል። ይሄ ሁሉ ሂደት ረጅም ጊዜ ይወስዳል።

አንዴ በጥናት ከተረጋገጠ በኃላ እንኳን ለብዙ ሰዎች እንዲሆን አድርጎ በስፋት ማምረት እንኳን ብዙ ጊዜ ይወስዳል። ቢያንስ ቢያንስ ሁለትና ሶስት ወራት ሊወስድ ይችላል። ስለዚህ ክትባት ማግኘቱን ቀላል ነገር ተደርጎ ቢታሰብም ለግለሰቦች እንዲባዛ አድርጎ ማቅረቡ በጣም ጊዜ ይወስዳል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ተጨማሪ በጀት ለፓርላማ ሊቀርብ ነው። የኢትዮጵያ መንግስት ከዓለም አቀፍ አበዳሪ ድርጅቶች ያገኘውን ድጋፍ እና ብድር የያዘ ተጨማሪ በጀት በቅርቡ ለፓርላማ አቅርቦ እንደሚያስጸድቅ የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ተናግረዋል። ይህ የተናገሩት ዛሬ በነበረው የምክር ቤቱ አስቸኳይ ስብሰባ ወቅት ነው። ተጨማሪ በጀቱ ፦ ➡️ ለዝቅተኛ ተከፋይ የመንግስት ሰራተኞች ለሚደረግ የደመወዝ ጭማሪ፣ ➡️ ለነዳጅ…
#Ethiopia : " የዋጋ ንረት (inflation) ጫና እንዳለ በተደጋጋሚ ተነስቷል።

ይሄ ሪፎርም (የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ማለታቸው ነው) በመጀመሪያዎቹ
#ወራት ወይም #ዓመት ጫና የሚያመጣ መሆኑ ይታወቃል።

በዘላቂነት የዋጋ ንረትን (inflation) ለመቆጣጠር ግን ከዚህ ውጭ አማራጭ የለንም። " - የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ (ለህ/ተ/ም/ቤት የተናገሩት)

ገና በመጀመሪያዎቹ ቀናት " ዶላር ጨምሯል " በሚል የታዩት መሰረታዊ ነገሮች ላይ ዋጋን የመጨመር አዝማሚያዎች ዜጎችን በተለይ ደግሞ በዝቅተኛ ገቢ ሚኖሩትን እጅግ በጣም ከፍተኛ ጭንቀት ላይ የጣለ ሆኗል።

ከዛሬ ነገስ ምን ይፈጠር ይሆን ? በሚልም እንቅልፍ ነስቷቸዋል።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia