TIKVAH-ETHIOPIA
1.44M subscribers
55.9K photos
1.4K videos
202 files
3.77K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
በሀገራችን #ተስፋ አንቆርጥም.../TIKVAH-ETHIOPIA/ ማለት ተስፋ ኢትዮጵያ ማለት ነው!

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የፍቅር #ጉዟችንን በተመለከተ...

በTIKVAH-ETH በኩል #የተሰባሰቡት ወጣቶች ከሁሉም የሀገሪቱ ክፍል የተውጣጡ ትክክለኛውን የኢትዮጵያ ቀለም የያዙ ናቸው። ሁሉም ወጣቶች እናት ሀገራቸውን የሚወዱ እና በሀገሪቱ ላይ አዲስ ታሪክ ለመፃፍ ከሳምንት እስከ ሳምንት ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ፤ የትምህርት እና የግል ጊዜያቸውን ትተው ለሰላምና ፍቅር የሚጓዙ ናቸው። ለዚህም ሰላም ወዳዱ የኢትዮጵያ ህዝብ #ሊያመሰግናቸው ይገባል።

ዩኒቨርስቲዎችን በተመለከተ፦

#StopHateSpeech በሁሉም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚካሄድ ሲሆን የመጀመሪያው ምዕራፍ ከተማሪዎች ጋር የሚደረግ #ውይይት እና #ንግግር የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ነው። ምክንያቱም ወጣቶች ከጥላቻ እና ከስሜታዊነት ርቀው ሀገር መገንባትና ለህዝብም #ተስፋ የሚሰጡ ዜጎች እንደሆኑ ማስመስከር ስለምንፈልግ ነው።

ይህ ጉዞ እና እንቅስቃሴ ከየትኛውም አይነት የፖለቲካ አመለካከት ነፃ የሆነ፤ ከየትኛውም ድርጅትም ሆነ ቡድን ገለልተኛ የሆነ በወጣቶች የሚደረግ እንቅስቃሴ ነው። ወጣቶቹም ትክክለኛ የሀገሪቱን ቅርፅ የያዙ በፍቅር እና በንግግር የሚያምኑ ሀገሪቷን ከጥላቻ አላቀው ትልቅ ሀገር የመገንባት ህልም ያላቸው ናቸው።

√ወጣቶቹ የሰላምን አርማ ይዘው በየሄዱበት የሚሰብኩት ስለፍቅር እና መተባበር እና መተጋገዝ ብቻ ነው። በሚዘጋጁት መድረኮችም የጥላቻ መዘዞችን ማስገንዘብ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀማቸውን እንዲያሻሽሉ ማስገንዘብ ነው።

√ውይይቶች በጠቅላላ የሚደረጉት #በወጣት የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች #መካከል ብቻ ነው። ሌላው ተናጋሪዎች ተማሪዎች እና የዩኒቨርሲቲው አካላት ብቻ ናቸው።

በቀጣይ ምዕራፍ 2፦ ከዩኒቨርሲቲ #አመራሮች እና #ሰራተኞች ጋር ተመሳሳይ መድረክ ይኖረናል።

ኢትዮጵያን በፍቅር እንገንባ!!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የአንድ እናት ልጆች ነን መስመር አይለየን...
የአንድ ቤት ልጆች ነን መስመር አይለየን...

#መቐለ_ዩኒቨርሲቲ የሰላም አምባሳደር!
#ፍቅር #ተስፋ #አንድነት #መቐለ_ዩኒቨርሲቲ
#ለጥያቄው_ምላሽ፦ TIKVAH-ETH የተመሰረተው እንደ ኢትዮጵያ አቆጣጠር በሃምሌ 19/2009 ዓ/ም ነው። TIKVAH በተመሰረተበት ወቅት የቤተሰቡ አባላት 20 አይደርሱም ነበር። የነበሩትም #ንቁ ተሳታፊ አልነበሩም። ዛሬ በሁሉም የኢትዮጵያ ክፍል የሚገኘው የቤተሰባችን አባል ከ320 ሺ በላይ ነው። በተመሰረተበት ወቅት ቀለል ያሉ የመዝናኛ ነክ ጉዳዮችንና ፎቶዎችን ያቀርብ ነበር። ለጥቂት ጊዜ ትውውቅ ከተደረገ በኃላ በወቅቱ በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ በነበረው ችግር ሳቢያ የሁሉም ኢትዮጵያዊ ተማሪ ድምፅ ሆኖ አገልግሏል።

TIKVAH ማለት #ተስፋ ማለት ነው!

√እኛ ማንም ሰው በሰውነቱ ብቻ የሚከበርበት፤ ሰውነቱ ሲከበር ብሄሩ፣ ቋንቋው፣ ባህሉ፣ አመለካከቱ፣ እምነቱ የሚከበርበት ሀገር እንደምትኖረን ተስፋ እናደርጋለን።

√እኛ አስተማማኝ ደህንንነት እና ሰላም ያለባት ሀገር እንደምትኖረን ተስፋ እናደርጋለን።

√እኛ ማንም ሰው በአመለካከቱ የማይገፋበት ለሁሉም ዜጎች እኩል የሆነች ሀገር እንደምትኖረን ተስፋ እናደርጋለን!

√እኛ አይደለም ለኢትዮጵያዊ በምድር ላይ ላለሰው ሁሉ የምትሆን ሀገር እንደምትኖረን ተስፋ እናደርጋለን።

√እኛ ዜጎቿ የማይበደሉባት ሀገር እንደምትኖረን ተስፋ እናደርጋለን።

#ተስፋችን_ደግሞ_በፍጡር_ሳይሆን_በፈጣሪ_ብቻ_ነው!

ይህ አቋማችን የዛሬ ሳይሆን የነበረ፤ ያለና ወደፊትም የሚኖር ነው!! #ETHIOPIA

🏷ይሄ ቤተሰብ "የኢትዮጵያ ተስፋ" ነው ብለን እናምናለን!! በመነጋገር የሚያምን ከጥላቻ የራቀ፤ ስድብ የሚፀየፍ አንድ ጠንካራ የሆነችን ሀገር ለመገንባት ዘውትር የሚተጋ የሰለጠኑ ኢትዮጵያዊያን ስብስብ ነው።

ፈጣሪ ሀገራችንን ይጠብቅልን!

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የዕለቱ መልዕክት፦

ከጭፍን ጥላቻ መላቀቅ ይቻላል!

አብዛኞቹ ሰዎች ጭፍን ጥላቻን በመሠረተ ሐሳብ ደረጃ የሚያወግዙ ቢሆኑም ከጭፍን ጥላቻ መዳፍ የሚላቀቁ ግን ጥቂቶች ናቸው። እንዲያውም ሥር የሰደደ ጭፍን ጥላቻ ያላቸው ብዙ ሰዎች ጥላቻ እንደሌላቸው ሊናገሩ ይችላሉ። ሌሎች ደግሞ ሰዎች ጭፍን ጥላቻቸውን ይፋ እስካላወጡ ድረስ ምንም ጉዳት የለውም ይላሉ።

ይሁን እንጂ ጭፍን ጥላቻ ሰዎችን የሚጎዳና የሚከፋፍል መጥፎ ነገር ነው። ጭፍን ጥላቻ የድንቁርና ልጅ ነው ቢባል የልጅ ልጁ ደግሞ ጠላትነት ነው። ቻርልስ ካለብ ኮልተን የተባሉት ደራሲ (1780-1832) “አንዳንድ ሰዎችን ስለማናውቃቸው #እንጠላቸዋለን። ስለምንጠላቸውም #ልናውቃቸው አንችልም” ብለዋል። ጭፍን ጥላቻን ሰዎች መማር እንደሚችሉ ሁሉ ማስወገድም ይችላሉ።

Via #JW

#ፍቅር #ሰላም #አንድነት #ተስፋ #ኢትዮጵያ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
342,200 የቤተሰብ አባላት #HOPE #ተስፋ #TIKVAH #ETHIOPIA

Voice of Hope🇪🇹TIKVAH-ETHIOPIA

@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ማህበረሰብ ተስፋ ሲቆርጥ ምን ይፈጠራል?

"...እንደ ህዝብ ደግሞ ህዝብ ተስፋ ከቆረጠ እሴቶቹን ይጥላል፤ ነገ ለውጥ የለም፤ ምንም ተስፋ የለንም ብሎ ካሰበ፤ ይጋደላል፣ ይሰዳደባል፣ ተስፋ የቆረጠ ሰራዊት ልታይ ትችላለህ ፌስቡክም ላይ ሚዲያም ላይ፤ ህዝብ ተስፋ ከቆረጠ መከባበሩ ይጠፋል፤ ትህትናው ይጠፋል፤ ፍቅሩ ይጠፋል፤ ሚታየው ነገር የለም። ሰውን ስነ ስርዓት ከሚያሲዙትና እሴቶቹን ጠብቆ እንዲኖር ከሚያደርጉት ነገሮች አንዱ ነገ መልካም ይሆናል የሚል #ተስፋ ነው" ዶክተር #ወዳጄነህ_ማሀረነ

#HOPE #TIKVAH/#ተስፋ/

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ETHIOPIA💪ክብር ይገባችኃል!

ስንተባባር በአንድነት ስንቆም ምንም ነገር አያቅተንም!! 6710 የልብ ህሙማን ህፃናትን አለንላችሁ እንበላቸው!!

#TIKVAH_ETHIOPIA_FAMILY

Screenshot ወደዚህ ግሩፕ👇

https://t.me/joinchat/FCD9AhWFZJX_rX95-4rWNQ

#አንድነት #ተስፋ #መተሳሰብ #ፍቅር #ቲክቫህ
❤️ከ3000 በላይ አባል❤️

6710 ላይ የህፃናት የልብ ህክምናን ለማገዝ በተከፈተው ግሩፕ ላይ እስካሁን ከ3 ሺህ የሚበልጡ የቤተሰባችን አባላት ተቀላቅለውናል!! በሺዎች የሚቆጠር ገንዘበ እንደ አቅማችን አስተዋፆ እያደረግን እንገኛለን!! ሀገር ወዳድነት መገለጫው ይህ ነው!!

Screenshot ወደዚህ ግሩፕ👇

https://t.me/joinchat/FCD9AhWFZJX_rX95-4rWNQ

እኔ ካለኝ ላይ አካፍያለሁ?? እናተስ??

ለአንድ መልዕክት የሚቆርጠው 1 ብር ብቻ ነው!!


በትንሹ 3 መልዕክት ይላኩ!

#አንድነት #ተስፋ #መተሳሰብ #ፍቅር #ቲክቫህ
TIKVAH-ETH 2011 ዓ/ም- የፎቶ ማጠቃለያ⬆️

•ሀረማያ
•ወሎ
•ደብረብርሃን
•ወልዲያ
•መቐለ
•ዋቸሞ
•መቐለ
•ወላይታሶዶ
•ሀዋሳ
•አርባምንጭ
•ጅማ

#ተስፋ #ፍቅር #ሰላም #TIKVAH

#STOP_HATE_SPEECH

በጎዞው ላይ ያልተሳተፋችሁ ደግሞ በያላችሁበት ሆናችሁ ዓላማውን በሀሳብ ስትደግፉ ነበር። ተመስግናችኃል!!

🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼

🔖በበጎ አድራጎቱ ስራም በአቅማችሁ ለቻላችሁት ሁሉ ፤ድጋፍ ለሚፈልጉ ወገኖችም ድጋፍ ያደረጋችሁበት አመት ነበር።

🔖የየአካባቢያችሁን እውነተኛ ክስተቶችም በማካፈል ፍፁም የተሳካ አመት ነበር። በተለይ ሀሰተኛ መረጃዎችን በመከላከል ትልቅ ስራ ሰርታችኃል።

🔖መልካምነት ጎልቶ እንዲታይ በየአካባቢው መልካም ስራዎችን ሰርታችሁ ያለፋችሁበት ዓመት ነበር።

🔖የቤተሰቡ አባላት ለሀገሪቱ ችግር ከመሆን ይልቅ የመፍትሄ አካል ለመሆን በሁሉም አቅጣጫ የሰራችሁበት ነበር።
.
.
.
ብዙ ብዙ ሌሎች ስራዎች!

በአጠቃላይ ጥሩ የሚባል አመት ነበር። ሁላችሁም የዚህ ቤተሰብ አባላት እንኳን አደረሳችሁ። አዲሱ አመት ደግሞ ትልልቅ ስራዎችን የምንሰራበት ነው። ተዘጋጁ!

@tsegabwolde @tikvahethiopia
በደንብ ተመልከቱ⬆️

እኛ እንዲህ ነን፤ ተያይዞ፣ ተቻችሎ፣ ተዋዶ መኖር ካልቻልን ተያይዞ መጥፋት ነው የሚሆነው፤ አንዱን ጠጠር ብታነሱት ሁሉም ይፈርሳል፤ ለሁሉም መኖር የአንዱ መኖር ወሳኝ ነው።

#እንዋደድ #እንከባበር #እንፋቀር #ሰላም #ፍቅር #ተስፋ

ሀሳቡ ከማህበራዊ ሚዲያ ተወሰደ!


🚪መስከረም 2 ቀን 2012 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
እንኳን ደስ አላችሁ!

#TIKVAH_ETH በሁለት ዓመት ከአንድ ወር ከሃያ አንድ ቀን ከመላው ሀገሪቱ እንዲሁም ከተለያዩ የውጭ ሀገራት ከ400,000 በላይ የቤተሰብ አባላት ማፍራት ችሏል።
_______________________________________

ሰው በሰውነቱ ብቻ የሚከበርባት ሀገር እንድትኖረን እንመኛለን፤ መመኘት ብቻ አይደለም ለዚህ እውን መሆን ያለእረፍት እንሰራለን፡፡

TIKVAH-ETHIOPIA❤️ተስፋ ኢትዮጵያ

አንዱ የአንዱን ባህል፣ ቋንቋና ሃይማኖት ማክበር ከቻለ፤ ከጥላቻ እና ከቂም በቀል ነጻ የሆነ አስተሳሰብ መፍጠር ከተቻለ፤ ልዩነቶችን በውይይት መፍታት ከተቻለ፤ ለመልካም ነገር ለመተባበር ደግሞ ልዩነታችን መሰናክል ካልሆነ #ተስፋ_አለን የኛ ኢትዮጲያ ለሁላችንም የምትመች ሀገር ትሆናለች፡፡ TIKVAH-ETH ውስጥ የተሰባሰብነው እርስ በእርሳችን በመከባበር እና በመዋደድ የተሻለች ሀገር ገንብተን ለመጭው ትውልድ ለማስረከብ ነው።

ሁላችሁንም እናከብራችኃለን!

ረጅም ርቀት አብረን እንጓዛለን!
ሰላም፤ ፍቅር፤ ተስፋ!
TIKVAH-ETH
እንኳን ደስ አለን፤ እንኳን ደስ አላችሁ!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ለኮሮና ቫይረስ በፍጥነት ክትባት ይገኝለት ይሆን ?

በአሜሪካ የጤና ተቋም CDC በኃላፊነት የሚሰሩት ዶክተር ኤርሚያስ በላይ #ETHIOTUBE ላይ ቀርበው ይህን ተናግረዋል ፦

ክትባትን ለመፍጠር ብዙ ሰዎች በተለያዩ ሀገሮች ብዙ ስራ እየሰሩ ነው ያለው። ይሄ ክትባት ሊገኝ እንደሚችል ብዙ ተስፋ አለኝ። በቫይረስ ጥቃት ለሚመጡ በሽታዎች ክትባት ማግኘት በአብዛኛው ጊዜ ብዙ አይከብድም። የሚከብድባቸው ሆኔታዎችም ግን አሉ።

የኢንፉሌንዛ ቫይረስን ብንመለከት በተመሳሳይ ሁኔታ ነው የሚተላለፈው፤ ለኢንፉሌንዛ ቫይረስ ክትባት በየአመቱ ይሰራል። ለዚህኛውም ቫይረስ ክትባት እንደሚገኝለት #ተስፋ አደርጋለሁ። ግን ይሄን ክትባት ለማግኘት ብዙ ጊዜ ይወስዳል። ከ8-12 #ወራት ሊወስድ ይችላል።

ቫይረሱ ቢጠቃ በክትባት ሊሸነፍ የሚችልበትን ቦታ ማግኘት ያስፈልጋል፤ ይሄ በላብራቶሪ ጥናት ከተደረገ በኃላ ለዛ ክትባት ተዘጋጅቶ በእንስሶች ውስጥ ሙከራ ማድረግ ይፈልጋል፣ ከዛም በሰዎች ላይ ጥናት ማድረግ ያስፈልጋል፣ ከዛም ቁጥሩ በዛ ያለ ህዝብ ላይ ይሄ ክትባት ከበሽታው መከላከል መቻሉ ማረጋገጥ ያስፈልጋል። ይሄ ሁሉ ሂደት ረጅም ጊዜ ይወስዳል።

አንዴ በጥናት ከተረጋገጠ በኃላ እንኳን ለብዙ ሰዎች እንዲሆን አድርጎ በስፋት ማምረት እንኳን ብዙ ጊዜ ይወስዳል። ቢያንስ ቢያንስ ሁለትና ሶስት ወራት ሊወስድ ይችላል። ስለዚህ ክትባት ማግኘቱን ቀላል ነገር ተደርጎ ቢታሰብም ለግለሰቦች እንዲባዛ አድርጎ ማቅረቡ በጣም ጊዜ ይወስዳል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#REPOST

ለኮሮና ቫይረስ በፍጥነት ክትባት ይገኝለት ይሆን ?

በአሜሪካ የጤና ተቋም CDC በኃላፊነት የሚሰሩት ዶክተር ኤርሚያስ በላይ #ETHIOTUBE ላይ ቀርበው ይህን ተናግረዋል ፦

ክትባትን ለመፍጠር ብዙ ሰዎች በተለያዩ ሀገሮች ብዙ ስራ እየሰሩ ነው ያለው። ይሄ ክትባት ሊገኝ እንደሚችል ብዙ ተስፋ አለኝ። በቫይረስ ጥቃት ለሚመጡ በሽታዎች ክትባት ማግኘት በአብዛኛው ጊዜ ብዙ አይከብድም። የሚከብድባቸው ሆኔታዎችም ግን አሉ።

የኢንፉሌንዛ ቫይረስን ብንመለከት በተመሳሳይ ሁኔታ ነው የሚተላለፈው፤ ለኢንፉሌንዛ ቫይረስ ክትባት በየአመቱ ይሰራል። ለዚህኛውም ቫይረስ ክትባት እንደሚገኝለት #ተስፋ አደርጋለሁ። ግን ይሄን ክትባት ለማግኘት ብዙ ጊዜ ይወስዳል። ከ8-12 #ወራት ሊወስድ ይችላል።

ቫይረሱ ቢጠቃ በክትባት ሊሸነፍ የሚችልበትን ቦታ ማግኘት ያስፈልጋል፤ ይሄ በላብራቶሪ ጥናት ከተደረገ በኃላ ለዛ ክትባት ተዘጋጅቶ በእንስሶች ውስጥ ሙከራ ማድረግ ይፈልጋል፣ ከዛም በሰዎች ላይ ጥናት ማድረግ ያስፈልጋል፣ ከዛም ቁጥሩ በዛ ያለ ህዝብ ላይ ይሄ ክትባት ከበሽታው መከላከል መቻሉ ማረጋገጥ ያስፈልጋል። ይሄ ሁሉ ሂደት ረጅም ጊዜ ይወስዳል።

አንዴ በጥናት ከተረጋገጠ በኃላ እንኳን ለብዙ ሰዎች እንዲሆን አድርጎ በስፋት ማምረት እንኳን ብዙ ጊዜ ይወስዳል። ቢያንስ ቢያንስ ሁለትና ሶስት ወራት ሊወስድ ይችላል። ስለዚህ ክትባት ማግኘቱን ቀላል ነገር ተደርጎ ቢታሰብም ለግለሰቦች እንዲባዛ አድርጎ ማቅረቡ በጣም ጊዜ ይወስዳል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
እንኳን አደረሳችሁ!

TIKVAH-ETHIOPIA እንኳን ለሲዳማ የፊቼ ጨምበላላ በዓል በሰላም አደረሰን ፤ አደረሳችሁ ለማለት ይወዳል። በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የደስታ፣ የመተሳሰብ ይሆን ዘንድ እንመኛለን!

ይህን ዓለምን ያስጨነቀ ወረርሽኝን አሸንፈን የዓለም ቅርስ የሆነውን 'ፊቼ ጨምባላላ በዓል' በአደባባይ ተሰባስበን የምናከብርበት ጊዜ ሩቅ እንደማይሆን #ተስፋ እናደርጋለን!!

በድጋሚ እንኳን አደረሳችሁ!

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#ETHIOPIA

የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች በሀገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ አመሠራረት እና ሂደት ፣ ከኮሚሽነሮቹ እና ከኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከፍተኛ አመራሮች ጋር እየተወያዩ ይገኛሉ።

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ አቶ ታገሠ ጫፎ ከፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ም/ቤት በቀረበ ጥያቄ መሠረት የውይይት መድረኩ እንደተዘጋጀ ጠቁመዋል።

የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ ዶክተር ራሄል ባፋ ፤ ሀገራዊ ምክክሩ #ተስፋ_የተጣለበት እና #ለሀገራችን_ብቸኛ_አማራጭ በመሆኑ ቀጣይ በሚኖረው ሂደት የፖለቲካ ፓርቲዎች ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን መግለፃቸውን የህ/ተ/ምክር ቤት አሳውቋል።

የኮሚሽነሮቹን የአሰያየም ሂደት በተመለከተ በምክር ቤቱ አፈ ጉባኤ እና በፍትህ ሚ/ሩ ጌዲዮን ጢሞቲዮስ (ዶ/ር ) ማብራሪያ መሰጠቱ ተገልጿል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የ2005 የ20/80 ባለ3 መኝታ ተመዝቢዎች ፦ " ... በ14ኛው ዙር የዕጣ አወጣጥ የከተማ አስተዳደሩ ቤቶች በቴክኖሎጂ ሆነ በማኑዋል ዕጣ የማውጣት ሂደቶች በሚፈጠሩ ችግሮች ሊወጣለት ከሚገባው ባለእድለኛ ወጪ ለሌላ ለማይመለከተው አካል እንዳይተላለፉ የሄደበትን ርቀት እናደንቃለን፡፡ ነገር ግን ይህ ቁርጠኝነት በባለ3 መኝታ 2005 ዓ.ም የ20/80 ተመዝቢዎችን ታሳቢ ባደረገ መልኩ እንዲገለጽ እንፈልጋለን፡፡…
#መልስ_ያላገኘው_ጥያቄ

የ2005 የ20/80 የባለ 3 መኝታ የጋራ መኖሪያ ቤት ቆጣቢዎች ባለፈው ሙሉ በሙሉ የተሰረዘው ዕጣ ሳይወጣ የእነሱ ጉዳይ ላይ የአ/አ ከተማ አስተዳደር ግልፅ የሆነ ማብራሪያ እንዲሰጣቸው በድጋሚ አሳሰቡ።

የጋራ መኖሪያ ቤት ይደርሰናል ብለው እየቆጠቡ ያሉ ወገኖች አለን ስላሏቸው ጥያቄዎች ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ ማሳወቃችን አይዘነጋም።

" ዛሬም ድረስ ግልፅ የሆነ ማብራሪያ የሚሰጠን አጥተናል " ያሉት ነዋሪዎቹ " ከልጆቻችን ምግብ ቀንሰን፣ በቤት ክራይ እየተሰቃየንና እየተማረርን ላለፉት 9 ዓመታት ቆጥበን ስለምን በዕጣው ልንካተት እንዳልቻልን በግልፅ ሊነገረን ይገባል " ብለዋል።

የቀጣዩ የጋራ መኖሪያ ቤት ዕጣ ከመውጣቱ በፊትም መፍትሄ እንዲፈለግላቸው ጠይቀዋል።

የ2005 ዓ/ም 20/80 ለባለ 3 መኝታ ቆጣቢዎቹ ፤ " #ቤቶቹ_የትገቡ ? ፣ #ተስፋ_አድርገን_ነበር#13ኛው_ዙር_ላይ_97_አልቋል_ብላችሁን_አልነበር?! ፤ #ባለ3_መኝታ_ኦዲት_ይደረግ#ፍትህ_እንሻለን! "በሚሉ እና በሌሎች ሀሽታጎች በተለይም በማህበራዊ ሚዲያ በመሰባሰብ ጥያቄያቸው መልስ እንዲያገኝ ዘመቻ እያካሄዱ መሆኑን ገልፀዋል።

https://t.me/tikvahethiopia/72439?single
https://t.me/tikvahethiopia/72244?single
https://t.me/tikvahethiopia/72384?single
https://t.me/tikvahethiopia/72271

@tikvahethiopia
#ተስፋ

በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ከምንም በላይ ለበርካታ ወራት የእናት አባቶቻቸውን ፤ የእህት ወንድሞቻቸውን ፣ የወዳጆቻቸውን ድምፅ ያልሰሙ እጅግ በርካቶች ስምምነቱ በፍጥነት #ወደተግባር ገብቶ ያናፈቋቸውን ሁሉ ድምፃቸውን ሊሰሙ ጓግተዋል።

ከዚህ ቀደም የባንክ አገልግሎት በመኖሩ እያገዟቸው የነበሩ መላ ቤተሰቦቻቸውን ዳግም አግኝተዋቸው የየትኛውም የእርዳታ ድርጅት እና ተቋም /አካል ደጅ እንዳይጠኑ ለማድረግና ያለባቸውን ችግር ለመቅረፍ እየተጠባበቁ ነው።

ቤተሰቦቻቸው " በህይወት ይኑሩ አይኑሩ " እርግጠኛ ያልሆኑ ሚሊዮኖች የሰላም ስምምነቱ እጅግ በፍጥነት ተተግብሮ ፣ መሰረታዊ አገልግሎት ጀምሮ ለማየት ተስፋን ሰንቀዋል።

ከማንም ከምንም በላይ የጦርነቱ ቀጥተኛ ተጎጂዎች ህመማቸው ፣ ናፍቆታቸው ፣ ሀዘናቸው የከፋ ነውና ይህ የሰላም ስምምነት ተግባራዊ እንዲሆን እና እፎይ እንዲሉ በተለይ #በማህበራዊ_ሚዲያ አፍራሽ ስራ የሚሰሩ ፣ የበለጠ ጥላቻን የሚዘሩ ፤ ሰላም በመሆኑ ጥቅማቸው የሚጎድልባቸው አካላት ከድርጊታቸው ቢታቀቡ መልካም ነው።

የሰላም ስምምነት መፈረሙ " የመጀመሪያው እርምጃ " እንጂ የመጨረሻ አይደለምና በተለይ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ለስኬቱ የራሳቸውን በጎ ድርሻ መጫወት ይጠበቅባቸዋል። በሰላም ሁሉም አሸናፊ ነውና ከብሽሽቅ ፣ ከጥላቻ ከአጉል የአሸናፊነት ስሜት መራቅ ይገባል።

#ሰላም

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Peace #GoE #OLA

በኢ.ፌ.ዴ.ሪ. መንግሥት እና በኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት (OLA መካከል ከዚህ ቀደም ታንዛኒያ ላይ ሁለት ጊዜ የሰላም ድርድር ተደርጎ ያለ ስምምነት / ወጤት መበተኑ ይታወሳል።

አሁንም ሌላ #ሶስተኛ_ዙር የሰላም ውይይት/ድርድር ሊኖር የሚችልበት ዕድል መኖሩን የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ተናግረዋል።

ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ምን አሉ ?

- የመጀመሪያው ንግግር በጣም ጥሩ ርቀት ሄዶ ነበር ፤ በዚህም ብዙ መካሰስ ቀርቶ ለሚቀጥለው ዙር ለመነጋገር እናመቻች በሚል ነው የተጠናቀቀው።

- ሁለተኛው የሰላም ድርድር መጀመሪያ ላይ ከሁለቱም ወገን አግባቢዎች ሄደው ከሳምንት በላይ ፈጅተዋል። አዝማሚያው ጥሩ ነበር።  መጨረሻ የማያግባቡ ነጥቦች መጡ። በዚህም ትንሽ የተሻለ ኃይል ያለው ሰው ይምጣ ተብሎ ከመንግሥትም ከነሱም ሄዷል። በዚህም ጊዜ ጥሩ ሂደት ነበር።

- በህገ-መንግስት ጥላ ስር "የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ፣ አንድነት መቀበል ላይ ፤ የኢትዮጵያን ሀገረ መንግስት በምርጫ የመጣ Legitimacy ያለው መሆኑ ላይ መግባባት ተደርሶ ነበር። ወደ ዝርዝር ሲመጣ ግን እነዚህን መግባባቶች የሚሸረሽር ነገር ነው የመጣው።

- ስምምነቱ በመጨረሻ ለህዝብ ይፋ የሚሆን ደረጃ / ወደ ሰነድ ደረጃ ሲደርስ ያልተጠበቁ ጥያቄዎች ተነስትዋል።

ምንድናቸው ?

* አንደኛው --- ' #ስልጣን_አካፍሉኝ ' ነው እያንዳንዱን ጠብመንጃ የያዘ፣ ጫካ የገባ ሁሉ ስልጣን ለማግኘት ከሆነ የሚደራደረው ይሄ ለሀገር ሰላም አይሰጥም።

ጫካ እየገቡ ፣ ግጭት የፈጠሩ ፣ ህዝቡን እያበሳሰቡ ከዛ እንነጋገር እያሉ " እሺ " ሲባል ስልጣን አካፍሉኝ የሚባል ነገር ካለ መቼም ስርዓት አይመጣም። ሀገር ሰላም አይሆንም።

ምሳሌ ብንወድስ ፦ ከአማራ፣  ከቤንሻንጉል ጉምዝም ከሌላውም የታጣቁ ኃይሎች ስልጣን አካፍሉኝ ካሉ ስንት የታጠቀ ኃይል ስልጣን ሲካፈል ይኖራል ? ይሄ ኢትዮጵያን ይጎዳል።

እንዲህ አይነት ጥያቄ ነው ይዘው የቀረቡት (OLAን ማለታቸው ነው)።

መንግሥት ስልጣን ላካልፍ ቢልም ፍፁም አይችልም ፤ መብትም የለውም። #ማሳተፍ ግን ይችላል። ሸኔን ጭምር ማሳተፍ ይችላል።

ዋናው መሰረታዊ ልዩነት ይሄ ነው። ስልጣን አካፍሉኝ ስሉም እራሳቸው ፕሮፖዛል አስቀምጠው ፤ እዚህ ላይ ስልጣን ስጡኝ የሚል ነበር።

* ሁለተኛው --- ወደ ' DDR ' አልገባም ነው።

በሰላም ለመታገል ፣ ፓርቲ አቋቁሞ ለመታገል ፣ ወደ ህዝብ ምርጫ ለመቅረብ የገጠር ትጥቅ ትግል ትቶ በሰላም ወደ ህዝብ መመለስ ነው። ለዚህ ደግሞ ትጥቅ መፍታት አለባቸው።

DDR / Disarm, Demobilized , Reintegrate መሆን አለባቸው። ይሄ ዓለም የሚሰራበት ነው። ማንኛውም ግጭት የተፈታውም በዚህ ነው። ይሄን ለመቀበል የመቸገር ነገር ተከስቷል።

ትጥቅ ሳይፈታ ፦
° እንዴት እንደራደራለን?
° እንዴት Demobilize ይሆናሉ?
° እንዴት ወደ ህብረተሰቡ ይቀላቀላሉ ?

መንግስት በግልፅ DDR ፕሮግራም ውስጥ መግባት አለብን ብሏል። በአንድ ሀገር በፍፁም ሁለት የታጠቀ ኃይል ሊኖር አይችልም። ትጥቅ የመያዝ መብት ያለው መንግስት ብቻ ነው።

ይሄንን #መቀበል_ነበረባቸው። በዓለም ላይ ይሄን ሳይቀበሉ ስምምነት የለም። ድርድር ብሎ ነገር የለም።

ንግግሩ ጥሩ ሄዱ ከላይ ባሉት ሁለት ምክንያት ነው መጨረሻ ላይ የቆመው።

- ሶስተኛ ዕድል ይኖራል ? እኔ የሚኖር ይመስለኛል።

- ሁለቱን #ያልተስማማንባቸው_ነጥቦችን በተሳሳተ መንገድ እንዲወስዱ በማድረግ ሌሎች ኃይሎች እጅ አላቸው። OLA ላይ ታዝሎ የሚሄዱ ኃይሎች አሉ። ከሀገር ውስጥም ከሀገ ውጭም አሉ። ባዕዳንም ዜጎችም እነዚህ ኃይሎች OLA በሰከነ መንገድ አይቶ ስምምነቱን እንዳይቀበል አድርገውታል። OLA ሌላ መስማት አልነበረባቸውም፤ ችግር ውስጥ ያሉት እራሳቸው ስለሆኑ እራሳቸው መወሰን ነበረባቸው።

(ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ እነዚ ኃይሎች እነማን እንደሆኑ በግልፅ አልተናገሩም)

- ሌላው ኃይል ጣልቃ ስለገባ በዓለም experience ታይቶ የማይታወቅ ቅድመ ሁኔታ በማቅረብ መንግሥትን አስቸግረዋል (OLA ማለታቸው ነው)።

- ሶስተኛ ዕድል ሊኖር ይችላል። ሰከን ብለው አስበው አደራዳሪዎች ጭምር የሚያምኑበት የመጨረሻው ወረቀት / ዶክመንት / የቀበል ደረጃ ከደረሱ ሶስተኛ ውይይት ሊኖር ይችላል።

- ምናልባት ሶስተኛ ውይይት እንደሁለተኛው ውይይት ሰፊ ላይሆን ይችላል እስካሁን የተደከመበት ሰነድን መቀበል ላይ ከተደረሰ ሶስተኛው ውይይት ሊኖር ይችላል፤ ሶስተኛው ውይይት የመጨረሻም ይሆናልም ብዬ ገምታለሁ ወደሰላም ለመምጣት ወይም እስከመጨረሻው ሁለተኛ ላለመነጋገር የመጨረሻ ሊሆን ይችላል።

🕊 የኢጋድ ዋና ፀሀፊ የሆኑት ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ ከሳምንታት በፊት ያለ ስምምነት የተጠናቀቀውን 2ኛው ዙር የኢትዮጵያ መንግሥት እና የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት የሰላም ድርድርን በተመለከተ ሰጥተው በነበረው መግለጫ ሌላ አዲስ ዙር ውይይት ይጀመራል ብለው #ተስፋ እንደሚያደርጉ መግለፃቸው አይዘነጋም።

@tikvahethiopia
#Ethiopia

ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) ብድር ለማግኘት ድርድር ላይ ናት።

እንደ ሮይተርስ ዘገባ ከ2020 ጀምሮ ምንም ፈንድ ያላገኘችው ኢትዮጵያ ብድር እንዲለቀቅላት ከIMF ተከታታይ ድርድሮች እያካሄደች ነው።

ከIMF 3.5 ቢሊዮን ዶላር ብድር እንደጠየቀች ተነግሯል።

ድርጅቱ ብደሩን ለመስጠት ኢትዮጵያ ብር ከዶላር አንጻር ያለው የመግዛት አቅም #እንዲዳከም ማድረግ እንዳለባት እንደጠየቀ ተጠቁሟል።

ግን ይህ እንደቅድመ ሁኔታ ይቀመጥ አይቀመጥ ድርጅቱ ማረጋገጫ አልሰጠም። ነገር ግን ተለዋዋጭ የሆነ የገበያ ሁኔታ የሚወስን የውጭ ምንዛሬ ተመን መኖር  እንዳለበት እንደሚያምን ሮይተርስ አስነብቧል።

ምንም እንኳን እየተካሄዱ ባሉ ተከታታይ ድርድሮች በኢትዮጵያ እና IMF መካከል ልዩነቶች ቢኖሩም ስምምነት ላይ የመድረስ #ተስፋ_እንዳለ የIMF የኢትዮጵያ ልዑክ አልቫሮ ፒርስ ተናግረዋል።

ፒስርስ ፥ " አሁንም ልዩነቶች ቢኖሩም ድርድር ግን ቀጥሏል። አስቸጋሪ ነግሮች ቢኖሩም ስምምነት ላይ የመድረሱ ተስፋ አለ " ብለዋል።

የኢትዮጵያን #የኢኮኖሚ_ሪፎርም_መደገፍ ላይ በአብዛኛው ስምምነት እንዳለ ነው የተሰማው።

ከዶላር አንጻር የብርን የመግዛት አቅም ማዳከም ከፍተኛ በሆነ የዋጋ ንረት እየተፈተነች ላለችው ኢትዮጵያ ይበልጥ ፈተና ሊሆንባት ይችላል።

ግን ደግሞ IMF የግዴታ ያ ካልተደረገ ብድር አለቀም ካለ ኢትዮጵያ በከፍተኛ ውጭ ምንዛሬ እጥረት ውስጥ የምትገኝ በመሆኑ ሌላ አማራጭ ላይኖራት ይችላል የሚሉ አሉ።

ከቀናት በፊት የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ ዶ/ር ኢዮብ ተካልኝ እና የብሄራዊ ባንክ ገዢው ማሞ ምህረቱ በተገኙበት ከIMF ኃላፊ ክሪስታሊያ ጆርጂያ ጋር ተገናኝተው መክረው ነበር።

ምክክሩ IMF በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን ሪፎርም በሚደግፍበት መንገድ ላይ ያተኮረ እንደሆነ ተጠቅሷል። ዝርዝር ጉዳዩ ግን አይታወቅም።

መረጃው የሮይተርስ ነው።

@tikvahethiopia