TIKVAH-ETHIOPIA
1.41M subscribers
55K photos
1.37K videos
199 files
3.67K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ምርጫ2013

የቁሳቁስ ስርጭትን በተመለከተ በተወሰኑ የምርጫ ክልሎች ላይ ሰማያዊ ሳጥኖች ተከፍተው መገኘታቸውን ምርጫ ቦርድ አሳወቀ።

ሳጥኖቹን ከፍተው የተገኙበት ምርጫ ክልሎች ላይ አንዳንዶቹ ወደወንጀል ምርመራ ሲላኩ አንዳንዶቹ #ምርጫ_እንዳይካሄድ ተወስኖባቸዋል።

- ደንቢያ የምርጫ ክልል ሰማያዊ ሳጥኖቹ ተከፍተው ፤ ውስጣቸው የድምፅ መስጫ ወረቀቶችን የሚያሳየው የቡክሌት ተከፍቶ ውስጡ ያለውን ነገር አይተው ተገኝቷል፤ በዚህ ምክንያት 3 አስፈፃሚዎች ላይ ምርመራ እንዲደረግ ለፌዴራል ፖሊስ ደብዳቤ ተፅፏል።

ደምቢያ ምርጫ ክልል የድምፅ መስጫ ቁሳቁሶችን መነካካት ፣ መክፈት በጥብቅ የተከለከለ የወንጀል ተግባር በመሆኑን አስፈፃሚዎች ምርመራ እንዲደረግባቸው ተልኳል።

በደምቢያ ምርጫ ክልል ምርጫው #አይካሄድም

- ተውለደሬ 1 እና 2 ሰማያዊ ሳጥን ተከፍቶ ውስጡ ያሉእጩዎች እነማን እንደሆኑ ፣ የድምፅ መስጫ ወረቀቱ ላይ ያሉትን እጩዎች የማየት (ፓርቲዎች ቅሬታ አለን ስላሉ ነው እዩ ተብለን ነው) በሚል ተክፍቶ ታይቷል።

በዚህ ምክንያት ተውለደሬ 1 እና 2 ነገ ድምፅ አይሰጥም፤ ታግዷል።

- ግንደበረት (ኦሮሚያ) ነገ ድምፅ #አይሰጥም ፦ ድምፅ የማይሰጥበት ምክንያት የድምፅ መስጫ ወረቀት እና ቁሳቁስ ስለተከፈተ ሳይሆን የአስፈፃሚዎች እጥረት ነበር። ከዚህ ውጭ ግን ወረዳው አስፈፃሚዎችን አሰልጥኖ ለማስፈፀም ለማሰማራት ሲል በመገኘቱ ገንደበረት ላይ ድምፅ አይሰጥም

- ነገሌ ምርጫ ክልል (ጉጂ-ኦሮሚያ) ፦ በምርጫ ክልሉ የሚወዳደር የግል ተወዳዳሪ በምርጫ መስጫ ወረቀቱ ላይ ዝርዝሩ ባለመካተቱ ባቀረበው ቅሬታ መሰረት ቦርዱ ምርጫውን ወደ ጳጉሜ 1 አዛውሮታል።

#TikvahEthiopia #SolianaShimeles

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Grade12NationalExam

ከዚህ ቀደም በ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ላይ ሲሰጡ ከነበሩ የትምህርት አይነቶች መካከል ሥነ ምግባርና የሥነ ዜጋ ትምህርት (Civics and Ethical Education) በዘንድሮው ዓመት 2016 ዓ/ም #አይሰጥም

የሥነምግባር እና ሥነ ዜጋ ትምህርት (Civics and Ethical Education) ፈተና ያልተካተተው በሁለቱም የተፈጥሮ ሳይንስ እንዲሁም የማህበራዊ ሳይንስ የትምህርት ዘርፎች ነው።

ይህ ፈተና ለምን በብሄራዊ ፈተናው ላይ እንዳልተካከተተ / እንዳይካተት ውሳኔ እንደተለለፈ ትምህርት ሚኒስቴር የሰጠው ዝርዝር ማብራሪያ የለም።

በሌላ በኩል ፤ ባለፉት ዓመታት ለማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ሳይሰጥ የቆየው #የኢኮኖሚክስ ትምህርት በዚህ ዓመት 2016 ፈተና ላይ ተካቷል።

በዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ፈተና የተፈጥሮ ሳይንስ እንዲሁም የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች እኩል ስድስት ትምህርቶችን ይወስዳሉ።

የተፈጥሮ ሳይንስ ፤ እንግሊዝኛ፣ ሒሳብ ፣ ፊዚክስ ፣ ኬሚስትሪ፣ ባዮሎጂ፣ ሶኮላስቲክ አፕቲቲውድ ቴስት ፈተና ሲወስዱ የማህበራዊ ሳይንስ ደግሞ እንግሊዝኛ፣ ሒሳብ፣ ታሪክ ፣ ጂኦግራፊ ፣ ኢኮኖሚክስ እና ስኮላስቲክ አፕቲቲውድ ፈተና የሚወስዱ ይሆናል።

በዚሁ ዝርዝር መሰረት ከሁለቱም ዘርፎች የሥነ ዜጋና ሥነምግባር (Civics and Ethical Education) ትምህርት የወጣ ሲሆን የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ፈተና ላይ ባለፉት ዓመታት ሳይሰጥ የቀረው ኢኮኖሚክስ ተካቷል።

ፈተናው የሚሰጥበት ትክክለኛውና ቁርጥ ያለው ቀን ባይታወቅም እንደ ከዚህ ቀደሞቹ ዓመታት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት (#ዩኒቨርሲቲዎች) በማስገባት እንደሚሰጥ ይጠበቃል።

@tikvahethiopia