TIKVAH-ETHIOPIA
1.44M subscribers
55.9K photos
1.4K videos
202 files
3.77K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ጥንቃቄ

" FIAS 777 " የተባለ ሰዎችን ትርፋማ አደርጋለው በሚል ከበርካቶች ኤጀንት በሚላቸው አካላት በኩል ገንዘብ ሲሰበስብ ከርሞ ዛሬ አድራሻውን ጥፍትፍት አድርጓል።

#ሌሎችም፦ መሰል ስራ የሚሰሩ አሉ፤ መደረግ ስላለበት ጥንቃቄ ከዚህ በፊት ያሰራጨነውን በድጋሚ ለማቅረብ ወደድን ፦

#REPOST

" የተለያዩ ገንዘብ የማግኛ ማትረፊያ መንገዶች " እየተባለ በዲጅታል ሚዲያው በኩል ከቀርብ ጊዜ ወዲህ በርካቶች እጅግ በስፋት እየተከሰቱ ነው።

እነዚህ አካላት ፍቃድ ይኑራቸው አይኑራቸው ፤ የመስሪያ አድራሻቸው ይታወቅ አይታወቅ ፣ የሚመራቸው / የሚያስተባብራቸው ግለሰብ ይኑር አይኑር የሚለውን በግልፅ ለማወቅ አዳጋች ነው።

ውድ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት ከዚህ በፊትም እንዳልናችሁ ገንዘብ ሊያስገኝ የሚችል እንቅስቃሴ ውስጥ ስትገቡ / ኢንቨስት ስታደርጉ እነዚህ ጥያቄዎች እንድትጠይቁ አደራ እንላለን ፦

1. ድርጅቱ / ተቋሙ እውቅና ያለው ፣ ፍቃድ ያለው ነው ? የሚሰራበትን ፍቃድ በይፋ አሳውቋል ?

2. በትክክል የሚታወቅ አድራሻቸው የት ነው ? ቢሯቸው ?

3. ለሚደርስብኝ ማንኛውም አይነት ነገር ማንን ተጠያቂ ማድረግ እችላለው ?

4. የሚሰራው ስራ ምን ያህል ቀጣይነት አለው ? ነገ እንደማይቆም ምን ማስተማመኛ አለ ? ይህንን ማንስተማመኛ ማን ይሰጠኛል ? የሚሉ ጥያቄዎችን መጠየቅ ያስፈልጋል።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በማህበራዊ ሚዲያው ላይ የማጭበርበር እና የማታለል ድርጊቶች እየሰፉ በመሆናቸው ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል።

ብዙሃንን ሊጠቅም ያሚችል ማንኛውም ህጋዊ ስራ በሚስጥር፣ በድብቅ ፈፅሞ ሊሰራ አይችልም እና ውድ ቤተሰቦቻችን ማንኛውም እንቅስቃሴ ስትጀምሩ ከላይ የተዘረዘሩ ጥያቄዎችን በቅድሚያ መልስ እንዳያገኙ አድርጉ።

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#iSonXperiences

ከትላንት ጀምሮ የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የጥሪ ማዕከል ሰራተኞች የሥራ ማቆም አድማ ላይ መሆናቸውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከቤተሰቦቹ የደረሰው መልዕክት ያሳያል።

ሰራተኞቹ የሥራ አድማውን ያደረጉት መስሪያ ቤታችን ቅሬታችንን ሊመልስልን አልቻለም በሚል መሆኑን ገልጸዋል።

ሰራተኞቹ ካቀረቡት ጥያቄዎች ዋነኛው " ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የጥሪ ማዕከል ሰራተኞቹን በራሱ ሥር ያካተን ፤ በኤጀንት ለምን ያሰራናል ? " የሚል ነው።

በተጨማሪ ፦

➢ ለሙያው ከሚገባውና ካለው የሥራ ጫና አንጻር ተገቢ ያልሆነ የደመወዝ አከፋፈል ፤ ደመወዝ አላግባብ ተቆራርጦ መድረስ እና በጊዜው አለመግባት

➢ ለሰራተኛ የሚገባውን የሕይወትና የአካል ጉዳት ኢንሹራንስ አለመግባት፤

➢ ሰራተኛው ለማጁን የሰለጠነበት የምስክር ወረቀት አለመስጠት፤

➢ ድርጅቱ በተለያዩ የቀን እና የለሊት ፈረቃ ለሚሰሩ ሰራተኞች ደህንነቱ የተጠበቀ እና ፍትሃዊ የመጓጓዣ አገልግሎት ጉድለት የሚሉና #ሌሎችም ቅሬታዎች አሏቸው።

ቲክቫህ ከቤተሰቦቹ እንደተረዳው የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የጥሪ ማዕከል ሰራተኞች በቀጥታ የተቀጠሩት በሳፋሪኮም ሳይሆን ISON Xprience በተባለ ድርጅት አማካኝነት ነው።

ከሰራተቹ ጥያቄ ጋር በተያያዘ የ " ISON Xprience " የሥራ አመራሮች ህዳር 1 ቀን ከሰራተኛ ተወካዮች ጋር ስብሰባ አካሂዶ ነበር።

በዚህ ስብሰባ ላይ ክፍያን በተመለከተ ፤ " በኢትዮጵያ ህግ ዝቅተኛ የደመወዝ መጠን ስለሌለ ደመወዝ በድርድር / በድርጅቱ የደመወዝ ስኬል የሚወሰን ነው።" ሲል ገልጿል።

ከቲክቫህ ቤተሰብ አባላት የደረሱን ቅሬታዎች ይዘን ሳፋሪኮም ኢትዮጵያን ለማነጋገር እና ምላሽ ለማግኘት ጥረት አድርገናል።

ሳፋሪኮም ፤ " የጥሪ ማዕከላችንን በሚያስተዳድርልን ድርጅት (ISON Xprience) እና በሰራተኛው መካከል አለመግባባቶች እንዳሉ ተረድተናል። " ያለን ሲሆን " በደርጅቱ ሥራ አስፈጻሚዎችና ሰራተኞች መካከል የተፈጠረው አለመግባባት ተፈትቶ መደበኛ የሥራ እንቅስቃሴዎች እንደሚቀጥሉ ተስፋ እናደርጋለን " ብሏል።

በዚህ ወቅት፤ ለደንበኞቹ የሚሰጣቸው አገልግሎቶች እንደከዚህ ቀደሙ ፤ በተለመደው መልኩ እንደ ቀጠለ ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ አሳውቆናል።

ያንብቡ 👇
https://telegra.ph/ISON-Xprience-11-16