TIKVAH-ETHIOPIA
1.43M subscribers
55.6K photos
1.39K videos
200 files
3.74K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#udate አርበኞች ግንቦት 7⬇️

በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ለውጥ እንዲመጣ የሁሉም ሀሳብ አራማጆች #ለዘለቄታዊ ለውጥ ቁጭ ብሎ መወያየት እንደሚገባ የአርበኞች ግንቦት ሰባት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ ንቅናቄ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ገለፁ።

ሊቀመንበሩ በቦሌ አየር ማረፊያ በሰጡት መግለጫ #የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ለመጠበቅ ከመጣር ይልቅ #ትክክለኛ ምርጫ ማካሄድ የሚችል ስርዓትና #ተቋማት መኖራቸውን ማረጋገጥ ቅድሚያ ሊሰጠው እንደሚገባ ገልፀዋል።

የለውጡ ኃይል የሀገሪቱን ረጅም የመከራ ቀን በመሳጠርም ትልቅ አስተዋፅኦ ማድረጉንም አስታውቀዋል።

ከሁሉ በላይ ሁላችንም ለሀገር ለውጥ #እንወያይ የሚል ሀሳብ አንግቦ ለተግባራዊነቱም መስራቱ መጪው ጊዜ #ብሩህ ይሆናል የሚል ተስፋ እንዳሰነቃቸውም ገልፀዋል።

የአርበኞች ግንቦት ሰባት ከሁሉም ኃይሎች ጋር ተመካክሮ የተገኘውን ይህን እድል መጠቀም እንደሚሻም ነው ያሰትወቁት ።

በፖለቲካ ምክንያት ሰውን እንደጥላት የማየት አስተሳሰብ ከህብረተሰቡ ሊወጣ ይገባል #መረጋጋት ያስፈልጋል ብለዋል ፕሮፌሰሩ።

የሀገሪቱን ዘለቂ ሰላም ለማምጣትና ዲሞክራሲያዊ ባህልን ለማጎልበት ህብረተሰቡ ለመወያየትና ለመደማመጥ የሚቻልበት ሁኔታ መፍጠር አለበት ስለዚህም ለሁሉም ነገር ነገሮችን #ተረጋግቶ ማሰብ ይገባል ብለዋል።

እኛ ዲሞክራሲያዊ ስርዓት እንዲመጣ ከማድርግ ውጪ ሌላ ዓለማ የለም ይህን ስራ ለመተግበር ግን ብዙ ስራ ይጠይቃል ይህንንም ከሁሉም ጋር በጋራ ለመስራት ፍቃደኛ ነን ብለዋል ሊቀመንበሩ በመግለጫቸው።

ፕሮፌሰር ብርሃኑ እኛ በህብረ ብሔራዊ ስሜት ሀገርን ለመገባት አስበን ብንመጣም #በብሔር ከተደራጁ አካት ጋርም ቢሆን በዲሞክራሲያዊ መልኩ #ለመወያየት ዝግጁ ነን ብለዋል።

©etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia