TIKVAH-ETHIOPIA
1.44M subscribers
55.9K photos
1.4K videos
202 files
3.77K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ከሞት የተነሳው ኢትዮጵያዊ🔝

በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ወለጋ ዞን ሲቡ ስሬ ወረዳ አንድ ግለሰብ ህይወቱ ካለፈ በኋላ መነሳቱ ተገለፀ። ሟች አቶ #ሂርጳ_ነገሮ ለረጅም ጊዜ በፅኑ ህመም ሲሰቃይ ቆይቶ ባለፈው ማክሰኞ ማለትም ህዳር 11 ቀን 2011 ዓ.ም ከጠዋቱ 4:30 ገደማ ህመሙ ፀንቶበት ህይወቱ ያልፋል። በአካባቢው ባህል መሰረትም ሳይገነዝ ለ1 ሰዓት አከባቢ ከቆየ በኋላ አስከሬኑ ተገንዞ ወደ ተዘጋጀለት ሳጥን ይገባል። የቀብር ስነ ስርዓቱን ለመፈፀምም ቤተሰቦቹ ሩቅ ላሉ ወዳጅ ዘመዶቻቸው መልዕክት ይልካሉ።

በመቀጠልም ወዳጅ ዘመዶቹ ቦታው እስኪደርሱ ቤተሰቦቹ የተለያዩ የሀዘን ስነ ስርዓቶችን እያከናወኑ ቆይታ አድርገዋል። ሥርዓቱ እየተከናወነ አስከሬኑ ሳጥን ውስጥ ገብቶ በግምት ከ5 ሰዓት በላይ ከቆየ በኃላ ግን አንድ አስደንጋጭ ነገር ተፈጠረ።ግብዓተ መሬቱ ሊፈፀም ስዓታት የቀሩት ሟች ከአስከሬን ሳጥኑ ወስጥ ድምፅ ማሰማት መጀመሩ ተነግሯል፡፡

ምንጭ: ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አቶ ሂርጳ 'ዳግም' ሞቱ‼️

ከሁለት ወራት በፊት የሞትን ብርቱ ክንድ አሸንፈው ተነሱ የተባሉት አቶ #ሂርጳ_ነገሮ ሞተው ሳሉ የገጠማቸውን ለቢቢሲ አጫውተው የነበረ ሲሆን ከ70 ቀናት በኋላ ትናንት 'ዳግም' ማረፋቸውን ከሁለት ጊዜ ገናዣቸው ተሰምቷል።

መቃብር ፈንቅለው ከወጡ በኋላ ጤናማ የነበሩት አቶ ሂርጳ ላለፉት ሁለት ሳምንታት ግን በፅኑ ታመው ከፈሳሽ ውጭ ምንም ነገር ይወስዱ እንዳልነበር BBC ከቤተሰቦቻቸው ማረጋገጥ ችሏል። እሳቸው አይሆንም ቢሉም ቤተሰቦቻቸው ነቀምት ሆስፒታል ወስደዋቸው ነበር። ቤተሰቦቻቸው አቶ ሂርጳ ዳግም መቃርብር ፈንቅለው ይነሳሉ የሚል #ተስፋ እንደሌላቸው ገልፀዋል።

Via BBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia