TIKVAH-ETHIO
671 subscribers
661 photos
27 videos
7 files
74 links
Download Telegram
Channel photo updated
#UPDATE

ሳዑዲ አረቢያ በፍጥነት እየተዛመት ነው የተባለውን አዲሱን የኮቪድ ዝርያ በመፍራት ሁሉንም አለም አቀፍ በረራዎች ለጊዜው አግዳለች።

እገዳው ለአንድ (1) ሳምንት ሲሆን ከዚህም ሊራዘም እንደሚችል የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር አሳውቋል።

የካርጎ በረራዎች ይቀጥላሉ።

ይህ እገዳ ስለአዲሱ የኮቪድ ዝርያ ግልፅ የሆነ የህክምና መረጃ እስኪገኝ ሊቀጥል እንደሚችልም ተጠቁሟል።

የሀገሪቱ የመሬት እና ባህር ወደቦችም ለአንድ ሳምንት ይዘጋሉ ተብሏል።

የሳዑዲ መንግሥት ባለፉት ሶስት ወራት ከአውሮፓ ሀገራት የመጣ ወይም በአውሮፓ ሀገራት በኩል ጉዞ ያደረገ ማንኛውም ሰው በአስቸኳይ የኮቪድ-19 ምርመራ እንዲያደርግ አዟል።

በተመሳሳይ ፦

ኩዌት በረራዎችን አግዳለች ፤ የመሬት እና የባህር ድንበሮቿን ከዛሬ ጀምሮ እስከ Jan 1 (ታህሳስ 23) ዘግታለች።

የካርጎ በረራ ይቀጥላል።

እንዲሁም ኦማን የባህር ፣ አየር፣ የመሬት ድንበሮቿን ከነገ ማክሰኞ ጀምሮ ለአንድ (1) ሳምንት ትዘጋለች።

@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA
ከፍተኛ ስጋትን የደቀነው አዲሱ የኮቪድ ዝርያ !

በርካታ የአውሮፓ አገራት ብሪታኒያ ላይ የጉዞ እቀባ እያደረጉ ነው።

ለዚህ ምክንያቱ በብሪታኒያ አዲስ ዓይነት የኮቪድ ዝርያ መገኘቱ ነው።

አዲሱ ዝርያ ገና በስፋት ያልተጠና ቢሆንም ከቁጥጥር ውጭ በሆነ መንገድ ከሰው ወደ ሰው ይዛመታል የሚለው ፍርሃት በርካታ አገራትን ድንጋጤ ውስጥ ከቷቸዋል።

እስከ አሁን ጀርመን ፣ አየርላንድ፣ ፈረንሳይ፣ ጣሊያንና ኔዘርላንድስ እና ቤልጂየም ሁሉም ወደ ብሪታኒያ የአየር በረራን አቋርጠዋል።

ዛሬ የአውሮፓ ኅብረት መሪዎች ስብሰባ ስለሚቀመጡ ከዚህ የባሰ የእቀባ ውሳኔ ሊኖር እንደሚችል እየተጠበቀ ነው።

አዲሱ ኮቪድ-19 ዝርያ በለንደንና በደቡብ ምሥራቅ ኢንግላንድ በአጭር ጊዜ ውስጥ ነው በስፋት የተሰራጨው።

ጠቅላይ ሚኒስትር ቦሪስ ጆንሰን ቅዳሜ በሰጡት አስቸኳይ ትእዛዝ ደረጃ 4 የጥንቃቄ ደንቦች እንዲከበሩ አዘዋል።

ለፈረንጆች ገና እና አዲስ ዓመት የእንቅስቃሴ ገደቦች ይላላሉ ተብሎ ታስቦ የነበረውን ሐሳብ ሰርዘዋል።

የጤና ባለሙያዎች አዲሱ የተህዋሲው ዝርያ ይበልጥ ገዳይ ስለመሆኑ ሆነ ለክትባት እጅ የማይሰጥ ስለመሆኑ ገና እርግጠኛ አልሆኑም።

ሆኖም ግን ከለመድነው የኮሮና ቫይረስ በ70 በመቶ በይበልጥ የመሰራጨት አቅም አለው መባሉ ማን ይተርፋል ? እንዲባል አድርጓል።

የብሪታኒያ የጤና ጥበቃ ሚኒስትር ይህ አዲስ ዝርያ ቫይረስ ከቁጥጥር ውጭ ሆኖብናል ፤ በቁጥጥራችን ልናውለው ይገባል ብለዋል።

የዓለም ጤና ድርጅት አዲሱን የኮሮና ቫይረስ ዝርያ በተመለከተ ከዩኬ (UK) ባለሥልጣናት ጋር በቅርበት እየተነጋገረ እንደሆነ አስታውቋል።

ምንጭ፦ ቢቢሲ
@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA
ሰመሓል መለስ ከእስር ተለቀቀች።

ወ/ሮ አዜብ መስፍን ልጃቸው ሰምሃል ከእሁድ ጀምሮ እስከ ሰኞ ምሽት ድረስ ለ36 ሰዓታት ተይዛ መቆየቷን ገልጸው ፤ ትናንት ምሽት እራሷ ደውላ መለቀቋን እንደገለጸችላቸው ዛሬ [ማክሰኞ] ጠዋት ተናግረዋል።

ምንጭ፦ ቢቢሲ
@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ባይደን የኮቪድ-19 ክትባት ተከተቡ።

ተመራጩ የአሜሪካው ፕሬዜዳንት ጆ ባይደን ትላንት ምሽት የኮቪድ-19 ክትባት ተከትበዋል።

ተመራጩ ፕሬዜዳንት ክትባቱን ሲወስዱ በቀጥታ የቴሌቪዥን ስርጭት ለህዝብ ተላልፏል።

ከጥቂት ቀናት በፊት የእስራኤሉ ጠ/ሚር ቤኒያሚን ኔታንያሁ በተመሳሳይ የኮቪድ - 19 ክትባት መከተባቸው የሚታወስ ነው።

@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA
#UPDATE

አዲሱ ተገኘ የተባለው የኮሮና ቫይረስ ዝርያ ለዓለም ሀገራት ስጋት እየሆነ ነው።

ከ40 በላይ አገራት ከUK ወደ አገራቸው የሚደረጉ በረራዎችን አግደዋል።

የአውሮፓ ሕብረት አባል አገራት በዚህ ዙሪያ የጋራ ፖሊሲ ለማውጣት እየተወያዩ ነው።

ዴንማርክ ውስጥ አዲሱ የቫይረስ ዝርያ በመታየቱ ስዊድን ወደ ዴንማርክ የሚደረግ ጉዞ አግዳለች።

ዝርያው በከፍተኛ ሁኔታ የሚሰራጭ ነው። በከፍተኛ ደረጃ ጎጂ ስለመሆኑ ግን እስካሁን የተገኘ መረጃ የለም።

የዓለም ጤና ድርጅቱ ማይክ ራየን ፥ አዲሱ የቫይረስ ዝርያ በወረርሽኙ ዝግመተ ለውጥ ሂደት የሚጠበቅ ነው ብለዋል።

የUK የጤና ሚንስትር ጸሐፊ ማት ሀንኮክ አዲሱ ዝርያ ከቁጥጥር ውጭ ሆኗል ቢሉም ማይክ ራይን አዲሱ ዝርያ "ከቁጥጥር አልወጣም" ብለዋል።

UK ከተገኘው የቫይረስ ዝርያ የተለየ አዲስ ዝርያ በደቡብ አፍሪካም ተገኝቷል። የደቡብ አፍሪካ ተጓዦች ላይ እገዳ እየተጣለም ነው።

እስካሁን የአዲሱ ቫይረስ ዝርያ በዴንማርክ፣ አውስትራሊያ፣ ጣልያን እና ኔዘርላንድስም ተገኝቷል።

አንዳንድ ባለሙያዎች እንደሚሉት ከሆነ ፤ የቫይረሱ ዝርያ ከተገኘባቸው ቦታዎች ውጪ ተሰራጭቶ ሊሆን ይችላል።

UK የዘረ መል ቅንጣት ላይ ጥናት በማድረጓ አዲሱን የቫይረስ ዝርያ እንደደረሰችበት አስረድተዋል።

በቤልጄም የሚሠሩት የቫይረስ አጥኚ ማርክ ቫን፤ "በቀጣይ ቀናት አዲሱ የቫይረሱ ዝርያ በብዙ አገሮች ይገኛል ብለን እንጠብቃለን" ብለዋል። (BBC)

@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA
#Ethiopia

ዛሬ ሀገራችን #ኢትዮጵያ ሁለተኛዋን ሳታላይት አምጥቃለች።

' ET-SMART-RSS ' በስኬት መምጠቋን የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት በይፋዊ ፌስቡክ ጉፁ ላይ አስታውቋል፡፡

@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA
#የኢትዮጵያ_ማሳሰቢያ

በካርቱም ሲካሄድ የነበረው 2ተኛው የኢትዮ ሱዳን የድንበር ጉዳዮች ከፍተኛ ደረጃ የፖለቲካ ውይይት መጠናቀቁን ፋና ዘግቧል።

ሁለቱም ወገኖች በጋራ የድንበር አካባቢ ወቅታዊ ጉዳዮችን በተመለከተ ሃሳብ ተለዋውጠዋል።

ከጥቅምት መጨረሻ ጀምሮ "በጋራ ድንበር" አካባቢ በሱዳን በኩል የተደረጉ አዳዲስ ለውጦችና እንቅስቃሴዎች የቀደሙ ስምምነቶችን የሚጥሱ መሆናቸው ተነስቷል፡፡

ከዚህ ባለፍ መሬት ላይ ያለውን እውነታ የሚለውጥ በመሆኑ በአስቸኳይ እንዲቆሙ እና ወደቀደመ ቦታቸው እንዲመለሱ ኢትዮጵያ አሳስባለች፡፡

@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA
#BenishangulGumuz

የኢትዮጵያ መንግሥት በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን ያለውን ችግር ከመሠረቱ ለመፍታት አስፈላጊውን የተቀናጀ ኃይል እንዲሠማራ ማድረጉን ጠ/ሚ ዶ/ር አብይ ዛሬ ጥዋት አሳወቁ።

በክልሉ መተከል ዞን ውስጥ በዜጎች ላይ እየተፈጸመ ያለው ጭፍጨፋ እጅግ አሳዛኝ ሆኗል ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።

በተፈጸመው ኢሰብአዊ የሆነ ተግባርም በእጅጉ ማዘናቸውን ገልፀዋል።

ጠ/ሚሩ ችግሩን በተለያዩ መንገዶች ለመፍታት የተደረገው ጥረት የሚፈለገውን ውጤት አላመጣም ብለዋል። መንግስት አሁን ላይ የተቀናጀ ኃይል እንዲሰማራ ማድረጉን በፌስቡክ ገፃቸው አሳውቀዋል።

@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA
ሀገር መከላከያ ሰራዊት በወሰደው እርምጃ 42 ታጣቂዎች ተደመሰሱ !

በመተከል ዞን ቡለን ወረዳ በኩጂ ቀበሌ በትናንትናው ዕለት በንጹኃን ዜጎች ላይ #ጥቃት ያደረሱ የታጠቁ ኃይሎች ላይ ሀገር መከላከያ ሰራዊት ተከታትሎ በወሰደው እርምጃ 42ቱ መደምሰሳቸውን የክልሉ ኮሚኒኬሽን ቢሮ ከደቂቃዎች በፊት አሰውቋል።

የመከላከያ ሠራዊት በወሰደው እርምጃ ታጣቂዎቹ ለጥፋት ሲጠቀሙባቸው የነበሩ በርካታ የጦር መሳሪያዎችን እና ቀስቶችን በቁጥጥር ስር አዉሏል።

@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA
#SecurityAlert

በመተከል ዞን ቡለን ወረዳ ኤማንጂ፣በኖሽ፣ ዶቢ ቀበሌዎች አሁንም ከፍተኛ የደህንነት ችግር እንዳለባቸውን የቲክቫህ አባላት አሳውቀዋል።

ትላንት ለሊቱን በዶቢ ቀበሌ የተኩስ ድምፅ ሲሰማ እንደነበረ ጠቁመዋል። ስለደረሰው ጉዳት አጣርተው እንደሚያሳውቁን ገልፀዋል።

በተጠቀሱት አካባቢዎች ነዋሪው ቤት ንብረቱን ጥሎ እየሸሸ መሆኑንም አባላቶቻችን መልዕክት አድርሰዋል።

www.tikvahethiopia.net ላይ በየአካባቢው ያለውን የፀጥታ እንዲሁም ደህንነት ስጋት ልታሳውቁን ትችላላችሁ።

#TikvahFamilyBulenWoreda

@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA
#TikvahFamilyBulenWoreda

ትላንት ለሊቱን በዶቢ ቀበሌ ከፍተኛ የተኩስ ድምፅ ሲሰማ ነበር።

በቀበሌው በተፈፀመው ጥቃት የአምስት ሰዎች ህይወታቸው እንዳለፈ በቡለን ወረዳ የቲክቫህ ኢትጵያ አባላት አሳውቀዋል።

አሁን በስልክ ያገኘናቸው የዶቢ ቲክቫህ አባላት የሟቾችን ስርዓተ ቀብር በስጋት ውስጥ ሆነው እያከናወኑ እንደሆነ ተናግረዋል።

ጥቃት አድራሾቹ ከበኩጂ ቀበሌ የተበተኑ የታጠቁ ኃይሎች እንደሆኑ የቲክቫህ አባላት በ www.tikvahethiopia.net ላይ ገልፀዋል።

አንድ አባላችን እንደገለፁልን ወደ #ዶቢ የገቡት ታጣቂዎች እስከ 300 የሚደርሱ ናቸው።

የመከላከያ ሰራዊት መረጃው ደርሶት በመግባት ምሽግ ይዞ ጥቃቱን ባይከላከል የሟቾች ቁጥር ሊጨምር ይችል ነበር ብለውናል።

አንድ የመከላከያ አባልም መጠነኛ ጉዳት ደርሶበታል።

የመተከል ዞን የቲክቫህ አባላት ለአካባቢው እንዲህ መሆን የክልሉ አመራሮችን ተጠያቂ ያደርጋሉ።

ነዋሪው ተስፋ ቆርጧል ፥ ግፍ ሰልችቶታል እጅግ በጣም አስቸኳይ መፍትሄ ይፈልጋል ብለዋል።

አሁንም ቢሆን በወረዳው የተለያዩ ቀበሌዎች ውስጥ ከፍተኛ የደህንነት ስጋት በመኖሩ የሚመመለከተው አካል ንፁሃንን እንዲታደግ አባላቶቻችን እየተማፀኑ ነው።

@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA
#የእሳት_አደጋ_በጅግጅጋ

በጅግጅጋ ከተማ በ ቀበሌ 02 በልዩ ስሙ ድብኡራሾ ሱቅ ተብሎ በሚታወቀው ቦታ ትላንት ከቀኑ 9 ሰዓት ላይ የእሳት አደጋ ተከስቶ ነበር።

መነሻ መንስዔው ያልታወቀው እሳቱ የተነሳው ከአንድ ሱቅ መሆኑ ተገልጿል።

በሰው ህይወት ላይ ምንም አይነት ጉዳት እንዳልደረሰ የተገለፀ ሲሆን እሳቱ በፍጥነት በመዛመቱ 7 የንግድ ቦታዎች ላይ ከፍተኛ አደጋ አድረሷል።

ድምሩ ወደ 1.2 ሚሊዮን ብር የሚጠጋ ንብረት ነው።

#እሳት_አደጋ_በመቅደላ_ወረዳ

ትላንት ምሽት በደቡብ ወሎ ዞን መቅደላ ወረዳ የእሳት አደጋ ተከስቶ ነበር።

የእሳት አደጋው መነሀሪያ ሸድ ላይ የተከሰተ ነበር።

በሰው ላይ የደረሰ ጉዳት የሌለ ሲሆን በንብረት ላይ የደረሰውን የጉዳት መጠን እና ተያያዥ ጉዳዮች እየተጣራ ነው።

ምንጭ፦ አዲስ ዘይቤ ድረገፅ፣ የመቅደላ ወረዳ ኮሚኒኬሽን
@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA
#Metekel

በትላንትናው ዕለት በኩጅ ቀበሌ በታጣቂዎች በተፈፀመው ጥቃት 100 ንጹሃን ዜጎች መሞታቸውን የመተከል ዞን ኮማንድ ፖስት አሳውቋል።

@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA
#Metekel

ዛሬ ጥዋት 2 የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከፍተኛ አመራሮች በቁጥጥር ስር ውለዋል።

በቁጥጥር ስር የዋሉት የክልሉ ግዢና ንብረት ማስወገድ ዋና ዳይሬክተር እንዲሁም የገጠር መንገድ ምክትል ዳይሬክተር ናቸው።

በትላንትናው ዕለት በኩጅ ቀበሌ የተፈጠው ችግር ከተከሰተ በኃላ እነዚህ ከፍተኛ አመራሮች #እጃቸው_አለበት ተብለው ተጠርጥረው ነው የታሰሩት።

አመራሮቹ ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉት ከህበረተሰቡ በተሰጠ ጥቆማ ነው።

በቀጣይም ከህብረተሰቡ በሚሰጥ ጥቆማ ለችግሩ መባባስ ድርሻ አላቸው የተባሉ የትኛውም የቤጉ ክልል አመራር ሆነ የፀጥታ አካል ተጣርቶ እርምጃ ይወሰድበታል ብሏል ክልሉ።

በትላንትናው ዕለት አምስት የክልሉ አመራሮች በቀጥጥር ስር እንደዋሉ መገለፁ ይታወሳል።

@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA
በትግራይ ክልል ጊዜያዊ የጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ፋሲካ ዐምደሥላሴ በዐይደር ሪፈራል ሆስፒታል የቀዶ ሕክምና ስፔሻሊስት ሆነው ሲያገለግሉ በነበረበትና የኢትዮጵያ መካልከያ ሠራዊት መቀሌን ሲቆጣጠሩ ነበረ ያሉትን ሁኔታ አስረድተዋል።

@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የካቢኔ አባላትን ይፋ አደረገ !

የጊዜያዊ አስተዳደሩ የጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ገብረመስቀል ካሳ ለኢዜአ እንደገለጹት በክልሉ አዲስ የካቢኔ አባላት ተሹመው ስራ ጀምረዋል፡፡ በክልሉ ከሚያስፈልጉ 16 የካቢኔ አባላት መካከል 11 ተሿሚዎች በይፋ ስራ መጀመራቸውን ኃላፊው አስታውቀዋል፡፡

በዚሁ መሠረት፡-

• ዶ/ር ካህሣይ ብርሃኑ - የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ሃላፊ

• ኢንጂነር አሉላ ሃብተአብ - የኮንስትራክሽን፣ መንገድና ትራንስፖርት ቢሮ ሃላፊ

• ዶክተር ፋሲካ አምደስላሴ - የጤና ቢሮ ሃላፊ

• አቶ አበራ ንጉሴ - የፍትህ ቢሮ ሃላፊ

• ወይዘሮ እቴነሽ ንጉሴ - የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ሃላፊ

• አቶ ዮሴፍ ተስፋይ - የንግድ፣ ኢንዱስትሪና ከተማ ልማት ቢሮ ሃላፊ

• ዶክተር ተስፋይ ሰለሞን - የትምህርት ቢሮ ሃላፊ

• ዶክተር ገብረህይወት ለገሠ - የውሃ ጥናትና ዲዛይን ቢሮ ሃላፊ

• አቶ ሰለሞን አበራ - የውሃ ሃብት ቢሮ ሃላፊ

• አቶ አብርሃ ደስታ - የማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ሃላፊ

• አቶ ገብረመስቀል ካሣ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የጽህፈት ቤት ሃላፊ ሆነው መሾማቸው ተገልጿል፡፡

ያልተሟሉ የካቢኔ አባላት በቀጣዮቹ ሳምንታት ተሟልተው ወደ ስራ እንደሚገቡ ይጠበቃል ተብሏል፡፡

@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA
#BuleHoraUniversity

የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የነባር የአንደኛ እና ከዛ በላይ የተማሪዎች ከነገ ማለትም ታህሣስ 16/2013 ጀምሮ ተማሪዎችን ይቀበላል፡፡

የዩኒቨርሲቲውን የቅበላ ዝግጅት የሚያሳዩ በፎቶዎችን ከላይ መመልከት ይቻላል።

በሌላ በኩል ፦

• ዶ/ር ጉሚ ቦሩ የቡሌ ሆራ ዩኒቨርስቲ የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዜዳንት ሆነው ተመድበዋል።

• ዶ/ር ታምሩ አኖሌ የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዜዳንት ሆነው ተመድበዋል።

• ዶ/ር ሮባ ደምቢ የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የአስተዳደር እና ተማሪዎች አገልግሎት ምክትል ፕሬዜዳንት ሆነው ተመድበዋል።

• ኢንጂነር አብርሃም ባያብል የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የቢዝነስና ተቋማዊ ልማት ምክትል ፕሬዜዳንት ሆነው ተመድበዋል።

@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA