ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ
15.5K subscribers
335 photos
80 videos
146 files
208 links
This channel is not operated by Deacon Yaregal Abegaz

https://youtube.com/@yaregalabegaz?si=1f5NHTaQ2l2LbxWQ

“ዕለት ዕለት የሚከብድብኝ የአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ አሳብ ነው።”
— 2ኛ ቆሮ 11፥28
Download Telegram
እያንዳንዱ ኦርቶዶክስ በውዴታ ግዴታ ሊያነበውና በቤቱ ሊኖረው የሚገባ መናፍቃንን እና እምነት የለሾችን(Atheists) ወደ እውነተኛ መንገድ የመለሰ ኦርቶዶክሶችን ደግሞ በእምነታቸው ያፀና ድንቅ መፅሀፍ

#መድሎተ_ጽድቅ (በሶስት ቅጽ)
👆👆👆👆👆
ሃይማኖት እና እምነት
* ሃይማኖት ምንድን ነው?
* እምነት ምንድን ነው?
* የእምነት አይነቶች በመጽሀፍ ቅዱስ
ሃይማኖት አያስፈልግምን ?
* ክርስትና ሃይማኖት አይደለምን?
* ድህነት በሃይማኖት አይደለምን?
* በሞተልን ጌታ የምንገኘው እንዴት ነው?
* ወንጌል በየትኛውም ሃይማኖት ቢሰበክ ችግር የለውምን?
* ዶግማ ማለት ምን ማለት ነው?
* ኦርቶዶክስ ተዋህዶበሰው የተመሰረተች ነችን?
* የሃይማኖት ክፍልፋይ ስም ነው ችግራችን? ወይስ የመጽሀፍ ቅዱስ አረዳድ?
* የመጽሀፍ ቅዱስ ክርስትና እንደምን ያለ ነው?
* በሃይማኖቶች መካከል ያለው የአስተምህሮ ልዩነት ችግር የለውምን?

#መድሎተ_ጽድቅ

#ዲያቆን_ያረጋል_አበጋዝ
ኑፋቄ (በዲያቆን ያረጋል አበጋዝ) (1).pdf
330.5 KB
ኑፋቄ

* ኑፋቄ ምንድን ነው?

በዘመናት የነበሩ ዋና ዋና መናፍቃንና ኑፋቄያቸው በአጭሩ

* ግኖስቲኮች/ ኖስቲኮች
* አርዮስ
* ንስጥሮስ
* ሄልቪዲየስ
* ጆቪኒያን
* ቪጂላንቲየስ
* አርዮስ ዘሴባስቴ
* ማርቲን ሉተር

#መድሎተ_ጽድቅ

#ዲያቆን_ያረጋል_አበጋዝ
ለካህን_መናዘዝና_ቀኖና_መቀበል_ለምን_በዲያቆን_ያረጋል_አበጋዝ.pdf
333.1 KB
ለካህን መናዘዝና ቀኖና መቀበል ለምን?

* የተሐድሶዎች ትምህርት ለካህን ስለመናዘዝና ቀኖና ስለመቀበል
* በዚህ ጉዳይ ላይ የተሐድሶዎች መሠረታዊ ስህተቶች
* ለንስሐ አባት መናዘዝና ቀኖና መቀበል በመፅሀፍ ቅዱስ ትምህርት
* ቀኖና የሚሰጥባቸው ምክኒያቶች
* ንስሐ አባትና ቀኖና በአበው ትምህርት

~ +++++ ~~

“ነቢዩ ናታን ንጉሥ ዳዊትን ኃጢአቱን ከነገረው በኋላ ወዲያውኑ ኃጢአቱን እንዳመነ አጽናንቶት ነበር፡፡ ሆኖም ብፁዕ ዳዊት ግን ምንም እንኳ እግዚአብሔር ደግሞ ኃጢአትህን አርቆልሃል፡ ኣትሞትም' (2 ሳሙ. 12፡13) የሚለውን የነቢዩን ቃል የሰማ ቢሆንም ንስሐ ከመግባት ግን አልተመሰለም፡፡ ንጉሥ የነበረ ቢሆንም በልብሰ መንግሥት ፋንታ አመድ ለበሰ በወርቅ ዙፋን ላይ በመቀመጥ ፋንታ በመሬት ላይ፣ ያውም በአመድ ላይ ተቀመጠ፡፡ በአመድ ላይ የተቀመጠ ብቻ ሳይሆን አመድንም ምግቡ አደረገ፤ እርሱ ራሱ “አመድን እንደ እህል ቅሜያለሁና፣ መጠጤንም ከእንባዬ ጋር ቀላቅያለሁና” (መዝ 101፡9) ብሏልና፡፡ ወደ ኃጢአት የተመለከተው ዓይኑ በዕንባ እስኪሟሟ ደረሰ፤ “ሌሊቱን ሁሉ አልጋዬን አጥባለሁ፣ በዕንባዬም መኝታዬን አርሳለሁ፤ ዓይኔ ከቍጡ ዕንባ የተነሣ ታወከች” እንዳለ፡፡ መዝ. 6፡6-7 መኳንንቱ እህል እንዲቀምስ በለመኑት ጊዜ እንኳ አልሰማቸውም፡፡ ጾሙን እስከ ሰባት ሙሉ ቀናት አራዘመ፡፡ ንጉሥ የነበረው እርሱ እንዲያ ባለ ሁኔታ ንስሐ ከገባ ተራ ግለሰብ የሆንከው አንተ ንስሐ ልትገባና ልትናዘዝ አይገባህምን?” (ቅዱስ ቄርሎስ ዘኢየሩሳሌም፣ ትምህርት 2 በእንተ ንስሐ ወሥርየተ ኀጢአት፣ ቁ 12)


#መድሎተ_ጽድቅ

#ዲያቆን_ያረጋል_አበጋዝ
ሁሉም_ክርስቲያን_ካህን_ነውን_በዲያቆን_ያረጋል_አበጋዝ.pdf
323.4 KB
ሁሉም ክርስቲያን ካህን ነውን?

* የ1ኛ ጴጥሮስ 2፥9 እንዲሁም የዮሀንስ ራዕይ 1፥6 ማብራሪያ እና ከ ዘጸአት 19፥6 አንፃር
* ክህነትን የተዳፈሩ ሰዎች
* ካህናት ትሆኑ ዘንድ ምን ማለት ነው?
* የክርስቲያኖች ሁሉ አጠቃላይ ክህነት

++++ ~~ +++++

እዚህ ላይ ጳውሎስ “ሰውነታችሁን እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝና ሕያው ቅዱስም መሥዋዕት አድርጋችሁ አቅርቡ” ሲል አሳሰበን። ሰውነት መሥዋዕት ሆኖ የሚቀርበው እንዴት ተደርጎ ነው? ብሎ የሚጠይቅ ይኖር ይሆናል። ዓይን ክፉ ነገርን አይመልከት፣ እንዲህ ካደረግህ ዓይንህ መሥዋዕት ሆኖ ቀርቧል ማለት ነው፤ እጅህ ሕገ ወጥ የሆነ ተግባርን አያድርግ፣ ይህ ከሆነ የተቃጠለ መሥዋዕት ሆኗል ማለት ነው። ወይም ይህም ብቻውን በቂ አይደለም፣ በዚህ ላይ መልካም ሥራን መሥራትም ይገባናል እንጂ። እጅ ምጽዋትን ይስጥ፣ አንደበት የሚረግሙትን ይመርቅ፣ ጆሮም የቅዱሳት መጻሕፍትን ትምህርት በመስማት ደስ ይሰኝ። መሥዋዕት ሆኖ የሚቀርብ ነገር አንዳችም ነውርና ነቀፋ ያለው ሆኖ ሊቀርብ አይችልምና። መሥዋዕት የሌሎች ተግባራት ሁሉ ቀዳምያት ነውና። ስለዚህም ከእጃችንም፣ ከእግራችንም፣ ከአንደበታችንም፣ ከሌላውም አካላችን ሁሉ ለእግዚአብሔር ቀዳምያትን እናቅርብ። ይህ ዓይነቱ መሥዋዕት መልካምና ደስ የሚያሰኝ ነው። (ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)


#መድሎተ_ጽድቅ
#ዲያቆን_ያረጋል_አበጋዝ
ምጽዋት (በዲያቆን ያረጋል አበጋዝ).pdf
199 KB
ምጽዋት

* ምጽዋት በመጽሀፍ ቅዱስ ትምህርት

* ምጽዋት በአበው ትምህርት

++++++++~~++++++

ከጥምቀት በኋላ የሚሠሩ ኃጢአቶችን ማስወገጃና ማጠቢያ መንገድ ማግኘት መቻል ምን ያህል ታላቅ ነገር መሆኑን ልብ በል! ምጽዋት መስጠት ምን ያህል ታላቅ ዋጋ እንዳለው አስተውል፡፡ እርሱ ምጽዋት ስጡ ባይለን ኖሮ፣ 'ገንዘብ መስጠትና ከሚመጣው ክፉ ነገር በምጽዋት አማካይነት መዳን የሚቻል ቢሆን ኖሮ እንዴት ጥሩ ነበር' የሚሉ ስንት ሰዎች በኖሩ ነበር! ነገር ግን አሁን እግዚአብሔር ለእኛ ካለው ቸርነት የተነሣ በምጽዋት አማካይነት ከሚመጣው ክፉ ነገር መዳን የምንችልበትን ዕድል ስለ ሰጠንና ይህን የሚቻል ስላደረገልን እንደገና ብዙዎች ተመልሰው ግድ የለሾች ሆነው ይታያሉ፡፡ አይ፣ እኔ ምጽዋት እሰጣለሁ እኮ ትል ይሆናል፡፡ ይህ ምንድን ነው? ሆኖም ግን መቀነቷን ፈትታ ሁለት ሣንቲሞችን እንደ ሰጠችው ሴት ያህል አልሰጠህም፡፡ ኧረ የእርሷን ግማሽ ያህል፣ እርሷ ከሰጠችው ጥቂቱን ያህል እንኳ አልሰጠህም፡፡ ካለህ ገንዘብ ብዙውን ክፍል ጥቅም በሌለው ነገር ላይ ታባክነዋለህና፡፡ በመጠጥ፣ በመባልዕት ቅጥ ባጣ አባካኝነት እያዋልክ ራስሀን ብቻ ሳይሆን ሌሎችንም እንደ አንተ እንዲያባክኑና ገንዘባቸውን በማይጠቅማቸውና ተገቢ ባልሆነ ነገር ላይ እንዲያጠፉት ፈተና ትሆንባቸዋለህና፡፡ በዚህም ቅጣትህ እጥፍ ድርብ ይሆንብሃል፤ የራስህ ጥፋት አንሶህ ሌሎችንም ወደ ጥፋት መርተሃቸዋልና፣ የኃጢአት ምክንያት ሆነሀባቸዋልና፡፡ (ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ፣ ትርጓሜ ወንጌለ ማቴዎስ፣ ክፍለ ትምህርት 67፣ ቁ. 5)


#መድሎተ_ጽድቅ
#ዲያቆን_ያረጋል_አበጋዝ
ክህነት_በሀዲስ_ኪዳን_በዲያቆን_ያረጋል_አበጋዝ_.pdf
247.5 KB
ክህነት በሀዲስ ኪዳን

* የተለየ ክህነት
* አዲስ ክርስቲያን ካህን መሆን ይችላል?
* ሽማግሌ ወይስ ካህን ?

++++++++++~~~~~+++++++++

ኃጢአትን ይቅር የማለትን ሥልጣን ለራሱ ለእግዚአብሔር ብቻ የሚገባ ሥልጣን ስለሆነ ይህን ለሌላ ለማንም አንሰጥም በማለት፣ እግዚአብሔርን ታላቅ በሆነ አክብሮት እናከብረዋለን ይላሉ። ሆኖም ግን እርሱ በግልጽ የተናገረውን ትእዛዙን እንደሚሽሩትና ለካህናት የሰጠውን ሥልጣን አንቀበልም እንደሚሉት እንደ እነርሱ አድርጎ የሚያቃልለው ሌላ ማንም የለም። ራሱ ጌታችን “መንፈስ ቅዱስን ተቀበሉ፣ ኃጢአታቸውን ይቅር ያላችኋቸው ሁሉ ይቀርላቸዋል፤ የያዛችሁባቸው ተይዞባቸዋል” ያላቸው ከሆነ፣ እግዚአብሔርን የሚያከብረው የእርሱን ትእዛዝ ተቀብሎ የሚታዘዘው ነው? ወይስ ትእዛዙን አልቀበልም የሚለው? .. " (ቅዱስ አምብሮስ በእንተ ንስሐ፣ መጽሐፍ 1፡6-7)

#መድሎተ_ጽድቅ

#ዲያቆን_ያረጋል_አበጋዝ
ወላዲተ_አምላክ_በዲያቆን_ያረጋል_አበጋዝ.pdf
352.7 KB
ወላዲተ አምላክ

*እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም "ወላዲተ አምላክ" ትባላለችን? ለምን?

* "ወላዲተ አምላክ" የቃሉ ትርጉም

* የቃሉ ነገረ መለኮታዊ ፋይዳ

* የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ወላዲተ አምላክነት በመጽሀፍ ቅዱስ ትምህርት

* የእመቤታችን ወላዲተ አምላክነት-በቀደምት አበው ትምህርት

+++++++++~~~+++++++

ቅዱስ ቄርሎስ ንስጥሮስ “ወላዲተ አምላክ” የሚለውን መቃወሙ በነገረ ክርስቶስና በነገረ ድኅነት ላይ የሚያስከትለው ነገር መሠረታዊ የሆነ ኑፋቄ መሆኑን በሚገባ አስረድቷል፡፡ እነዚህን ነገሮችም እንደሚከተለው በሚገባ ለይቶ አውጥቷቸዋል፡-

ከድንግል ማርያም የተወለደው አካላዊ ቃል የእኛን ባሕርይ ነሥቶ (ተዋሕዶ) ሥግው ቃል ካልሆነና ሰው ብቻ (ዕሩቅ ብእሲ) ከሆነ መዳናችን አደጋ ላይ ይወድቃል፡፡ ምክንያቱም ክርስቶስ የተቀበላቸው ሕማማትና መከራዎች የሥግው ቃል (ሥጋን የተዋሐደውና የእኛን ባሕርይ ባሕርዩ አድርጎ ሰው ሆኖ በሥጋ የተገለጠው አካላዊ የእግዚአብሔር ቃል) ሕማማትና መከራዎች ሳይሆኑ የዕሩቅ ብእሲ (የስው ብቻ) ይሆናሉና፡፡ ፍጡር በሆነ በሰው ብቻ መዳን አይቻልምና ስለዚህ ድነናል ማለት አይቻልም፡፡ ስለዚህ ወላዲተ አምላክ የሚለውን ቃል መካድ የአምላክን ሰው የመሆን ምሥጢር (ምሥጢረ ሥጋዌን) እና የሰውን መዳን መካድ ነው፡፡

እንደዚሁም አካላዊ ቃል አዲሱን ሰው ዳግማዊ አዳምን ለመፍጠር አካላዊ ቃል ከእኛ ባሕርይ ጋር ሊያደርግ የሚያስፈልገው ተዋሕዶ፡ ንስጥሮስ እንዳለው ዓይነት አፍኣዊና የጉርብትና ዓይነት ዝምድና ሳይሆን፣ ውሳጣዊና ባሕርያዊ የሆነ ጥብቅ እና አማናዊ የሆነ ተዋሕዶ ያስፈልገው ነበር፡፡ ይህ አይደለም ከተባለ የባሕርያችን መታደስ፡ በሐዲስ ተፈጥሮ የመዳናችን ነገር ሁሉ ከንቱ ይሆናል፡፡

#መድሎተ_ጽድቅ

#ዲያቆን_ያረጋል_አበጋዝ