TIKVAH-ETHIOPIA
1.5M subscribers
56.7K photos
1.41K videos
203 files
3.87K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ጎንደር ዩኒቨርሲቲ‼️

የተቋሙ ተማሪዎች በግቢው ውስጥ የተፈጠረው ችግር በዘላቂነት እንዲፈታ እና አስተማማኝ ሰላም እንዲሰፍን ሁሉንም ያካተተ #ውይይት ሊደረግ ይገባል ብለዋል። ትላንት የተወሰኑ ተማሪዎች ተስማምተው ግቢው ውስጥ ሰላም ወርዶ የነበር ቢሆንም ምሽት ላይ ተማሪ ተጋጭቶ ነበር በዚህም የፀጥታ አካላት እርምጃ ውስደዋል ሲሉ ተማሪዎች ገልፀዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
አ.አ.ሳ.ቴ🔝የአዲስ አበባ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ (AASTU) ተማሪዎች ከፀጥታ አካላት ጋር #ውይይት በማድረግ ላይ ይገኛሉ።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የህዳሴው ግድብ‼️

በኢትዮጵያ ታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባታ ላይ የተለዩ ክፍተቶችን በማስተካከል
በፈረንጆቹ 2022 #እንደሚጠናቀቅ ተገለፀ።

በዛሬው ዕለት የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ያለበትን ደረጃ አስመልክቶ #ውይይት እየተካሄደ ነው።

ጥልቅ ጥናትና ምርምር ስራ ሳይከናወንለት ግንባታው በመጀመሩ ምክንያት ግንባታ ጊዜው ሊጓተት እንደቻለ የውሃ፣መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታውቋል።

ታላቁ የኢትዮዽያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ያስከተለው ጉዳት ሀገሪቷ በየዓመቱ 800 ሚሊየን ዶላር እንድታጣ አድርጓታል ተብሏል።

የግንባታው ስራው በአሁን ወቅት የሚገኝበት ደራጀም በዛሬው ዕለት እየተካሄደ በሚገኘው ውይይት ወቅት ይፋ ሆኗል።

በዚህም በሳሊኒ ሲሰራ የነበረው የሲቪል ምህንድስናው ስራው 82 በመቶ ላይ የሚገኝ ሲሆን፥ የኤሌክትሮ መካኒካል ስራው ደግሞ 25 በመቶ ላይ ይገኛል ተብሏል በውይይቱ ወቅት።

በአጠቃላይ የህዳሴ ግድብ ግንባታ 65 በመቶ መጠነቀቁ ተነግሯል። ከዚህ ባለፈ የግንባታው ፅህፈት ቤት ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይልና ከውሃ፣ መስኖና ኢነርጅ ሚኒስቴር የግንባታ ሂደቱን ለማፋጠን በትብብር እየሰሩ ይገኛሉ።

የህዝባዊ ተሳትፎን ፣ ከታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ጋር ባለው የሶስትዮሽ ግንኙነት እና የኃይል ሽያጭ ትስስር ላይ ትኩረት ባደረጉ አራት ጉዳዮች ላይ ውይይቱ ነው እየተካሄደ የሚገኘው።

ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ከዛላምበሳ ግምባር የጦር መሳሪያ ጭነው ወደ መሀል ሀገር ሲንቀሳቀሱ #የታገቱ የመከላከያ ተሽከርካሪዎች #ተለቀዋል። የመከላከያ ተሽከርካሪዎቹ የተለቀቁት ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር #ውይይት ተደርጎ ስምምነት ላይ በመደረሱ ነው።

ምንጭ፦ ኢትዮጵያ ላይቭ ሀፕዴት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፖሊስ በቂ ዝግጅት አድርጓል~ሀዋሳ‼️

በሃዋሳ ከተማ ነገ ለሚካሄደው የሲዳማ ህዝበ ውሳኔ #ይፋጠንልን ህዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ በሰላም እንዲጠናቀቅ በቂ ዝግጅት ማድረጉን የሃዋሳ ከተማ ፖሊስ አስታወቀ። 

የከተማው ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ኮማንደር #መስፍን_ዴቢሶ ለኢዜአ እንደገለጹት ነገ በሃዋሳ የሚካሄደውን ሰልፍ ተከትሎ #ሰላማዊ በሆነ መንገድ እንዲጠናቀቅ ዝግጅት ተደርጓል።

የከተማው ፖሊስ ከዞን፣ ከክልሉ ልዩ ሃይልና ከፌደራል ፖሊስ ጋር በመቀናጀት ሰልፉ በሚካሄድባቸው አካባቢዎች በቂ ጥበቃ ያደርጋልም ብለዋል፡፡

ፖሊስ አዛዡ እንዳሉት ከሪፈራል አደባባይ ጠዋት አንድ ሰዓት የሚጀመረው ሰላማዊ ሰልፍ መዳረሻው ከቀኑ ስድስት ሰዓት ሃዋሳ አለም አቀፍ ስታዲየም ነው፡፡

ሰልፉ ወደ ብሉናይል የሚያወጣውን አስፓልት ይዞ ተስፋዬ ግዛው ህንጻ አደባባይ ሲደርስ ወደ ሃዋሳ አለም አቀፍ ስታዲየም እንደሚገባና ማጠቃለያውን እንደሚያደርግ ተናግረዋል፡፡

በዚህ ምክንያት መንገዶቹ ለተሸከርካሪ ዝግ ይሆናሉ ያሉት ኮማንደር መስፍን፤ በበቂ የፀጥታ ሃይል ጥበቃ እንደሚደረግም ገልጸዋል፡፡

የከተማው ነዋሪ በሰልፉ ምክንያት ስጋት ውስጥ እንዳይገባ በየክፍለ ከተማው #ውይይት መደረጉን ገልጸው ህዝቡም ለሰልፉ ሰላማዊነት የበኩሉን እንዲወጣ ጠይቀዋል፡፡

የሰልፉ አስተባባሪ ኮሚቴ የሚዲያ ተጠሪ አቶ ሳሙኤል በላይነህ በበኩሉ የሲዳማ ብሄር በክልል የመደራጀት ህገ-መንግስታዊ ጥያቄውን ተከትሎ ህዝበ ውሳኔው በመዘግየቱ የተዘጋጀ ሰልፍ ነው” ብሏል።

ዓላማውም “ከዞን ምክር ቤት ጀምሮ በክልሉ ምክር ቤት ጸድቆ ለህዝበ ውሳኔ ለምርጫ ቦርድ የተላከው ሪፈረንደም ጥያቄ ዘግይቷል ይፋጠንልን” የሚል መሆኑን ተናግሯል።

ጥያቄው ህገ-መንግስታዊ ስርዓቱን ተከትሎ የቀረበ ቢሆንም ምላሹ በመዘግየቱ በዞኑ ካሉ ወረዳዎችና ከሃዋሳ ከተማ የተውጣጡ ነዋሪዎች መንግስትን በሰላማዊ መንገድ የሚጠይቁበት እንደሆነም ተናግሯል፡፡

“ሰልፉ በሰላማዊ መንገድ እንዲጠናቀቅ ከከተማው ፖሊስና ከሃዋሳ ከተማ ነዋሪዎች ጋር በቅንጅት እየሰራን ነው” ብሏል፡፡

በሰላማዊ ሰልፉ የመንግስት አካላት፣ የተለያዩ ተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎችና የሰልፉ ደጋፊዎች ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

ምንጭ፦ ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሀዋሳ‼️

ነገ ለሚደረገው #ሰላማዊ_ሰልፍ የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ ከዞን ፖሊስ፣ ከክልሉ ልዩ ሃይልና #ከፌደራል_ፖሊስ ጋር በመቀናጀት ሰልፉ በሚካሄድባቸው አካባቢዎች በቂ ጥበቃ ያደርጋል። ከሪፈራል አደባባይ ጠዋት አንድ ሰዓት የሚጀመረው ሰላማዊ ሰልፍ መዳረሻው ከቀኑ ስድስት ሰዓት ሃዋሳ አለም አቀፍ ስታዲየም ነው፡፡

ሰልፉ ወደ ብሉናይል የሚያወጣውን አስፓልት ይዞ ተስፋዬ ግዛው ህንጻ አደባባይ ሲደርስ ወደ ሃዋሳ አለም አቀፍ ስታዲየም እንደሚገባና ማጠቃለያውን እንደሚያደርግ ተናግሯል። በዚህ ምክንያት መንገዶቹ ለተሸከርካሪ #ዝግ ይሆናሉ እንዲሁም በበቂ የፀጥታ ሃይል ጥበቃ ይደረጋል፡፡ የከተማው ነዋሪ በሰልፉ ምክንያት #ስጋት ውስጥ እንዳይገባ በየክፍለ ከተማው #ውይይት መደረጉ ተገልጿል፤ ህዝቡም ለሰልፉ ሰላማዊነት #የበኩሉን እንዲወጣ ተጠይቋል፡፡

በተጨማሪ፦

የሀዋሳ ከተማ ነዋሪ በማህበራዊ ሚዲያ ከሚሰራጩ #ሀሰተኛ_መረጃዎች ራሱን እንዲያርቅ ጥሪ ቀርቧል። ነዋሪው ምንም አይነት ሰላም የማደፍረስ እንቅስቃሴ ካየ ለፀጥታ ሀይሉ #ጥቆማ እንዲያደርስ ጥሪ ተላልፏል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
"ብቻዬን ብቀር እንኳ #ትግሌን እቀጥላለሁ" ጃል መሮ የኦነግ ጦር አዛዥ
.
.
በመንግሥትና በኦነግ መካከል በሽማግሌዎች አማካይነት የተደረሰውን ስምምነት ተከትሎ በርካታ የግንባሩ አባላት ተሰማርተው ከነበሩባቸው ቦታዎች #በሰላም እየተመለሱ ቢሆንም በምዕራብ ኦሮሚያ የሚንቀሳቀሰው የኦነግ ኃይል አዛዥ ግን ይህንን ለመፈፀም ዝግጁ እንዳልሆነ ገልጿል።

በተለያዩ የኦሮሚያ አካባቢዎች ተሰማርተው የሚገኙ የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ጦር አባላት የአባገዳዎችን ጥሪ ተከትለው #ትጥቅ_ፈትተው ወደ ጦር ካምፖች ከመግባታቸው በፊት ወደተዘጋጁላቸው ጊዜያዊ ማቆያ ስፍራዎች በዚህ ሳምንት እየገቡ እንደሆነ እየተዘገበ ነው።

ሽምግልናውን የመሩትና ስምምነቱ ከፍጻሜ እንዲደርስ ጥረት እያደረጉ ያሉት አባገዳዎች እና የየአካባቢዎቹ ባለስልጣናት ለውሳኔው ተገዢ በመሆን ወደተዘጋጁላቸው ስፍራዎች ከነትጥቃቸው ሲመጡ አቀባበል እያደረጉላቸው ይገኛል።

ይህ በእንዲህ እንዳለም የአባገዳዎችን ጥሪ ተከትሎ ሁሉም የኦነግ ጦር አባላት እየተመለሱ እንዳልሆነ ከተመለሱት የኦነግ ጦር አባላት ተሰምቷል።

ለዚህም እንደምክንያት የሚጠቀሰው የምዕራብ ኦሮሚያ የኦነግ ጦር አዛዥ የሆነው ኩምሳ ድሪባ ወይም በትግል ስሙ በስፋት የሚታወቀው ጓድ መሮ የአባገዳዎችን ጥሪ አለመቀበሉ ነው።

በምዕራብ ኦሮሚያ የሚገኘው የኦነግ ጦር አዛዥ እንደሆነ በስፋት የሚነገርለት ኩምሳ ድሪባ (መሮ) ወይም መሮን ቢቢሲ ስለዚሁ ጉዳይ በስልክ አነጋግሮታል። እንደተባለውም መሮ ባለው ሁኔታ ስምምነቱን ተቀብሎ ለመግባት ዝግጁ እንዳልሆነ ገልጿል።

የአባገዳዎችን ጥሪ ለመቀበል እና እርቅ ለማውረድ ዝግጁ ስለመሆኑ ሲጠየቅም "የእርቅ የተባለው ኮሚቴ እኔን በአካል አግኝተው ለማነጋገር ፍላጎት የላቸውም። ትኩረት ያደረጉት ጦሩን አንድ በአንድ እጁን እንዲሰጥ ማድረግ ላይ ነው" በማለት እሱም እነሱን ለማግኘት ያደረገው ጥረት አለመሳካቱን ይናገራል።

እንዲያውም "ጦሩን የመበታተን ዓላማ ይዘው ነው እየተንቀሳቀሱ ያሉት" ሲል ይከሳል።

የኦነግ ሊቀመንበር የሆኑት አቶ ዳውድ ኢብሳ የእርቅ ኮሚቴውን በመደገፍ የኦነግ ጦር ጥሪውን ተቀብሎ ወደተዘጋጀለት ስፍራ እንዲሄድ መልዕክት ማስተላለፋቸው ይታወሳል። የጦሩ መሪ መሮ የግንባሩ ሊቀመንበር ተገዢ መሆን አለመሆኑን ተጠይቆ ሲመልስ "ሊቀመንበሩ የእርቅ ኮሚቴውን ያሉት፤ 'የኦነግ ጦር የእናንተው ነው። ሂዱና አወያይታችሁ የሚሉትን ስሟቸው' ነው ያሉት" ብሏል።

ጨምሮም እንደተናገረው "እኔ በመሰረታዊ ጉዳዮች ላይ እንወያይ ነው ያልኩት እንጂ የፖለቲካ ፕሮፖጋንዳ ጥቅም የለውም፤ የኦሮሞ ህዝብ መሰቃየት የለበትም ነው የምለው። እነሱ ግን የጦሩ አባላት የእጅ ስልክ ላይ እየደወሉ አንድ በአንድ ጦሩን የማፍረስ ሥራ ነው እየሰሩ የሚገኙት" ሲል ገልጸወል።

ያለው ችግር ከስር መሰረቱ ምፍትሄ አላገኘም ብሎ የሚያምነው መሮ አሁን እየተደረገ ያለው "በተለያዩ ስፍራዎች የሚገኙ ሰዎችን አንድ በአንድ የማስኮብለል ሥራ ነው። ከዚህ የተለየን ጦር 5 በመቶ እንኳ አይሆንም። 95በመቶ አሁንም እንደታጠቀ ነው የሚገኘው" በማለት ተናግሯል።

"ወደፊት መራራ ትግል ማድረጋችንን እንቀጥላለን" ያለው መሮ "ብቻዬን ብቀር እንኳ #ትግል ማድረጌን እቀጥላለሁ እቅዴም ይሄው ነው" በማለት በትጥቅ ትግሉ እንደሚቀጥል ጠንከር በማለት ተናግሯል።

የቀረበውን የእርቅ ጥሪ ተቀብለው ከገቡት የኦነግ አባላት መካከል አንዱ የሆኑት የግንባሩ ጦር የሞራል እና ፖለቲካ መምህር የ57 ዓመቱ የዕድሜ ባለጸጋ አቶ #ታፈሰ_ኦላና በመሮ በኩል ያሉት ወታደሮች እየተመለሱ እንዳልሆነ አረጋግጠዋል።

ጨምረውም "መሮ መመለስ አይፈልግም፤ ስልክ እየደወለ #ጸያፍ_ቃል እየተናገረን ነው። 'እጃችሁን ለአባገዳዎች እየሰጣችሁ ሰዎች ከትግላችን ዓላማ ውጪ የሆነ ተግባር እየፈጸማችሁ ነው። ታሪክ ይፋረዳችኋል' እያለ ያስጠነቅቀናል።"

አቶ ታፈሰ እንደሚሉት አሁንም በምዕራብ ኦሮሚያ ትዕዛዝ የሚሰጠው መሮ መሆኑንና "የኦሮሞን ምድር የጦር አውድማ ማድረግ ነው የሚፈልገው። ህዝብ ሰላም እየፈለገ እሱ ግን አሁንም ደም ማፍሰስ የሚፈልግ ከሆነ ተሳስቷል" ብለዋል።

የኦነግ የምዕራብ ኦሮሚያ ጦር አዛዥ መሮ በአባ ገዳዎች የቀረበውን ጥሪ ተቀብለው ወደተዘጋጀላቸው ስፍራ የሄዱ የጦሩ አባላት ላይ ይሰነዝራል ስለተባለው ማስፈራሪያን በተመለከተ "የምን ማስፈራራት ነው። መሳሪያ ይዘን እያየናቸው እኮ ነው እየሄዱ ያሉት። ምርጫቸው ነው። ማንም ማንንም አላስፈራራም" ሲል ምላሽ ሰጥቷል።

መሮ ችግሩን ለመፍታትም እንደቅድመ ሁኔታ የሚጠይቀው "በደቡብ ኢትዮጵያ እና በተለያዩ ዞኖች ከሚገኙ አባላቶቻችን ጋር በቅድመ ሁኔታዎች ላይ #ውይይት ማድረግ አለብን" በማለት የሽምግልና ኮሚቴውም እንዲያወያያቸውና "አንድ በአንድ የጦሩን አባላት ማስኮብለል" ያለውን ድርጊት ማስቆም እንዳለባቸው ተናግሯል።

የእርቅ ኮሚቴው ጸኃፊ የሆነውን #ጀዋር_መሐመድ በበኩሉ የኮሚቴው አባላት በተንቀሳቀሱባቸው ስፍራዎች ሁሉ የኦነግ የጦር አመራሮችን ለማግኘት ያደረጉት ጥረት የጦሩ አመራሮች ፍቃደኛ ሳይሆኑ በመቅረታቸው ሳይሳካ እንደቀረ ይናገራል።

ጃዋር ''ወደ ምዕራብ ኦሮሚያ የተጓዙት አቶ በቀለ ገርባ እና አባ ገዳ በየነ ሰንበቶ ያደረጉት ሙከራ #አልተሳካላቸውም። ወደ ደቡብ ኦሮሚያ የሄድኩት ደግሞ እኔ ነበርኩኝ። የኦነግ የምዕራብ ዞን የጦር ኃላፊ ሊያገኘን ፍቃደኛ #አልነበረም።'' ሲል ተናግሯል።

ምንጭ፦ BBC አማርኛ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ጠ/ሚር #ዐቢይ_አሕመድ በአሁኑ ሰዓት ከአፋር፣ ከሶማሌ፣ ከሐረሪ፣ ከቤንሻንጉል ጉምዝና ከጋምቤላ ክልል አጋር ፓርቲዎች የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ጋር #ውይይት እያካሄዱ ነው።

#PMOEthiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በአፋር እና በሱማሌ ክልሎች #አዋሳኝ አካባቢዎች ምንም አይነት የፀጥታ ችግር እንዳይከሰት እንደሚሰሩ የሁለቱ ክልል ከፍተኛ ርዕሰ መሰተዳደሮች ገለፁ፡፡

የሱማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ #ሙስጠፋ_መሀመድ እና የአፋር ክልል ርዕሰ መሰተዳደር አቶ #አወል_አርባ ዛሬ በአዲስ አበባ በሁለቱ ክልሎች የፀጥታ ችግር መፍትሄ ዙሪያ ላይ ተወያይተዋል፡፡ በውይይታቸውም በሁለቱ ክልል አዋሳኝ ቦታዎች አንድም ሰው እንዳይሞት እና ግጭት እንዳይከሰት የማድረግ ሰራ እንደሚሰሩ ተናግረዋል፡፡

የሰላም ሚኒስትር ዲኤታው አቶ #ዘይኑ_ጀማል በበኩላቸው ችግር በተፈጠረባቸው አካባቢዎች በአስቸኳይ የሀገር ሽማግሌዎች ቡድን እንዲቋቋምና ችግሩ በዘላቂነት ሊፈታ እደሚገባው ተናግረዋል፡፡ በአጠቃላይ ጉዳይ ላይም በህዝብ ለህዝብ #ውይይት ሊፈታ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ ክልሎቹ #ከማንነት እና #ከወሰን ጋር ያሉ ችግሮችን ዘላቂ መፍትሄ እንዲያገኙ እንደሚሰሩ ተናግረዋል፡፡

Via ebc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከደኢህዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ የተሰጠ መግለጫ፦

የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ደኢህዴን) የክልሉን ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች በሰጡት ህገ-መንግስታዊ የሥልጣን ውክልና ላለፉት ሃያ ስድስት ዓመታት ሕዝቡን በማስተባበር እና በክልሉ ውስጥ ያለውን እምቅ የልማት ፀጋዎች እንዲሁም ውስን የሆነው የካፒታል አቅሞች አቀናጅቶ በመምራት አበረታች ውጤቶችን ማስመዝገቡን ሕዝቡም በየደረጃው
ተጠቃሚ መሆን ስለመቻሉ ሕዝቡ ራሱ የሚመሰክረው ሀቅ ነው፡፡

ይሁን እንጂ አሁንም ቢሆን በርካታ ያልተፈቱ የሰላም፣ የልማት እና የዴሞክራሲ ጥያቄዎች ያሉት መሆኑን ደኢህዴን በተገቢ ሁኔታ ይገነዘባል፡፡
በአገር ደረጃ ለመጣው አዲስ የለውጥ ምዕራፍ ደኢህዴን ከፍተኛ የማይተካ ሚና ተጫውቷል፡፡ የተጀመረው የለውጥ እንቅስቃሴ በትክክለኛ አቅጣጫ እንዲመራ እና ሕዝቡም በለውጡ የተሟላ ተጠቃሚነቱ እንዲረጋገጥ አበክሮም ይሰራል፡፡

በ10ኛው የደኢህዴን ድርጅታዊ ጉባኤ የተቀመጡ አቅጣጫዎች አፈጻጸማቸው የደረሰበትን ደረጃ የድርጅቱ የሥራ አስፈጻሚ እና ማዕከላዊ ኮሚቴ በዝርዝር ገምግሟል፡፡ ከጉባኤ ማግስት ጀምሮ
በኃላፊነት መንፈስ መፍትሄ እና ምላሽ ማግኘት ያለባቸውን ጥያቄዎች በድርጅቱ መሪነት እየተፈጸመ ያለበትን ሁኔታ ፈትሸዋል፡፡ ሥራ አስፈጻሚው እና ማዕከላዊ ኮሚቴው በዝርዝር የገመገማቸውን ጉዳዮች እና በቀጣይ ወራት ርብርብ ማድረግ በሚገቡ ጉዳዮች ላይ በየደረጃው ከሚገኘው የደኢህዴን አመራሮች ጋር ውይይት ለማድረግ ከየካቲት 28 እስከ መጋቢት 1/07/2011 ዓ.ም በክልሉ ርዕሰ መዲና ሀዋሣ ውይይት እየተደረገ ይገኛል፡፡

ይሁን እንጂ ውይይቱ በሰከነ ሁኔታ እየተካሄደ ባለበት የተወሰኑ በብድን የተደራጁ አካላት ውይይቱ አዳራሽ ጭምር በመግባት ህግንና ሥርዓትን ባልተከተለ አግባብ የውይይት መድረኩ እንዲታወክ፣ እንዲቋረጥ እንዲሁም
በአንዳንድ አመራሮች ላይ ድብደባ ፈጽመዋል፡፡ ድርጊቱን የደኢህዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ ጽ/ቤት በጽኑ ያወግዛል፡፡ ሁኔታው ወደ ከፋ ጫፍ እንዳይደርስ የውይይቱ ተሳታፊ አመራሮች ያሳዩትን ኃላፊነት የተሞላበት ትዕግስትና ጨዋነት የደኢህዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ ያደንቃል፡፡

ለውይይቱ መነሻ የተዘጋጀውን ሰነድ አስመልክቶ #የተሳሳቱና #የተዛቡ መረጃዎች ለህብረተሰቡ እየተላለፈ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡ ሰነዱ የትኛውንም የሕዝብ ሁኔታ በአሉታዊና በነቀፌታ የማይገልጽ የድርጅትና የመንግስት ስራዎችን የሚዳስስ፣ በድርጅቱ አሰራርና አካሄድ መሰረት መስተካከልና መጥራት የሚገባቸውን ጉዳዮች፣ የተከሰቱ ችግሮችና መፍትሄዎችን በተገቢው ሁኔታ የሚያሳይ ሰነድ ነው፡፡ በመሆኑም ደኢህዴን የሕዝቦቻችንን ቱባ ባህልና እሴቶቻቸውን የሚያከብር የታገለለትንና በክልላችን እየደመቀ የመጣውን የሕዝቦችን ሁለንተናዊ መብትና ጥቅም ማንነት፣ ቋንቋ፣ እና ትውፊት አክብሮ የሚንቀሳቀስ ሕዝባዊ ድርጅት ነው፡፡ ለዚህም ሁልጊዜ ጽኑ አቋምና የጠራ መስመር ያለው ድርጅት ነው፡፡

ሰነዱ በድርጅቱ ባህል መሰረት ዝርዝር ጉዳዮች #የተፈተሹበትና ችግሮችን አንጥሮ ያወጣ ሰነድ ሲሆን ሰነዱ ላይ የተመላከተው ዝርዝር ግምገማ ያልጣማቸው ግለሰቦች የሚፈጥሩት #ውዥንብር እንደሆነ ደኢህዴን ማስገንዘብ ይወዳል፡፡ ይህ ሰነድ ለበርካታ ቀናት በደኢህዴን ማዕከላዊ ኮሚቴና በሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ዘንድ የሰላ #ውይይት ተደርጎበትና በሁሉም ዘንድ የጋራ መግባባት ተደርሶበት የተዘጋጀ ሰነድና የዳበረ በቀጣይም የድርጅትና የመንግስት ሥራዎችን በክልላችን በሰከነ አግባብ ለመምራት እንዲሁም የክልላችን ሕዝቦች ዘላቂ ጥቅምና መብት የሚያስጠብቅ ሁኔታ ከሁሉም የክልላችን አመራሮች ጋር የጋራ መግባባት ለመፍጠር እና በቀጣይ ለመስራት የተዘጋጀ ሰነድ መሆኑን በአጽንኦት ለማረጋገጥ ይወዳል፡፡

የሲዳማ ሕዝብ ባለው #ኩሩ እና #ቱባ ባህላዊ እሴቶች በባለፉት ሃያ ሰባት ዓመታት ከሌሎች የክልሉ ሕዝቦች ጋር አብሮ የመኖር የዳበረ የእንግዳ ተቀባይነት ባህል ያለው ታላቅ ሕዝብ ነው፡፡ የሲዳማ ብሔር ሌሎች ሕዝቦችን "ዳኤቡሹ" ብለው ተቀብሎ አቅፎ የሚኖር፣ የሚያስተናግድ ታላቅ እንግዳ ተቀባይ ሕዝብ ነው፡፡ ደኢህዴንም ለዚህ ታላቅ ሕዝብ ከፍተኛ አክብሮት አለው፡፡
ሕዝቡም በደኢህዴን መስመር ተጠቃሚ በመሆኑ ኩራት ይሰማዋል፡፡

ይሁን እንጂ ሕዝቡን የማይወክሉ የተወሰኑ ቡድኖች እየተካሄደ የነበረውን የውይይት መድረክ እንዲቋረጥ አድርገዋል፡፡ የትኛውም ጥያቄ በዴሞክራሲያዊ አግባብ በሰለጠነ መንገድ መስተናገድ ሲገባው የኃይል እርምጃን አማራጭ በማድረግ የሚቀርብ ጥያቄ ተቀባይነት የሌለውና ተገቢነት የጎደለው በመሆኑ ደኢህዴን ያወግዛል፡፡ ሕግን የተላለፉ አካላትንም መንግስት ተከታትለው ለሕግ እንዲያርብ ይጠብቃል፡፡ የዜጎች ሕገ መንግስታዊ፣ በነጻነት የመዘዋወር እና የመሰብሰብ መብታቸው ሊከበር ይገባል፡፡

በሀዋሳ እና በሲዳማ ዞን የሚትገኙ የሀገር ሽማግሌዎች፣ ኃይማኖት መሪዎች፣ ሴቶች፣ ወጣቶች እና መላው የህብረተሰብ አባላት ሁኔታዎች እንዳይባባሱ ላሳያችሁት ትዕግስትና ጨዋነት ለተሞላበት ኃላፊነት ደኢህዴን አድናቆቱን ያቀርብላቸኋል፡፡ ይኸው አርአያነት ያለው ተግባራችሁ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ደኢህዴን ሙሉ እምነት አለው፡፡

በውይይቱ መሰነካከልና መስተጓጎል ምክንያት የተረበሻችሁ አመራሮች ድርጅታችሁ ደኢህዴን ታላቅ ይቅርታ ይጠይቃል፡፡ የተቋረጠው ውይይትም ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ደኢህዴን ያረጋግጣል፡፡ በውይይቱ የሚቀመጡ አቅጣጫዎች ለክልላችን ሕዝቦች ተጠቃሚነታቸውና ጥያቄያቸው ምላሽ እንደሚያገኝ ማረጋገጥ እንወዳለን፡፡

ደኢህዴን ወትሮኑም ፈተናዎችን ተጋፍጦ እንደሚያልፈው ሁሉ በቀጣይ ጊዜ ይበልጥ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ለመላው አባሎቻችንና ደጋፊዎቻችን እንዲሁም ለክልላችን ሕዝቦች ለማረጋገጥ እንወዳለን፡፡

የደኢህዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ ጽ/ቤት
የካቲት 29/2011 ዓ.ም
ሀዋሣ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ🔝

"በአሁን ሰዓት የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እና ሰራተኞች ከፕሮፌሰር #መረራ_ጉዲና ጋር ስለሀገሪቱ ወቅታዊ ሁኔታዎች ላይ #ውይይት እያደረጉ ይገኛሉ። የዩኒቨርሲቲው ፕሬዘዳንት የሆኑት ፕሮፌሰር #ደጀኔ_አየለም ተገኝተው ተማሪውን እያወያዩ ነው።" Dagi D.

ፎቶ: ዳጊ እና ጌድዮን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ጠ/ሚር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ ዛሬ ጠዋት ወደ ገደብ ወረዳ በመጓዝ በጊዜያዊ መጠለያ ጣቢያ የሚገኙ #የጌዲዮ ማኅበረሰብ አባላትን ሁኔታ ተዘዋውረው ጎበኙ። ተፈናቃዮቹ #ቅሬታቸውን ለጠ/ሚር ዐቢይ አሕመድ አቅርበዋል። በአሁኑ ሰዓት ጠ/ሚሩ ከተፈናቃዮቹ ተወካዮች ጋር ረጅም #ውይይት እያደረጉ ይገኛሉ። ፌዴራል መንግሥት ከዞንና ክልል አስተዳደር ባለፈው ሳምንት መጀመሪያ በቀረበ ጥሪ መሠረት በብሔራዊ የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን አስተባባሪነት ከመጋቢት 2 ቀን 2011 ጀምሮ አስቸኳይ የምግብና ሌሎችም አስፈላጊ አቅርቦቶችን ለተረጂዎች በማድረስ ላይ ይገኛል፡፡

#PMOEthiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኢንተርን ሀኪሞች...

በጅማ ዩኒቨርስቲ #የኢንተርን_ሀኪሞች ባነሷቸው ጥያቄዎች ዙሪያ አዲሱ #ፕሬዘዳንት/ዶክተር ጀማል አባፊታ/ ከሚመለከታቸው የፌደራል መስሪያ ቤት #ተወካዮች እና ሌሎች አካላት ጋር #ውይይት ያደርጋሉ።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የፍቅር #ጉዟችንን በተመለከተ...

በTIKVAH-ETH በኩል #የተሰባሰቡት ወጣቶች ከሁሉም የሀገሪቱ ክፍል የተውጣጡ ትክክለኛውን የኢትዮጵያ ቀለም የያዙ ናቸው። ሁሉም ወጣቶች እናት ሀገራቸውን የሚወዱ እና በሀገሪቱ ላይ አዲስ ታሪክ ለመፃፍ ከሳምንት እስከ ሳምንት ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ፤ የትምህርት እና የግል ጊዜያቸውን ትተው ለሰላምና ፍቅር የሚጓዙ ናቸው። ለዚህም ሰላም ወዳዱ የኢትዮጵያ ህዝብ #ሊያመሰግናቸው ይገባል።

ዩኒቨርስቲዎችን በተመለከተ፦

#StopHateSpeech በሁሉም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚካሄድ ሲሆን የመጀመሪያው ምዕራፍ ከተማሪዎች ጋር የሚደረግ #ውይይት እና #ንግግር የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ነው። ምክንያቱም ወጣቶች ከጥላቻ እና ከስሜታዊነት ርቀው ሀገር መገንባትና ለህዝብም #ተስፋ የሚሰጡ ዜጎች እንደሆኑ ማስመስከር ስለምንፈልግ ነው።

ይህ ጉዞ እና እንቅስቃሴ ከየትኛውም አይነት የፖለቲካ አመለካከት ነፃ የሆነ፤ ከየትኛውም ድርጅትም ሆነ ቡድን ገለልተኛ የሆነ በወጣቶች የሚደረግ እንቅስቃሴ ነው። ወጣቶቹም ትክክለኛ የሀገሪቱን ቅርፅ የያዙ በፍቅር እና በንግግር የሚያምኑ ሀገሪቷን ከጥላቻ አላቀው ትልቅ ሀገር የመገንባት ህልም ያላቸው ናቸው።

√ወጣቶቹ የሰላምን አርማ ይዘው በየሄዱበት የሚሰብኩት ስለፍቅር እና መተባበር እና መተጋገዝ ብቻ ነው። በሚዘጋጁት መድረኮችም የጥላቻ መዘዞችን ማስገንዘብ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀማቸውን እንዲያሻሽሉ ማስገንዘብ ነው።

√ውይይቶች በጠቅላላ የሚደረጉት #በወጣት የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች #መካከል ብቻ ነው። ሌላው ተናጋሪዎች ተማሪዎች እና የዩኒቨርሲቲው አካላት ብቻ ናቸው።

በቀጣይ ምዕራፍ 2፦ ከዩኒቨርሲቲ #አመራሮች እና #ሰራተኞች ጋር ተመሳሳይ መድረክ ይኖረናል።

ኢትዮጵያን በፍቅር እንገንባ!!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ

በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የተፈጠረው ችግር ዛሬም ድረስ እልባት አላገኘም። እሁድ ምሽት ከነበረው ውጥረት በኃላ ሰኞ ውይይት ለማድረግ ተሞክሮ ነበር በውይይቱ ላይ በተደረሰው ስምምነትም ተማሪዎች ማክሰኞ ጥዋት ትምህርት እንዲጀምሩ ተደርጎ ነበር ነገር ግን ጥያቄዎቻችን አልተመለሱም በሚል ከማክሰኞ ከሰዓት በኃላ እስከአሁን ድረስ ትምህርት እንደተቋረጠ ነው። ዋነኛው የተማሪዎች ጥያቄ እንደሆነ የሰማሁት ሰሞኑን በተቋሙ ከተፈጠረው ችግር ጋር በተያያዘ የታሰሩ ተማሪዎች እንዲፈቱላቸው ነው። እንዲሁም ሌሎች በግቢው ያሉ ችግሮችን የሚመለከተው የፌደራል መንግስት አካላት ከተቋሙ ጋር #ውይይት አድርገው እንዲፈቱ እንደሚፈልጉ ለጉዳዩ ቅርብ የሆነ ሰው ነግሮኛል።

ትኩረት ለድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ‼️
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Somali #Afar #ሰላም #ውይይት

ትላንት የአፋርና የሱማሌ ኢሳ ማህበረሰብ የሰላም ኮንፈረንስ በአዳማ ተካሂዶ ነበር።

የሰላም ኮንፈረንሱ በሁለቱ ማህበረሰብ መካከል ያሉ አለመግባባቶችን በውይይት በመፍታት ዘላቂ ሰላምን ማምጣት ዓላማ ያደረገ ነው መሆኑን ሰላም ሚኒስቴር አሳውቋል።

በአካባቢዎቹ የሚታዩ አለመግባባቶችን በውይይት በመፍታት ሰላምን ለማምጣት ወደ ግጭት ለሚያመሩ ጉዳዮችም መፍትሔዎች ተለይተው የተቀመጡበት መድረክ ነው ተብሏል።

የተዘጉ መንገዶች እንዲከፈቱ ማድረግ፤ በግጭት ምክንያት ከኖሩበት ቀዬአቸው ተፈናቅለው በየመጠለያ ጣቢያ እና በዘመድ አዝማዶቻቸው ቤት ተጠልለው እየኖሩ ችግሮችን እየተጋፈጡ ያሉ ወገኖች ወደ ቀደመው ሰላማዊ ህይወታቸው እንዲመለሱ ሊደረጉ የሚያስፈልጉ ጉዳዮችንም በመድረኩ መነሳቱን ከሰላም ሚኒስቴር በኩል የወጣው መረጃ ያሳያል።

ባለፈው ዓመት በተነሳ ግጭት ከዘጠኝ ወር በላይ ቤታቸው ተፈናውለው በየመጠለያ ጣቢያ እና በየዘመዶቻቸው ቤት የተጠለሉ በርካታ ወገኖች እንዳሉ ይታወቃል።

@tikvahethiopia
#EHRC

" ... ጉዳዩ ከዚህ የበለጠ ሳይባባስ ፓርላማው የመንግስት አስፈፃሚ አካሉን በአስቸኳይ ሊያሳስብ ይገባል " - ዶ/ር ዳንኤል በቀለ

ዛሬ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) የ9 ወራት የእቅድ አፈፃፀሙን ሪፖርት ለህ/ተ/ም/ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አቅርቧል።

በዚህም ወቅት የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ ፥ በአማራ ክልል የሰብዓዊ መብት ጉዳዮች አሳሳቢ እንደሆኑ ቀጥለዋል ብለዋል።

ከቅርብ ጊዜ አንስቶ መንግሥት በአማራ ክልል እያካሄደ ያለው ወታደራዊ እንቅስቃሴ ከሰብዓዊ መብቶች አንፃር በጣም የሚያሰጋነው ሲሉ ገልጸዋል።

ዋና ኮሚሽነሩ ፤ በአሁን ወቅት በአማራ ክልል እየተካሄደ ባለው ወታደራዊ እንቅስቃሴ #በሲቪል ሰዎች ላይ ፦
- የሞት፣
- የንብረት መውደም፣
- የመፈናቀል ጉዳት መድረሱን በዚህም የሰብዓዊ መብት ስጋቱም መቀጠሉን አንስተዋል።

" መንግሥት የፀጥታ እርምጃ በአማራ ክልል በማካሄድ ላይ የሚገኝ መሆኑን አሳውቋል ፤ " ያሉት ዶ/ር ዳንኤል " ነገር ግን ይህ ወታደራዊ እርምጃ የሰብዓዊ መብት እንድምታ ስላለው ፣ የሰብዐዊ መብት ተፅእኖ ስለሚፈጥር ይሄን በቅርበት እየተከታተልን ነው " ብለዋል።

" እስካሁን ባለው መረጃ በመነሳት ከሰብዓዊ መብቶች አንፃር በጣም የሚያሰጋ ስለሆነ ኢሰመኮ #ውይይት እና #ሰላማዊ መፍትሄ አስፈላጊነትን አበክሮ በማሳሰብ ጉዳዩ ከዚህ የበለጠ ሳይባባስ ፓርላማው የመንግስት አስፈፃሚ አካሉን በአስቸኳይ ሊያሳስብ ይገባል። " ሲሉ አክለዋል።

ከዚህ በተጨማሪ ዶ/ር ዳንኤል ባቀረቡት ሪፖርት የዘፈቀደ እስር ፣ ሰዎች ሲታሰሩ የሚያዙበት መንገድ፣ ለሰብዓዊ ጉዳዮች አሳሳቢ ሆኖ ቀጥሏል ብለዋል።

ዶ/ር ዳንኤል ፤ " በተለያዩ አካባቢዎች የሚፈፀመው የዘፈቀደ እስር እና በእስር ወቅት የሚፈፀሙ ተገቢ ያልሆኑ አያያዞች / አንዳንድ ቦታዎች ድብደባን ጨምሮ ተገቢ ያልሆነ አያያዝና እስራት እንዲሁም የፍርድ ቤት ትዕዛዝ አለመከበርም ቀጥሏል "  ብለዋል።

ዋና ኮሚሽነሩ ፤ አንዳንድ ቦታዎች ላይ የሚፈፀሙት የዘፈቀደ እስሮች #የቤተሰብ አባላትን ጭምር ለማጥቃት የሚውሉ ናቸው ሲሉ ለፓርላማው በሪፖርታቸው አሳውቀዋል።

@tikvahethiopia
" አሁንም ያለው ችግር በውይይት እና በድርድር የሚፈታበት መንገድ ዝግ ባለመሆኑ ተከታታይ ጥረቶች ይደረጋሉ " - የብሔራዊ መረጃ እና ደህንነት

የብሔራዊ መረጃ እና ደህንነት አገልግሎት ዛሬ ምሽት መግለጫ አውጥቶ ነበር።

በዚሁ መግለጫው በአማራ ክልል ያለው ችግር አሁንም በ #ውይይት እና በ #ድርድር የሚፈታበት መንገድ ዝግ እንዳልሆነ ጠቁሟል።

መ/ቤቱ በመግለጫው ፤ " ከድርድር እና ውይይት ይልቅ መንግሥታዊ ሥልጣንን በኃይል ለመያዝ የሚጥሩ እንዲሁም አጋጣሚዎችን በማቀነባበር ዝርፊያ ለመፈጸም የሚፈልጉ የታጠቁ ቡድኖች፣ ፅንፈኛና አክራሪ ኃይሎች ከውጭ ፀረ ሰላም ኃይሎች ጋር በመቀናጀት ሀገራዊ የጸጥታ ሥጋት ለመደቀን ሙከራ እያደረጉ ነው " ብሏል።

በአማራ ክልልም እየታየ ያለው ሁኔታ ይኸው ነው ሲል ገልጿል።

" ከኢ-መደበኛ አደረጃጀቶች ጋር በተያያዘ የተከሰቱ ችግሮች በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱ ጥረቶች ቢደረጉም ችግሩ በሚፈለገው ልክ አልተፈታም " ያለ ሲሆን ፤ " ለዘረፋ የተደራጁ ጥቂት ኃይሎች አሁን ላይ መንግሥታዊ መዋቅሮች እንዲፈርሱ፤ የፋይናንስ ተቋማት አገልግሎት እንዲቋርጡ፤ አንዳንድ ከፌዴራል መንግሥት ጋር የሚያገናኙ የመንገድ መሠረት ልማቶች እንዲዘጉ በማድረግ፤ ሕዝቡ ላይ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ጫና ለመፍጠር ሙከራ እያደረጉ ይገኛሉ " ብሏል።

ብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ፤ አስቸኳይ ጊዜ አዋጁን የሚያስፈፅመው የጠቅላይ መምሪያ ዕዝን በማስተባበር የክልሉን ሰላምና ደኅንነትን በአጭር ጊዜ ለማረጋገጥ የሚያግዝ ስምሪት ወስዶ እየሠራ መሆኑን ገልጾ " በማወቅም ይሁን ባለማወቅ ሕገወጥ እንቅስቃሴ ውስጥ እየተሳተፉ ያሉ ግለሰቦችና ቡድኖች ከድርጊታቸው ይቆጠቡ " ሲል አሳስቧል።

አሁንም በአማራ ክልል ያለው ችግር #በውይይትና #በድርድር የሚፈታበት መንገድ ዝግ ባለመሆኑ ተከታታይ ጥረቶች ይደረጋሉ ሲል አሳውቋል።

" ለዝርፊያ ከተደራጁ ቡድኖች ጋር የሚንቀሳቀሱ አካላት ካሉ ግን አስፈላጊው እርምጃ እንደሚወሰድ እና ሕግ የማስከበር ሂደቱ ተጠናክሮ ይቀጣላል " ሲል ገልጿል።

@tikvahethiopia
#AmharaScholarsCouncil

በአማራ ክልል የምሁራን መማክርት ጉባኤ በላከልን መግለጫ ፤ በክልሉ ውስጥ አሁን የተፈጠረው ቀውስ በዘላቂነት የሚፈታው በውይይት መሆኑን ገልጾ መንግስትና የታጠቁ ሀይሎች ተኩስ አቁመው እንዲወያዩ ጥሪ አቅርቧል።

ጉባኤው  በመግለጫው ፤ " ሕዝባችን ባለፉት አመታት ተደጋጋሚ የሆኑ ማንነትን መሰረት ያደረጉ ግፎች እና በደሎች እየደረሱበት ይገኛል " ብሏል።

ይህንን ለማስቆምና መሠረታዊ ጥያቄዎቹ መልስ እንዲያገኙ በተደራጀ መልኩ መታገል እንደሚያስፈልግ ገልጿል።

ይህ አይነቱ ፖለቲካዊ ትግል ዘላቂ መፍትሔ እንዲያስገኝ በ #መነጋገር እና በ #ውይይት ላይ የተመሠረተ ሊሆን እንደሚገባው አስገንዝቧል።

" በዚህ ረገድ ባለፉት አመታት በርካታ ጥረቶች ተደርገዋል " ሲልም ገልጿል።

የአማራ ምሁራን መማክርት ጉባኤ፤ " ዛሬ ሕዝባችን ዘር የሚዘራበትና የማዳበሪያ እና ምርጥ ዘር ዕጥረቱን ለመቀነስ አይን አይን እያየበት ያለበት ወቅት ነው። በተጨማሪም ትላንት አብረውት ተሰልፈው የተዋደቁ ኃይሎች ዛሬ ከሀገር መከላከያ ሠራዊት ጋር የሚጋጩበት ሁኔታ ሊፈጠር አይገባም። " ብሏል።

ስለሆነም ክልሉ ውስጥ አሁን የተፈጠረው ቀውስ በዘላቂነት የሚፈታው በውይይት መሆኑ ታውቆ መንግስትና የታጠቁ ሀይሎች ተኩስ አቁመው እንዲወያዩ ጥሪ አቅርቧል።

በየአካባቢው ያሉ የሀገር ሽማግሌዎች የሀይማኖት አባቶች እና ምሁራን ሰላም እንዲሰፍን ችግሮች በውይይት እና በሰላም እንዲፈቱ የበኩላቸውን ጥረት እንዲያደርጉ ጥሪውን አስተላልፏል።

(መግለጫው ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia