TIKVAH-ETHIOPIA
1.39M subscribers
54.8K photos
1.37K videos
198 files
3.65K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update የሰኔ 16ቱ የቦንብ ጥቃት⬇️

በሰኔ 16ቱ የመስቀል አደባባዩ ላይ የተወረወረ አይነት ተመሳሳይ #ቦምብ በተጠርጣሪ መኖሪያ ቤት ውስጥ ማግኘቱን መርማሪ ፖሊስ አስታወቀ።

መርማሪ ፖሊስ ዛሬ በተረኛ የጊዜ ቀጠሮን በሚመለከተው የፌደራል የመጀመሪያ ፍርድ ቤት 1ኛ ተረኛ ወንጀል ችሎት በቀረቡ ስድስት ተጠርጣሪዎች ላይ የደረሰበትን የምርመራ ደረጃ ለፍርድ ቤት ባስረዳበት ወቅት ተመሳሳይ ቦምብ ማግኘቱን አስታውቋል።

ከዚህ በተጨማሪም መርማሪ ፖሊስ ከሰኔ 16ቱ የጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ ድጋፍ ሰልፍ ላይ የከቦምብ ፍንዳታ ጋር በተያያዘ ተጠርጥራ በአማኒኤል ሆስፒታል ከአይምሮ ህመም በህክምና ላይ የምትገኘውን የህይወት ገዳን ምርመራን ማቋረጡንም በዛሬው ችሎት አብራርቷል።

በችሎቱ በቀዳሚነት የተጠርጣሪ በየነ ቡላና የአብዲሳ መገርሳን የተደረሰውን የምርመራ ደረጃ አዳምጧል።

መርማሪ ፖሊስም በርካታ የምርመራ ስራዎችን ማከናወኑን በመጠቆም ተጨማሪ የኤፍ ቢ አይ የቴክኒክ ምርመራ ውጤትን እና መሰል ማስረጃዎቸን ለመቀበል ተጨማሪ የ14 ቀን ጊዜ ቀጠሮ ጠይቋል።

የተጠርጣሪ አብዲሳ መገርሳ ጠበቃ በበኩላቸው የተጠረጠረበት ጉዳይ ስለፍንዳታው ለግብረ አበሮቹ ሪፖርት አድርገሃል ተብሎ ነው።

ረጅም ጊዜ ምርመራው የሚወስድ አይደለም ጉዳዩም ዋስትና የሚያስከለከል ባለመሆኑ በዋስ ሊወጣ ይገባል ሲሉ የፖሊስን ተጨማሪ ጊዜ ተቃውመዋል።

ተጠርጣሪ በየነ ቡላ በበኩሉ እኔ በፍቼ ነው የተያዝኩት ሆን ተብሎ እኔን ለማጥቃት የሚደረግ ድርጊት ነው በማለት ከዘርና ከፖለቲካ ጋር አያይዘው ላቀረቡት አስተያየት ፍርድ ቤቱ በችሎት ህጋዊ ድርጅትን መዝለፍ አይፈቀድም ሲል ንግግራቸውን አስቁማል።

ፍርድ ቤቱም ተጠርጣሪዎች ላይ የተገኘ ተጨባጭ ማስረጃ እንዳለ መርማሪ ፖሊስ እንዲያበራራ ጠይቋል።

መርማሪ ፖሊስም ከፍተኛ አመራሮች የሚገኙበት የድጋፍ ሰልፍ በመሆኑ በዋናነትም ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድን ለመግደል እና ሌሎች ከፍተኛ ባለሰልጣኖች ላይ ጥቃት ለመሰንዘር የታቀደና የተሞከረበት ይህ ድርጊትን በ160 ንጹሃን ዜጎች ላይ የአካል
ጉዳትና የሁለት ሰው ሞት እና ቤተሰቦቻቸውን ማሰብ ያሰፈልጋል ብሏል።

ይህ የወንጀል ድርጊት ከላይኛው አመራር እስከ ታቸኛው አመራር ድረስ ተሳትፎ ያለበት መሆኑን ፖሊስ ጠቅሷል።

በየነ ቡላን በተመለከተ ከሌሎች ከተጠረጠሩ ግብረ አበሮች ጋር በመሆን ቦምቡን እንዴት እንደሚያፈነዱ በመነጋገር በማመቻቸት ቦምቡ
እንዲፈነዳ ማስደረጉን የሚጠቁም ማስረጃ እንዳለው ገልጿል።

ሁለተኛ ተጠርጣሪ አብዲሳ መገርሳም ከቦምብ ፍንዳታው በኋላ ፍንዳታው ጉዳት ማን ላይ እንደደረሰና የቦምቡን ጉዳት ሁኔታ ለግብረ አበሮቹ ሪፖርት ማደረጉን የሚያመላከት ማስረጃ አለኝ ሲል ዋስትናቸውንም ተቃውሟል።

የሁለቱንም ጉዳይ የተከታተለው ፍርድ ቤቱ ምርመራው ውስብስብና የወንጀል ድርጊቱ ከባድ ጊዜ የሚጠየቅ መሆኑን በመጥቀስ ለመርማሪ ፖሊስ ምርመራውን አጠናቆ ለመጨረሻ እንዲቀርብ ፖሊስ የጠየቀውን የ14 ቀን ተጨማሪ ጊዜን ፈቅዷል።

በሁለተኛ ደረጃ ችሎቱ የተመለከተው የእነ አብዲሳ ቀነኔ፣ ደሳለኝ ተስፋዬ፣ ጌቱ ግርማና ባህሩ ቶላን ጉዳይ ሲሆን፥ መርማሪ ፖሊስ ከእነዚህ ተጠርጣሪዎች ጋር አብራ ምርመራ ሲከናወንባት የነበረችው ህይወት ገዳ ጉዳይን ማቋረጡን አስታውቋል።

በተመሳሳይ የምራመራ ስራውን ማከናወኑን በመግለጽ ከኤፍ ቢ አይ የቴክኒክ ምርመራን እና መስል ማስረጃን ለማቀረብ የ14 ቀን ጊዜ እንዲሰጠው ጠይቋል።

የአብዲሳ ቀነኔ ጠበቃ በበኩላቸው አብዲሳ የተያዘው ሰው ለመጠየቅ አቤት ሆስፒታል በሄደበት ጊዜ እንጂ ድርጊቱን አልፈፀመም ፖሊስ የድርጊቱ መፈጸምን የሚያሰረዳ ማስረጃ መዝገቡን አቅርቦ ሊያሳይ ይገባል ፖሊስ ምስክር እንዲሆነን የሚያቀርበው ጥያቄ ተገቢ አይደለም ሲሉ በዋስ ሊወጣ ይገባል ሲሉ የፖሊስ ተጨማሪ ጊዜ ጥያቄን ተቃውመዋል።

በተመሳሳይ ሌሎች ተጠርጣሪዎችም የተጨማሪ ጊዜን በመቃወም ከድርጊቱ ጋር ግንኙነት የለንም በማለት ዋስትና እንዲፈቀድላቸው ፍርድ ቤቱን ጠይቀዋል።

ፍርድ ቤቱም የተጠርጣሪዎቹን የተጠረጠሩበት ድርጊት በማስረጃ መረጋገጡን ፖሊስ እንዲያሰረዳ በጠየቀው መሰረት ፖሊስ ጌቱ ግርማ
መኖሪያ ቤት ውስጥ በሰኔ 16 የመስቀል አደባባዩ የቦምብ ጥቃት ለማድረስ የተወረወረ አይነት ተመሳሳይ ቦምብ መገኘቱን ገልጿል።

#አብዲሳ_ቀነኔ ባለው የህክምና ሙያ ተጠቅሞ ቦምቡን አፈንድቶ በራሱ ላይም ጉዳት የደረሰበትን ለማስመለጥ አቤት ሆስፒታል ሄዶ በጀርባ በኩል ለማስመለጥ ነርሶችን ሲያግባባ እንደነበርና ለዚሀም ማስረጃ እንዳለው ፖሊስ ገልጿል።

ተጠርጣሮዎቹ ቦምንቡን ለማፈንዳት እንዴት፣ የትና በምን ሁኔታ የሚለውን ጉዳይ አስቀድመው መረጃ የተለዋወጡበትን ሆነ ከፈነዳ በኋላ
የተለዋወጡበት መረጃም ሆነ ሌሎች ማስረጃዎች አሉኝ ሲል አብራርቷል።

ጉዳዩን የተከታተለው ፍርድ ቤትም ምርመራው ውስብስብና የወንጀል ድርጊቱ ከባድ ጊዜ የሚጠየቅ መሆኑን በመጥቀስ ለመርማሪ ፖሊስ ምርመራውን አጠናቆ ለመጨረሻ ጊዜ እንዲቀርብ ፖሊስ የጠየቀውን የ14 ቀን ተጨማሪ ጊዜን ፈቅዷል።

የምርመራ መዝገቡን ከሁለት ቀን በፊት አቀርቦ እንዲያሳይ አዟል።

©ፋና
@tsegbwolde @tikvahethiopia
#update የሰኔ 16ቱ የቦንብ ጥቃት⬇️

በሰኔ 16 ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶክትር #አብይ_አህመድ የድጋፍ ሰልፍ ላይ #ቦምብ በመወርውር በማቀበል የተጠረጠሩ ጥላሁን ጌታቸውና ብርሃኑ ጃፋር ላይ ፍርድ ቤቱ የመጨረሻ የክስ መመስረቻ ጊዜ ሰጠ፡፡

ቀደም ሲል አቃቢ ህግ በሁለቱ ተጠርጣሪዎች ላይ በቦምብ ጉዳት የደረሰባቸው ተጨማሪ ቃል ለመቀበልና የስልክ ልውውጥ ማስረጃን እንዲሟላ ለመርማሪ ፖሊስ መዝገቡን መመለሱንና ማስረጃዎችንም ለሟሟላት ጊዜ መስጠቱ የሚታወስ ነው፡፡

በዚህ መሰረት በዛሬው ዕለት መርማሪ ፖሊስ ለፌደራል የመጀመሪ ደረጃ አንደኛ ተረኛ ወንጀል ችሎት ተጨማሪ ማስረጃውን አሟልቶ አጠናቆ ለአቃቢ ህግ መመለሱን አስረድቷል፡፡

የፌደራል ጠቅላይ አቃቢ ህግ በበኩሉ የምርመራ መዝገቡን መቀበሉን በመግለጽ ይህንን ተጨማሪ ጊዜ ይሰጠኝ በማለት ፍርድ በቱን ጠይቋል፡፡

እስከዚያውም አቃቤ ህግ ተጠርጠሪዎቹ በእስር እንዲቆዩ በማለት ፍርድ ቤቱን ጠይቋል፡፡

ተጠርጣሪ ጥላሁን ጌታቸውም ጨለማ ቤት እንደሚገኝ እንዲሁም በቦምብ አደጋ የደረሰብኝ በመሆኑ ህክምና እያገኘሁ አይደለም ሲል በዋስ ልወጣ ይገባል በማለት ፍርድ ቤቱ ጥያቄውን አቅርቧል፡፡

መርማሪ ፖሊስም በባለሙያ እየተደገፈ አቤት ሆስፒታል ህክምና እንዲያገኝ እየተደረገ መሆኑን በመግለጽ ለዚህም የተያዘ ቃለጉባዔ መኖሩንም ገልጿል፡፡

ጨለማ ቤት የተባለውም ጉዳይ ሐሰት መሆኑንና በአሁኑ ወቅት ጨለማ ቤት የሚባል እስር ቤት እንደሌለ ፖሊስ ለችሎት አስረድቷል፡፡

ተጠርጣሪ ብርሃኑ ጃፋር በበኩሉ እኔ ከተያዝኩ ብዙ ቀናትን ያስቆጠርኩ በመሆኑ እንዲሁም በተደጋጋሚ የጊዜ ቀጠሮ የተጠየቀብኝ ሲሆን አሁን የጊዜ ቀጠሮ ሊሰጥ አይገባም በማለት የዋስትና ይፈቀድልኝ ሲል ፍርድ ቤቱን ጠይቋል፡፡

አቃቢ ህግም ተጠርጣሪዎቹ የፈጸሙት ወንጀል ከባድና ውስብስብ እንዲሁም በርካታ ዜጎች ላይ ጉዳት ማድረሱ ለሁለት ሰዎች ህልፈት ምክንያት በመሆኑ ዋስትና ሊፈቀድላቸው አይገባም በማለት ጥያቄያቸውን ተቃውሟል፡፡

የሁለቱን ክርክር ያደመጠው ፍርድ ቤትም የዋስትና ጥያቄያቸው በማለፍ ጥላሁን ጌታቸው ላይ እስከ መስከረም 10 ባለው ጊዜ ውስጥ #ክስ እንዲመሰርት ብርሃኑ ጃፋር ላይ ደግሞ እስከ መስከረም ዘጠኝ ቀን የክስ መመስረቻ ጊዜ ፈቅዷል፡፡

©fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ፌደራል ፖሊስ⬇️

የህዝቡን #ደህንነት እና #ሰላም ለመጠበቅ ሲል መንግስት አስፈላጊውን #እርምጃ እንደሚወስድ የፌደራል ፖሊስ ገለፀ።

የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ከሚሽነር ጀነራል ዘይኑ ጀማል በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ዛሬ መግለጫ ሰጥተዋል።

በመግለጫቸው ላይ የመንግስት ትእግስት #ገደብ እንዳለው በመግለፅ #ጉልበተኞችን እንደማይታገስ አስታውቀዋል።

አሁን ላይ እየተስተዋሉ ያሉት #ሁከቶች #በሁለት የፖለቲካ ድርጅቶች ስም የተቀነባበሩ መሆናቸውን ኮሚሽነር ጀነራሉ ጠቁመዋል።

ባለፉት ሦስት ቀናት በቡራዩና አካባቢው ብዛት ያላቸው ወንጀለኞች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን በመጠቆም፥ በተለያዩ ቦታዎች ተዘርፈው የነበሩ ንብረቶችን የማሰባሰብ ስራ መሰራቱንም ነው ያስታወቁት።

በአጠቃላይም በቡራዩ ከ300 አስከ 400 የሚደርሱ ተጠርጣሪዎች ሲያዙ በአዲስ አበባ ደግሞ ከ300 በላይ ተጠርጣሪዎች መያዛቸውን ገልጸዋል፡፡

በአዲስ አበባ #ገንዘብ ተከፍሏቸው ብሄርን ከብሄር ለማጋጨት እንዲሁም ብሄርን መሰረት ያደረጉ ስድቦችንም ጭምር በማሰራጨት #የተጠረጠሩ ግለሰቦች መያዛቸውንም አንስተዋል።

ይህ ድርጊት #በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባና በአርባ ምንጭ መታየቱን ጠቅሰዋል።

ኮሚሽነሩ በቡራዩና አካባቢው የተፈፀመውን ግድያ ለማውገዝ በርካታ ሰላማዊ ሰው መውጣቱን ጠቅሰው #የተወሰኑ ቡድኖች ግን አዝሚሚያቸው ሌላ ነበር ብለዋል።

ከእነዚህ የተወሰኑ ግለሰቦች መካከልም #ቦምብ ይዘው የነበሩ በህብረተሰቡ ትብብር መያዛቸውን ገልጸዋል።

ከዚህ በተጨማሪም በፒያሳና በመርካቶ #ለዝርፊያ የሚቃጡ ግለሰቦች እንደነበሩ ነው የጠቀሱት።

የተወሰኑት የጸጥታ ኃይሎች ደግሞ ጠብመንጃ ለመንጠቅ ሙከራ ያደረጉ ሲሆን በዚህም ከጸጥታ ኃይሉ ጋር #ግብግብ ገጥመው ነበር ብለዋል።

ይህንንም ተከትሎ የአምስት ሰዎች ህይወት ያለፈ ሲሆን፥ ቁጥራቸው ያልታወቁ ሰዎች መቁሰላቸውን ገልጸዋል።

በአጠቃላይ ይህ ግርግር ሆን ተብሎ የተጀመረውን ለውጥ #እንዳይሳካ #ታስቦበት የተከናወነ መሆኑን ነው ያነሱት።

©fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የሰኔ 16ቱ የቦንብ ጥቃት⬇️

ጠቅላይ አቃቢ ህግ በሰኔ 16ቱ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር #አብይ_አህመድ በተደረገው የድጋፍ ሰልፍ ላይ #ቦምብ አፈንድተዋል ያላቸው አምስት ግለሰቦች ላይ #ክስ መሰረተ፡፡

አምስቱ ግለሰቦች ጌቱ ግርማ፣ ብርሃኑ ጃፈር፣ ጥላሁን ጌታቸው፣ ባህሩ ቶላ እና ደሳለኝ ተስፋዬ ናቸው አቃቤ ህግ ቦምብ በማፈንዳት ወንጀል ክስ የመሰረተባቸው፡፡

ክሱ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተረኛ ወንጀል ችሎት የተከፈተ ሲሆን ክሱን ለእያንዳንዳቸው በችሎት እንዲደርስ ይደረጋል ተብሏል፡፡

የጠቅላይ አቃቤ ህግ እንደሚያመላክተው አንደኛ ተከሳሽ ጌቱ ግርማ ከሁለተኛ ተከሳሽ ጋር ሱሉልታ ላይ በመገናኘት ሰልፉን የጠራው ገለልተኛ ወገን ሳይሆን ኢህአዴግ ነው ኤችአር 128 የተባለውን በአሜሪካ ኮንግረስ የተላለፈውን ውሳኔ ተግባራዊ እንዳይሆን ያደርጋል የሚል ምክንያቶችን በመግለጽ ቦምቡን #በመወርወር እንዲበተን እናድርግ በማለት እንዲዘጋጅ መግለጹን በክሱ ተመላክቷል፡፡

ለሦስተኛ ተከሳሽ #ደውሎም ቦምብ የሚወረውር ሰው አንዲፈልግ ተልዕኮ መስጠቱ በክሱ ተጠቅሷል፡፡

ሁለተኛ ተከሳሽ ብርሃኑ ጃፈር ደግሞ በሚያዝያ ወር 2010 ዓመተምህርት ሁለት ኤፍ 1 እና አንድ የጭስ ቦምብ ያለው መሆኑን ለአንደኛ ተከሳሽ መግለጹን የጠቀሰው አቃቤ ህግ ሱሉልታ ከተማ ተገናኝተው ቦምቡን የድጋፍ ሰልፉ ላይ በመወርወር ጥቃት ለማድረስ በመነጋገር ቦምቡን መወርወር የሚችሉ ልጆች እንዲዘጋጁ ከአንደኛ ተከሳሽ ጋር ተነጋግረዋል ሲል አቃቤ ህግ በክሱ ጠቅሷል፡፡

ሦስተኛ ተከሳሽ ጥላሁን ጌታቸው በድጋፍ ሰልፉ ላይ ቦምብ እንዲያፈነዳ በአንደኛ ተከሳሽ ተገልጾለት ለአራተኛ ተከሳሻ በመደወል ቦምብ ለመወርወር ማቀዱን በመግለጽ በጉዳዩ ላይ #ለመወያየት እንዲገናኙ ማድረጉ ተገልጿል፡፡

አራተኛ ተከሳሽ ባህሩ ቶላ በአንደኛ ተከሳሽ አማካኝነት መስቀል አደባባይ ቦምቡን ለመወርወር ማቀዱን በመጥቀስ በሁኔታው ለመወያየት #አስኮ የተቀጣጠሩ ሲሆን ከዚያም ቡራዩ ላይ በአምስተኛ ተከሳሽ ቤት ተገናኝተዋል፡፡

ከተገናኙ በኋላም በአምስተኛ ተከሳሽ ቤት ያደሩ ሲሆን አንደኛ እና ሁለተኛ ተከሳሾች በሰኔ 16 2010 ዓመተምህረት ከንጋቱ 11፡00 ሰዓት ላይ ሁለተኛ ተከሳሽ በሚያሽከረክረው የሰሌዳ ቁጥር ኮድ2 262335 አዲስ አበባ በሆነ መኪና ውስጥ ሁለት ኤፍ 1 ቦምብ እና አንድ የጭስ ቦምብ በመያዝ አንደኛ ተከሳሽ ቤት ማስቀመጣቸውን በክሱ ተጠቅሷል፡፡

ያስቀመጡትን ቦምብም በዚሁ ተሸከርካሪ ጭነው አዲስ አበባ ውንጌት አካባቢ ከሦስተኛ፣ ከአራተኛ እና ከአምስተኛ ተከሳሽ ጋር በመገናኘት ፒያሳ አካባቢ የገቡ ሲሆን በምን መልኩ ጥቃቱን ማድረስ እንዳለባቸው መወያየታቸውም ተገልጿል፡፡

እንዲሁም በዕለቱ የዶክተር አብይ አህመድ ምስል ያለበትን ቲሸርት ገዝተው እንዲለብ ሱ በማድረግ በተጠቀሰው መኪና ቴዎድሮስ አደባባይ ድረስ በመሸኘት ቦምቡ እንዲፈነ ዳ ተልዕኮ በመስጠት የተመለሱ ሲሆን ሦስተኛ፣ አራተኛ እና አምስተኛ ተከሳሾች በተሰጣቸው ተልዕኮ መሰረት ከሰልፈኞች ጋር በመቀላቀል ሦስተኛ ተከሳሽ በሐራምቤ አቅጣጫ በማድረግ ወደ መስቀል አደባባይ መግባቱ የተጠቀሰ ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ንግግር አድርገው ሲጨርሱ ከመድረኩ በቅርብ ርቀት ላይ በመገኘት ቦምቡን ወርውሮ ማፈንዳቱን አቃቢ ህግ ጠቅሷል፡፡

በዚህም ሙሳ ጋዲሳና ዮሴፍ አያሌው የተባሉ ግለሰቦች በፍንዳታው ህይወታቸው ማለፉን በክሱ ተጠቅሷል፡፡

በፍንዳታው ከ163 በላይ በሆኑ ንጹሃን ግለሰቦች ላይ ከባድና ቀላል ጉዳት አድርሰውባቸዋል ተብሏል፡፡

©fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ሰኔ 16ቱ ጥቃት⬇️

በሰኔ 16ቱ የቦምብ #ፍንዳታ ተጠርጥሮ በእስር ላይ በሚገኘው የብሄራዊ መረጃ ደህንነት መምሪያ አዛዢ #ተስፋዬ_ኡርጌ ፖሊስ በቢሮው አገኘሁት ያለወን #ቦምብ መስቀል አደባባይ ከፈነዳው ቦምብ ቅሪት አካል ጋር ለማመሳከር ጊዜ ይሰጠኝ ሲል ፍርድ ቤቱን ጠይቋል።

የፌዴራል የመጀመሪያ ፍርድ ቤት ተረኛ ወንጀል ችሎት በዛሬ ውሎው ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ የጠየቀበትን ምክንያትና የተጠርጣሪውን አስተያየት አዳምጧል።

መርማሪ ፖሊስ ምርመራችንን አጠናቀን ለፌዴራል አቃቢ ህግ ያስረከብን ቢሆንም አቃቢ ህግ መስከረም 15 ቀን 2011 ዓመተ ምህረት አቶ ተስፋዬ ኡርጌ ቢሮ ውስጥ ያገኘነውን ቦንብ መስቀል አደባባይ ከፈነዳው ቦምብ ቅሪት አካል ጋር በቴክኒክ ለማመሳከር ተጨማሪ ማስረጃ ይቅረብልኝ ማለቱን ተከትሎ ለፌዴራል ፖሊስ ፈንጅ አምካኝ ኦፕሬሽን ዲቪዢን ደብዳቤ ልከናል ሲል አብራርቷል።

ይህንን የቴክኒክ ምርመራ ምላሽ ለማቅረብ ተጨማሪ ጊዜ ይሰጠኝ ብሏል።

ጉዳዩ ያለ አግባብ እየተራዘመ መሆኑን የገለጹት አቶ ተስፋዬ ኡርጌ በበኩላቸው ፍርድቤቱ አጭር ቀጠሮ ሰጥቶ ለመጨረሻ ትዛዝ ይስጥልኝ ሲሉ ጠይቀዋል።

ፍርድቤቱም በተጠየቀው የጊዜ ገደብ የቴክኒክ ምርመራው ለምን #አልተጠናቀቀም የሚል ጥያቄ ያቀረበ ሲሆን፥ ፖሊስም ደብዳቤ ልከን ምላሽ ስላልተሰጠ እየጠበቅን ነው ሲል አብራርቷል።

የፌዴራል የመጀመሪያ ፍርድቤት ተረኛ ወንጀል ችሎትም ፖሊስ ለመጨረሻ ጊዜ የቴክኒክ ምርመራውን ይዞ እንዲቀርብ ለተጨማሪ ስምንት ቀን ቀጠሮ በመስጠት ለጥቅምት አራት(4) ቀን ተለዋጭ ቀጠሮ ሰቷል።

ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ያማል---እጅግ በጣም ያማል‼️

በዚህ ሳምንት #የመን ርዕሠ-ከተማ #ሰነዓ ውስጥ በሁለት ትምሕርት ቤቶች አቅራቢያ በተጣለ #ቦምብ 14 ህጻናት መገደላቸዉን የተመድ #የህጻናት መርጃ ድርጅት ዩኒሴፍ አወገዘ።

የድርጅቱ የመካከለኛ ምሥራቅ እና የሰሜን አፍሪቃ ክፍል ሃላፊ ጊርት ካፔላሬ እንዳሉት ህጻናትን መግደል እና አካለቸዉን ማጉደል የህጻናትን መብቶች የሚጻረሩ እጅግ ከባድ ወንጀሎች ናቸው። እርምጃው ወላጆችም ልጆቻቸውን ወደ ትምሕርት ቤት እንዳይልኩ የሚያደርግ መሆኑን ጠቅሰዋል። በጥቃቱ ሌሎች 16 ተማሪዎች ጉዳት ደርሶባቸዋል። አብዛናዎቹ እድሜያቸው ከ9 ዓመት በታች ነው። #ሰንአ ሆስፒታል የህክምና እርዳታ ከሚደረግላቸው ክፉኛ ከተጎዱት ውስጥ በአስጊ ሁኔታ ላይ የሚገኙም እንዳሉ ገልጸዋል።

ባለፈው እሁድ የየመን አማጽያንን የሚወጋው ሳዑዲ መራሹ ህብረት ሰንአ ውስጥ በመኖሪያ አካባቢዎች ላይ ባካሄደው የአየር ድብደባ ቢያንስ 11 ሰላማዊ ሰዎች መገደላቸውን በኢራን ይደገፋሉ የሚባሉት የሁቲ አማጽያን ተናግረዋል። እንደ አማጽያኑ ከተገደሉት አብዛኛዎቹ ተማሪዎች ናቸው።

Via የጀርመን ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

" ተማሪዎች ላይ የደረሰ ጉዳት የለም " - የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የጤና ሳይንስ ኮሌጅ ሁነኛ አካል

በአማራ ክልል ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ጥበበ ግዮን ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የሚገኙ ተማሪዎች ማክሰኞ ጥር 28 ቀን ከምሽቱ 2፡30 ገደማ ታጣቂዎች በካምፓሱ ውስጥ ተኩስ መክፈታቸውን፣ ተማሪዎቹ ከግቢው እንዲወጡም ማስጠንቀቂያ መስጠታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸው፣ የሚመለከተው አካል ሰላም ወዳለበት ግቢ እንዲቀይርላቸው ጠይቀዋል።

በኮሌጁ የጸጥታ ችግር አለ የሚል መረጃ ደርሶናል እውነት ነው ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ ያቀረበላቸው ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ አንድ የኮሌጁ ሁነኛ አካል ፣ " ተማሪዎቹ የነገሯችሁ #እውነት ነው። ችግሩ ተፈጠረ፣ ግቢው ተደበደበ። ተማሪዎች ወጡ " ሲሉ አረጋግጠዋል።

በተማሪዎች ላይ የደረሰ ጉዳት አለ ? ተብሎ ለቀረበላቸው ጥያቄ ፤ " ተማሪዎች ላይ የደረሰ #ጉዳት የለም። ከግቢው ገቡ፣ ከዚያ ተኩስ ተጀመረ፣ ከዚያ #ቦምብ አፈነዱ፣ ጥይት ተተኮሰ " ሲሉ አስረድተው፣ " ‘ተማሪዎች መውጣት አለባችሁ የሚል ነገር ተናገሩ እነርሱ (ታጣቂዎቹ) " ብለዋል።

ታጣቂዎቹ ተማሪዎቹን ከግቢ መውጣት እንዳለባቸው ይህን ካላደረጉ ግን በቀጥይ እርምጃ እንደሚወስዱ እንዳስጠነቀቁ ገልጸዋል።

የሴቶች ብሎክ 1 እና 3 ሕንጻ የተወሰነ በታጣቂዎች መመታቱን የገለፁ ሲሆን " ተማሪ ግን #አልጎዱም  " ብለዋል።

" ተማሪዎች ላይ ታርጌት አላደረጉም ሕንጻውን ነው የደበደቡት። ቦምቡ ደግሞ ከተማሪዎች ወደ ካፌ መሄጃ በኩል እዚያው ከግቢው ውስጥ ፈንድቷል። የፈነዳበት ቦታ ይታወቃል " ሲሉ አክለዋል።

ተኩስ የከፈቱት ታጣቂዎች ፍላጎታቸው ምንድን ነው ? ለሚለው ጥያቄ እኚሁ ግለሰብ " ‘ዩኒቨርሲቲ በቃችሁ፣ ከመጀመሪያውስ ለምን መጣችሁ?’ እያሉ ሲናገሩ ነበር " ያሉ ሲሆን " ‘አሁንም ግቢውን ለቃችሁ ውጡ። ዛሬ አንጎዳችሁም። ቀጣይ ግን ስንመጣ ብናገኛችሁ ቀጥታ እርምጃ እንወስዳለን’ የሚል እንድምታ ነበር ብለዋል።

በግቢው አጠቃላይ ከ1,500 እስከ 2,000 ተማሪ የሚገኝበት ሲሆን ከትላንት ጠዋት ጀምሮ #አብዛኞቹ ተማሪዎች ግቢውን ለቀው መውጣታቸውን ተናግረዋል።

" ወደ ቤት የሚሄዱ አሉ (ምክንያቱም በጣም ጭንቅ ነበር በተለይ ሴቶች፣ ሌሊትም #ሲያለቅሱ ነበር) ዘመድ ጋ ወደ ከተማ የሚጠጉም አሉ። #ሆቴል ይዘው ያደሩ ልጆችም አሉ። ቤተሰብ ሩቅ የሆነባቸው፣ ገንዘብ የሌላቸው ተማሪዎች አሉ ግቢ ውስጥ ቁጭ ብለው በጭንቀት " ሲሉ የሁኔታውን አሳሳቢነት አስረድተዋል።

ታጣቂዎቹ ወደ ካምፓሱ ሲገቡ ጥበቃዎች አልነበሩም ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ላቀረበው ጥያቄ ፣ " የእኛ ካምፓስ አዲስ ስለሆነ አጥር የለውም። በዙሪያው ጥበቃዎች አሉ። ግን ጥበቃዎች በኮማንድ ፓስቱ ምክንያት መሣሪያ አይዙም። መሣሪያ ቢይዙም የመጣው ኃይል በጣም ብዙ ነው " ብለዋል።

የተማሪዎቹ ፍላጎትስ ምንድነው ? ለሚለው ጥያቄም፣ " ተማሪዎች መማር ይፈልጋሉ። ምክንያቱም በኮሮና ጊዜ፣ በጦርነት ምክንያት አማራ ክልል ላይ ብዙ ታሹ። አብዛኛው ተማሪ መማር ይፈልጋል፣ ግን ደግሞ ከሕይወት የሚበልጥ ነገር የለም " የሚል ምላሽ ተሰጥተዋል።

የካምፓሱ ከፍተኛ ባለስልጣናት በጉዳዩ ዙሪያ ረቡዕ ጥር 29 ቀን 2016 ዓ/ም አስቸኳይ ስብሰባ እንደነበራቸው፣ በዚህም " በጥበቃ (በመከላከያ) ተጠብቀው ይማሩ ወይስ ሌላ ግቢ እናመቻችላቸው ? " በሚለው ጉዳይ እንደተወያዩና ውሳኔው ግን እንዳልታወቀ ተመላክቷል።

መረጃው የተዘጋጀው በአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኦሮሚያ #ኖኖ #ስልክአምባ በኦሮሚያ ክልል ፤ በምዕራብ ሸዋ ዞን ፤ ኖኖ ወረዳ ሰርገኞችን ዒላማ ባደረገ ጥቃት ከ20 በላይ ሰዎች መገደላቸውን የአካባቢው ኮማንድ ፖስት እና ነዋሪዎች ገለጹ። የኖኖ ወረዳ ኮማንድ ፖስት ኃላፊ አቶ ተሾመ ሰቦቃ ለቢቢሲ አፋን ኦሮሞ በሰጡት ቃል ፥ ጥቃቱ ቅዳሜ ሰኔ 8 ንጋት ላይ ነው የተፈጸመው። ጥቃት አድራሾቹ " ጽንፈኛ የአማራ ታጣቂዎች  ናቸው " ብለዋል። ኃላፊው…
* Update

በኦሮሚያ ክልል ፣ በኖኖ ወረዳ በተፈጸመው ጥቃት የሟቾች ቁጥር ከ30 ማለፉን ፣ 12 ቁስለኞች ወሊሶ ሆስፒታል መግባታቸውን ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

" ታጣቂዎቹ በሰርገኞች ቤት #ቦምብ ወረወሩባቸው። ሁሉም አልቀዋል። ትልላቅ ሰዎች ትንሽ አጥንታቸው ይታያል። ህጻናት ግን ተቃጥለው አልቀዋል " ሲሉ ነው ያስረዱት።

የሟቾች ቁጥር ከ30 በላይ እንደደረሰ፣ በተፈናጣሪው 12 ሰዎች እንደቆሰሉና ሆስፒታል እንደገቡ የገለጹት ነዋሪዎቹ፣ 4 ቤቶችም እንደተቃጠሉ አመልክተዋል።

ከኖኖ ወረዳ ጥቃት ማግስት በምዕራብ ደቡብ ሸዋ ዞን አማያ ወረዳ ታጣቂዎቹ ሰነዘሩት በተባለ ሌላ ጥቃት 2 ሰዎችና 15 ላሞችን እንደተገደሉ ነዋሪዎቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

በወቅቱ ፤ የተኩስ ድምጽ ይሰማ እንደነበር ፤ በኃላም መከላከያ ሰራዊቱ ወደ ስፍራው እንደገባና ሁኔታውን መቆጠጠሩን ፤ ነዋሪዎች ግን ወደ አጎራባች ቦታዎች ለመፈናቁል እንደተገደዱ አስረድተዋል።

የኖኖ ወረዳ ኮማንድ ፖስት ኃላፊ አቶ ተሾመ ሰቦቃ ስለ ጉዳዩ ጠይቀናቸው " መረጃው የለኝም " ብለዋል።

የወረዳው አስተዳዳሪ አቶ አለማየሁ ወርቁ ፣ የአማያ ወረዳ ባለስልጣናት ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ አልሆኑም።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia