TIKVAH-ETHIOPIA
1.43M subscribers
55.4K photos
1.39K videos
199 files
3.72K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ወንድማችን⬆️እዚህ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖር ኤርትራዊ ወንድማችን የሀገሩን #ጥሪ አስመልክቶ ካየው ዜና ጋር በተያያዘ አስተያየቱን ልኮልኛል። #ምንም ሳልጨምር ሳልቀንስ አስተያየቱን ወደናተ አቅርቤዋለሁ⬇️
.
.
Hii,Tesgsh thank you for everything you are doing. I am Eritrean. I live in Ethiopia. We need complete political change. Post this one on behalf of all Eritreans.

We need...

1.The constitution to be implemented

2.Rule of law should be respected

3.Innocent Eritreans in different prisons should be released.

4.The regime should apilogize for what it did in the last 20 years.

5.Our war heroes the so-called G-15 and journalists and other political prisons should be freed.

6.Religious fathers should be released

8.etc...

All in all complete political should be safeguarded. If you,tsegish, love the Eritrean people, do that for me and the Eritrean people. Post it in your information center. Thank you!

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን⬇️

የኬንያ የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች ማህበር የኢትዮጵያ አየር ክልል ደህንነትን በተመለከተ ያወጣው መግለጫ በፍጹም እውነት #እንዳልሆነ የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽ ባለስልጣን አስታወቀ፡፡

የኢትዮጵያ የአየር ተቆጣጣሪ ሰራተኞች የስራ አድማ በመምታታቸው በኢትዮጵያ አየር ክልል ውስጥ #ምንም ዓይነት የደህንነት ስጋት ባለመፈጠሩ ማህበሩ ያወጣው መግለጫ መሰረተ ቢስ በመሆኑ ባለስልጣኑ በምንም መልኩ እንደማይቀበለው ገልጿል፡፡

ሰራተኞቹ አድማ ቢመቱም አሁንም በበቂ ሁኔታ ስለጠና በወሰዱ፤ በሙያው ዘርፍ ከፍተኛ እውቀት ባከበቱ እና ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቁ ሰራተኞች ስራቸውን እያከናወኑ በመሆኑ ምንም ዓይነት ስጋት አይፈርም ብሏል፡፡

በመሆኑም የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን የኢትዮጵያ አየር ክልል የተጠበቀ መሆኑን ለአየር መንገዶች፤ ለሃገራት ሲቭ አቪዬሽ ባለስልጣናት፤ ለዓለም አቀፍና ቀጠናዊ አካላትም እንደሚያረጋግጥ ገልጿል፡፡

📌የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ለጥያቄዎቻችሁ መልስ‼️

ዛሬን ጨምሮ ከዚህ በፊት እንደዚህ አይነት ጥያቄዎች ቀርበውልኛል፦

"ምንድነው የምትንዘባዘበው መረጃ ከሌለህ ትርኪ ምርኪ ነገር ለምን ትፖስታለህ?"

"ትንንሽ ጉዳዮችን ለምን ትፅፋለህ?"

"አንተ የመንግስት አጨብጫቢ ነህ?"

"አንተ ከዚህ ብሄር ነህ #መሰለኝ ለዚህኛው ታደላለህ..." እና ሌሎችም።

እንዲሁም አስተያየት መሰል ብዙ ስድቦች ይደርሱኛል።
.
.
በመሰረቱ ይህን ቻናል ለህዝብ ጥቅም እና ለመረጃ ልውውጥ የከፈትኩት ነው። ከየትኛውም ወገን ንፁህ ነው። እኔም ከየትኛውም ወገንተኝነት 1000000% ንፁህ ነኝ። እኔ ራሴን የሁሉም ሰው አድርጌ ነው የምቆጥረው። ለሁሉም የሰው ፍጡር እጅግ በጣም ትልቅ ክብር ነው ያለኝ! የኔ መስፈርት ሰው መሆን ላይ ነው። በመሆኑም መረጃዎች ሲላኩልኝ መጀመሪያም መጨረሻም የማየው ከየትኛው ወገን፣ ከየትኛው ብሄር፣ ከየትኛው ሀይማኖት ተከታይ ሰዎች ተላከልኝ ሳይሆን ይህን መረጃ ባሰራጨው ለተከበረው የኢትዮጵያ ህዝብ ምን ይጠቅመዋል? የሚል ጥያቄ ነው የማነሳው።

በፍፁም ያለአንዳች ግብ እዚህ ገፅ ላይ የሚለጠፈው ፅሁፍ የለም። በተለይ ቻናሉ ለሰላም የሚሰራ ነው። ይህ ማለት ችግር ሲፈጠር ይደብቃል ማለት አይደለም። መረጃዎቹ ሁሉ እንዲመቱልኝ የምፈልገው ግብ አለ። የአያንዳንዱን ከተማ እንቅስቃሴ ሰላም መሆኑን ሰው በሰላም እየተንቀሳቀሰ እለታዊ ተግባሩን መፈፀሙን የሚገልፁ ፅሁፎችን የምለጥፈው መቀለ ሆኖ ስለ ወለጋ፤ ባህር ዳር ሆኖ ስለ ሀዋሳ፤ ሞያሌ ሆኖ ስለ ቤንሻንጉል ጉዳይ መሰማት ስላለበት ነው። ለኛ ስናነባቸው ትንሽ እና ተራ የሚመስሉን ነገሮች ብዙ ሺዎችን በእንቅስቃሴያቸው እንዳገዛቸው በቂ ማረጋገጫ አለኝ።

ይሆነ ቦታ ወጣቶች የሚሰሩትን ጥሩ ስራ ሳቀርብ ሌላውም በነጋታው አስቦት ያድራል። እዚህ ከተማ እንዲህ አይነት ሰላማዊ እንቅስቃሴ ተከናወነ፣ ተከበረ የምለውም በሌሎች ቦታዎች ላይ የሚያሳድረው ተፅዕኖ ስላለው ነው።

ከዚህ ቀደም የእስልምና እምነት ተከታዮች የሚያከብሩትን በዓል እንዲሁም የክርስትና እምነት ተከታዮች የሚያከብሩትን በዓላት በየከተማው በየቀበሌው #በሰላም ስለመከበሩ የማበስረው የዚህን ቻናል ግብ ለማሳካት ነው። 😁ብችል የእያንዳንዱን ሰው ሰላማዊ ውሎ ብዘግብ ደስ ይለኛል።

እና ወዳጆቼ በሰላም ተከበረ በሰላም አለቀ የሚሉ ቃላቶች ማደጋገማቸውን እንደትንሽነት እና እንዳላዋቂነት አትቁጠሩት ትልቅ ትልቅ ጥቅም አላቸው።

ሌላው ከናተ የሚመጡት መረጃዎች እውነት ስለመሆናቸው ፈጣሪ ታማኞች አድርጎ ስለፈጠራችሁ አያሳስበኝም።

መረጃዎች #እንደወረዱ የሚቀርቡት በፍፁም የኔ እጅ እንዳይገባበት ነው። መረጃ ስትልኩልኝ ነጥብ አላስተካክልም። የላካችሁትን አቅርባለሁ። ይህ እኔ ምፈነጭበት እና እራሴን ማስተዋውቅበት መድረክ አይደለም። ይሄ የናተ ገፅ ነው! የፃፋችኋትን #ምንም ኢዲት ሳላደርግ ቃል በቃል አቀርባለሁ። ወደፊትም በዚሁ ቀጥላለሁ።

ማጠቃለያው፦ እዚህ ቤት #ትንሽ ጉዳይ የለም! ኢትዮጵያዊያን በሚኖሩባት ምድር ምንም የማልፈው ነገር የለም። ይህ አቋሜ ነው። ደረጃ እና ጥራት እያሉ መመፃደቅ አይሰራም። ከእናተ ቤት ተነስተን እንስከ ሀገር ድረስ መረጃዎችን እንዳስሳለን። ለማቅራራት እና ዝነኛ ወይም ገንዘብና ስልጣን ባላቸው ሰዎች ለመወደድ አይደለም የምሰራው! እኔም ሆንኩ ቻናሉ ለእያንዳንዱ ጥቃቅን ጉዳይ info እንሰጣለን። ይህን ማድረግ ትንሽነት እና አለማወቅ ከሆነ ትንሽ እና አላዋቂ ሆኜ ልሙት!
.
.
አዎን የተላከ ሁሉ አይቀርብም! መረጃ ሲላክ ለአካባቢው እና ለሌላ ቦታ ይህ ነገር ይጠቅማል?? የሚለውን ጠይቄ ነው። ሌላው በውስጥ በኩል መረጃ የምሰጣቸው አሉ።
.
.
TIKVAH-ETH ለዝና የሚንቀሳቀስ አይደለም! ለሰላም፣ ለፍቅር እና ለተስፋ ነው የሚሰራው።

እዚህ የሰበሰበን ሰውነት ነው፤ ከዛም ኢትዮጵያዊነት! ነፁ ኢትዮጵያዊ ደግሞ እራሱን የሚያውቅ ሁሉንም የሰው ፍጡር እንደራሱ የሚያይና #የሚያከብር ነው።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ProfessorSenaitFisseha ዛሬ የጤና ሚኒስቴር በሀገር አቀፍ ደረጃ አዳዲስ ምሩቃን ሀኪሞችን በቅጥር ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችል ፕሮጀክት ከክልል እና ከከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮዎች ጋር ተፈራርሟል። ፕሮጀክቱ ዘንድሮ ጀምሮ ለ3 ዓመት ይቆያል። በመጀመሪያ አመት 2,898 ሃኪሞች ወደስራ ለማስገባት ታቅዷል። ለዚሁ ለመጀመሪያው ዓመት ስራ የሚያስፈልገው ገንዘብ ከፌዴራል እና ከልማት አጋር…
#MoH

➤ በአዲስ አበባ ለ161 ጠቅላላይ ሀኪሞች ቅጥር ወጥቶ ለመቀጠረ ያመለከቱት 2,300 ናቸው።

0⃣ በሶማሌ እና አፋር ክልል ለጠቅላላ ሀኪሞች የስራ ቅጥር ቢወጣም #ምንም አመልካች ጠቅላላ ሀኪም ለማግኘት አልተቻለም።

ጤና ሚኒስቴር እና ገንዘብ ሚኒስቴር ከልማት አጋሮች ጋር በመተባበር 2,898 አዳዲስ ምሩቃን ሀኪሞችን በሃገር አቀፍ ደረጃ በመቅጠር ወደ ስራ ለማሰማራት ከሁሉም ክልል ጤና ቢሮዎች እና ከተማ አስተዳደሮች ጋር በተደረገ ስምምነት ታህሳስ 21 ቀን 2014 ዓ.ም አንድ ፕሮጀክት በይፋ መጀመሩ ይታወሳል።

ይህ እኩል በእኩል መዋጮ ፕሮጀክት የሶስት ዓመት ፕሮጀክት ሲሆን በመጀመሪያዉ የፕሮጀክት ዓመት ወደ ስራ ለማሰማራት ከታቀደው 2,898 ጠቅላላ ሐኪሞች እና በተጨማሪ ከፕሮጀክቱ በጀት ዉጪ በክልሎች ተጨማሪ በጀት ➙ 961 ሃኪሞች በድምሩ ➙ 3,701 አዳዲስ ምሩቃን ጠቅላላ ሀኪሞች ለመቅጠር ከወራት በፊት በሁሉም የከተማ አስተዳደር እና የክልል ጤና ቢሮዎች የቅጥር ማስታወቂያ ወጥቶ ነበር።

የቅጥር ማስታወቂያ ቢወጣም አመልካች ጠቅላላ ሀኪሞች በሁሉም የቅጥር ማስታወቂያ በወጣባቸው ቦታዎች ላይ #በወጥነት እንዳላመለከቱ በተደረገ ክትትል ታውቋል።

ለአብነት ያህል ፤ አዲስ አበባ ላይ ለ161 የቅጥር መደብ 2,300 ጠቅላላ ሀኪሞች ናቸው ለመቀጠር ያመለከቱት።

ከዚህ በተቃራኒ ደግሞ በአንዳንድ ክልሎች ለቅጥር ማስታወቂያ ከወጣባቸዉ መደቦች በጣም ባነሰ ቁጥር ያመለከቱ ሲሆን በአንዳንድ ክልሎች ደግሞ ምንም አመልካች አልተገኘም።

ምንም አመልካች ጠቅላላ ሀኪም ያልተገኘው ሶማሌ እና አፋር ክልሎች ላይ ነው።

እስካሁን ድረስ በአጠቃላይ 1,309 ጠቅላላ ሃኪሞች ብቻ የተቀጠሩ ሲሆን ይህም ከሚጠበቅው የቅጥር ብዛት አንፃር 35% ላይ ይገኛል።

ይህንኑ ታሳቢ በማድረግ ጠቅላላ ሃኪሞች በተለይም አዳዲስ ምሩቃን ሀኪሞች የቅጥር ማስታወቂያ በወጣባችው ክልሎች ፦
➡️ አማራ ክልል፣
➡️ አፋር ክልል፣
➡️ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል
➡️ ጋምቤላ ክልል፣
➡️ ኦሮሚያ ክልል፣
➡️ ሲዳማ ክልል፣
➡️ ደቡብ ክልል፣
➡️ ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል እና ሶማሌ ክልል ለ2,392 ጠቅላላ ሃኪሞች ክፍት የሆነ የቅጥር ቦታ እንዳለ አውቀው እድሉን እንዲጠቀሙ ጤና ሚኒስቴር ጥሪ አቅርቧል።

@tikvahethiopia
" በየቤቱ የቁም እንስሳት ማረድ / በየአካባቢው ቅርጫ አድርጎ መከፋፈል አልተከለከለም " - የአዲስ አበባ የሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ

የአዲስ አበባ ከተማ የሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ፥ ከትንሳዔ በዓል ጋር በተያያዘ " ህብረተሰቡ በየቤቱ የቁም እንስሳት እርድ በማካሄድ ወይም በየአካባቢው ቅርጫ በማድረግ የሚከፋፈልበት አሰራር ተከልክሏል " በሚል በማህበራዊ ሚዲያ እየተሰራጨ ያለው መረጃ #ሐሰተኛ ነው ሲል አሳወቀ።

ከዚህም ጋር በተያያዘ #ምንም_ዓይነት_ክልከላ ያልተደረገ መሆኑን አረጋግጧል።

ነገር ግን በየአካባቢው #በሕገወጥ_መንገድ እርድ በመፈፀም ለሆቴሎች እና ለስጋ ቤቶች በማከፋፈል ተግባር ላይ የተሰማሩ አካላት የቁም እንስሳቱ ጤንነት ባልተረጋገጠበት ሁኔታ ድርጊቱ በከተማው ነዋሪዎች ጤንነት ላይ ጉዳት የሚያደርስ በመሆኑ ጥብቅ ቁጥጥር ይደረጋል ብሏል።

የከተማዋ ነዋሪዎችም ትብብር እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርቧል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኦዲት የተሰበሰበው ገቢ #ትክክለኛነቱን ለማረጋገጥ ሂሳብ ኦዲት ሲደረግ በኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት #በዶላር የተሰበሰበ 1.3 ሚሊዮን ገቢ ትክክለኝነቱን ማረጋገጥ #አልተቻለም። የፌዴራል ዋና ኦዲተር ማንኛውም ገቢ ተገቢ ማስረጃ ሳይሟላ በገቢ መመዝገብ ፍጹም ትክክል እንዳልሆነ አስገንብዝቦ የገቢ ማስረጃዎች በትክክል ተደራጅቶ እንዲያዝ ተገቢው ማስተካከያም እንዲደረግና እርምጃ እንዲወሰድ አሳስቧል።…
#ኢትዮጵያ #ኦዲት

በ11 መስሪያ ቤቶች 43.5 ሚሊዮን ብር #ምንም ማስረጃ ሳይኖር ወጪ ተደርጓል።

በ2015 የበጀት ዓመት መ/ቤቶች የተፈቀደላቸውን በጀት በአግባቡ ወጪ ማድረጋቸውን / በአግባቡ መጠቀማቸውን ፣ ተገቢ ማስረጃ መቅረቡንና ሂሳቡ በትክክል መመዝገቡን ለማጣራት ኦዲት ተደርጓል።

በዚህም ፥ ምንም አይነት ማስረጃ ሳይቀርብ በወጪ የተመዘገበ ክፍያ / ሂሳብ ተገኝቷል።

በ11 መ/ቤቶች 43.5 ሚሊዮን ማስረጃ ሳይኖረው በወጪ ሂሳብ የተመዘገበ ሲሆን ማስረጃም ባለመቅረቡ ትክክለኛነቱን ማረጋገጥ አልተቻለም።

የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን 17.4 ሚሊዮን
የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት ባለስልጣን 8.7 ሚሊዮን
የመንገድ ደህንነትና መድህን ፈንድ አገልግሎት 8.7 ሚሊዮን
ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ 4.4 ሚሊዮን
የኢትዮጵያ አካል ድጋፍ አገልግሎት 3.3 ሚሊዮን ዋና ዋናዎቹ ናቸው።

ከዚህ ባለፈ ፤ በወጪ ለተመዘገቡ ክፍያዎች የተሟላ ማስረጃ መቅረቡን ለማረጋገጥ በተደረገው ኦዲት በ 48 መ/ቤቶች የተሟላ ማስረጃ ሳይቀርብ 44 ሚሊዮን 440 ሺህ በወጪ ተመዝግቦ ተገኝቷል።

የተሟላ ማስረጃ ሳይዙ ወጪ ከመዘገቡት መካከል ፦
🔴 ማዕድን ሚኒስቴር 5 ሚሊዮን 719 ሺህ
🔴 ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ 5 ሚሊዮን 716 ሺህ
🔴 የጤና ሚኒስቴር 4 ሚሊዮን 677 ሺህ
🔴 ገንዘብ ሚኒስቴር 3 ሚሊዮን 34 ሺህ
🔴 በስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር ገዋኔ የግብርና የቴክኒክ ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጅ 2 ሚሊዮን 450 ሺህ
🔴 የኢትዮጵያ ጂኦሎጂካል ኢንስቲትዩት 2 ሚሊዮን 185 ሺህ ዋና ዋናዎቹ ናቸው።

የፌዴራል ኦዲተር መስሪያ ቤት ፤ ማስረጃ ካልቀረበ የሂሳቡን #ትክክለኝነት_ማረጋገጥ_እንደማይቻል ፤ የወጪ ማስረጃ ላልቀረበላቸው ክፍያዎች የወጪ ማስረጃ እንዲቀርብላቸው የማይቀርብላቸው ከሆነ #ገንዘቡ_ተመላሽ እንዲደረግ አሳስቧል።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia