TIKVAH-ETHIOPIA
1.49M subscribers
56.6K photos
1.41K videos
203 files
3.86K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Mali 🇲🇱

በአፍሪካዊቷ #ማሊ የታጠቁ አማፂያን በፈጸሙት ጥቃት ከ100 በላይ ንፁሀን ዜጎች መገደላቸውን የሀገሪቱ መንግስት አስታውቋል።

ጥቃቱ ማዕከላዊ ማሊ ውስጥ መፈፀሙ ነው የተነገረው።

ጥቃቱን ' Katiba Macina ' የተባለው የታጠቀ ቡድን አባላት ቅዳሜ ለሊት ለእሁድ አጥቢያ የፈፀሙ ሲሆን ፤ ሞፕቲ ክልል ውስጥ በሚገኘው ባንካስ የገጠር ማህበረሰብ ውስጥ ቢያንስ በሶስት መንደሮች ላይ ባደረሱት ጥቃት በትንሹ 132 ንፁሃን ሰዎች በግፍ መደገላቸውን የሀገሪቱ መንግስት ገልጿል።

ጥቃቱን ተከትሎ የማሊ መንግስት ዛሬ የሶስት ቀን ብሄራዊ ሀዘን አውጇል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" ከአሁን ጀምሮ ግብረሰዶማዊነት እና ተዛማጅ ድርጊቶች ሁሉ የተከለከሉ ናቸው " - የቡርኪናፋሶ ሁንታ

ቡርኪናፋሶ ግብረ ሰዶማውያንን ወንጀለኛ የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አወጣች።

ረቂቁ ሕጉ ስራ ላይ እንዲውል በፓርላማ ቀርቦ ድምጽ ይሰጥበታል።

ትላንትና የቡርኪናፋሶ ወታደራዊ መንግስት በሰጠው መግለጫ ፥ የተሻሻለ የቤተሰብ ህግ ረቂቅ አዋጅ በወታደራዊው መሪ ኢብራሂም ትራኦሬ በሚመራ ሳምንታዊ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ቀርቦ ተቀባይነት አግኝቷል።

የሀገሪቱ ጊዜያዊ ፍትህ ሚኒስቴር ፥ " ከአሁን ጀምሮ ግብረሰዶማዊነት እና ሌሎች ተዛማጅ ድርጊቶች ሁሉ የተከለከሉ እና በህግ የሚያስቀጡ ናቸው " ብሏል።

ሕጉ ወደ ትግበራ  ፓርላማ ቀርቦ ድምጽ ሊሰጥበት ይገባል ፤ በተጨማሪ ትራኦሬ ማወጅ እንዳለባቸው ሮይተርስ ዘግቧል።

ሀገሪቱ በተካሄደ መፈንቅለ መንግስት በወታደራዊ አገዛዝ ስር የምትገኝ ሲሆን በተመሳሳይ በመፈንቅለ መንግስት ስልጣን ከያዙት ጎረቤቶቿ #ኒጀር እና #ማሊ ወታደራዊ መንግስታት ጋር በኮንፌዴሬሽን #ለመዋሀድ ከቀናት በፊት ነው የተስማማቸው።

@tikvahethiopia