TIKVAH-ETHIOPIA
1.43M subscribers
55.6K photos
1.39K videos
200 files
3.74K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ለነገ አርብ የውጭ ምንዛሬ ዋጋ ጨምሯል። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የነገ አርብ ምንዛሬ ዋጋን ዛሬ ምሽት ይፋ አድርጓል። በዚህም አንዱ የአሜሪካን ዶላር መግዣው 83 ብር ከ9413 ሳንቲም ፤ መሸጫው 85 ብር ከ6201 ሳንቲም እንዲሆን ቆርጧል። ፓውንድ ስተርሊንግም በእጅጉ ጨምሯል። መግዣው 101 ብር ከ9101 ሳንቲም ፤ መሸጫው 103 ብር ከ9483 ሆኖ ይውላል ብሏል። ዩሮም ጨምሯል።…
#Update

ዶላር መሸጫው ከ100 ብር አለፈ።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የነገ ቅዳሜ ምንዛሬ ዋጋን ዛሬ ምሽት ይፋ አድርጓል።

በዚህም አንዱ የአሜሪካን ዶላር መግዣው 95 ብር ከ6931 ሳንቲም ፤ መሸጫው 101 ብር ከ4347 ሳንቲም እንዲሆን ቆርጧል።

ፓውንድ ስተርሊንግም በእጅጉ ጨምሯል። መግዣው 116 ብር ከ6881 ሳንቲም ፤ መሸጫው 123 ብር ከ6894 ሆኖ ይውላል ብሏል።

ዩሮም እጅግ በጣም ጨምሯል። መግዣው 104 ብር ከ4107 ሳንቲም መሸጫው 110 ብር ከ6754 ሳንቲም እንደሚሆን አሳውቋል።

የUAE ድርሃም በተመሳሳይ ጨምሯል። አንዱ ድርሃም ነገ በ23 ብር ከ3201 ሳንቲም እየተገዛ ፤ በ24 ብር ከ7194 ሳንቲም ይሸጣል ብሏል።

#TikvahEthiopia #CBE #Floatingexchangerate

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ዶላር መሸጫው ከ100 ብር አለፈ። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የነገ ቅዳሜ ምንዛሬ ዋጋን ዛሬ ምሽት ይፋ አድርጓል። በዚህም አንዱ የአሜሪካን ዶላር መግዣው 95 ብር ከ6931 ሳንቲም ፤ መሸጫው 101 ብር ከ4347 ሳንቲም እንዲሆን ቆርጧል። ፓውንድ ስተርሊንግም በእጅጉ ጨምሯል። መግዣው 116 ብር ከ6881 ሳንቲም ፤ መሸጫው 123 ብር ከ6894 ሆኖ ይውላል ብሏል። ዩሮም እጅግ በጣም…
#Ethiopia : በዛሬውና ነገ በሚውለው በዶላር ምዛሬ ዋጋ መግዣው ላይ የ12 ብር ልዩነት ፤ በመሸጫው ላይ የ15 ብር ልዩነት ታይቷል።

ዛሬ የነበረው መግዣ 83 ብር ከ9413 ሳንቲም ሲሆን መሸጫው 85 ብር ከ6201 ሳንቲም ነበር።

ነገ ማለትም
#ቅዳሜ ሐምሌ 27 የሚውለው የምንዛሬ ዋጋ መግዣው 95 ብር ከ6931 ሳንቲም ፤ መሸጫው ደግሞ 101 ብር ከ4347 ሳንቲም ነው።

ሌላው በጣም ልዩነት የታየበት ዩሮ ነው ዛሬ 90 ብር ከ5307 ሳንቲም መግዣ ፤ መሸጫው 92 ብር ከ3413 ሳንቲም ሆነ ነበር የዋለው።

በነገው ምንዛሬ ግን የአንዱ ዩሮ መግዣው 104 ብር ከ4107 ሳንቲም ፤ መሸጫው 110 ብር ከ6754 ሳንቲም ሆኖ ይውላል።

ብዙም የምይነገርለት
#የኩዌይት_ዳናር ደግሞ የአንዱ መሸጫ ከ315 ብር አልፏል።

በነገ ምንዛሬ አንዱ ዲናር በ298 ብር ከ8463 ሳንቲም እየተገዛ በ316 ብር ከ7771 ሳንቲም ይሸጣል ተብሏል።

ይህ መረጃ በ ' ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ' ያለውን ምንዛሬ የሚያሳይ ሲሆን የግል ባንኮች ደግሞ ምን ይዘው እንደሚመጡ ጥዋት ይታያል።

#TikvahEthiopia #Floatingexchangerate

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia : በዛሬውና ነገ በሚውለው በዶላር ምዛሬ ዋጋ መግዣው ላይ የ12 ብር ልዩነት ፤ በመሸጫው ላይ የ15 ብር ልዩነት ታይቷል። ዛሬ የነበረው መግዣ 83 ብር ከ9413 ሳንቲም ሲሆን መሸጫው 85 ብር ከ6201 ሳንቲም ነበር። ነገ ማለትም #ቅዳሜ ሐምሌ 27 የሚውለው የምንዛሬ ዋጋ መግዣው 95 ብር ከ6931 ሳንቲም ፤ መሸጫው ደግሞ 101 ብር ከ4347 ሳንቲም ነው። ሌላው በጣም ልዩነት የታየበት…
#DailyExchangeRate

ዛሬግል ባንኮች ያለው የውጭ ምንዛሬ ዋጋ ከላይ ተያይዟል።

ከላይ የ7 የግል ባንኮች ዕለታዊ ምዛሬ ቀርቧል።

ከነዚህ ባንኮች 3ቱ ማለትም ኦሮሚያ፣ አባይ ፣ ዳሽን የዶላር መግዣቸውን በ90 ብር አድርገው በሳንቲም ይለያያሉ መሸጫቸው ግን ልዩነት አለው።

ኦሮሚያ የዶላር መግዣው 102 ብር ከ3848 ሳንቲም ነው ፤ ሲሆን በአባይ 102 ብር ከ9560 ሳንቲም ፤ በዳሽን ደግሞ 100 ብር ከ7768 መሸጫው ነው።

ሌሎቹ ባንኮች አቢሲንያ፣ አዋሽ ፣ ሲዳማና የኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንኮች መሸጫቸውም መግዣቸውም ይለያያል።

አቢሲንያ ዛሬ ሁለት (ጥዋት እና ከሰዓት) የዶላር ምንዛሬ ነው የተጠቀመው ።

ጥዋት ላይ በ90 ብር ከ0690 ሳንቲም መግዣ መሸጫ ደግሞ 106 ብር ከ7318 ሳንቲም ነበር ፤ አሁን ይፋ ባደረገው የከሰዓት ምንዛሬ ግን መግዣውን ወደ 96 ብር ከ3738 ሳንቲም መሸጫውን 107 ብር ከ9387 ሳንቲም አሳድጎታል።

አዋሽ ዶላር መግዣው 96 ብር ከ3011 ሳንቲም ሲሆን መሸጫው 106 ብር ከ8941  ሳንቲም ነው። ሲዳማ በ96 ብር ከ6500 ገዝቶ በ106 ብር ከ3110 ሳንቲም እንደሚሸጥ ገልጿል። ኦሮሚያ ህብረት ስራ በበኩሉ መፍዣው 97 ብር ከ7329 ሳንቲም ሲሆን መሸጫው 107 ብር ከ5062 ሳንቲም ነው።

ከዶላር ውጭ ያሉ ምንዛሬዎችም በግል ባንኮች ዋጋቸው ጨምሯል። ዝርዝሩን ከላይ ይመልከቱ።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
#Ethiopia

° " በርካታ መሰረታዊ ሸቀጥ የያዙ ተሽከርካሪዎች ከጉምሩክ ጣቢያዎች ተንቀሳቅሰዋል " - መንግሥት

° " የዋጋ ጭማሪ ቁጥጥር የአንድ ሰሞን ወሬና ወከና ሆኖ በዛው ጨምሮ እንዳይቀር ተከታተሉልን ፤ከዚህ ቀደም በዘይት የሆነውን አይተናል። ኑሮውን መቋቋም አልቻልንም " - የ4 ልጆች እናት ሰራተኛ
(ከአ/አ)

የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ተግባራዊ ተደረገ ከተባለበት ጊዜ አንስቶ መሰረታዊ በሚባሉ ሸቀጦች ላይ ጭማሪ፣ እንዲሁም " የለም " የማለት ነገር እያጋጠማቸው እንደሆነ ዜጎች ተናግረዋል።

ይህም ሁኔታ እያማረራቸው እንደሆነ ያመለክታሉ።

በተለይም አንዳንድ ምርቶችን ለመግዛት ሲሄዱ ከፍ ያለ ብር ተጨምሮ እንደሚነገራቸው ፤ ከዚህ ባልፈ ደግሞ " አሁን ምርት የለም " እየተባሉ እንደሚጉላሉ በምሬት ይናገራሉ።

መንግሥት በበኩሉ ገበያው እንዳይናጋ የቁጥጥር ስራ እየሰራ እንደሆነ እየገለጸ ነው።

ዋጋ ጨምረው የተገኙ በርካታ ሱቆችን ከማሸግ በተጨማሪ የአቅርቦት እጥረት እንዳይፈጠረ ሸቀጥ በገፍ እንዲገባ እየሰራ መሆኑን በተደጋጋሚ እያሳወቀ ይገኛል።

የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር በማሻሻያው ምክንያት የገበያ መናጋት እንዳይፈጠር እርምጃዎች እየተወሰዱ እንደሆነ ገልጿል።

ለአብነት በጉምሩክ ጣቢያዎች መሰረታዊ ሸቀጥ ጭነው የቆሙ ተሽከርካሪዎች እንዲወጡ መፍትሄ እየተሰጠ እንደሆነ አመልክቷል።

በተለይ ገንዘብ ሚኒስቴር አዲስ ባወጣው የቫት ክፍያ ምክንያት ቆመው የሚገኙትን እንዲንቀሳቀሱ የማድረግ ስራዎች እየተሰሩ ነው ተብሏል።

ከዚህ ጋር በተያያዘ በዛሬው ዕለት ፦
➡️ 101 ከባድ ተሽከርካሪዎች ከነተሳቢያቸው 44,000 ሌትር ዘይት የያዙ ፤
➡️ 80 ከባድ ተሽከርካሪዎች ከነተሳቢያቸው 32,000 ኩንታል ስኳር የጫኑ
➡️ 23 ከባድ ተሽከርካሪዎች ከነተሳቢያቸው 9,200 ኩንታል ሩዝ የጫኑ
➡️ 69 ከባድ ተሽከርካሪዎች ከነተሳቢያቸው 27,600 ኩንታል የስንዴ ዱቄት የጫኑ በጥቅሉ 273 ተሽከርካሪዎች ከነተሳቢያቸው የጉምሩክ ስነስርዓት ጨርሰው ወደ መዳረሻቸው እንደተንቀሳቀሱ የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትሩ ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ተናግረዋል።

በነገው እለትም እጅግ ከፍተኛ ቁጥር ያለው መሰረታዊ ሸቀጥ ከጉምሩክ ጣቢያዎች ወደ መላው ሀገሪቱ አከባቢዎች እንደሚጓጓዝም አሳውቀዋል።

በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች " ዶላር ጨምሯል " በሚል በተለይ መሰረታዊ ምርቶች ላይ የሚታየው ጭማሪ ዜጎችን እያማረረ እንደሆነ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለመረዳት ችሏል።

በተለይ እንደ ዘይት፣ ስኳር፣ ያሉት ምርቶችን አንዳንድ ቦታ ማግኘት እንደማይቻል ሲገኝ ደግሞ ዋጋው ጨምሮ ነው ለሸማች የሚነገረው።

ቃላቸውን የሰጡን የ4 ልጆች እናት ሰራተኛ ፥ " እኔ ደመወዜ አንድም ጊዜ ሳይጨምር ይኸው ዘይት ጨምሮ ጨምሮ በሺህ ቤት ገብቷል። እንዴት መኖር እንዳለብኝ አልገባኝም። ደመወዘኔ ምኑን ከምኑ እንደማደረገውም ጠፍቶብኛል " ሲሉ በሀዘን ተናግረዋል።

" የሆነ ነገር በተፈጠረ ቁጥር የሚጨምረው ዋጋ ቁጥጥሩ የአንድ ሰሞን ወሬና ወከባ ይሆንና ዋጋው በዛው ጨምሮ ጣራ ነክቶ ይቀራል ፤ ይህ ከዚህ በፊት በዘይት አይተነዋል " ብለዋል።

" ነጋዴው አያዝንልን፣ የመንግስት ሰዎች ተገቢና ዘላቂ ቁጥጥር አያደርጉልን፣ መፍትሄ አይሰጡን፣ የሚመጣው ሁሉ ግን እኛ ላይ ያርፋል። እንደ ከዚህ ቀደሙ ዋጋ ጨመረ ተብሎ ቁጥጥሩ የአንድ ሰሞን ግርግር ሆኖ በዛው ዋጋው ተሰቅሎ እንዳይቀር መደረግ ያለበት ይደረግ፤ ኑሮው በጣም ከብዶናል። " ሲሉ አክለዋል።

#Tikvahethiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
የዛሬው ዕለታዊ የውጭ ምንዛሬ ምን ይመስላል ?

(ሐምሌ 29/2016 ዓ/ም)

በኢትዮያ ንግድ ባንክ የዛሬ ምንዛሬ ከቅዳሜው ምንዛሬ ዋጋ የተለየ ነገር የለም።

የአሜሪካ ዶላር መግዣው 95.6931 ፤ መሸጫው 101.4347 ሆኖ ዛሬ ቀጥሏል።

የሌሎች ውጭ ምንዛሬዎች ላይም በቅዳሜው ነው የቀጠለው።

በግል ባንኮች ግን ፉክክሩ ደርቷል።

ለአብነት (
#CASH)፦

አቢሲንያ ባንክ

💵 ዶላር መግዣው 100.2288 ፤ መሸጫው 113.2585
💷 ፓውንድ መግዣው 122.2153 ፤ መሸጫው 138.1033
💶 ዩሮ መግዣው 109.3596 ፤ መሸጫው 123.5763

➡️ ወጋገን ባንክ

💵 ዶላር 101.6434 መግዣ ፤ መሸጫው 113.8406
💷 ፓውንድ መግዣ 130.1137 ፤  መሸጫ 145.7273
💶 ዩሮ መግዣ 110.9031 ፤ መሸጫው 124. 2115

➡️ ዳሸን ባንክ

💵 ዶለር መግዣው 100.9253 ፤ መሸጫው 112.0271
💷 ፓውንድ መግዣ 124.0748 ፤ መሸጫ 137.7230
💶ዩሮ መግዣው 109.4334 ፤ መሸጫው 121.4711
🇸🇦የሳውዲ ሪያል 24.3462 መግዣው ፤ መሸጫው 27.0243
🇦🇪የUAE ድርሃም መግዣው በ24.8666፤ መሸጫው 27.6019

➡️ ንብ ባንክ

💵 ዶላር መግዣው 101.0959 ፤ መሸጫው 111.2055
💷 ፓውንድ መግዣው 129.3521 ፤ መሸጫው 142.2874
💶ዩሮ መግዣው 110.3056 ፤ መሸጫው 121.3362
🇦🇪የUAE ድርሃም መግዣው 27.5263 ፤ መሸጫው 30.2789
🇸🇦የሳዑዲ ሪያል መግዣው 26.9446 ፤ መሸጫው 29.6390

➡️ ኦሮሚያ ባንክ

💵 ዶላር መግዣው 100.8445 ፤ መሸጫው 113.9543
💷 ፓውንድ መግዣው 128.5263 ፤ መሸጫው 145.2347
💶 ዩሮ መግዣው 108.8012 ፤ መሸጫው 122.9453
🇰🇼 የኩዌት ዲናር መግዣው 329.8724 ፤ መሸጫው 372.7558

ፀደይ ባንክ

💵 ዶላር መግዣው 101.0348 ፤ መሸጫው 111.1383
💷 ፓውንድ መግዣው 123.2017 ፤ መሸጫው 135.5219
💶 ዩሮ መግዣው 110.2390 ፤ መሸጫው 121.2629

ብርሃን ባንክ

💵 ዶላር መግዣው 96.1716 ፤ መሸጫው 110.5973
💷 ፓውንድ መግዣው 118.2188 ፤ መሸጫው 135.9516
💶 ዩሮ መግዣው 104.2746 ፤ መሸጫው 119.9158

ቡና ባንክ

💵 ዶላር መግዣው 101.0000 ፤ መሸጫው 113.6250
💷 ፓውንድ መግዣው 125.8698 ፤ መሸጫው 138.4568
💶 ዩሮ መግዣው 106.5545 ፤ መሸጫው 117.2100

ፀሐይ ባንክ

💵 ዶላር መግዣው 100.9253 ፤ መሸጫው 115.0548
💷 ፓውንድ መግዣው 130.1137 ፤ መሸጫው 146.3779
💶 ዩሮ መግዣው 112.5666 ፤ መሸጫው 126.6375

#Floatingexchangerate #TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ብር ለኢትዮጵያ የ800ሜትር ሴቶች ውድድር ፍፃሜውን ሲያገኝ አትሌት ፅጌ ድጉማ ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ ለሀገራችን ሁለተኛውን የብር ሜዳሊያ አስገኝታለች። @tikvahethiopia
#TsigeDuguma

ፈረንሳይ ፓሪስ ላይ በ800 ሜትር የሴቶች ፍጻሜ ለሀገሯ ኢትዮጵያ የብር ሜዳሊያ ያስገኘችው ፅጌ ዱጉማ ከውድድሩ በኃላ " JESUS IS LORD ! " የሚል ጽሁፍ አሳይታለች።

ፅጌ ስሟ ተጽፎ ደረቷ ላይ ከተለጠፈበት ወረቀት የጀርባ ክፍል ላይ ነው ይህን መልዕክት ፅፋ ገብታ ያስተላለፈችው።

የዘንድሮ የፓሪስ ኦሎምፒክ የመክፈቻ ስነስርዓት በክርስቲያኖች ዘንድ ቁጣ ቀስቅሶ እንደነበር ይታወሳል።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia @tikvahethsport
TIKVAH-ETHIOPIA
🔈 #የነዋሪዎችድምጽ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣ አሶሳ ከተማና ወምበራ ወረዳ የኤሌክትሪክ አገልግሎት በመቋረጡ ችግር ላይ መውደቃቸውን ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናገሩ። በተለይም በወምበራ ወረዳ አገልግሎቱ ከተቋረጠ አራት ወራት እንዳስቆጠረ ገልጸው፣ እስካሁን (ይህ ዘገባ እስከተዘጋጀበት ጊዜ ድረስ) መፍትሄ እንዳልተገኙ ተናግረዋል። ሞባይል በጀነሬተር ቻርጅ ለማድረግ እንኳ በየቀኑ 20 ብር እንደሚያወጡ…
🔈 #የነዋሪዎችድምጽ

በቤንሻንጉል ጉሙዝ የተለያዩ ቦታዎች ኤሌክትሪክ እንደተቋረጠ፤ በተለይም በአንዳንዶቹ አካባቢዎች ከተቋረጠ ከ3 ወራት በላይ እንዳስቆጠረ ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አቤት ማለታቸው ይታወሳል፡፡

አሁንም ድረስ ችግሩ መቀጠሉን መብራት እንደሌለ ክረምቱን እጅግ እንዳከበደባቸው፣ ህይወታቸውንም ማመሰቃቀሉን እንደቀጠለ ተናግረዋል።

እኛም የወገኖቻችንን ጥያቄ ይዘን ' ይመለከታቸዋል ' የሚባሉትን አነጋግረናል።

ለምን ኃይል ተቋረጠ ? ችግሩን ለመፍታት ምን እየተሰራ ነው ?

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮሚኒኬሽን " እኛ እኮ ኃይል ማቅረብ ነው ከዚያ የዘለለ የስርጭት ሥራ አንሰራም፡፡ ስለዚህም የሥርጭት ሥራን የሚሰሩትን ብትጠይቁ ነው የተሻለ የሚሆነው " አለን።

እሺ ብለን፣  የኤሌክትሪክ አገልግሎት ኮሚኒኬሽን ጠየቅን ፥ " እኛ አይደለንም የምንሰራው፤ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ነው፤ ከተማ ውስጥ አይደለም የተቋረጠው የከፍተኛ መስመር ላይ ነው " ሲል መለሰልን።

" ከፍተኛ መስመር ላይ ጉዳት ደርሶ ኃይል እየደረሰን አይደለም ለኛም፡፡ ኃይል ከእነርሱ ነው የምንገዛው። ስለዚህ እነርሱ ኃይል እያደረሱን አይደለም፡፡ ችግሩ ምን እንደሆነ እነርሱ ናቸው ባለቤቶቹ የሚያውቁት " ሲል አክለልን።

እሺ የኤሌክትሪክ ኃይልን እንጠይቅ ብለን ደወልን " ከኛ ጋር የሚገናኝ ነገር ስለሌለው ነው " ተባልን።

ቆይ ታዲያ የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥን ማንን ነው የሚመለከተው ? የት ብለን እንጠይቅ አልን ፥  " ኃይል በተለያዬ ምክንያት ሊቆራረጥ ይችላል፡፡ መቋረጥ ሁሉ ወደ እኛ አይመጣም ። አጠቃላይ ክልሉ ላይ አይደለም ችግሩ አለ ያላችሁት የተወሰኑ አካባቢዎች ላይ ነው፡፡ የተወሰኑ አካባቢዎች ደግሞ ችግር ካለ ከስርጭት ሊሆን እንደሚችል ነው እኛ የምንገምተው። " ብሎናል።

እስከዛሬ ድረስ ችግሩን አልዳሰሳችሁትም ? ወንበራ ላይ ለምሳሌ አራት ወራት ሊሆነው ነው፤ የመተከል ደግሞ አመታት አስቆጥሯል፤ ብለን ጠየቅን ፥ " መተከል ወደ 2 ዓመት ይስለኛል፡፡ እርሱ ላይ እርግጠኛ አይደለሁም " ብሏል።

አጣርታችሁ ምላሽ እስከምትሰጡን እንጠብቅ ? ስንል ላቀረብነው ጥያቄ " ይሄ እኛን የሚመለከት ስላልሆነ ምንም የተለዬ የማጣራው ነገር የለም " የሚል ምላሽ ተሰጥቶናል።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#Ethiopia

" አዲስ የጨዋታ ሕግ ነው ኢትዮጵያ ውስጥ እየመጣ ያለው " - ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር)

መንግሥት አሁን ላይ በኢኮኖሚው ውስጥ ካለው እንቅስቃሴ አንጻር " ገቢ ገና አልሰበሰብኩም ፤ ገና አልጀመርኩ " ብሎ ያስባል።

ይህንን ለማስተካከል እና ሀገራዊ ገቢን ለማሳደግ በአዲሱ ሪፎርም ብዙ ስራዎች ይሰራሉ ብሏል።

ገቢ ለማሳደግ በሚሰራው ስራ ግን ተጨማሪ ታክስ አይጣልም፣ የታክስ መጥናኔም አይጨምርም ሲል ገልጿል።

ታዲያ በምን መንገድ ገቢውን ለማሳደግ ነው ያሰበው ?

የገንዝብ ሚኒስትር ዴኤታ ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) ፦

" በየዓመቱ የገቢ መሰብሰብ አቅማችን እየተሻሻለ መምጣቱ የሚታይ ነው። ግን ኢኮኖሚ ውስጥ ካለው አቅም አንጻር ገቢ ገና አልሰበሰብንም / አልጀመርንም የሚል ድምዳሜ ላይ ነው መንግሥት የደረሰው።

ጎረቤት ሀገር አማካይ 15% እና 14% በመሆነበት ሁኔታ እኛ 7% አካባቢ ከሀገራዊ ምርት አንጻር እየሰበሰብን ገቢ እየሰበሰብን አይደለም።

ይህ ሪፎርም አንዱ አንጓ በፊሲካል ፖሊሲው ስር የተቀመጠው ሀገራዊ ገቢ ማሳደግ ነው።

4% GDP በሚቀጥለው ሶስት ዓመት እንጨምራለን ማለት ቀላል ስራ አይደለም ከባድ ነው። በዚህ ዓመት ሰኔ 30 ላይ 527 ቢሊዮን አካባቢ ገቢ አውጀን ከወር በኋላ 851 ቢሊዮን ማወጅ በጣም ከባድ ነው።

ይህንን ስናደርግ ግን ሌሎች ሀገራት እንዳደረጉት ተጨማሪ ታክስ በመጣል፣ ወይም የታክስ ምንጣኔ በመጨመር አይደለም። ኢኮኖሚ ውስጥ ያለውን distortion በማስተካከል ነው ለመጨመር ያሰብነው።

አንድ ምሳሌ ላንሳ፦ የመኪና አስመጪዎች ጋር ገበያ ተኪዶ መኪና ሲገዛ የመኪና ዋጋው 10 ሚሊዮን ከሆነ ገቢዎች ሄደው ደረሰኝ የሚሰጡት ወይ የ1 ሚሊዮን ወይ 2 ሚሊዮን ነው። ስንት እንደሚሸጥ እየታየ ማንም ሰው ገበያው ላይ የሚያውቀውን። ይሄ መስተካከል አለበት።

ከዚህ በፊት በነበረ ሁኔታ እነሱም ችግር ነበረባቸው (መኪና አስመጭዎች) LC የሚሰጣቸው 1000 ዶላር ይሆናል ፤ ሌላው ብር ከኤክስፖርተር ገዝተው ወይ ከጥቁር ገበያ አሰባስበው መኪና ገዝተው ፣ ጅቡቲ አምጥተው ነው የሚሸጡት ይሄን ችግር በመሰረታዊነት ነው ሪፎርሙ የሚቀይረው።

ሁሉ ነገር ግልጽ ይሆናል። ዋጋ እንዲታወቅ እና ግልጽ በሆነ መንገድ እንዲሆን ይደረጋል ሪፎርሙ።

ይህንን መሰል እና በተለያየ ቦታ ያልሰበሰብናቸው ፦

- መርካቶ አካባቢ ያለው የንግድ እንቅስቃሴ ይታወቃል፣

- የንግድ ሂደት ላይ ደረሰኝ መቁረጥ አለመቁረጥ ችግር ይታወቃል

- ጉምሩክ ላይ የ1 ሚሊዮን አይተም አስገብቶ እዛ ቀረጥ ከፍሎም አስገብቶ ገቢዎች ሄዶ ሪፖርት የሚያደርገው ምናልባት የ100 ሺህ እቃ ይሆናል ... ያንን የሚያስታርቅ ዳታውን reconcile የሚያደርግ ሲስተም እየዘረጋን ነው።

እስካሁን ታክስ ሳይከፍል ይከብር የነበረው ባለሃብት አሁን ቶሎ ወደ መስመር መግባት አለበት። ይሄን የሚፈቅድ ነገር አይኖርም።

ጠንካራ የሆነ የ enforcement ስራ ይካሄዳል። እነዚህ የዳታ ጉዳዮችም አሉ። ታክስ ሳይከፍል ሃብት የሚያፈራውን ደግሞ even ያፈራውን ሃብት መውረስ የሚያስችል ለህግ ድጋፍ ተቀምጧል።

ስለዚህ አዲስ የጨዋታ ሕግ ነው ኢትዮጵያ ውስጥ የመጣ ያለው። ይሄ የታክስ መሰብሰብ አቅማችንን እንድናሳድግ ትልቅ አቅም ይሆነናል። የልማት ትልማችንን ለማሳካት፣ የራሳችንን ወጪ በራሳችን ገቢ ለመሻፈን ያስቀመጥነውን ራዕይ እንድናሳካ እድል ይፈጥርልናል። "

#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ዛሬም ሜዳሊያ ውስጥ አልገባንም። @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#Ethiopia

በ3000 ሜትር መሰናክል ፍጻሜ ወደ ማጠናቀቂያው በጥሩ ኃይል ወደፊት እየመጣ የነበረው እና ለኢትዮጵያ ሜዳሊያ ሊያስገኝ ይችላል ተብሎ የተጠበቀው ለሜቻ ግርማ ወድቆ ውድድሩን ማጠናቀቅ አልቻለም።

ጉዳቱ የከፋ እንዳይሆንበትና ጤናው  ደህና እንዲሆን እንመኛለን።

ሳሙኤል ፍሬው 6ኛ ፤ ጌትነት ዋለ ደግሞ 9ኛ ሆነው ነው የጨረሱት።

ሞሮኮ፣ አሜሪካ እና ኬንያ ሜዳሊያዎቹን ወስደዋል።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Ethiopia

" በእግሩ እና በጭንቅላቱ ላይ ጉዳት አልደረሰበትም " - የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን

ኢትዮጵያዊው አትሌት ለሜቻ ግርማ ራሱን ከሳተበት በመንቃት መናገር መጀመሩን ሌኪፕ የተሰኘው ታቃዊው የፈረንሳይ ጋዜጣ አስነብቧል።

በአሁን ሰዓት ተጨማሪ የህክምና ክትትል እየተደረገለት እንደሚገኝም ጋዜጣው ገልጿል።

የፓሪስ 2024 ኦሎምፒክ ቃል አቀባይ በበኩላቸው ፤ " አትሌት ለሜቻ ግርማ አስፈላጊ የሆነ አፋጣኝ ህክምና ተደርጎለታል " ብለዋል።

ስለ ጉዳቱ ዝርዝርና የህክምና ውጤቱን በተመለከተ ግን በይፋ ምንም የተባለ ነገር የለም።

በሌላ በኩል ደግሞ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፥ " አትሌት ለሜቻ ግርማ በውድድሩ ላይ በደረሰበት የመውደቅ አደጋ ወደ ሆስፒታል ተወስዶ በተደረገለት የሲቲ ስካን ምርመራ በእግሩና በጭንቅላቱ ላይ ጉዳት እንዳልደረሰት ከሆስፒታል የሚገኙ የህክምና ባለሙያዎች አረጋግጠዋል " ሲል በይፋ አሳውቋል።

#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia