TIKVAH-ETHIOPIA
1.4M subscribers
54.8K photos
1.37K videos
198 files
3.65K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#BOLIVIA

ቦሊቪያ ውስጥ ወታደሮች የሀገሪቱን ፕሬዜዳንት ቤተመንግሥት በኃይል ሰብረው በመግባት መውረራቸው ተሰማ።

እንቅስቃሴው " መፈንቅለ መንግሥት " ሳይሆን እንዳልቀረ ተነግሯል።

የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ሉዊስ አርሴ የሀገሪቱን ጦር " መደበኛ ያልሆነ እንቅስቃሴ እያደረገ ነው " በማለት አውግዘዋል።

ወታደሮቹ በአስቸኳይ ከቤተመንግሥት እንዲበተኑ ጠይቀዋል።

በቦሊቪያ ቴሌቪዥን ላይ የተሰራጨው ቪዲዮ አርሴ ከሠራዊቱ ዋና አዛዥ ጄነራል ጁዋን ጆሴ ዙኒጋ ጋር በቤተ መንግሥቱ ኮሪደር ላይ ሲፋጠጡና ሲነጋገሩ ታይተዋል።

አርሴ ፤ " እኔ የአንተ አለቃ ነኝ፣ ወታደሮቹንም እንድታስወጣ አዝዤሃለሁ እናም ለትዕዛዜ መገዛት አለብህ !! " ሲሉ ተደምጠዋል።

ዙኒጋ ወታደሮቹን ይዘው ወደ ቤተመንግሥት ሳይገቡ በፊት ውጭ ላይ ለሪፖርተሮች በሰጡት ቃል ፥ " ማጥፋት ይቁም፣ ሀገራችንን ወደ ድህነት መምራት ይቁም ፣ ሰራዊታችንን ማዋረድ ይቁም " ብለዋል።

የጦሩ አዛዥ ዙኒጋ ፥ " አዲስ የሚኒስትሮች ካቢኔ ይዋቀራል ፤ በእርግጠኝነት ነገሮች ይቀየራሉ፣ ሀገራችን ከዚህ በኋላ አሁን ባለው ሁኔታ መቀጠል አትችልም " ሲሉ ተደምጠዋል።

ፕሬዜዳንት አርሴ በቪድዮ ባሰራጩት መልዕክት ፥ ሀገሪቱን ከሚታየው የመፈንቅለ መንግሥት እንቅስቃሴ ለመታደግ ህዝቡ ተሰባስቦ እና ተደራጅቶ ወደ ጎዳና እንዲወጣና ዲሞክራሲውን እንዲታደግ ጥሪ አቅርበዋል።

#Bolivia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Video
#Update

በቦሊቪያ የተሞከረው መፈንቅለ መንግሥት ከሸፈ።

ሙከራው ሰዓታትን እንኳን አልቆየም።

የፕሬዜዳንቱን ቤተመንግሥት በኃይል ሰብረው ገብተው የወረሩት ወታደሮች ከቤተመንግሥቱ አካባቢ መሄዳቸው ተሰምቷል።

ፕሬዜዳንት ሉዊስ አርሴ ፤ ወታደሮችን እየመሩ ቤተመንግሥት የገቡትን የሠራዊቱን አዛዥ ጄነራል ጁዋን ጆሴ ዙኒጋን ከስልጣን አውርደው በሌላ ተክተዋል።

አዲሱ የሠራዊት አዛዥ ጆሴ ዊልሶን ሳንቼዝ ሁሉም ቤተመንግሥት የመጡ ወታደሮች ወደ የመጡበት ወታደራዊ ሰፈር /ክፍል እንዲመለሱ አዘዋል።

ይህን ተከትሎም ወታደሮቹ ከስፋራው ለቀው ሄደዋል።

ፕሬዝዳንት አርሴ አዲስ የአየር ኃይል አዛዥ እና የባህር ኃይል አዛዥም ሾመዋል።

ፕሬዝዳንቱ ወታደሮች ቤተመንግሥቱን ሰብረው መግባታቸውን እና መውረራቸውን ተከትሎ ህዝቡ በነቂስ ተደራጅቶ ወደ ጎዳና እንዲወጣና የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ እንቅስቃሴውን እንዲያከሽፍ እና ዴሞክራሲውን እንዲያስጠብቅ ጥሪ አቅርበው ነበር።

በዚህም በርካቶች የሀገሪቱን ባንዲራ ይዘው በቤተመንግሥቱ አካባቢ ተሰብሰበው ነበር።

ፕሬዝዳንቱ ሙከራው መክሸፉን ተከትሎ ህዝቡን  በእጅጉ አመስግነዋል።

ወታደሮችን እየመሩ ቤተመንግሥት የገቡት ጄነራል ጁዋን ጆሴ ዙኒጋን ምንም እንኳን የመፈንቅለ መንግሥቱ መሪ ነኝ ብለው በግልጽ ባይናገሩም ፥ " ጥፋት ይቁም ፤ ሀገራችንን ወደ ድህነት መምራት ይቁም፣ ሠራዊታችንን ማዋረድ ይቁም " ሲሉ ተደምጠው ነበር።

ጦሩ ዴሞክራሲን ወደነበረበት ለመመለስ እና የፖለቲካ እስረኞችን ነጻ ለማድረግ እንደሚጥርም ሲናገሩ ተደምጠዋል።

ዙኒጋን አዲስ የሚኒስትሮች ካቢኔ እንደሚቋቋም ከአሁን በኃላ ሀገሪቱ አሁን ባለው መንገድ እንደማትቀጥልም ገልጻው ነበር።

ጄነራል ዙኒጋን ከሽፏል ከተባለው የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ በኃላ ቀጣይ ዕጣፋንታቸውን እና በምን ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ ለጊዜው አልታወቀም።

ቦሊቪያ 🇧🇴 ፦ በደቡብ አሜሪካ የምትገኝ ከ12 ሚሊዮን በላይ ህዝብ የሚኖሩባት ሀገር ናት።

#Bolivia
#failedcoup

@tikvahethiopia
" እስራዔል ምዕራባውያንን ተማምና ጦርነቱን የምታሰፋ ከሆነ ቱርክ ሊባኖስን ለመደገፍ ትገደዳለች " - ቱርክ

የቱርኩ ፕሬዝዳንት ረሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን፣ " እስራዔል የጦርነቱን አድማስ የማስፋት ፍላጎት አላት " ሲሉ ተናግረዋል፡፡

" እስራዔል ትኩረቷን ሊባኖስ ላይ አድርጋለች፤ የምዕራቡ ኃይሎች ከሁነቱ ጀርባ ሆነው እስራዔልን እየገፋፉ ነው " ብለዋል ፕሬዝዳንቱ፡፡

ጠ/ሚ ኒታንያሁ ግጭቱን አስፍተው አካባቢያዊ ቀውስ ለመፍጠር ተዘጋጅተዋል ሲሉ ወቅሰዋል፡፡

" እስራዔል ምዕራባውያንን ተማምና ጦርነቱን የምታሰፋ ከሆነ ቱርክ ሊባኖስን ለመደገፍ ትገደዳለች " ብለዋል።

More 👇
https://t.me/+LM-bJ8NzZMcxMjA8

#shafaqnews
@thiqaheth
TIKVAH-ETHIOPIA
Video
#Update

ወታደሮችን እየመሩ የቦሊቪያው ፕሬዚዳንት አርሴ ቤተ መንግስትን በኃይል ሰብረው በመግባትና በመውረር የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ ያደረጉት ጄነራል ሁዋን ሆዜ ዙኒጋ በሀገሪቱ ፖሊስ በቁጥጥር ስር ውለው እስር ቤት ገብተዋል።

@tikvahethiopia
#AddisAbaba

የአዲስ አበባ ፖሊስ ሰኔ 17/2016 ዓ/ም አንዲት መና ከበደ የተባለች የ26 ዓመት ወጣት ሴትን በመኪና ስርቆት ወንጀል በመጠርጠር በቁጥጥር ስር አውሏል።

ፖሊስ፥ ግለሰቧ ጥዋት 12:30 ገደማ ' ቤተል ቢጫ ፎቅ ' አካባቢ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3-B32912 አ.አ የሆነች ተሽከርካሪን የግል ተበዳይ መኖሪያ ቤቱ ደጃፍ ላይ ሞተር ሳያጠፋ አቁሞት ጃኬት ለመደረብ በገባበት ይዛ መሰወሯንና ከግማሽ ቀን ፍለጋ በኋላ ሰሚት አካባቢ መያዟን አስረድቷል።

ፖሊስ ግለሰቧንም ከነተሽከርካሪው ፎቶ በማንሳት አሰራጭቷል።

ከዚህ ጋር በተያያዘ ግለሰቧን እናውቃታለን ያሉ ሰዎች በማህበራዊ ሚዲያዎች ፤ መኪናውን መውሰድ አለመውሰዷን በግልጽ ባያሰፍሩም የሃብታም ልጅ እንደሆነች ፣ ስህተት እንደተፈጠረና ከወንጀሉ ነጻ ተብላ ወደ ቤት መግባቷን ጽፈዋል።

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ይፋ ባደረገው መረጃ በተሽከርካሪ ስርቆት የተጠረጠረችው ግለሰብ መና ከበደ ክስ እንደተመሰረተባት አሳውቋል።

በዛሬው ዕለት ፍርድ ቤት መቅረቧንም አመልክቷል።

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ግለሰቧ ተሽከርካሪውን በመስረቋ ፓሊስ ምርመራ አጣርቶ መዝገቡን ለአቃቤ ህግ ልኮ ክስ እንዲመሰረትባት ማድረጉን አስረድቷል።

" በአንዳንድ  ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ' ግለሰቧ ተለቃለች ' እና ' ወንጀሉን ሳታውቅ ነው የፈፀመችው ' የሚሉ መረጃዎች እየተሰራጩ  ይገኛል " ያለው ፖሊስ የግል ተበዳይ መኪናቸው መሰረቁን ለፖሊስ እንዳመለከቱ ግለሰቧም ተሽከርካሪውን ለረጅም ሰዓት ይዛ መሰወሯ  ታሳቢ በማድረግና ድርጊቷም በማስረጃ በመረጋገጡ ዓቃቤ ህግ በተሽከርካሪ ስርቆት ክስ መመስረቱን አሳውቋል።

#AddisAbabaPolice

@tikvahethiopia
#AddisAbaba⛽️

በአዲስ አበባ የሚታየው የነዳጅ እጥረት በቀጣይ ቀናት እንደሚፈታ የኢትዮጵያ የነዳጅ አቅራቢዎች ድርጅት አሳውቋል።

የነዳጅ እጥረት በከተማዋ መከሰቱን የገለጸው ድርጅቱ " እጥረቱ ያጋጠመው በዒድ አል አድሃ አረፋ በዓል ምክንያት እሑድ ሰኔ 9 በማግሥቱ ሰኔ 10 ቀን 2016 ዓ/ም ነዳጅ ከጂቡቲ ባለመጫኑ ነው " ብሏል።

የነዳጅ ማጓጓዝ ሒደቱ አምስት እና ስድስት ቀናትን የሚወስድ መሆኑንና አሁን የሚስተዋለው እጥረት በመጪዎቹ ቀናት እንደሚፈታ አሳውቋል።

ከሱሉልታ መጠባበቂያ ቤንዚን ከአዋሽ መጠባበቂያ ደግሞ ናፍጣ እየተጓጓዘ መሆኑንም በማመልከት የነዳጅ ችግሩ በእርጠኝነት በ2 ቀናት እንደሚፈታ ተናግሯል።

በየተለያዩ የነዳጅ ማደያዎች ላይ ከሚታየው የነዳጅ እጥረት ባለፈ ማደያዎች ነዳጅን ከተጠቃሚዎች እንደሚደብቁ አሽከርካሪዎች ለሪፖርተር በሰጡት ቃል ገልጸዋል፡፡

ሕገወጥ በሆነ መንገድ በውኃ ፕላስቲኮች ጭምር የሚሸጡ መኖራቸውንም ተናግረዋል፡፡

በዚህም ምክንያት ባለፉት ሳምንታት በመዲናዋ ነዳጅ ለመቅዳት የሚጠብቁ ረዣዥም የተሽከርካሪ ሠልፎች መታየታቸውንና አሁንም እጥረቱ እንዳለ አክለዋል፡፡ #ሪፖርተር

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia ላለፉት ስድስት ቀናት በመላ አገሪቱ ሲሰጥ የቆየው የመውጫ ፈተና ተጠናቋል። 57 የመንግሥት እና 124 የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተማሪዎቻቸውን ማስፈተናቸውን የትምህርት ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። ከመውጫ ፈተናው ጋር በተያያዘ ቅሬታ አለን ያሉ ተማሪዎች ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል። በተለይ ከተነገርን ይዘት እና ከተዘጋጀው ብሉ ፕሪንት ጋር የሚገናኝ አይደለም ብለው…
#MoE

የ2016 ዓ/ም የመውጫ ፈተና እና የሪሚዲያል ማጠቃለያ ፈተና ውጤቶች መቼ ይፋ ይደረጋሉ ?

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የ2016 ዓ/ም የሪሚዲያል ተማሪዎች የማጠቃለያ ፈተና እና የዕጩ ተመራቂዎች የመውጫ ፈተና መቼ ይፋ እንደሚደረግ ትምህርት ሚኒስቴርን ጠይቋል።

የትምህርት ሚኒስቴሩ ከፍተኛ አመራር ፥ የሪሚዲያል ተማሪዎቹ ውጤት ከሀገር አቀፍ የመውጫ ፈተና መጠናቀቅ በኋላ ባሉት ቀናት ይፋ እንደሚደረግ ተናግረዋል።

በጣም ከዘገየ እስከ ሰኞ ሰኔ 24/2016 ዓ.ም ይፋ ይሆናል ብለዋል፡፡

የመውጫ ፈተና ውጤት በቀጣይ ቀናት ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎቻቸውን ማስመረቅ ከመጀመራቸው በፊት ይፋ እንደሚደረግ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልፀዋል፡፡

#TikvahEthiopia

Via @tikvahuniversity
#eQUB_APP

መልካም ዜና ለዕቁብተኞች! የዕቁብ ክፍያዎን ካሉበት ቦታ ሆነው ለአጠቃቀም ቀላል እና ምቹ በሆነው የዕቁብ መተግበርያ ከያሉበት ቦታ ሆነው ህልሞን ያሳኩ።

የዕቁብ መተግበርያን አሁን ይጫኑ👇
📱 Android - Google Play | 📱 iPhone - App Store

Telegram Channel: @equbapp

ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥራችን 0116671717 ወይም 0116670404 ይደውሉ።
#DStvEthiopia

🔥 ከከባድ የምድብ ጨዋታዎች በጓላ የአወሮፓ ጨዋታ ቅዳሜ ምሽት ጥሎ ማለፍ ጫዋታዎች ይጀምራሉ!

🤔 ፉክክሩም አይሏል! እነማን ወደ ሩብ ፍፃሜ ያልፋሉ? የእናንተን አስተያየት ከስር አጋሩን!

ለናንተ ምርጡ ቡድንስ ማነው? መልሶቻችሁን ከስር አጋሩን!

በጀርመን የሚደረጉትን ደማቅ ጨዋታዎች በቀጥታ በዲኤስቲቪ ሱፐርስፖርት ቻናሎች በወር ከ350 ብር ከጎጆ ፓኬጅ ጀምሮ ይከታተሉ!

የዲኤስቲቪ አገልግሎቶችን ለማግኘት ከታች ያለውን የMyDStv Telegram bot ሊንክ ይጫኑ!
👇
https://bit.ly/3RFtEvh

#Euro2024onDStv #ሁሉምያለውእኛጋርነው #DStvEthiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia ላለፉት ስድስት ቀናት በመላ አገሪቱ ሲሰጥ የቆየው የመውጫ ፈተና ተጠናቋል። 57 የመንግሥት እና 124 የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተማሪዎቻቸውን ማስፈተናቸውን የትምህርት ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። ከመውጫ ፈተናው ጋር በተያያዘ ቅሬታ አለን ያሉ ተማሪዎች ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል። በተለይ ከተነገርን ይዘት እና ከተዘጋጀው ብሉ ፕሪንት ጋር የሚገናኝ አይደለም ብለው…
#MoE

ትናንት የተሰጠው የፋርማሲ ትምህርት የመውጫ ፈተና ተሰርዞ በድጋሚ ይሰጣል ተብሏል።

ትምህርት ሚኒስቴር ፈተናው " የቴክኒክ ችግር " አጋጥሞት እንደነበር ገልጿል።

ተማሪዎች በበኩላቸው ቀደም ብሎ ፈተናው ወጥቶ በወረቀት እትም እና በPDF መሰራጨቱንና ተማሪዎችም ሰርተው መግባታቸውን አመልክተዋል።

ትምህርት ሚኒስቴር ግን ፈተናው " የቴክኒክ ችግር " ስላጋጠመው ፈተናው በድጋሜ  በድጋሜ ቅዳሜ ሰኔ 22/2016 ዓ.ም ጠዋት ከ3:00 ሰዓት ጀምሮ እና ከሰአት ከ8:00 ሰዓት ጀምሮ ይሰጣል ብሏል።

ምን አይነት የቴክኒክ ችግር እንደሆነ በዝርዝር ያለው ነገር የለም።

ለፈተናው ተቀምጠው የነበሩ የፋርማሲ ተማሪዎች በየተፈተኑበት የፈተና ጣቢያ በሰዓቱ በመገኘት በድጋሜ የሚሰጠውን ፈተና እንዲወስዱ ማሳሰቢያ ተላልፏል።

ተማሪዎች ምን አሉ ?

የጥዋቱም ይሁን የከሰዓቱ ፈተና ሙሉ በሙሉ በሚባል መልኩ እንዴት እንደሆነ ባይታወቅም ወጥቶ ተማሪዎች በበድን ሰርተውት እንደገቡ ገልጸዋል።

ሌላው ፈተናው ከብሉፕሪነቱ ጋር እንደማይጣጣም ፤ ትምህርቱንም የሚመዝን ፈተና እንዳልወጣ አመልክተዋል።

የባለፉት ፈተናዎችን እንዳዩና የዚህ አይነት ፈተና ግን እንዳልነበር ጠቁመው ፈተናው ማስተካከያ እንዲደረግበት አሳስበዋል።

የ2016 ዓ/ም ፈተና ትላንት መጠናቀቁ ይታወሳል።

የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፥ " የዘንድሮው ፈተና ከ220 በላይ ፕሮግራሞች ያለምንም ችግር Smoothly ነው የተሰጠው " ብሎ ነበር።

" ከፈተናዎቹ ጋር የተያያዘም ምንም አይነት Issue አላጋጠመንም፤ አንድም ቅሬታ ለትምህርት ሚኒስቴር አልደረሰም " ሲል ነበር ያስረዳው።

ሚኒስቴሩ ይህን ቢልም  ፤ በተለይ ከተነገርን ይዘት እና ከተዘጋጀው ብሉፕሪንት ጋር የሚገናኝ አይደለም ብለው ፦
- የማኔጅመንት
- የማርኬቲንግ ማኔጅመንት
- የሀይድሮሊክና ውሃ ሃብት
- የቬተርነሪ ሜድስን
- የኸልዝ ኢንፎርማቲክስ ተማሪዎች ተማሪዎች ቅሬታ አቅርበዋል።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray የትግራይ ክልል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዜዳንት እና ምክትል ፕሬዜዳንት በጋራ የስራ መልቀቂያ ደብዳቤ አስገቡ። ስራ መልቀቂያውን ያስገቡት ፤ " በፍትህ እና የዳኝነት ሰርዓቱ ለውጥ ለማምጣት ያሰብናቸው ፣ ያቀድናቸው የጀመርናቸው ያስቀመጥናቸው አቅጣጫዎች ለማሳካት የሚያስችል ሁኔታ ማግኘት ስላልቻልን ነው " ብለዋል። ሰኞ ሰኔ 17/2016 ዓ.ም የተፃፈው የስራ መልቀቅያ ደብዳቤ በበርካታ የማህበራዊ…
#Update

" ጊዚያዊ አስተዳደሩ ጥያቄያችን ለመመለስ ቃል ስለገባ የስራ መልቅቅያ ጥያቄያችን ትተነዋል " - የትግራይ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዜዳንትና ምክትል ፕሬዜዳንት

የትግራይ ክልል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዜዳንትና ምክትል ፕሬዜዳንት ያስገቡትን የመልቀቂያ ደብዳቤ እንደተውት አሳወቁ።

ፕሬዜዳንቱና ምክትል ፕሬዜዳንቱ ይፋ ባደረጉት መግለጫ ፤ ሰኔ 17 ቀን 2016 ዓ.ም ያቀረቡት የስራ መልቀቂያ ደብዳቤ ተከትሎ ሰኔ 18 /2016 ዓ.ም ከክልሉ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ ውይይት ማደረጋቸውን ገልጸዋል።

በዚ ውይይት ያቀረቡዋቸው ጥያቄዎች ለመመለስ ቃል በመገባቱ ስራ የመልቀቅ ጥያቄያቸውን እንደተውት አሳውቀዋል።

ያቀረቡዋቸው ጥያቄዎች ምን እንደሆኑ በግልፅ ያላብራሩ ሲሆን ከላይ እስከ ታች የሚገኘው የፍርድ ቤት አካል ስራውን ተረጋግቶ እንዲሰራ መልእክት አስተላልፈዋል።

ፕሬዜዳንቱና  ምክትል ፕሬዜዳንቱ የስራ መልቀቂያ ማስገባታቸው ተከትሎ የወረዳና የዞን ፍርድ ቤቶች ስራ የማቆም አድማ መምታት ጀምረው ነበር

ከክልሉ ፕሬዜዳንት ከተደረገው ውይይት በኃላ ችሎቶች ተከፍተው አገልግሎት በመስጠት ላይ መሆናቸው የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል በአካል ተዘዋውሮ ተመልክቷል።

ከመቐለ ውጪ በመላው ክልል ያሉ ፍርድ ቤቶች መደበኛ አገልግሎት መስጠት መቀጠላቸው የከፍተኛ ፍርድ ቤቱ የፕሮቶኮል ሹም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጠዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia            
#ጎንደር

° “ ውሃ ካጣን ከወራት በላይ ሆነን፤ እንኳን ለመታጠብ ለመጠጥም አልተገኘም ” - የጎንደር ከተማ ነዋሪዎች

° “ ጉድጓድ ስናስቆፍር በ4 ወራት ይደርሳል ብለን አንድ ዓመት ከ8 ወራት ወስዷል ” - የከተማው ውሃና ፍሳሽ 


በአማራ ክልል የጎንደር ከተማ ነዋሪዎችና የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል ኢንተርን ሀኪሞች፣ የውሃ ችግር እንደፈተናቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

የከተማው ነዋሪዎች በሰጡት ቃል፣ “ ውሃ ካጣን ከወራት በላይ ሆነን፤ እንኳን ለመታጠብ ለመጠጥም አልተገኘም። በአፋጣኝ መፍትሄ እንሻለን ” ብለዋል።

በከተማው የውሃ አቅርቦት እንደሌለ፣ በተለይ ህፃናት የውሃ ጥሙን መቋቋም እንዳልቻሉ፣ ሰው የክረምት ውሃ ለመጠጣት መገደዱን ነዋሪዎቹ አስረድተዋል። 

ከዚህ ባለፈ ነዋሪዎች የጉርጓድ ውሃ በሰልፍ የመጠቀም ደረጃ እንደደረሱ አመልክተዋል።

ለቅሬታው ምላሽ እንዲሰጡ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የጠየቃቸው የጎንደር ከተማ ውሃና ፍሳስ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ወርቅነህ አያል ፤ “ እውነት ነው። እንዲያውም ማህበረሰቡ ታጋሽ ነው ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

“ አሁን ዝናብ ስለዘነበ ትንሽ ይቀንሳል እንጂ በአንድ ወር ነው ሰው ውሃ ሲያገኝ የነበረው። ግድቡ ሙሉ ለሙሉ ቆሞ ነበር። አሁን ትንሽ ውሃ ስለያዘ ምርት ስለጀመርን አሁን ወደ 25 ቀን እየወረደ ነው ” ብለዋል።

የኢንተርን ሀኪሞቹን ቅሬታ በተመለከተ፣ “ ሆስፒታል ላይ ግን 24 ሰዓት ነው የምንሰጠው። መብራትና አጠቃላይ ምርት ቆሞ ካልሆነ አይቋረጥም ” ነው ያሉት።

“ የማህበረቡ ቅሬታ ግን እውነቱን ለመናገር ከቅሬታ ባለፈ ሌላ ነገር ቢሉም አይፈረድባቸውም ትክክል ናቸው ” ያሉት አቶ ወርቅነህ፣ “ እንደዚህ ትዕግስተኛ የሆነ ማህበረሰብ የለም ” ሲሉ ተናግረዋል።

ችግሩ ከቆዬ ለምን በወቅቱ መፍትሄ እንዳልተቸረው ሲያስረዱም፣ “ ጉድጓድ ስናስቆፍር በ4 ወራት ይደርሳል ብለን አንድ ዓመት ከ8 ወራት ወስዷል። እንደዚህ አይነት ቻሌንጆች አሉብን ” ብለዋል።

ችግሩን ለመቀረፍ የገጠማችሁ ዋናው ችግር ምንድን ነው ? ለሚለው ጥያቄ የፋይናንስ ችግር እንዳለባቸው ገልጸው፣ ምን ያህል በጀት እንደሚያስፈልግ ከመናገር ግን ተቆጥበዋል።

“ ችግሩን መነሻ ተደርጎ የአጭር፣ የአስቸኳይ፣  የመካከለኛ እና የረጅም ጊዜያት ተብሎ ስራዎች እየተሰሩ ነው። አንዳንዶቹን ቶሎ እናጠናቅቃቸዋለን ” ብለዋል።

ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት የሚበጀውን በተመለከተ፣ መንግስት ለጉዳዩ ትኩረት ሰጥቶ ሊሰራ እንደሚገባ አሳስበው፣ ማህበረሰቡ ላሳየው ታጋሽነት ምስጋና አቅርበዋል። 

ለነዋሪዎቹ ከሚያስፈልገው የውሃ መጠን እየቀረበ ያለው ምን ያህሉ እንደሆነ፣ ምን ያህል ጉድጓድ እየተቆፈረ እንደሆነ፣ ችግሩን በተጨባጭ እስከ መቼ ለመቅረፍ እንደታሰበ በቀጣይ መረጃ የምናደርሳችሁ  ይሆናል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Kenya የኬንያ ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ በሀገሪቱ ከፍተኛ የሆነ ተቃውሞ የቀሰቀሰው የፋይናንስ ረቂቅ ሕግን እንደሚያስቀሩት / እንደማይፈርሙበት አስታውቀዋል። ሩቶ እዚህ ውሳኔ ላይ የተደረሱት ተቃውሞውን ተከትሎ ቢያንስ 20 ሰዎች ከተገደሉ በኋላ ነው። ፕሬዜዳንቱ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ፤ " ኬንያውያን በሕጉ ዙሪያ ያሰሙትን ተቃውሞ በደንብ ተከታትያለሁ፤ ስለዚህም ሕጉን እንደማይፈልጉት በግልጽ ተናግረዋል፤…
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#ኬንያ

ምንም እንኳን ትላንትና የኬንያ ፕሬዜዳንት ዊሊያም ሩቶ በፋይናንስ ረቂቅ ሕጉ ላይ ፊርማቸውን እንደማያኖሩ እና ሙሉ በሙሉ ውድቅ እንደተደረገ ቢያሳውቁም ዛሬም ተቃዋሚዎች አደባባይ ወጥተው ነበር።

ናይኖቢ ውስጥ የመንግስት ጸጥታ ኃይሎች አደባባይ በወጡ ተቃዋሚዎች ላይ አስለቃሽ ጪስ ተኩሰዋል።

ወደ ፕሬዜዳንቱ ቤተመንግስት የሚወስደውን መንገድ ዘግተውታል።

ዛሬም በከተማይቱ በርካታ የንግድ ተቋማት ባደረባቸው ስጋት በራቸውን ሳይከፍቱ ነው የዋሉት።

ከናይሮቢ በተጨማሪ ሞምባሳና ኪሱሙ ተቃዋሚዎች አደባባይ ወጥተው ነበር።

ትላንት ሩቶ ውሳኔያቸው ካሳወቁ በኃላ ተቃዋሚዎች ፦
- ቀጣይ ወዳሉበት ቤተመንግስት እንመጣለን። ይጠብቁን !
- ' ከሃዲ ፣ ወንጀለኞች ' እያሉ በቴሌቪዥን ለተናገሩት ዋጋ ይከፍላሉ
- ስልጣን የህዝብ ነው
- ለውሳኔው አርፍደዋል
- አሁን ደግሞ የስልጣን መልቀቂያ ለማስገባት ይዘጋጁ !
- ስልጣን ለመልቀቅ ይዘጋጁ የሚሉ መልዕክቶችን በማህበራዊ ሚዲያ ላይ በስፋት ሲያሰራጩ ነበር።

ኬንያውያን የፋይናንስ ረቂቁን " ኑሮ ያስወድድብልናል ፣ የስራ አጥነት እጅግ በከፋበት ሰዓት ግብር መጨመር አይገባም ፣ ተደራራቢ ግብር በቃን " በሚል ነበር ተቃውሞ የጀመሩት።

በወጣቶች በተመሩ የጎዳና ላይ ተቃውሞዎች ቢያንስ 20 ሰዎች ህይወታቸውን እጥተዋል። ተቃውሞው እየበረታ ሲመጣም ሩቶ " በቃ ረቂቅ ሕጉን ትቼዋለሁ " የሚል ውሳኔያቸውን አሳውቀዋል።

#Kenya

@tikvahethiopia