TIKVAH-ETHIOPIA
1.44M subscribers
55.9K photos
1.4K videos
202 files
3.77K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Ethiopia

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የግል የውጭ ምንዛሪ ቢሮዎችን ለመክፈት የሥራ ፈቃድ ማመልከቻዎችን መቀበል ጀመረ።

ከሐምሌ 22 ቀን 2016 ጀምሮ ሥራ ላይ በዋለው የውጭ ምንዛሪ መመሪያ ቁ.01/2016 መሠረት የግል የውጭ ምንዛሪ ቢሮ ለመከፈት የሚፈልጉ የሥራ ፈቃድ ማመልከቻ እንዲያቀርቡ ብሔራዊ ባንክ ጥሪ አቅርቧል።

በገበያ ላይ ተመሥርተው የውጭ ምንዛሪ በጥሬ ገንዘብ መሸጥና መግዛት የሚፈልጉ የግል የውጭ ምንዛሪ ቢሮዎች እንዲቋቋሙ በተፈቀደው መሠረት የኢትዮጵያ ዜግነት ያላቸው በሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጭ የሚኖሩ እንዲሁም የሌላ ሀገር ዜግነት ያላቸው ትውልደ ኢትዮጵያውያን የውጭ ምንዛሪ ቢሮ መስፈርቱን አሟልተው ከብሔራዊ ባንክ ፍቃድ ሲያገኙ መክፈት ይችላሉ፡፡

የውጭ ምንዛሪ ቢሮ ለመክፈት የሚያስፈልገው የካፒታል መጠን እንዲሁም ሌሎች ለሥራው የሚያስፈልጉ መስፈርቶች ከላይ ተያይዟል።

ካፒታልን በተመለከተ በመመሪያው ላይ የሰፈረው ይህ ነው ፦

Fulfills the minimum capital requirement of Birr 15 million and is able to provide a Security Deposit of Birr 30 million to be placed in a blocked account (which can be interest-earning) at any bank:


ዝቅተኛ 15 ሚሊዮን ብር ካፒታል እና በዝግ በየትኛውም ባንክ የተቀመጠ 30 ሚሊዮን ብር ያስፈልጋል።

ባንኩ " የግል የውጭ ምንዛሪ ቢሮዎች መቋቋም የውጭ ምንዛሪ ገበያን መሠረት ለማስፋትና ለማጠናከር እንዲሁም የውጭ ምንዛሪ በጥሬ ገንዘብ ለመሸጥም ሆነ ለመግዛት የሚሹ ደንበኞችን ፍላጎት ለማርካት እንደሚረዳ እሙን ነው " ብሏል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ አቶ ማሞ ምህረቱ ፣ " የግል የውጭ ምንዛሪ ቢሮዎች እንዲከፈቱ የሥራ ፈቃድ መስጠታችን የኢትዮጵያን የፋይናንስ ዘርፍ ለውጭ ኢንቨስትመንት ለመክፈትና ዘርፉን በቀጣይ ዓመታት ከዓለም ምርጥ ተሞክሮዎችና አሠራሮች ጋር የተመጣጣነ እና ተወዳዳሪ የሆነ ለማድረግ የጀመርነውን አዲስ ምዕራፍ እንዲሁም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የጀመረውን ስትራቴጂካዊ የሆነ ለውጥ ከግብ ለማድረስ በቁርጠኝነት መነሣሣቱን የሚያመለከት ነው " ብለውታል።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
የደመወዝ ማሻሻያ / ጭማሪ ይፋ ተደርጓል ?

አጭር መልስ ፦ ሀሰት ነው ! ምንም ይፋ የተደረገ ነገር የለም።

እስካሁን የመንግሥት ሠራተኞች የደመወዝ ማሻሻያ / ጭማሪ ዝርዝር መረጃ ይፋ አልተደረገም።

በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ በቴሌግራም ፣ በፌስቡክ እየተዘዋወረ ያለው " የፌዴራል መንግሥት ሲቪል ሰርቫንት ደመወዝ ማሻሻያ " የሚለው መረጃ ምንም ምንጩ የማይታወቅ ነው።

የተሰራጨው የደመወዝ ማሻሻያ ሰንጠረዥ ፤ የፅሁፍ ስህተቶች ጎልተው የሚታዩበት፣ የአጻጻፉ ግድፈት ያለበት፣ የድምር ጭምር ግልጽ እና ቀላል ስህተት ያለበት ነው።

ሌላው ማን ይፋ እንዳደረገው አይታወቀም።

ማህተም አላፈረበትም ፤ መረጃውንም ያወጣው መ/ቤትም አይታወቅም።

እስካሁን በይፋ ለህዝብ የተሰራጨ የደመወዝ ጭማሪ ዝርዝር መረጃ የለም።

በመሆኑንም እየተዘዋወረ ያለው የደመወዝ ጭማሪ ሰንጠረዥም ሆነ የደመወዝ ጭማሪ መረጃ ሀሰተኛ ነው።

መንግሥት በቅርቡ የደመወዝ ጭማሪ እንደሚደረግ ማሳወቁ ይታወሳል።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
#Ethiopia

በማራቶን ውድድር ላይ " ተጠባባቂ ነህ " ተብሎ የተያዘውና ለውድድሩ የተመረጠ ሌላ አትሌት መጎዳቱን ተከትሎ ሀገሩን ወክሎ የተሳተፈው ጀግናው አትሌት ታምራት ቶላ ለሀገሩ ኢትዮጵያ ወርቅ ማምጣት ብቻ ሳይሆን በሚደንቅ ብቃት የኦሎምፒክ ሪከርድም ጭምር ነው የሰበረው።

ጀግናው አትሌት ታምራት ከአትሌት ገዛኸኝ አበራ በኋላ (ከ24 ዓመታት በኃላ) ነው የመጀመሪያውን የኦሎምፒክ የወርቅ ሜዳልያ ለሀገራችን ያስገኘው።

ሌላው አንጋፋው ኢትዮጵያ ሁል ጊዜ በስራው የምታመሰግነው የ42 ዓመቱ አትሌት ቀነኒሳ በቀለ 39ኛ ደረጃ ይዞ እጅግ ከባድ የነበረውን የፓሪስ ማራቶን አጠናቋል።

አትሌት ደሬሳ ገለታም 5ተኛ ደረጃ በመውጣት እጅግ በጣም አበረታችና ተስፋ ሰጪ ውጤት አስመዝግቧል።

ምንም እንኳን ዛሬ በወንዶች ማራቶን የተገኘው ውጤት አስደሳችንና የሚያኮራ ቢሆንም በፓሪስ እየተመዘገበ ያለው ውጤት ኢትዮጵያን የሚመጥናት አይደለም።

በጭቅጭቅና ንትርክ በተሞላው በዚህ ውድድር ኢትዮጵያ ያገኘችው እስካሁን 3 ሜዳሊያ ብቻ ነው። 1 ወርቅ እና 2 ብር ብቻ።

የአትሌቲክሱ ዘርፍ ትኩረት ተሰጥቶ ያሉ ችግሮች እና ኢትዮጵያን ዝቅ ያደረጉ ነገሮች ሁሉ ተፈትሸው መለወጥ እንዳለባቸው የፓሪስ ኦሎምፒክ በግልጽ አመላክቷል።

ከሚዲያ በዘለለ ስለዚህ ሀገር አትሌቲክስ ሁሉም " የሀገር ክብር ያሳስበኛል " የሚል ቁጭ ብሎ ተነጋግሮ በአስቸኳይ ለውጥ ማምጣት አለበት። እንዲህ ከቀጠለ በዓለም ደረጃ የነበረን ክብር የማናጣበት ምክንያት የለም።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
በዚህም ምንም ሜዳሊያ አላገኘንም። የኬንያዋ ኪፕዬጎን ወርቁን ወስዳዋለች። አውስትራሊያ ብር እንዲሁም እንግሊዝ ነሐስ አግኝተዋል። ድርቤ ወልተጂ 4ኛ እንዲሁም ጉዳፍ ፀጋይ 12ኛ በመሆን አጠናቀዋል። @tikvahethiopia
#Kipyegon : የኬንያዋ አትሌት ፌዝ ኪፕዬጎን በሶስት (3) ተከታታይ ኦሎምፒክ በ1500 ሜትር የወርቅ ሜዳሊያ ለሀገሯ ገቢ በማድረግ ታሪክ ሰርታለች።

ዛሬ በ 3:51.29 በመግባት የኦሎምፒክ ሪከርድ ሰብራለች።

አትሌቷ የ1500 ሜትር የዓለም ሪከርድ ባለቤትም ናት።

#TikvahEthiopia #WA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#TPLF

ህወሓት የምርጫ ቦርድን ውሳኔ ፤ " ጥያቄው ሌላ መልሱ ሌላ " ሲል ውድቅ አድርጎታል።

ህወሓት ባወጣው መግለጫ ፥ " የስራ ኃላፊዎቼ ከክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩና ከሚመለከታቸው የፌደራል መንግስት የስራ ኃላፊዎች ጋር ተደጋጋሚ ውይይቶችን በማካሄድ ሕጋዊ ሰውነታችን እንዲመለስ መግባባት ላይ ተደርሷል " ብሏል።

" በአፍሪካ ህብረት ፓናል ውይይትም ይህ ጉዳይ ተነስቶ ህጋዊ ሰውነቱ መመለስ እንዳለበት ስምምነት ተደርሶበታል " ሲል ገልጿል።

ይህን ተከትሎ " ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ህጋዊ ሰውነታችን ወደነበረበት እንዲመለስልን ብቻ በሀምሌ 19 ቀን 2016 ዓ.ም ጥያቄ አቅርበናል " ብሏል።

ሆኖም " ቦርዱ የፕሪቶሪያውን ስምምነት፣ ከዚህ በፊት በሌሎች የፌደራል ተቋማት የተሰጡትን ውሳኔዎች፣ ሌሎች ህጎችና ከጠቅላይ ሚኒስትሩ የተደረሱ መግባባቶች ወደጎን በመተው ጥያቄውን ' በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ስነ ምግባር አዋጅን ለማሻሻል በወጣው አዋጅ ' መልሷል " ሲል ገልጿል።

ይህን ተከትሎ ህወሓት " ጥያቄው ሌላ መልሱ ሌላ ሆኗል " በማለት የምርጫ ቦርድን ውሳኔ " አልቀበልም " ሲል አሳውቋል።

" በምርጫ ቦርድ ውሳኔ ላይ የተካተቱት ዝርዝር ይዘቶች አዲስ በወጣው ማሻሻያ ህግ መሰረት የተቀመጡና ካቀረብነው ጥያቄ ጋር የማይገናኙ ናቸው " ሲልም አክሏል።

" የቦርዱ ውሳኔ ህጋዊ ሰውነቴን ወደነበረበት እንዲመለስ የቀረበውን ጥያቄ የማይመልስ ፤ የነበሩ ውይይቶችን የሚቃረኑ ዝርዝር ይዘቶች የሚጭንብን በመሆኑ አልተቀበልኩትም " ያለው ህወሓት " ጥያቄያችን እስኪመለስ ድረስ የፓርቲው ሕገ ደንብ በሚፈቅድልን መልኩ ተያያዥ ስራዎችን እናከናውናለን " ብሏል።

የፌደራል መንግስቱም የማስተካከያ እርምጃ እንዲወስድ ሲልም ጥሪ አቅርቧል።

በቅርቡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር በመከሩበት ወቅት ፦

- TPLF እና መሰል ፓርቲዎች በሕጋዊ መንገድ ተመዝግበው ሕጋዊ ፓርቲ እንዲሆኑ አዋጅ መሻሻሉ፤
- አቃቤ ህግ ለምርጫ ቦርድ መጻፍ የነበረበትን ማለትም ስራውን ሰርቶ የሚያጣራውን አጣርቶ በሕጋዊ መንገድ እንዲፈቅድላቸው፤
- የአስፈጻሚውን ስራ 100% መሰራቱን፤
- ፓርቲ ለፓርቲ ፤ የመንግሥት ለመንግሥት ውይይቶች ላይ ጥያቄዎች ተነስተው ምላሽ እንደተሰጠ፤
- TPLF ምርጫ ቦርድ ሄዶ የሚጠበቅበትን ዶክመንት አሟልቶ በሕጋዊ መንገድ ተመዝግቦ ጉባኤ ማድረግ እንዳለበት ፤ ይህን ባያደርግ ምርጫ ቦርድም ካልተቀበለው፤ TPLFን ሕጋዊ ፓርቲ ካላለው ፦
በምርጫ ሊሳተፍ እንደማይችል ፤
መንግሥትም ሊሆን እንደማይችል ይህ ደግሞ ተመልሶ ጦርነት ውስጥ የሚያስገባ እንደሆነ፤
- ተመልሶ ጦርነት ውስጥ ከመግባት በተበጀው ሕግ ፤ በተደረሰው ስምምነት ህወሓት የቀረውን ጉዳይ አሟልቶ በሕጋዊ መንገድ ጉባኤ አካሂዶ ፓርቲውን መልሶ ወደ ፖለቲካ ስርዓት መመለስ እንዳለበት መግለጻቸው ይታወሳል።

#Ethiopia #TPLF #TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የተስፋ አለመቁረጥ ምሳሌ👏

የጀመርኩትን አላቋርጥም ያለችው አትሌት መነጋገሪያ ሆናለች።

ሀገሯ ቡታንን በመወከል የሮጠችው ኪንዛንግ ላሃሞ የተባለች አትሌት በሴቶች የማራቶን ውድድር የወርቅ ሜዳሊያ ካገኘችው አትሌት ሲፋን ሀሰን ከ1 ከሰዓት ከ30 ደቂቃ በኃላ በመግባት ውድድሯን አጠናቃለች።

አትሌቷ ውድድሯን ስትጨርስ በቦታው የነበረው ታዳሚ እጅግ በጋለ ሞራል ተቀብሏታል።

የመጨረሻ ደረጃ ይዛ ያጠናቀቀችው አትሌቷ በፍጹም የጀመርኩትን ውድድር አላቋርጥም ብላ የውድድሩ የወርቅ አሸናፊ ከታወቀ ከ1 ሰዓት ከ30 ደቂቃ በኃላ ገብታለች።

80ኛ ደረጃ የወጣችው አትሌቷ ውድድሯን ለመጨረስ 3 ሰዓት ከ52 ደቂቃ / 4 ሰዓት ደገማ ወስዶበታል።

በዚህ ሁሉ ፥ የቴሌቪዥን ስርጭት ያልተቋረጠ ሲሆን እያንዳንዷ እንቅስቃሴዋን ሲያሳይ ነበር ፤ በስፍራው የነበረው ተመልካችም የትም ሳይሄድ በክብርና በትልቅ ሞራል ተቀብሏታል።

የቡታኗ አትሌት የጀመረችውን ውድድር እስከመጨረሻ ድረስ ያለ ማቋረጥ ተፋልማ በመጨረሷ በበርካቶች " የተስፋ አለመቁረጥ ምሳሌ " ተደርጋ ተወስዳለች።

ሁላችንም በምንም አይነት ሁኔታ ቢሆን የጀመርነውን መጨረስ፣ ለቆምንለት ዓላማ እስከመጨረሻው መሄድ እንዳለብን ያስተማረ ነው።

" እኔ አልችልም " ብሎ ፣ ተስፋም ቆርጦ አለመቆም እንጂ በተንቀሳቀስን ቁጥር ግባችን ጋር መድረሳችን የማይቀር ነው።

#TikvahEthiopia

ቪድዮ፦ ከሱፐር ስፖርት

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Bangladesh : ለ15 ዓመታት ያህል ባንግላዴሽን የመሩት ሺህክ ሀሲና የተነሳባቸውን ጠንካራ ተቃውሞ ተከትሎ ሀገር ጥለው  ጠፍተዋል። የተቆጡ ተቃዋሚዎችም ወደ ሚኖሩበት ቤተመንግስት በኃይል ሰብረው በመግባት ወረው በመኖሪያ ቤታቸው እንዳሻቸው እየፈነጩበት ነው። ግማሹ አልጋ ላይ ፣ ግማሹ በየክፍሉ እየዞረ እቃቸውን ይፈትሻል፣ ግማሹ ይጨፍራል። ከመንግሥት የስራ ኮታ ስርዓት ጋር በተያያዘ ተማሪዎች…
#Bangladesh

ተማሪዎች በቀሰቀሱትና በኃላም ሌላውም ዜጋ በተቀላቀለው የመንግሥት የስራ ኮታ ተቃውሞ ምክንያት ስልጣናቸውን ለቀው ከሀገር ወጥተው የሄዱት የቀድሞ የባንግላዴሽ ጠ/ሚኒስትር ሼኪህ ሀሲና ከስልጣን እንዲወርዱ " የአሜሪካም እጅ አለበት " ማለታቸውን ' ታይምስ ኦፍ ኢንዲያ ' አስነብቧል።

ልጃቸው ግን " ውሸት ነው " ሲል አጣጥሏል።

ሀሲና አሁን ላይ ሀገራቸውን ጥለው ህንድ ነው ያሉት።

እሳቸው ናቸው የተናገሩት ብሎ ' ታይምስ ኦፍ ኢንዲያ ' እንዳስነበበው ሀሲና ፤ " የደም መፋሰስ እንዳይፈጠርና እሱን ላለማየት ስልንነው ስልጣን የለቀቅኩት " ብለዋል።

" በተማሪዎች እሬሳ ላይ ተረማምደው ስልጣን መያዝ ፈልገው ነበር ግን እኔ ያንን አልፈቀድኩም፤ በዚህም የጠቅላይ ሚኒስትርነት ስልጣኔን ለቅቂያለሁ " ሲሉ መግለጻቸውን አስነብቧል።

ሀሲና " የሴንት ማርቲን ደሴትን ሉዓላዊነት አሳልፌ ብሰጥና ፤ አሜሪካ የቤይ ኦፍ ቤንጋልን እድትቆጣጠር ብፈቅድ ኖሮ በስልጣን ላይ እቆይ ነበር " ማለታቸውን ገልጿል።

አሜሪካ ተቃውሞ ማቀናበሯንና ይህን ያደረገችው የአገዛዝ ለውጥ አድርጋ ፍላጎቷን ለማሟላት እንደሆነ እንደጠቆሙ ነው ' ታይም ኦፍ ኢንዲያ ' ያስነብበው።

አሁን ላይ አሜሪካ የሚኖረው ልጃቸው ሳጂብ ዋዜድ ፤ " እናቴ ከስልጣን መልቀቋን በተመለከተ የሰጠችው መግለጫ ተብሎ በጋዜጣ ታትሞ የወጣው ሙሉ በሙሉ ውሸትና የተቀናበረ ነው፤ ከራሷ እንዳረጋገጥኩት ዳካን ከመልቀቋ በፊትና በኃላ ምንም መግለጫ እንዳልሰጠች ነው " ብለዋል።

ከዚህ ቀደም ሀሲና ባንግላዴሽ ፓርላማ " አሜሪካ በሀገሪቱ የአገዛዝ ለውጥ ለማድረግ እየሞከረች ነው " በማለት አሜሪካንን ወንጅለው ነበር።

ሴንት ማርቲን ደሴት ከ1971 (እ.አ.አ) አንስቶ በባንግላዴሽን ፖለቲካ ትልቅ ተጽእኖ ያላት ትንሽዬ ግን በጣም ወሳኝ ደሴት ናት።

ቦታው ከቤይ ኦፍ ቤንጋል ያለው ርቀት እንዲሁም ከማይናማር ጋር ያለው የባህር ወሰን በስፍራው ከፍተኛ ዓለም አቀፍ ፍላጎት እንዲኖር አድርጓል።

' ቤይ ኦፍ ቤንጋል ' ን ለመቆጣጠር እንዲሁም የህንድ ውቂያኖስ ላይ ያለውን እንቅስቃሴ ጭምር ለመከታተል ፤ ስትራቴጂክ የሆነ ስፍራ ነው።

በዚህም በቀጠናው ኃይሏን ለማጠናከር የተሟላ ቁጥጥር እንዲኖራትና በቻይና ላይም የበላይነት ለመውሰድ አሜሪካ ወታደራዊ ቤዟን ለማቋቋም እንደምትፈልግ ይናገራል።

አሜሪካ ግን ከበርካታ ዓመታት በፊት ይህንን ቦታ እንደማትፈልገው እና በስፍራው ወታደራዊ ቤዝ እንዲኖርት እቅድ እንደሌላት አሳውቃ ነበር።

#TikvahEthiopia #TimesofIndia

@tikvahethiopia
#እንድታውቁት

" ከዛሬ ጀምሮ ከአያት አደባባይ ወደ መገናኛ ፤ ከመገናኛ ወደ አያት አደባባይ የተቃራኒ ጉዞ ተከልክሏል " - የትራፊክ ማኔጅመንት ኤጀንሲ

በአዲስ አበባ፣ ከአያት አደባባይ ወደ መገናኛ ፤ ከመገናኛ ወደ አያት አደባባይ ድረስ በስራ የመውጫ እና የመግቢያ ሰዓቶች ላይ ይፈጠር የነበረውን የትራፊክ መጨናነቅ ለመቀነስ በሚል በጊዜያዊ መፍትሄነት ከአያት አደባባይ እስከ ሴንቸሪ ሞል በሁለቱም መስመሮች የተቃራኒ ጉዞ ተፈቅዶ ነበር።

ነገር ግን መጨናነቁን ይፈጥር የነበረው የሳዕሊተ ምህረት አደባባይ በመቀየሩ ከዛሬ ነሐሴ 6 ቀን 2016 ዓ/ም ጀምሮ በሁለቱም መስመሮች የተቃራኒ ጉዞ መከልከሉን የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ኤጀንሲ አሳውቋል።

አሽከርካሪዎች ይሄን ተገንዝበው የመደበኛ የጉዞ መስመሮችን ብቻ እንዲጠቀሙ ማሳሰቢያ ተላልፏል።

#AddisAbaba #TMA

#TikvahEthiopia
@TikvahEthiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update " ድርጅቱ ጉባኤውን እንዳያካሂድ እንቅፋት የሚሆን ከድርጅቱ የተፈለፈለ ከፍተኛ አመራር አለ " - ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የህወሓት ከፍተኛ አመራሮችን ለሁለት የከፈለውና በብሔራዊ ምርጫ ቦርድም እውቅና የተነፈገው የህወሓት 14ኛ ጉባኤ መክፈቻ ዛሬ ተደርጓል። የህወሓት ሊቀ-መንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) በመክፈቻው ባሰሙት ንግግር ምን አሉ ? ሊቀመንበሩ " ድርጅቱ ህጋዊ…
#TPLF

' ህወሓት ' ውስጥ እየሆነ ያለው ምንድነው ?

ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ከትግራዩ ጦርነት በፊት እንደ ህጋዊ ፓርቲ በምርጫ ቦርድ ስር ተመዝግቦ ይንቀሳቀስ ነበር።

ነገር ግን  ቦርዱ ፓርቲው " ኃይልን መሰረተ ያደረገ የአመጽ ተግባር ላይ ተሰማርቷል " በሚል ሰርዞታል።

የተወካዮች ምክር ቤትም ፓርቲውን " ሽብርተኛ ድርጅት " ሲልም ፈርጆት ነበር።

ደም አፋሳሹና አስከፊው ጦርነት እንዲያበቃ ፕሪቶሪያ ላይ ስምምነት ሲፈረም አንዱ ፈራሚ ይኸው ህወሓት ነበር።

በስምምነቱ ላይ ፓርቲው የተለጠፈበት የሽብርተኝነት ፍረጃ እንደሚፋቅ በግልጽ ሰፍሯል።

በዚህ መሰረት ከወራት በፊት ድርጅቱ ከሽብርተኛነት ተሰርዟል።

ነገር ግን የምዝገባው ጉዳይ ሌላ ነው።

ክፍፍሉ እና ' የቀደመ ህጋዊ ሰውነት ይመለስልኝ ' ጥያቄ ምንድነው ?

ህወሓት የፕሪቶሪያ ሰላም ስምምነት ከተፈረመ በኃላ በውስጥ የኃይል ሽኩቻ ላይ ነበር።

አመራሮቹም ቀስ በቀሰ በሂደት የለየለት መከፋፈል ውስጥ ገብተዋል።

ምንም እንኳን በይፋ ባይወጣም ግልጽ ክፍፍል ይታይ ነበር።

ይህም በአቶ ጌታቸው ረዳ እና በዶ/ር ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል ቡድኖች መካከል ነው።

ባለፉት ወራት እጅግ በርከታ ስብሰባዎች ተደርገው የነበረ ቢሆንም ልዩነቶች ግን እየሰፉ እንጂ እየጠበቡ ሲሄዱ አልታዩም።

ከአንድነት ይልቅ መከፋፈሉ እና ሽኩቻው ጨምሮ ታይቷል።

በዚህ ሂደት ላይ ግን ህወሓት ፥ " ህጋዊ ሰውነታችን ወደነበረበት እንዲመለስ " የሚል ጥያቄ ለምርጫ ቦርድ ይቀርባል (ሚያዚያ ወር ላይ)።

ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ግን አንድ በአመጽ ተግባር ላይ ተሳትፎ የሰረዘውን ፓርቲ የቀደመው ህልውና መመለስ የሚያስችልበት የሕግ ድንጋጌ የለውም። በዚህም ጥያቄውን ሳይቀበለው ይቀራል።

ህወሓትንና ሌሎችንም ለመመዝገብ በሚል አዋጅ እስኪሻሻል ተደርጓል።

ህወሓትም ዳግም " ህጋዊው ሰውነቴ ወደነበረበት ይመለስ " ሲል በሊቀመንበሩ ዶ/ር ደብረጽዮን በኩል ጥያቄ ያቀርባል።

በእርግጥ ሁሉም አመራሮች " የነበረው ህልውና ይመለስ " የሚለው ላይ ልዩነት የላቸውም።

የተሻሻለው አዋጅም ግን በአመጽ ተሳትፎ ለተሰረዘ ፓርቲ የቀደመ ህልውናውን መመለስ የሚያስችል የህግ ድንጋጌ አልያዘም።

ይህን ተከትሎም ቦርዱ " #በልዩ_ሁኔታ " በሚል ፓርቲውን መዝግቦታል።

ዶ/ር ደብረጽዮን ገ/ሚካኤልም ወደ አዲስ አበባ ሄደው ከምርጫ ቦርድ የተሰጠውን " በልዩ ሁኔታ " መመዝገቡን የሚገልጽ ህጋዊ የሰውነት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ፈርመው ወስደው መቐለ ሄደዋል።

ከዚህ በኃላ መቐለ ሄደው በሰጡት መግለጫ " እኛ ይሄን አንቀበልም ፤ የጠየቅነው ሌላ የተሰጠን ሌላ ነው " ሲሉ መግለጫ ሰጥተዋል።

" እኛ እንደዛ አልነበረም የተነጋገርነው ፤ የተባልነውም እንደዛ አልነበረም " የሚል ነገር አንስተዋል።

የእውቅና ምስክር ወረቀቱን ፈርመው ከወሰዱ በኃላ  " ከምቀደው ብዬ ነው ይዤው የመጣሁት " ብለዋል። ምዝገበውን እንደማይቀበሉት እና እንደተመዘገቡም እንደማይቆጠር ነው የገለጹት።

እነ አቶ ጌታቸው ረዳ በምስክር ወረቀቱ ጉዳይ ምንድነው አቋማቸው ?

- በምዝገባ ጉዳይ ለምርጫ ቦርድ የተላከው ደብዳቤ ማእከላዊ ኮሚቴ የማያውቀው በግለሰቦች የተላከ ነው።

- የተወሰኑ ግለሰቦች ናቸው ከድርጅቱ አሰራር ውጪ በቡድን በመሆን የፈረሙት እንጂ እኛ ለምዝገባ ብለን የፈረምነው ማንኛውም ሰነድ የለም።

- የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ' ህወሓት ' ን አስመልክቶ ለተወሰኑ ግለሰቦች የሰጠው እውቅና #የተጭበረበረ በመሆኑ ዳግም ሊያጤነው ይገባል ... የሚል ነው።

ጉባኤው ?

የህወሓት ፅህፈ ቤት እና ማህተምን የተቆጣጠረው የነ ዶ/ር ደብረጾን ገ/ሚካኤል ቡድን ክፍፍሉ እና ከምርጫ ቦርድ ጋር ያለው ልዩነት ሳይፈታ ለጉባኤ ዝግጅት ሲያደርግ ነበር።

በጣም አጭር ጊዜ ውስጥም የጉባኤ ተሳታፊ ለይቶ ጉባኤ ማካሄድ ጀምሯል።

ይህ ጉዳይ በቀጥታ የሚመለከተው አንዱ የህወሓት ቁጥጥር ኮሚሽን " አካሄዱን የጠበቀ አይደለም " በማለት ራሱን አግልሏል።

አቶ ጌታቸው ያሉበት 14 የማእከላዊ ኮሚቴ አባላት " እኛ የለንበትም " ብለው ራሳቸውን አግልለዋል።

የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ደግሞ ባለው አሰራር አንድ ህጋዊ ፓርቲ ጠቅላላይ ጉባኤ ከማድረጉ ከ21 ቀናት በፊት ለቦርዱ ማሳወቅ እንዳለበት ይገልጻል።

በመሆኑንም ፤ የቦርዱን አሰራር ያልተከተለ ፣ ቦርዱ ባልተገኘበት የሚደረግ ጉባኤ ላይ የሚተላለፉ ውሳኔዎችን እውቅና እንደማይሰጥ አሳውቋል።

ህወሓት ግን መቐለ ላይ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድና በርካታ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት በሌሉበት ጉባኤ እያካሄደ ነው።

ጉባኤ ማድረግ ምድነው ጥቅሙ ?

አንድን ጉባኤ ህጋዊ የሚያደርገው በሚመለከተው አካል እውቅና አግኝቶ አሰራሩን ተከትሎ ሲካሄድ ነው።

የፓርቲዎችን ጉዳይ የሚመለከተው ምርጫ ቦርድ በመሆኑ " አካሄዱ ትክክል አይደለም። እውቅናም አልሰጥም " ባለበት ሁኔታ ጉባኤ ቢደረግ ተሰብስቦ ከመበተን ውጭ ውጤት የለውም የሚሉ አሉ።

ዶ/ር ደብረጽዮን ግን ፥ " ህወሓትን አድኖ ህዝብ ከጥፋት መታደግ የጉባኤው ዋነኛ አላማ ነው " ብለዋል።

" የድርጅቱና የህዝቡ የተሟላ ድህንነት ማረጋገጥ በሚችል መልኩ በዴሞክራሲያዊ ውይይትና ክርክር ብቃት ያላቸው አመራሮች መምረጥ ይገባል "ም ብለዋል።

" የአሁኑ ጉባኤ ለድርጅቱ የሞት የሽረት ጉዳይ ነው " እንደሆነ ገልጸዋል።

አቶ ጌታቸው ፍጹም መግባባት ሳይሰረግበት እየተካሄደ ያለ መሆኑን ያነሳሉ።

የጉባኤው ውጤት ምን ሊሆን ይችላል ?

ጉባኤ ማድረግ ምን ችግር ላይፈጥር ይችላል።

ጉባኤውን ተከትሎ የሚተላለፉ ውሳኔዎች እውቅና ስለማያገኙ ሌላ ጭቅጭቅ እና ልዩነት መፍጠሩ ይጠበቃል።

ጉባኤው ላይ በእነ አቶ ጌታቸው እና ቡድናቸው ምትክ ሌሎች የመምረጥ ነገር ካለ ይበልጥ ነገሩ ይከራል።

አቶ ጌታቸውም " #ይቃወሙናል " የሚሏቸውን አመራሮች ለማስወገድ የሚደረግ ጉባኤ እንደሆነ ተናግረዋል።

ጉባኤው የሚያመጣው የግጭት ስጋት አለ ?

በትግራይ ፖለቲካውን የሚከታተሉ አካላት አሁን ላይ በተጨባጭ የሚታይ የግጭት ስጋት የለም ባይ ናቸው።

ጉባኤውን ተከትሎ ምርጫ ተደርጎ ፤ አመራሮችን የማስወገድ ነገር ከመጣ ግን በሂደት ጭቅጭቁና ንትርኩ መጨመሩ እንደማይቀር ያነሳሉ።

በፓርቲው ጉዳይ ከፌዴራል መንግሥት ጋር ያለው ልዩነት የመስፋት እድል ሊኖረው እንደሚችል ይገልጻሉ።

በፓርቲው ያሉት አንጃዎች የራሳቸው ደጋፊ ስላላቸው ልዩነታቸው በሰፋ ቁጥጥር በሂደት ወደ ኃይል እርምጃ እንዳይሄዱ ያሰጋል።

አሁን ላይ ግን በተጨባጭ የሚታይ የግጭት ስጋት ግን የለም።

#ትግራይ : ትግራይ ከአስከፊው ጦርነቱ በቅጡ ሳታገግም ፣ ብዙ ተጎጂ ባለበት ፣ ገና ተጠያቂነት ባልተረጋገጠበት ፣ ብዙ እገዛ የሚፈልግ ባለባት ፣ ተፈናቃይ ተሟልቶ ባልተመለሰበት ... ሌሎችም ብዙ ስራዎች ባልተሰሩበት ይህ የጉባኤ እና ምዝገባ ጉዳይ የህዝብ አጀንዳ እንዲሆን መደረጉ በርካቶችን ያስቆጣ ሆኗል። ይህ ጉዳይ ቀስ በቀስ በሂደት መሄድ እንደሚችልና መቅደም ያለባቸው ህዝባዊ ጉዳዮች መቅደም እንደነበረባቸው የሚያነሱ ብዙዎች ናቸው።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
#Ethiopia #ፍትሕ

በአሰቃቂ ሁኔታ ተደፍራ የተገደለችው የ7 ዓመቷ ህጻን ሔቨን ታሪክ የበርካቶችን ልብ የሰበረ ጉዳይ ሆኗል።

ይህ ድርጊት የተፈጸመው ከዛሬ #አንድ_ዓመት በፊት በባህርዳር ከተማ እንደሆነ ዛሬም ድረስ መሪር ሀዘን ውስጥ የምትገኘው እናት " ኢዮሃ " በተሰኘ የማህበራዊ ሚዲያ ላይ ቀርባ ተናግራለች።

ህጻን ሔቨን የተደፈረችው ተከራይተው ይኖሩበት በነበረ ግቢ አከራይ ነው።

የተደፈረችበት መንገድም ወደ ሽንት ቤት በምትሔድበት ጊዜ ጠብቆ ወደ ቤት በማስገባት ነው። እጅግ በጣም አሰቃቂም ነበር።

ህጻን ሔቨንን የደፈረው ወንጀለኛ በምትደፈርበት ወቅት አንገቷን አንቆ ፤ አፏን አፍኖ ድርጊቱን የፈጸመ ሲሆን ወድቃ የሞተች ለማስመሰል ደሟን አንጠባጥቦ በር ላይ ጥሏት መሄዱን እናት ታስረዳለች።

እናት ልጇን ብቻ አይደለም ያጣችው ፤ ፍትህ ስትጠይቅ ይህንን ግፍ ሰምተው እንዳልሰማ የሆኑ ጎረቤት እና ቤተሰቦች ፤ በጥቅም ወንጀለኛውን ነጻ ለማስወጣት የሰሩ ፤ እናትን ጭምር ተባብረው ለማጥፋት ረጅም ርቀት የተጓዙ ፤ ማስፈራሪያ ደርሷቸው ቃላቸውን ከመስጠት የጠፉ ሁሉ ለእናት ፈተና ሆነውባታል።

ይህም ሆኖ ጥቂት የሚባሉ (የሴቶች እና ህጻናት ወንጀል መሪማሪ ፖሊሷ፤ የሴቶችና ህጻናት ቢሮ) አንዳንዶቹ ማስፈራሪያ ጭምር እየደረሳቸው አግዘዋት ከብዙ መከራ በኋላ ድርጊቱን የፈጸመው ግለሰብ በ25 ዓመት ጽኑ እስራት ይፈረድበታል።

እናት ግን ዛሬም ትኩስ ሀዘን ላይ ነች።

ሥራ እየሰራች መኖር አልቻለችም።

ነገ ከእስር ሲለቀቅ እሷንም ጭምር ለመግደል እንደሚፈልግ ፤ ለዚህም ደግሞ ዳግም ሥራ ከጀመረችበት ቦታ ቤተሰቦቹ ተከታትለዋት ጥላ መውጣቷን እናት አስረድታለች።

ዛሬም እውነተኛ ፍትሕ አጥታ ትንከራተታለች።

ግፍ ላይ ግፍ !

በመሰረቱ በዚህች ምስኪን አንድ ፍሬ ፤ ክፉ ደግ በማታውቅ ህጻን ላይ አሰቃቂ የመድፈር እና ኃሏም ህይወቷን ያሳጣ የወንጀል ድርጊት የፈጸመ ሰው እንዴት 25 ዓመት ይፈረድበታል ? እውነት ይህ ማስተማሪያ ነው ? ወይስ ሌላ ነው ዓላማው ?

የሔቨን ታሪክ የብዙ ህጻናት ታሪክ ጭምር ነው።

ከዚህ በፊት ሴቶች፣ ህጻናት ጭምር ሲደፈሩ የሚተላለፉ የፍርድ ውሳኔዎች ህዝቡን እያስቆጣ መሆኑን አሳውቀን ነበር።

ዛሬም ፍትሕ ተጓድሏል። ፍትሕ ይስፈን።

ዛሬ አጋጣሚ ይህ ጉዳይ አደባባይ ወጣ እንጂ ስንቷ እናት ቤቷ ዘግያ እያለቀሰች ይሆን ? ስንት ሴቶች በግፍ ሰለባ ሆነው እያነቡ ይሆን ?

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia